ለምን አልሰለምኩም?
3.01K subscribers
52 photos
10 videos
42 files
187 links
ይህ ቻነል ቅዱሱ የአምላካችን ቃል በ1ኛ ጴጥ 3:15 ላይ ባዘዘን መሠረት ሙስሊም ወገኖቻችን በክርስትና ላይ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች እና ትችቶች ምላሽ የምንሰጥበት፣ ጥያቄዎቻቸውን ከነመልሳቸው በየጊዜው እያዘጋጀን የምንለጥፍበት፣ ለምን እንዳልሰለምን ፣ እንደማንሰልምም የምንገልጥበት ፣ የኢስላምን የጨለማ መንገድነት በእውነት ብርሀን የሚገልጡ ፅሁፎችን የምናስነብብበት መድረክ ነው።
Download Telegram
🤔እውነት እየሱስ የተላከው ለእስራኤል ሕዝብ ብቻ ነውን??🤔

እስልምና እና ሙሓመዳውያን የ ጀርባ አጥንት የሌለው ሙግት ይዞ መቅረብ የጀመሩት አብዛኞቻችን እንደምናስበው ከ "ዘመነ አህመድ ዲዳት" ወዲህ ሳይሆን ልክ ሙሓመድ "ጅብሪልን አየሁ" ብሎ ማንነቱ እንኲን የማይታወቅና  የሞት ያህል እስኪሰማው ድረስ ሙሓመድን ከ ድንጋይ ጋር ጨፍልቆ በመያዝ  ያሰቃየውን ፍጡር  ማየት ከጀመረ ወዲህ እንደሆነ የ እስልምና መጽሓፎች ሕያው ምስክር ናቸው። ሙግቶቹን በየጊዜው አንድ በ አንድ እያየን የምንሔድ ሲሆን ዛሬ የ ሙሓመድ ፍሬዎች ከሚያነሱያቸው ነጥቦች አንዱን እናያለን።

እንግዲህ ሙሓመዳውያን እየሱስ የ አለም ሁሉ አዳኝ ሳይሆን ለ እስራኤል ብቻ የተላከ ነብይ ለመሆኑ ቀጥሎ ያለውን ጥቅስ ይጠቀማሉ።

" እርሱም መልሶ። ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 15:24)

መልሶቻችን፦

የ እስራኤል ህዝብ በ እግዚያብሔር ዘንድ የተመረጠ ህዝብ መሆኑን መፅሓፍ ቅዱስ ቢቻ ሳይሆን ቁርዓንም ይመሰክራል።ለምሳሌ፣

ሱራቱል በቅራ 2:47
"የእስራኤል ልጆች ሆይ! ያችን በናንተ ላይ የለገስኳትን ጸጋዬንና እኔም በዓለማት ላይ ያበለጥኳችሁ (አባቶቻችሁን በጊዜያቸው ከነበሩት ዓለማት ያበለጥኩዋቸው) መኾኔን አስታውሱ፡፡'

"O Children of Israel, remember My favor that I have bestowed upon you and that I preferred you over the worlds."
 
 የ እየሱስን ተልዕኮ ለ ሁለት ከፍለን እናያለን።
1. የማዳን ስራው በ መስቀል ላይ ሳይፈፀም
2. የ ማዳን ስራው በ መስቀል ላይ ከተፈፀመ በኊላ

1. የ ማዳን ስራው ከመሰራቱ በፊት እየሱስ እስራኤላውያን የተመረጡ የ ኪዳን ልጆች ስለሆኑ እንደ ልዩ መብት "previlage"   አስቀድሞ ከ ማንም በፊት እነሱን ማስተማር  እቅዱ ነው።

ማስረጃ፦
" እናንተ የነቢያት ልጆችና እግዚአብሔር ለአብርሃም። በዘርህ የምድር ወገኖች ሁሉ ይባረካሉ ብሎ፥ ከአባቶቻችን ጋር ያደረገው የኪዳን ልጆች ናችሁ።"
ለእናንተ #አስቀድሞ #እግዚአብሔር #ብላቴናውን #አስነሥቶ፥ እያንዳንዳችሁን ከክፋታችሁ እየመለሰ ይባርካችሁ ዘንድ፥ ሰደደው።
(የሐዋርያት ሥራ 3:25-26)

ስለዚህ ምድር ላይ በሚመላለስበት ጊዜ ክርስቶስ የሚያስተምረው ይሄ የተመረጠ ህዝብን ነው ማለት ነው።  ሌሎችን ቢያስተምርም የ እስራኤልን አምላክ ከ ጥንት ጅምሮ ስለማያውቁና ስለማይረዱት ለ ተልዕኮው( አምነው ተረድተውም አለምን ሁሉ የማዳረስ) ውጤታማነት አይረዳውም። ስለዚህ መጀመሪያ አስቀድሞ ሕዝቡን ማስተማር በ መቀጠል ደግሞ በነሱ በኩል አለምን ማድረስ እቅዱ ሆኖ እናገኘዋለን።

ዋናው ጥያቄ፤ የ እየሱስ የ ማዳን ስራ ለ እስራኤል ብቻ ነውን??? የ ሚል ሲሆን፣ መልሱ #አይደልም ነው። እየሱስ አንድም ቦታ
 " በኔ የሚገኘው ድነት ለ ኢስራኤል ብቻ ነው" አላለም።

ይልቁንስ በ ክርስቶስ የሚገኘው ድነት ለ አለም ሁሉ መሆኑን የምንረዳው የተልዕኮው ሁለተኛ ክፍል ላይ  ፦
1: እየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ሲያስተምራቸው ከነገራቸው ጥቅሶች
2.እየሱስ ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ወደ አለም ሁሉ መላክ ሲጀምር መሆኑን መፅሓፍ ቅዱስ ግልጽ ነው።

1. " በእርሱ የሚያምን #ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ #ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።"
(የዮሐንስ ወንጌል 3:16)

2." እንዲህም አላቸው። ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥"በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት #ከኢየሩሳሌም ጀምሮ #በአሕዛብ #ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል።"
(የሉቃስ ወንጌል 24:46-47)

3." ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም #እስከ #ምድር #ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።"
(የሐዋርያት ሥራ 1:8)
4." ኢየሱስም። ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤"" ሕያው የሆነም #የሚያምንብኝም #ሁሉ ለዘላለም አይሞትም፤ ይህን ታምኚያለሽን? አላት።"" እርስዋም። አዎን ጌታ ሆይ፤ አንተ ወደ #ዓለም የሚመጣው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ እኔ አምናለሁ አለችው።"
(የዮሐንስ ወንጌል 11:25-27)

5. " ሰዎች #ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው።"
(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:3-4)

6." ራሱንም #ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤"
(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:6)

ቁርዓንስ ምን ይላል???

ሱረቱል መሪየም 19:21
አላት (ነገሩ) እንደዚህሽ ነው ፤ ጌታሽ ፦ እርሱ በእኔ ላይ ገር ነው፤ ለሰዎችም ታምር፣ ከኛም ችሮታ(ምህረት=mercy) ልናደርገው (ይህንን ሠራን) የተፈረደም ነገር ነዉ አለ፤ (ነፋባትም)።

He said, "Thus [it will be]; your Lord says, 'It is easy for Me, and We will make him a sign to the people and a mercy from Us. And it is a matter [already] decreed.' "

ልብ በሉ ቁርዓን እራሱ እየሱስን "ለ ሰዎች ምህረት ልናደርገው" ይላል እንጂ "ለ ኢስራኤል" አይልም!!!!

ስለዚህ ሙስሊሞች "እየሱስ ለናንተም ሞቷል" ሞትንም አሸንፎ ተነስቷል። ሙሓመድ ግን ለራሱም መዳኑን እርግጠኛ አልነበረም( Sahih al-Bukhari, Volume 5, Book 58, Number 266,  ቁርአን 46:8,9) ። ስለዚህ ከዘላለም ጥፋት 'ይዳን አይዳን' የማይታወቅ
ነብይ ከመከተል "የሞትና የ ሲኦል መክፈቸ በ እጄ ነው" ያለውን ክርስቶስን ተከተሉ ጥሪያችን ነው!!
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified
📌አምላክ እንዴት አምላክ ይኖረዋል?📌

ሙሓመዳውያን ስለ እየሱስ አምላክነት ሲጠይቁን ውሃ ከማይቋጥሩ ሙግታቸው መካከል አንዱ "እየሱስ እራሱ እግዚያብሔር አብን አምላኬ ብሏል፤ታድያ እናንተ እየሱስን አምላክ የምትሉት ከዬት አምጥታችሁት ነው?? አምላክስ አምላክ ሊኖረው ይችላልን??" የሚል ነው።

በመጀመሪያ ደረጃ እኛ እግዚያብሔር አብ የ እየሱስ አምላክ ("የሰውነት ማንነቱ") መሆኑን ጠንቅቀን እናውቃለን።  እየሱስም ወደ ምድር ሲመጣ በ አምላክነት ማንነቱ የ ሰውነት ማንነተ ስለተዋሃደ  ጠቅልለን "የ እየሱስ ክርስቶስ አባትና አምላክ" እንላለን።

ሙግት አንድ

እየሱስ መጽሓፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚያብሔር አብን "አምላኬ" ብሎ ጠርቶታል (ማቴዎስ 27:46)፤ ጳውሎስም "የእየሱስ ክርስቶስ አባትና አምላክ" ብሏል።
" በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1:3)። እየሱስ ካረገ በኋላም "አምላኬ" ብሏል። (ራእይ 3:2)


ታድያ እየሱስ አማላክ ከሆነ እንዴት አምላክ ይኖረዋል??

" እነሆ፥ እኔ የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ  "יְהוָ֔ה" እግዚአብሔር "אֱלֹהֵ֖י" ነኝ"(ትንቢተ ኤርምያስ 32:27)
"27 Behold, I [am] the LORD ""  , the God of all flesh: is there any thing too hard for me?"
(Jeremiah 32:27)

በዚህ በክፍል ላይ እግዚአብሔር ያህዌ #የስጋ #ለባሽ ሁሉ አምላክ እንደሆነ ግልፅ ነው። እየሱስ ደግሞ ወደ ምድር ሲመጣ ስጋን ለብሷል። ልበ በል "ማንነቱን (essence) ቀየረ" ሳይሆን፤ ሌላ ማንነትን (ሰውነትን) ጨመረ ማለት ነው። ስለዚህ እየሱስ ሁለት ማንነት በ አንድ አካል (one person) ሆኖ ተገልጧል ማለት ነው። ስለዚህ እየሱስን በ አረፍተ ነገር ውስጥ ስናመለክት ሁለቱ ማንነቶች የተለያዩ ቢሆኑም ለይተን አንጠራም ማለት ነው። ስለዚህ እየሱስ የሰውነት ማንነት(human nature) ስላለው፣ በ ኤርሚያስ 32:27 መሰረት፣ ስጋ ያልለበሰውን እግዚያብሔር አብን "አምላኬ" ብሎ መጥራት ነበረበት። ስለዚህ እየሱስ እግዚያብሔር አብን አምላኬ ስላለ እየሱስ አምላክ አይደለም ማለት አይደለም። ምክኒያቱም በአምላክነት ማነቱ ለዘለአለም ከ አብ ገር " አንድ ማንነት (one being)" ኖሮት ይኖር ስለነበረ። 

" #አሁንም፥ አባት ሆይ፥ #ዓለም #ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ #በነበረኝ #ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ።"(የዮሐንስ ወንጌል 17:5)፤  

(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 1)
----------
1፤ በመጀመሪያው ቃል ነበረ( En arche(ልብ በል "ኤጌኔቶ" አይልም) en o logos)፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።

2፤ ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ።

(የዚህን ክፍል ጥልቅ ማብራሪያ በ ግሪክ ሰዋስውና ፊሎሶፊ በቅርብ ቀን እናያለን።)

ስለዚህ እየሱስ እግዚያብሔር አብን "አምላኬ" ብሎ እንዲጠራው ያደረገው የሰውነት ባህሪይ ነው እንጂ ፍጡር ስለሆነ #አይደለም

ሙግት ሁለት፦ ካረገ በኋላስ??

እየሱስ ካረገ በኋላም በሁለቱ ማንነቶቹ ይኖራል። ሲጀመር የትንሳኤ ሃሳብ እራሱ የስጋ ማንነትን "pre suppose"  ያደረገ ነው።(ሉቃስ 24:39)
ለዚያም ነው ጳውሎስ ሲናገር "አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤"(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:5) ብሎ የሰውነት ማንነቱን ብቻ የ ገለፀው። የ እየሱስ ክርስቶስ መካከለኛነት በ ስጋዊ ባህሪው (በመሞት) የተፈፀመ ስለሆን "ሰው የሆነው" ብሎም ተናግሯል። ልብ በሉ "ሰው ብቻ" አላለም። ከሁለቱ ማንነቱ አንዱን በ አውዱ (መካከለኛ መሆን) መርጦ ተናግሯል። ጳውሎስም በ ኤፌሶን 1፡3 "የ እየሱስ አባትና አምላክ" ያለው አሁንም እየሱስ በ ሁለት ማንነቱ ስላለ ነው።

ሙግት ሶስት፦ አንተ ብቻ እውነተኛ አምላክ

" እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።"(የዮሐንስ ወንጌል 17:3)
"3 And this is life eternal, that they might know thee the only true God, and Jesus Christ, whom thou hast sent."(John 17:3)

እግዚያብሔር አብ ብቻ እውነተኛ አምላክ ከተባለ እየሱስ እንዴት እምላክ ይሆናል??

መልሱ " ስላሴ ውስጥ ነው። ሎጂኩን ላሳያቹ

1. ስላሴ ብቻ እውነተኛ አምላክ ነው
2 ስላሴ በ አንድ አምለክ ማንነት ( in only one being=God) ሶስት አካል (person) ለዘለአለም በአምላክነት ባህሪያቸው እኩልና አንድ የሆኑ አብ፣ወልድና መንፈስ ቅዱስ አሉ። ስለዚህ እያንዳንዱ የስላሴ አካል በ ነጠላም ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው

መደምደሚያ። አብ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው፤ ወልድ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው፣ መንፈስ ቅዱስ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው። ልብ በል፤ "እውነተኘ አምላክ" አንድ "essence" ነው፤ "አካል" (person) አይደለም። ሶስቱ ደግሞ "አካል ናቸው"።

ስለዚህ በ ስላሴ አውድ "አብ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው" ማለት ወልድ #አይደለም ማለት አይደለም።

ይቀጥላል...
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified
1👍1