#፪ ነፍስ ገዳዮች!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።
#ይኸው ዛሬም ድረስ!
የሰንበር ሀምሳያው ፥ ገመድ ተደራርቶ
አክሊለ እሾሁ ፦
ተምሳሌት እንዲሆን ፥ ለምስክር ወጥቶ
እየደበደቡ.. .. እየቀጠቀጡ
ግጥም አሰናኝተው ዜማ የሚያወጡ
እስክስታ 'ሚወርዱ ...
ከበሮ አንጋቾች አሉ በመንገዱ።
#ደግሞም ወዲህ ማዶ !
የሙት አካል ቆዳን
እየረመረሙ እየረጋገጡ
ስልቻ አበጅተው ገበያ ሚወጡ
በካቻምና ዝናብ ...
ዛሬ አርሰናል ብለው ፥ መግለጫ ሚሰጡ
አሉ ጎዳናው ላይ ፥
ሀቅታ ነው ብለው ፥ እብለት እየሸጡ ።
#ይኸው ተመልከቺ.. .
ከነ መግላችን ፣ ከነ ሰንበራችን
እሳት ባነፈረው ፥ ተበዳይ ገላችን
ሽቱ ሆነን ለሳሎን
ለእልፍኝ ለአዳራሽ...
እጣን ናቸው ብለው ቤታቸው ሲጫጫስ
#እይ ተመልከቺ
ጌጥ ሆነን ለአያያዝ ፥ ቅንጦት ሆነን ለአማኝ
ክሩ ደምስራችን.. .ለመዝሙራት ሲቃኝ
#እይ ተመልከቺ !
ከሙት አካላችን ...
ከፍራሽ ገላችን ፥ በሸለቱት ቆዳ
ከበሮዋቸው ሆነን ፥ ዜማቸው ሲቀዳ
#እይ ተመልከቺ !
እኛ በጨመቅነው ፥ በዘራነው እንባ
ውሀ ነው ተብሎ ...
ገዳያችን ሊፀድቅ ፥ ከጥምቀት ሲገባ
#እይ ተመልከቺ!
ከስጋችን ማዶ ፥ መንፈሳችን ሲቀል
ባልዋልንበት ሜዳ ...
ኩበት ተሰብስቦ ፥ ዳቦዋቸው ሲበሰል።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።
#ይኸው ዛሬም ድረስ!
የሰንበር ሀምሳያው ፥ ገመድ ተደራርቶ
አክሊለ እሾሁ ፦
ተምሳሌት እንዲሆን ፥ ለምስክር ወጥቶ
እየደበደቡ.. .. እየቀጠቀጡ
ግጥም አሰናኝተው ዜማ የሚያወጡ
እስክስታ 'ሚወርዱ ...
ከበሮ አንጋቾች አሉ በመንገዱ።
#ደግሞም ወዲህ ማዶ !
የሙት አካል ቆዳን
እየረመረሙ እየረጋገጡ
ስልቻ አበጅተው ገበያ ሚወጡ
በካቻምና ዝናብ ...
ዛሬ አርሰናል ብለው ፥ መግለጫ ሚሰጡ
አሉ ጎዳናው ላይ ፥
ሀቅታ ነው ብለው ፥ እብለት እየሸጡ ።
#ይኸው ተመልከቺ.. .
ከነ መግላችን ፣ ከነ ሰንበራችን
እሳት ባነፈረው ፥ ተበዳይ ገላችን
ሽቱ ሆነን ለሳሎን
ለእልፍኝ ለአዳራሽ...
እጣን ናቸው ብለው ቤታቸው ሲጫጫስ
#እይ ተመልከቺ
ጌጥ ሆነን ለአያያዝ ፥ ቅንጦት ሆነን ለአማኝ
ክሩ ደምስራችን.. .ለመዝሙራት ሲቃኝ
#እይ ተመልከቺ !
ከሙት አካላችን ...
ከፍራሽ ገላችን ፥ በሸለቱት ቆዳ
ከበሮዋቸው ሆነን ፥ ዜማቸው ሲቀዳ
#እይ ተመልከቺ !
እኛ በጨመቅነው ፥ በዘራነው እንባ
ውሀ ነው ተብሎ ...
ገዳያችን ሊፀድቅ ፥ ከጥምቀት ሲገባ
#እይ ተመልከቺ!
ከስጋችን ማዶ ፥ መንፈሳችን ሲቀል
ባልዋልንበት ሜዳ ...
ኩበት ተሰብስቦ ፥ ዳቦዋቸው ሲበሰል።
@getem
@getem
@getem
👍1
#ያንድ መስቀል እውነት! !
(ሚካኤል አስጨናቂ)
.
ውዴ አንተ ጌታ ...
እነሆኝ ያቃልህ የረቡዕ ትዝታ
ትጉና ፀልዩ የሚሉ ቃላቶች
ፍርሀትን በእምነት
ድልመንሳት የመቻል ልዩ ምልክቶች
.
ይኸው የረቡዕ ዕለት
የምክራቸው ስ'ተት .. .
.
#አንተ ኤልሻዴይ ጌታ !
ምሉዕ ሆነህ ሳለህ አልፋና ኦሜጋ
እንደምን ተዋረድህ በመክበርህ ፈንታ ?
ለምን ተሰቃይተህ ስጋህ ተንገላታ ?
ብዬ እንዳልጠይቅ ከእግርህ ስር ወድቄ
በፊትህ ጥፊዎች አለሁኝ ደምቄ ።
.
አንተ የእኔ እራት
የሀሙስ ግብዣዬ
በልቼህ የጠገብሁ ፣ ጠጥቼህ የረካሁ
ከዘመን በደሌ ፥ እስር የተፈታሁ
ከጎኔ ቁጭ ብለህ ፥ ጥበብ የለገስከኝ
ሞትህ ቅኔ ሆኖ ፥ አለሁኝ ሲደንቀኝ።
.
ውዴ አንተ ጌታ
እነሆኝ ያ ስቃይ የአርቡ ትዝታ
ሺህ ጠበኛ እጆች የሚገፉት አካል
የዓለም ፈራጅ ስጋህ ጅራፍ ይቀበላል
ፊትህ ደምግባትህ ምራቅ አርፎበታል
መስቀል ያጎበጠው ትከሻህ ተናንሶ
የእናትህ ሀዘን ይሰማኛል ለቅሶ
.
#ደግሞም ወዲህ ማዶ ...
ለቅኔው ስቃይህ መልስ የማጣው እኔ
አንተን ለማሰቀል ከበርባን ወግኜ
በሞትህ ቀናቶች መሀል ተከልዬ
አዳምን እንዳየው ጥልቁን ተለይቶ
መሲሁ ይታሰር ወምበዴው ተፈቶ
እላለሁኝ ቆ ሜ ጮሄ ባደባባይ
ስቅለት ህ ድህነት ነው የሚጣፍጥ ስቃይ።
@getem
@getem
@paappii
(ሚካኤል አስጨናቂ)
.
ውዴ አንተ ጌታ ...
እነሆኝ ያቃልህ የረቡዕ ትዝታ
ትጉና ፀልዩ የሚሉ ቃላቶች
ፍርሀትን በእምነት
ድልመንሳት የመቻል ልዩ ምልክቶች
.
ይኸው የረቡዕ ዕለት
የምክራቸው ስ'ተት .. .
.
#አንተ ኤልሻዴይ ጌታ !
ምሉዕ ሆነህ ሳለህ አልፋና ኦሜጋ
እንደምን ተዋረድህ በመክበርህ ፈንታ ?
ለምን ተሰቃይተህ ስጋህ ተንገላታ ?
ብዬ እንዳልጠይቅ ከእግርህ ስር ወድቄ
በፊትህ ጥፊዎች አለሁኝ ደምቄ ።
.
አንተ የእኔ እራት
የሀሙስ ግብዣዬ
በልቼህ የጠገብሁ ፣ ጠጥቼህ የረካሁ
ከዘመን በደሌ ፥ እስር የተፈታሁ
ከጎኔ ቁጭ ብለህ ፥ ጥበብ የለገስከኝ
ሞትህ ቅኔ ሆኖ ፥ አለሁኝ ሲደንቀኝ።
.
ውዴ አንተ ጌታ
እነሆኝ ያ ስቃይ የአርቡ ትዝታ
ሺህ ጠበኛ እጆች የሚገፉት አካል
የዓለም ፈራጅ ስጋህ ጅራፍ ይቀበላል
ፊትህ ደምግባትህ ምራቅ አርፎበታል
መስቀል ያጎበጠው ትከሻህ ተናንሶ
የእናትህ ሀዘን ይሰማኛል ለቅሶ
.
#ደግሞም ወዲህ ማዶ ...
ለቅኔው ስቃይህ መልስ የማጣው እኔ
አንተን ለማሰቀል ከበርባን ወግኜ
በሞትህ ቀናቶች መሀል ተከልዬ
አዳምን እንዳየው ጥልቁን ተለይቶ
መሲሁ ይታሰር ወምበዴው ተፈቶ
እላለሁኝ ቆ ሜ ጮሄ ባደባባይ
ስቅለት ህ ድህነት ነው የሚጣፍጥ ስቃይ።
@getem
@getem
@paappii