#ከፋኝ
ንቄም ከፋኝ ስቄም ከፋኝ
አክብሬ ስናቅ ደስታ ከዳኝ
እውነት አጣኝ
በገባኝ ልክ እየኖርኩ በሰማውት ልክ ሳላወራ
የሌለኝን የለኝ ብዬ በያዝኩትም ሳልኩራራ
ጥርሴን ወገግ
አይኔን ገርበብ
ለሚያወሩት እኔ እያፈርኩ
ጆሮዬን ግን ክፍት እያረኩ
ሳላምንበት እሺ ብዬ ሳልረዳ ብቀበልም
ውስጥ ውስጤ ግን አይገኝም
#ለምን?????
ለምን ላለኝ ለምን ጥሩ
ከፋኝ ያልኩት ከጅምሩ
ማጣት አይደለም ሚስጥሩ
በኔ አይደለም ክፍት ያለኝ
በኔ አይደለም መረበሼ
ይልቅስ እማዝነው ምድሪቱ ላይ ለሰፈረው
ጥዋት ማታ ለሚበክነው
ላሁን ዘመን ላሁን ሰው ነው።
ሀ በል ሲባል ፊደል ትቶ አፉን ሚከፍት
ለ በል ሲባል ሰውን ረግጦ ለኔ ለኔ እሚጋፋ
ለበላዩ አሸርግዶ በታቹ ላይ ሚደነፋ
እኔስ ማዝነው ላሁን ዘመን ለዚህ ሰዎ ነው።
ግና የኔ ማዘን ምን ሊጠቅም
ለዚህ ሁሉ መልስ አይሆንም
እናም በማስበው ባቅሜ ልክ
የገባኝን መፍትሄ ልስጥ.......
ሀ ተብሎ ምን ቢበላ ቢጠገብም
ርሀብን አያስቀርም
ለኔ ለኔ ምን ቢባልም
ከሰው በላይ የራስ ስጋ የራስ ምቾት ቢወደድም
በቀን መሀል ለሚመጣው ለክፉ ቀን ስንቅ አይሆንም
ስለዚህ......
ሀ በሉ ሲባል ከ ሀ እስከ ሆ
ለ በሉ ሲባል ከ ለ እስከ ሎ
እንደያኔው ህፃንነት
ፊደል ጠርተን ተማምረን
እንለፋት እቺን ዘመን
ምህረቱን እስኪያድለን
ቸርነትን እስኪቸረን። 🙏🙏🙏🙏
@getem
@getem
#nata
ንቄም ከፋኝ ስቄም ከፋኝ
አክብሬ ስናቅ ደስታ ከዳኝ
እውነት አጣኝ
በገባኝ ልክ እየኖርኩ በሰማውት ልክ ሳላወራ
የሌለኝን የለኝ ብዬ በያዝኩትም ሳልኩራራ
ጥርሴን ወገግ
አይኔን ገርበብ
ለሚያወሩት እኔ እያፈርኩ
ጆሮዬን ግን ክፍት እያረኩ
ሳላምንበት እሺ ብዬ ሳልረዳ ብቀበልም
ውስጥ ውስጤ ግን አይገኝም
#ለምን?????
ለምን ላለኝ ለምን ጥሩ
ከፋኝ ያልኩት ከጅምሩ
ማጣት አይደለም ሚስጥሩ
በኔ አይደለም ክፍት ያለኝ
በኔ አይደለም መረበሼ
ይልቅስ እማዝነው ምድሪቱ ላይ ለሰፈረው
ጥዋት ማታ ለሚበክነው
ላሁን ዘመን ላሁን ሰው ነው።
ሀ በል ሲባል ፊደል ትቶ አፉን ሚከፍት
ለ በል ሲባል ሰውን ረግጦ ለኔ ለኔ እሚጋፋ
ለበላዩ አሸርግዶ በታቹ ላይ ሚደነፋ
እኔስ ማዝነው ላሁን ዘመን ለዚህ ሰዎ ነው።
ግና የኔ ማዘን ምን ሊጠቅም
ለዚህ ሁሉ መልስ አይሆንም
እናም በማስበው ባቅሜ ልክ
የገባኝን መፍትሄ ልስጥ.......
ሀ ተብሎ ምን ቢበላ ቢጠገብም
ርሀብን አያስቀርም
ለኔ ለኔ ምን ቢባልም
ከሰው በላይ የራስ ስጋ የራስ ምቾት ቢወደድም
በቀን መሀል ለሚመጣው ለክፉ ቀን ስንቅ አይሆንም
ስለዚህ......
ሀ በሉ ሲባል ከ ሀ እስከ ሆ
ለ በሉ ሲባል ከ ለ እስከ ሎ
እንደያኔው ህፃንነት
ፊደል ጠርተን ተማምረን
እንለፋት እቺን ዘመን
ምህረቱን እስኪያድለን
ቸርነትን እስኪቸረን። 🙏🙏🙏🙏
@getem
@getem
#nata
👍1