"መሸ ደግሞ ………!!"
።።።።።።።።።።።።።።።
የክንድህን ብርታት ልርታው
ያብራክህን ቅኔ ልፍታው።
ያዘኝና ገነት ግባ ፥ ከኤደን ጠበል ንከረኝ
ልመጽውትህ ተመጽወተኝ፥ልዘከርህ ተዘከረኝ።
ባርኮትህን አትሰስት ፥ ቡራኬዬን አልሰስትም
ሀጥያትን ብሰራ 'ኳን ፥ ባንተ ከሆን ከቶ አልስትም።
ዝምም ብለን እንመንን ፥ ያለስንቅ ያለቀለብ
በፍቅር እሳት በፍቅር እቶን እንለብለብ።
አትተንፍስ ወደ ውጪ ፥ ንፋስ እንኳን እንዳይሰማን
ከባህሩ ከንፈር አርፎ ፥ ለማዕበል እንዳያማን።
አይገለጥ ቡሉኳችን ፥ ይጠቅጠቅ የጣራው ሽንቁር
አይሹለክ የሌሊቱ ውርጭ ፥ አይንካን የማለዳ ቁር።
ቢነጋም አትውጣ ከጄ ፥ ትቅናብን ፀሐይ ትቅደመን
አይንጋ ሌሊቱ ይርዘም ፥ ሳንድን በፍቅር ታመን
መቅኔን ቆሌህ ያውግዘው ፥ በጠሉ እያረጠበ
ዓለሜ በፍቅርህ ቁመት ፥ ይከርከም እየጠበበ።
ምክንያቱም!"
መንጋት መመሸቱን ማስታውስ ፥ የቀናት እድሜን ምለካ
በምትዘርፍልኝ ቅኔና ፥ በውብ ጣቶችህ ነው ለካ።
#ዝናቡ_ግን_ዛሬ_ምን_አስቦ_ነው_ ¿¿
#Dagim_Hiwet
@getem
@getem
@getem
።።።።።።።።።።።።።።።
የክንድህን ብርታት ልርታው
ያብራክህን ቅኔ ልፍታው።
ያዘኝና ገነት ግባ ፥ ከኤደን ጠበል ንከረኝ
ልመጽውትህ ተመጽወተኝ፥ልዘከርህ ተዘከረኝ።
ባርኮትህን አትሰስት ፥ ቡራኬዬን አልሰስትም
ሀጥያትን ብሰራ 'ኳን ፥ ባንተ ከሆን ከቶ አልስትም።
ዝምም ብለን እንመንን ፥ ያለስንቅ ያለቀለብ
በፍቅር እሳት በፍቅር እቶን እንለብለብ።
አትተንፍስ ወደ ውጪ ፥ ንፋስ እንኳን እንዳይሰማን
ከባህሩ ከንፈር አርፎ ፥ ለማዕበል እንዳያማን።
አይገለጥ ቡሉኳችን ፥ ይጠቅጠቅ የጣራው ሽንቁር
አይሹለክ የሌሊቱ ውርጭ ፥ አይንካን የማለዳ ቁር።
ቢነጋም አትውጣ ከጄ ፥ ትቅናብን ፀሐይ ትቅደመን
አይንጋ ሌሊቱ ይርዘም ፥ ሳንድን በፍቅር ታመን
መቅኔን ቆሌህ ያውግዘው ፥ በጠሉ እያረጠበ
ዓለሜ በፍቅርህ ቁመት ፥ ይከርከም እየጠበበ።
ምክንያቱም!"
መንጋት መመሸቱን ማስታውስ ፥ የቀናት እድሜን ምለካ
በምትዘርፍልኝ ቅኔና ፥ በውብ ጣቶችህ ነው ለካ።
#ዝናቡ_ግን_ዛሬ_ምን_አስቦ_ነው_ ¿¿
#Dagim_Hiwet
@getem
@getem
@getem