TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ቅዱስ ፓትርያርኩ ጳጉሜን 1 ቀን 2014 ዓመተ ምህረት ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በሰሜን አሜሪካን የነበራቸውን የሕክምና ክትትል በማጠናቀቅ ላይ መሆናቸው ተገልጿል። ጤናቸውንም በተመለከተ የተወሰነ መሻሻል ማሳየቱ ታውቋል። በመሆኑም ቀደም ሲል በተያዘው…
#Update

ቅዱስ ፓትርያርኩ ለህክምና ከሄዱበት አሜሪካ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ሲገቡ አቀባበል ይደረግላቸዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሕክምናቸውን አጠናቀው ነገ ጷጉሜን 1 ቀን 2014 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያና ወቅዱስ መንበራቸው ይመለሳሉ።

ቅዱስ ፓትራርኩ ወደ ኢትዮጵያና ወቅዱስ መንበራቸው መመለሳቸውን ተከትሎ ከቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ጀምሮ አቀባበል እንደሚደረግላቸው ታውቋል።

የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በጤና ወደ መንበራቸው መመለሳቸው የቤተ ክርስቲያን ደስታ ነው ያለ ሲሆን በዚሁ መጠን ይፋዊ አቀበበል ዝግጅት ተደርጓል ሲል አሳውቋል።

የቅዱስነታቸውን ወደ አገር ቤት መመለስን አስመልክቶ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የአቀባበል ኮሚቴ ተቋቁሞ ሲሰራ የቆየ ሲሆን አሁን ላይ የአቀባበል ቅድመ ዝግጅቱ #መጠናቀቁን ለማወቅ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስነታቸው ወደ ሀገራቸውና ወቅዱስ መንበራቸው መመለስን ተከትሎ ነገ ለሚደረገው አቀባበል ሁሉም ሚዲያዎች ጥዋት 1 ሰዓት ላይ ቦሌ ኤርፖርት (VIP) እንዲገኙላት ጥሪ አቅርባለች።

@tikvahethiopia
👍1.93K625🙏177🥰124😢32😱29👎2
" ዝግጅቱ ተጠናቋል " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዝግጅት #መጠናቀቁን አስታወቀ።

ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል።

በሚኒስቴሩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፤ " የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎችን እውቀትና ብቃት ለመለካት የሚሰጠው የመውጫ ፈተና ዝግጅት ተጠናቋል " ብለዋል።

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የትክክለኛ ተፈታኞችን ቁጥር እንዲያጣራ በማድረግ ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 95 ሺህ 755 እንዲሁም ከመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች 74 ሺህ 776 ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ ሲሉ ገልጸዋል።

ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎቸ ዲግሪ እንደማይሰጣቸው እና የትምህርት ሚኒስቴር በሚያዘጋጀው የፈተና ጊዜ መሰረት ድጋሚ እንደሚፈተኑ አመልክተዋል።

ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው ከተማሯቸው የትምህርት ዓይነቶች መካከል መሰረታዊ የሚባሉ ከ12 እስከ 17 የትምህርት ዓይነቶች ፈተና እንደሚወጣ ገልጸዋል፡፡

ለዚህም የፈተና ንድፍና የብቃት መመዘኛ መስፈርቶች መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ከግንቦት 15 ጀምሮ ለ211 የትምህርት ፕሮግራሞች የፈተና ጥያቄዎች በማውጣት ለፈተናው ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል።

ፈተናው በኦንላየን የሚሰጥ በመሆኑም አስፈላጊ የቴሌኮም እና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።

በሀገሪቱ ካሉ 325 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 161 እና ከመንግስት ደግሞ 44 ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንደሚያስፈትኑ ጠቅሰዋል።

ዶ/ር እዮብ ፤ " ገበያው የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የመውጫ ፈተናው ከ2015 ጀምሮ በሁሉም የትምህርት መስኮችና መርሐ ግብሮች መስጠት እንዲቻል ስራዎች ከአንድ ዓመት በላይ ሲሰሩ ቆይቷል " ሲሉ አስታውሰዋል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
👎1.87K👍960141😱48😢35🙏27🕊26🥰19🤔1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በዓሉ #በሰላም ተጠናቋል " - ግብረ ኃይሉ

የ2016 የሆራ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርአቱን በጠበቀ መልኩ #በሰላም መከበሩን የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታውቋል።

ግብረ ኃይሉ ፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች ተገኝተውበታል ያለድ የዘንድሮው የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በሰላም ተከብሮ #መጠናቀቁን ገልጿል።

የነገው የሆራ አርሰዴ ኢሬቻ በዓለም በተመሳሳይ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ እና ለፀጥታ ኃይሉ እገዛውን እንዲያጠናክር ተጠይቋል።

@tikvahethiopia
😡1.14K🙏548152🕊60🥰36😢30😱9
TIKVAH-ETHIOPIA
#AU #ETHIOPIA ትላንትና ምሽት ላይ ለ37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመጡ መሪዎች በብሄራዊ ቤተመንግስት የእራት ግብዣ ተደርጎላቸው ነበር። ዛሬ የጠ/ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ባሰራጫቸው ምስሎች የኬንያው ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ፣ የጅቡቲ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌህን ጨምሮ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በእራት ግብዣው ላይ ተገኝተው የነበረ ሲሆን የጎረቤት ሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን…
#Update #ተጠናቋል

የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ በሰላምና በስኬት #መጠናቀቁን ኢትዮጵያ አስታውቃለች።

የሁሉም ሀገራት መሪዎች እና የጉባኤው ተሳታፊዎች ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ከዚህ ቀደም ከነበረው በደመቀ ሁኔታ ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ክብርን እና ፕሮቶኮልን በጠበቀ መልኩ አቀባበል እንደተደረገላቸው ፤ በአዲስ አበባ ቆይታቸውም በልዩ እንክብካቤ እንደተያዙ በኢትዮጵያ መንግሥት ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ለዚህ ጉባኤ ስኬት ላለፉት 6 ወራት ስትዘጋጅ መቆየቷን የተገለጸ ሲሆን በተለይም ከሰላምና ደህንነት አንፃር በርካታ ባለድርሻ አካላት ሲሳተፉ መቆየታቸውን ተጠቁሟል።

በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ የፀጥታ እና ደህንነት ኃይሎች ተሰማርተው እንደነበረም ተመላክቷል።

ለጉባኤው ስኬታማነት በተለይ በተለይ የአዲስ አበባ ህዝብ ከቅድመ ጉባኤው ዝግጅት አንስቶ ስብሰባው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ የትራፊክ፣ የመንገድ መዘጋጋት እና ሌሎች ጉዳዮችንም ታግሶ ፤ ከፀጥታ ኃይሉም ጋር በመተባበር እንግዶች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲስተናገዱ ልዩ የእግዳ አቀባበል በማድረጉ መንግሥት ምስጋና አቅርቧል።

በተጨማሪ የፀጥታ እና ደህንነት ኃይሎች ፣ የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ የፕሮቶኮል ሰዎች፣ ሆቴሎች ፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ መገናኛ ብዙሃን .. ሌሎችም አስተዋፅኦ ያደረጉ ሁሉ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።

@tikvahethiopia
👏729137😡100🕊44🙏24😢17😭11😱7🥰6