እስቲ የገጣሚ ሶሎሞን ሳህለን "ያማል" ወደ ወቅታዊ ጉዳይ እንከርብታት
(በላይ በቀለ ወያ) #ሼር ይደረግ
።
እና እንደ ነገርኩሽ
ሀገር አሸባሪን
ወታደሮች ቀጥሮ ፣ልክ እንደማስጠበቅ
በቄሮዎች ዱላ ፣ ተመቶ እንደመውደቅ
ሬሳ ሲጎተት ፣ አይቶ እንደመሳቀቅ
ለውጡ "ውጡ" ብሎ ፣ ጎዳና እንደመውደቅ
ስቃይ በበዛባት ፣ በዚች ቧልተኛ ሀገር
ከዚህ የበለጠ ፣ የለም ሚያም ነገር።
ዘረኝነት ያማል
የመንጋ ፍርድ ያማል
ሜንጫ ዱላው ያማል
ምስኪን መግደል ያማል
ጳጳስ ሲያለቅስ ያማል
መስጂድ ማፍረስ ያማል
ካህን ማረድ ያማል
መንገድ መዝጋት ያማል
የማይጎድል ፣ የዘር ጎርፍ ፣ የደም ማዕበሉ
የዕንባ ቅጥልጥሉ
ቤተስኪያን ማጋየት ፣ ንብረት ማቃጠሉ
በድንጋይ ተወግሮ ፣ ድሀ መገደሉ
ምን ብዬ ልንገርሽ ፣ ያማል ይሄ ሁሉ!
።።።
እና እንደ ነገርኩሽ
ቄሮ ሚወደውን ፣ ሌላው ካልወደደ
ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ፣ ሌላ ሀገር ከሄደ
ነገር ተበላሸ ፣
ሀገር ተረበሸ
ጭካኔና በቀል ፣ በግፍ ተወለደ
መንገዱ ተዘጋ ፣ ምስኪኑ ታረደ
ተርፎ ይህን ያየ ፣ጨጓራው ነደደ
አንጀቱ በገነ
የሚሆነው ሳይሆን የማይሆነው ሆነ
ተከበብኩኝ ብሎ
አንድ ሰው በቃዠው ፣ ከእንቅልፉ ሳይነቃ
ሁሉም ተቀይሮ ፣ ተተካ በሲቃ
ምንብዬ ልንገርሽ? ይሄም ያማል በቃ!
።።
ፈንካች ተፈንካቹ
ገዳዩና ሟቹ
እብሪቱ ጥጋቡ
ያለምንም ምክንያት ፣ የጠፋበት ግቡ
ከመርፌ ቀዳዳ ፣ አእምሮ መጥበቡ
በቆራጭ ሜንጫ ፊት ፣ እልፍ አንገት መቅረቡ
ውል የሌለው ቅዠት ፣የተኛን መክበቡ
እልፍ አእላፍ በደል ፣ መግለጫን ማጀቡ
ደሞ ለሱ ግጥም ፣እናቱን መግለጫ
ምንብዬ ልንገርሽ ፣
ይሄ ሁሉ ነገር ፣ ያማል እንደ ሜንጫ።
።።።
እና እንደ ነገርኩሽ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ
ግራ ወይ ቀኝ እግሩ
የሌላ ሀገር ምድርን ፣ ልክ እንደረገጠ
አንዱ መንገድ ዘጊ ፣ ወደኔ አፈጠጠ
ዱላ የጨበጠ ፣ አንድ እጁን ሰንዝሮ
በአንድ እጁ ደግሞ ፣ ድንጋይ ተወራውሮ
ምን ልታዘዝ ይላል…?? ፣ ደረቱን ወጥሮ!
ምን ልታዘዝ ይላል?
እንዴት መንገደኛ ፣ መንገድ ዘጊን ያዛል?!
ክፍት መንገድ ልዘዝ?
አንዲት ሀገር ልዘዝ?
አንድ ፍቅር ልዘዝ?
አንድ ሰላም ልዘዝ?
@getem
@getem
#getem le hulum
(በላይ በቀለ ወያ) #ሼር ይደረግ
።
እና እንደ ነገርኩሽ
ሀገር አሸባሪን
ወታደሮች ቀጥሮ ፣ልክ እንደማስጠበቅ
በቄሮዎች ዱላ ፣ ተመቶ እንደመውደቅ
ሬሳ ሲጎተት ፣ አይቶ እንደመሳቀቅ
ለውጡ "ውጡ" ብሎ ፣ ጎዳና እንደመውደቅ
ስቃይ በበዛባት ፣ በዚች ቧልተኛ ሀገር
ከዚህ የበለጠ ፣ የለም ሚያም ነገር።
ዘረኝነት ያማል
የመንጋ ፍርድ ያማል
ሜንጫ ዱላው ያማል
ምስኪን መግደል ያማል
ጳጳስ ሲያለቅስ ያማል
መስጂድ ማፍረስ ያማል
ካህን ማረድ ያማል
መንገድ መዝጋት ያማል
የማይጎድል ፣ የዘር ጎርፍ ፣ የደም ማዕበሉ
የዕንባ ቅጥልጥሉ
ቤተስኪያን ማጋየት ፣ ንብረት ማቃጠሉ
በድንጋይ ተወግሮ ፣ ድሀ መገደሉ
ምን ብዬ ልንገርሽ ፣ ያማል ይሄ ሁሉ!
።።።
እና እንደ ነገርኩሽ
ቄሮ ሚወደውን ፣ ሌላው ካልወደደ
ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ፣ ሌላ ሀገር ከሄደ
ነገር ተበላሸ ፣
ሀገር ተረበሸ
ጭካኔና በቀል ፣ በግፍ ተወለደ
መንገዱ ተዘጋ ፣ ምስኪኑ ታረደ
ተርፎ ይህን ያየ ፣ጨጓራው ነደደ
አንጀቱ በገነ
የሚሆነው ሳይሆን የማይሆነው ሆነ
ተከበብኩኝ ብሎ
አንድ ሰው በቃዠው ፣ ከእንቅልፉ ሳይነቃ
ሁሉም ተቀይሮ ፣ ተተካ በሲቃ
ምንብዬ ልንገርሽ? ይሄም ያማል በቃ!
።።
ፈንካች ተፈንካቹ
ገዳዩና ሟቹ
እብሪቱ ጥጋቡ
ያለምንም ምክንያት ፣ የጠፋበት ግቡ
ከመርፌ ቀዳዳ ፣ አእምሮ መጥበቡ
በቆራጭ ሜንጫ ፊት ፣ እልፍ አንገት መቅረቡ
ውል የሌለው ቅዠት ፣የተኛን መክበቡ
እልፍ አእላፍ በደል ፣ መግለጫን ማጀቡ
ደሞ ለሱ ግጥም ፣እናቱን መግለጫ
ምንብዬ ልንገርሽ ፣
ይሄ ሁሉ ነገር ፣ ያማል እንደ ሜንጫ።
።።።
እና እንደ ነገርኩሽ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ
ግራ ወይ ቀኝ እግሩ
የሌላ ሀገር ምድርን ፣ ልክ እንደረገጠ
አንዱ መንገድ ዘጊ ፣ ወደኔ አፈጠጠ
ዱላ የጨበጠ ፣ አንድ እጁን ሰንዝሮ
በአንድ እጁ ደግሞ ፣ ድንጋይ ተወራውሮ
ምን ልታዘዝ ይላል…?? ፣ ደረቱን ወጥሮ!
ምን ልታዘዝ ይላል?
እንዴት መንገደኛ ፣ መንገድ ዘጊን ያዛል?!
ክፍት መንገድ ልዘዝ?
አንዲት ሀገር ልዘዝ?
አንድ ፍቅር ልዘዝ?
አንድ ሰላም ልዘዝ?
@getem
@getem
#getem le hulum