መለያየት_ማለት
.
✍(#ኤፍሬም_ስዩም)
.
.
ይኸው ትላንትና ከትላንትም በስትያ
ያዩሽ ሰዎች ሁላ ከእቅፌ ጉያ
ዛሬን ተራርቀን ብቻዬን ቢያዩኝ
ከድታዋለች ብለው ከንፈር መጠጡልኝ
እባክሽ የኔ አለም!! ፈጥነሽ ንገሪያቸው
ሴትን ማፍቀር እንጂ ማባበል አይችልም
ብለሽ አስረጃቸው::
ለኔ ና ላንቺ እኮ መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት.....
ያለመተያየት
መፋቀርም ማለት
በምናልባት ተስፋ የምትቆም ህይወት
ዘወትር....
ዘወትር ምናልባት......... ምናልባት እያለች
የምትኖር ህይወት በተስፋዋ መሀል ጥቂት ደስታ አላት።
በታስፋችን መሀል መፋቀሩ ካለን
ናፍቆት አካል ገዝቶ እንተያያለን
ብለሽ ንገሪያቸው....
ልቤና ልቦናው ተጣብቀዋል በያችቸው
እንጂ በኛ መሀል መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት.
በሩቅ መሰማማት ነው በድምፅ አልባ ቃላት።
@Getem
@getem
@lula_al_greeko
.
✍(#ኤፍሬም_ስዩም)
.
.
ይኸው ትላንትና ከትላንትም በስትያ
ያዩሽ ሰዎች ሁላ ከእቅፌ ጉያ
ዛሬን ተራርቀን ብቻዬን ቢያዩኝ
ከድታዋለች ብለው ከንፈር መጠጡልኝ
እባክሽ የኔ አለም!! ፈጥነሽ ንገሪያቸው
ሴትን ማፍቀር እንጂ ማባበል አይችልም
ብለሽ አስረጃቸው::
ለኔ ና ላንቺ እኮ መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት.....
ያለመተያየት
መፋቀርም ማለት
በምናልባት ተስፋ የምትቆም ህይወት
ዘወትር....
ዘወትር ምናልባት......... ምናልባት እያለች
የምትኖር ህይወት በተስፋዋ መሀል ጥቂት ደስታ አላት።
በታስፋችን መሀል መፋቀሩ ካለን
ናፍቆት አካል ገዝቶ እንተያያለን
ብለሽ ንገሪያቸው....
ልቤና ልቦናው ተጣብቀዋል በያችቸው
እንጂ በኛ መሀል መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት.
በሩቅ መሰማማት ነው በድምፅ አልባ ቃላት።
@Getem
@getem
@lula_al_greeko
#የአንድ_አፈር_አፈሮች
•
ፍቅራችንን
ድንበር ወሰን ላይገድበው
ሁለት ክልል ላይመጥነው
መገዳደል ፍት' ላይሆነው
በሽንፈትህ እሠይ ላልል
በሽንፈቴ እፎይ ላትል
ከቂም በቀል ፍቅር ላይበቅል
ልጅህ በእጄ ለምን ይሙት
ልጄስ በእጅህ ለምን ትሙት
እኔና አንተ እኮ
የአንድ እናት ልጆች
ወንድማማቾች
ያንድ አፈር አፈሮች
ርስት አፈሩማ
ይቅርም ከወደዚህ ይሂድም ወደዚያ
ያው ነው የኢትዮጵያ ያንድ አፈር መጠሪያ
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ ወዲህ ካለው የእስካሁኗ
ግዳይ ጥዬ በልጅህ ደም በጀግንነት ላልጠራ
ግዳይ ጥለህ በልጄ ደም ላትፎክር ላታቅራራ
ወንድም ገድለው ላይፎክሩ
ጀብዱ ሰርተው ላይኩራሩ
ያዘን ሙሾ ሊዘምሩ
እንደ ማተብ የእምነት ክር ፍቅር ድሩ ላይበጠስ
ባዘናችን ላትዘፍኑ በሞታችሁ ላንደንስ
ስሙር አይሁን ነጭ ሴራው ደስ አይበለው የጠላት ነፍስ
ልጅህ አይሙት በልጄ ጣት
ልጄም አይሙት በልጄ ቀስት
እኔና አንተ እኮ
ከዘመናት በፊት
በታሪክ በሃይማኖት
በባህል በትውፊት
በደስታ በችግር
ስም የለሽ ስመ-ጥር
በጋሻና በጦር ጀብደኛ ባላገር
ያንድ አያቶች ዘር የሁለት አፈር ሠፈር
ስም የለሽ በጥጋብ
ስመ-ጥር በረሃብ
እያሉ ሲተቹህ እያሉ ሲተቹን
በሙጫ ስድብ አጣብቀውን
ሲተቹን መተቸት ሲተቹን መተቸት
እንዳለ ስናውቀው እንዳለ ስታውቁት
ካንድ እናት ተወልደን በሁለት አባት አድገን
አንድ ውሃ ተራጭተን አንድ አፈር አቡክተን
ቃታ ስንሳሳብ
እሺ ላይለው ልብህ ደስ ላይለው ልቤን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
እኔና አንተ እኮ
ያንድ እናት ልጆች
ወንድምና እህቶች
ያንድ አፈር አፈሮች
እናም ወንድም ስማኝ ልስማህ
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ጸብ ሲያቃባ
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ
በመሞትህ ደስ ላይለኝ ውስጥ ልቤ እዥ ሊያነባ
የናቱ ልጅ ልጅህ ገድሎ ላያሰማ ጉሮ ወሸባ
ፍቅር እንጂ ግድባችን ወሰን አይኑር የደም ካባ
ይልቅስ ልንገርህ
ኩራቴ ኩራትህ
ታሪኬ ታሪክህ
የሚያመጻድቀኝ የሚያመጻድቅህ
የኔም ያባቴ ነው ያንተም የአባትህ
ከቢዘን ባስቀድስ ከግሸን ብትሰልስ
በአክሱም ብትኮራ
ብሸልል በአስመራ
ያንተ አባት አባቴ አባቴ አባትህ
የሚያመያጻድቀኝ የሚያጻድቀኝ ታሪኬ ታሪክህ
መሆኑን ስናውቀው መሆኑን ስታውቁት
በደምና ባጥንት በስጋ በጅማት በታሪክ በትውፊት
መንታ ናቸው ሲሉን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
በብቀላ ጸጸት በቀር ወንድም ጥሎ ላይፎክር
ጀግና ተብሎ ሜዳይ ላይኖር
በናቴ ልጅ በመጨከን እሺ ላይለኝ የልቤ በር
ወንድ ልጄን ግዳይ ጥለህ ላይፈታ የደምህ ስር
ካንድ ደብር አድገን በአንድ አስቀድሰን አንድ ዳዊት ደግመን
ካንድ መስጊድ ኖረን ባንድ ሰላት አድገን አንድ ቁርዓን ቀርተን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
ለጉዳትህ ተሰዉቼ
ላንተ ክብር ብዙ ሞቼ
ስላንተ ነጻነት ካገርህ ደሜ አለ
በናቕፋ ተራሮች እቅፍ የታዘለ
መጎዳቴን እምቢ ብለህ
ስለ ክብሬ ተሰውተህ
የሰጠኸኝ ክቡር ደምህ
ያንተም አጽም ዓድዋ አለ
ለጦቢያ ነጻነት ስለኔ የዋለ
መንታ ናቸው ሲሉን
ፍቅር ናቸው ሲሉን
እያወቁት ልቦናችን
ሁለት ክልል ላይመጥነን
ድንበር ወሰን ላይገድበን
መገዳደል ፍት' ላይሆነን
በሽንፈትህ ስንዘምር "በለው" ያሉን ሊታዘቡን
ነጭ ሴራ ወጣው ሊሉን
ስጋ ክንድህ ሲደማብህ ልቦናችን ሊያዝብን
ባለም ዜና ድላችንን ደም ጥማት ነው ብለው ሊሉን
ልጅህ በጄ ለምን ይሙት
ልጄስ በእጅህ ለምን ይሙት
ስማኝ ወገን
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ጸብ ሲያቃባ
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ
ርስት አፈሩማ
ይቅርም ከወደዚህ ይሂድም ወደዚያ
ያው ነው የኢትዮጵያ ያንድ አፈር መጠሪያ
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ ወዲህ ካለው የእስካሁኗ
እናም በሞቱት ሞት
እኔና አንተ አንሙት
እኔና አንተማ
የአንድ እናት ልጆች
ወንድምና እህቶች
ያንድ አፈር አፈሮች
#ኤፍሬም_ስዩም
@getem
@getem
@getem
•
ፍቅራችንን
ድንበር ወሰን ላይገድበው
ሁለት ክልል ላይመጥነው
መገዳደል ፍት' ላይሆነው
በሽንፈትህ እሠይ ላልል
በሽንፈቴ እፎይ ላትል
ከቂም በቀል ፍቅር ላይበቅል
ልጅህ በእጄ ለምን ይሙት
ልጄስ በእጅህ ለምን ትሙት
እኔና አንተ እኮ
የአንድ እናት ልጆች
ወንድማማቾች
ያንድ አፈር አፈሮች
ርስት አፈሩማ
ይቅርም ከወደዚህ ይሂድም ወደዚያ
ያው ነው የኢትዮጵያ ያንድ አፈር መጠሪያ
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ ወዲህ ካለው የእስካሁኗ
ግዳይ ጥዬ በልጅህ ደም በጀግንነት ላልጠራ
ግዳይ ጥለህ በልጄ ደም ላትፎክር ላታቅራራ
ወንድም ገድለው ላይፎክሩ
ጀብዱ ሰርተው ላይኩራሩ
ያዘን ሙሾ ሊዘምሩ
እንደ ማተብ የእምነት ክር ፍቅር ድሩ ላይበጠስ
ባዘናችን ላትዘፍኑ በሞታችሁ ላንደንስ
ስሙር አይሁን ነጭ ሴራው ደስ አይበለው የጠላት ነፍስ
ልጅህ አይሙት በልጄ ጣት
ልጄም አይሙት በልጄ ቀስት
እኔና አንተ እኮ
ከዘመናት በፊት
በታሪክ በሃይማኖት
በባህል በትውፊት
በደስታ በችግር
ስም የለሽ ስመ-ጥር
በጋሻና በጦር ጀብደኛ ባላገር
ያንድ አያቶች ዘር የሁለት አፈር ሠፈር
ስም የለሽ በጥጋብ
ስመ-ጥር በረሃብ
እያሉ ሲተቹህ እያሉ ሲተቹን
በሙጫ ስድብ አጣብቀውን
ሲተቹን መተቸት ሲተቹን መተቸት
እንዳለ ስናውቀው እንዳለ ስታውቁት
ካንድ እናት ተወልደን በሁለት አባት አድገን
አንድ ውሃ ተራጭተን አንድ አፈር አቡክተን
ቃታ ስንሳሳብ
እሺ ላይለው ልብህ ደስ ላይለው ልቤን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
እኔና አንተ እኮ
ያንድ እናት ልጆች
ወንድምና እህቶች
ያንድ አፈር አፈሮች
እናም ወንድም ስማኝ ልስማህ
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ጸብ ሲያቃባ
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ
በመሞትህ ደስ ላይለኝ ውስጥ ልቤ እዥ ሊያነባ
የናቱ ልጅ ልጅህ ገድሎ ላያሰማ ጉሮ ወሸባ
ፍቅር እንጂ ግድባችን ወሰን አይኑር የደም ካባ
ይልቅስ ልንገርህ
ኩራቴ ኩራትህ
ታሪኬ ታሪክህ
የሚያመጻድቀኝ የሚያመጻድቅህ
የኔም ያባቴ ነው ያንተም የአባትህ
ከቢዘን ባስቀድስ ከግሸን ብትሰልስ
በአክሱም ብትኮራ
ብሸልል በአስመራ
ያንተ አባት አባቴ አባቴ አባትህ
የሚያመያጻድቀኝ የሚያጻድቀኝ ታሪኬ ታሪክህ
መሆኑን ስናውቀው መሆኑን ስታውቁት
በደምና ባጥንት በስጋ በጅማት በታሪክ በትውፊት
መንታ ናቸው ሲሉን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
በብቀላ ጸጸት በቀር ወንድም ጥሎ ላይፎክር
ጀግና ተብሎ ሜዳይ ላይኖር
በናቴ ልጅ በመጨከን እሺ ላይለኝ የልቤ በር
ወንድ ልጄን ግዳይ ጥለህ ላይፈታ የደምህ ስር
ካንድ ደብር አድገን በአንድ አስቀድሰን አንድ ዳዊት ደግመን
ካንድ መስጊድ ኖረን ባንድ ሰላት አድገን አንድ ቁርዓን ቀርተን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
ለጉዳትህ ተሰዉቼ
ላንተ ክብር ብዙ ሞቼ
ስላንተ ነጻነት ካገርህ ደሜ አለ
በናቕፋ ተራሮች እቅፍ የታዘለ
መጎዳቴን እምቢ ብለህ
ስለ ክብሬ ተሰውተህ
የሰጠኸኝ ክቡር ደምህ
ያንተም አጽም ዓድዋ አለ
ለጦቢያ ነጻነት ስለኔ የዋለ
መንታ ናቸው ሲሉን
ፍቅር ናቸው ሲሉን
እያወቁት ልቦናችን
ሁለት ክልል ላይመጥነን
ድንበር ወሰን ላይገድበን
መገዳደል ፍት' ላይሆነን
በሽንፈትህ ስንዘምር "በለው" ያሉን ሊታዘቡን
ነጭ ሴራ ወጣው ሊሉን
ስጋ ክንድህ ሲደማብህ ልቦናችን ሊያዝብን
ባለም ዜና ድላችንን ደም ጥማት ነው ብለው ሊሉን
ልጅህ በጄ ለምን ይሙት
ልጄስ በእጅህ ለምን ይሙት
ስማኝ ወገን
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ጸብ ሲያቃባ
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ
ርስት አፈሩማ
ይቅርም ከወደዚህ ይሂድም ወደዚያ
ያው ነው የኢትዮጵያ ያንድ አፈር መጠሪያ
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ ወዲህ ካለው የእስካሁኗ
እናም በሞቱት ሞት
እኔና አንተ አንሙት
እኔና አንተማ
የአንድ እናት ልጆች
ወንድምና እህቶች
ያንድ አፈር አፈሮች
#ኤፍሬም_ስዩም
@getem
@getem
@getem
👍1
#የአንድ_አፈር_አፈሮች
#ኤፍሬም_ስዩም
•
ፍቅራችንን
ድንበር ወሰን ላይገድበው
ሁለት ክልል ላይመጥነው
መገዳደል ፍት' ላይሆነው
በሽንፈትህ እሠይ ላልል
በሽንፈቴ እፎይ ላትል
ከቂም በቀል ፍቅር ላይበቅል
ልጅህ በእጄ ለምን ይሙት
ልጄስ በእጅህ ለምን ትሙት
እኔና አንተ እኮ
የአንድ እናት ልጆች
ወንድማማቾች
ያንድ አፈር አፈሮች
ርስት አፈሩማ
ይቅርም ከወደዚህ ይሂድም ወደዚያ
ያው ነው የኢትዮጵያ ያንድ አፈር መጠሪያ
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ ወዲህ ካለው የእስካሁኗ
ግዳይ ጥዬ በልጅህ ደም በጀግንነት ላልጠራ
ግዳይ ጥለህ በልጄ ደም ላትፎክር ላታቅራራ
ወንድም ገድለው ላይፎክሩ
ጀብዱ ሰርተው ላይኩራሩ
ያዘን ሙሾ ሊዘምሩ
እንደ ማተብ የእምነት ክር ፍቅር ድሩ ላይበጠስ
ባዘናችን ላትዘፍኑ በሞታችሁ ላንደንስ
ስሙር አይሁን ነጭ ሴራው ደስ አይበለው የጠላት ነፍስ
ልጅህ አይሙት በልጄ ጣት
ልጄም አይሙት በልጄ ቀስት
እኔና አንተ እኮ
ከዘመናት በፊት
በታሪክ በሃይማኖት
በባህል በትውፊት
በደስታ በችግር
ስም የለሽ ስመ-ጥር
በጋሻና በጦር ጀብደኛ ባላገር
ያንድ አያቶች ዘር የሁለት አፈር ሠፈር
ስም የለሽ በጥጋብ
ስመ-ጥር በረሃብ
እያሉ ሲተቹህ እያሉ ሲተቹን
በሙጫ ስድብ አጣብቀውን
ሲተቹን መተቸት ሲተቹን መተቸት
እንዳለ ስናውቀው እንዳለ ስታውቁት
ካንድ እናት ተወልደን በሁለት አባት አድገን
አንድ ውሃ ተራጭተን አንድ አፈር አቡክተን
ቃታ ስንሳሳብ
እሺ ላይለው ልብህ ደስ ላይለው ልቤን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
እኔና አንተ እኮ
ያንድ እናት ልጆች
ወንድምና እህቶች
ያንድ አፈር አፈሮች
እናም ወንድም ስማኝ ልስማህ
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ጸብ ሲያቃባ
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ
በመሞትህ ደስ ላይለኝ ውስጥ ልቤ እዥ ሊያነባ
የናቱ ልጅ ልጅህ ገድሎ ላያሰማ ጉሮ ወሸባ
ፍቅር እንጂ ግድባችን ወሰን አይኑር የደም ካባ
ይልቅስ ልንገርህ
ኩራቴ ኩራትህ
ታሪኬ ታሪክህ
የሚያመጻድቀኝ የሚያመጻድቅህ
የኔም ያባቴ ነው ያንተም የአባትህ
ከቢዘን ባስቀድስ ከግሸን ብትሰልስ
በአክሱም ብትኮራ
ብሸልል በአስመራ
ያንተ አባት አባቴ አባቴ አባትህ
የሚያመያጻድቀኝ የሚያጻድቀኝ ታሪኬ ታሪክህ
መሆኑን ስናውቀው መሆኑን ስታውቁት
በደምና ባጥንት በስጋ በጅማት በታሪክ በትውፊት
መንታ ናቸው ሲሉን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
በብቀላ ጸጸት በቀር ወንድም ጥሎ ላይፎክር
ጀግና ተብሎ ሜዳይ ላይኖር
በናቴ ልጅ በመጨከን እሺ ላይለኝ የልቤ በር
ወንድ ልጄን ግዳይ ጥለህ ላይፈታ የደምህ ስር
ካንድ ደብር አድገን በአንድ አስቀድሰን አንድ ዳዊት ደግመን
ካንድ መስጊድ ኖረን ባንድ ሰላት አድገን አንድ ቁርዓን ቀርተን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
ለጉዳትህ ተሰዉቼ
ላንተ ክብር ብዙ ሞቼ
ስላንተ ነጻነት ካገርህ ደሜ አለ
በናቕፋ ተራሮች እቅፍ የታዘለ
መጎዳቴን እምቢ ብለህ
ስለ ክብሬ ተሰውተህ
የሰጠኸኝ ክቡር ደምህ
ያንተም አጽም ዓድዋ አለ
ለጦቢያ ነጻነት ስለኔ የዋለ
መንታ ናቸው ሲሉን
ፍቅር ናቸው ሲሉን
እያወቁት ልቦናችን
ሁለት ክልል ላይመጥነን
ድንበር ወሰን ላይገድበን
መገዳደል ፍት' ላይሆነን
በሽንፈትህ ስንዘምር "በለው" ያሉን ሊታዘቡን
ነጭ ሴራ ወጣው ሊሉን
ስጋ ክንድህ ሲደማብህ ልቦናችን ሊያዝብን
ባለም ዜና ድላችንን ደም ጥማት ነው ብለው ሊሉን
ልጅህ በጄ ለምን ይሙት
ልጄስ በእጅህ ለምን ይሙት
ስማኝ ወገን
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ጸብ ሲያቃባ
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ
ርስት አፈሩማ
ይቅርም ከወደዚህ ይሂድም ወደዚያ
ያው ነው የኢትዮጵያ ያንድ አፈር መጠሪያ
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ ወዲህ ካለው የእስካሁኗ
እናም በሞቱት ሞት
እኔና አንተ አንሙት
እኔና አንተማ
የአንድ እናት ልጆች
ወንድምና እህቶች
ያንድ አፈር አፈሮች
•
©ገጣሚ #ኤፍሬም_ስዩም
@getem
@getem
#ኤፍሬም_ስዩም
•
ፍቅራችንን
ድንበር ወሰን ላይገድበው
ሁለት ክልል ላይመጥነው
መገዳደል ፍት' ላይሆነው
በሽንፈትህ እሠይ ላልል
በሽንፈቴ እፎይ ላትል
ከቂም በቀል ፍቅር ላይበቅል
ልጅህ በእጄ ለምን ይሙት
ልጄስ በእጅህ ለምን ትሙት
እኔና አንተ እኮ
የአንድ እናት ልጆች
ወንድማማቾች
ያንድ አፈር አፈሮች
ርስት አፈሩማ
ይቅርም ከወደዚህ ይሂድም ወደዚያ
ያው ነው የኢትዮጵያ ያንድ አፈር መጠሪያ
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ ወዲህ ካለው የእስካሁኗ
ግዳይ ጥዬ በልጅህ ደም በጀግንነት ላልጠራ
ግዳይ ጥለህ በልጄ ደም ላትፎክር ላታቅራራ
ወንድም ገድለው ላይፎክሩ
ጀብዱ ሰርተው ላይኩራሩ
ያዘን ሙሾ ሊዘምሩ
እንደ ማተብ የእምነት ክር ፍቅር ድሩ ላይበጠስ
ባዘናችን ላትዘፍኑ በሞታችሁ ላንደንስ
ስሙር አይሁን ነጭ ሴራው ደስ አይበለው የጠላት ነፍስ
ልጅህ አይሙት በልጄ ጣት
ልጄም አይሙት በልጄ ቀስት
እኔና አንተ እኮ
ከዘመናት በፊት
በታሪክ በሃይማኖት
በባህል በትውፊት
በደስታ በችግር
ስም የለሽ ስመ-ጥር
በጋሻና በጦር ጀብደኛ ባላገር
ያንድ አያቶች ዘር የሁለት አፈር ሠፈር
ስም የለሽ በጥጋብ
ስመ-ጥር በረሃብ
እያሉ ሲተቹህ እያሉ ሲተቹን
በሙጫ ስድብ አጣብቀውን
ሲተቹን መተቸት ሲተቹን መተቸት
እንዳለ ስናውቀው እንዳለ ስታውቁት
ካንድ እናት ተወልደን በሁለት አባት አድገን
አንድ ውሃ ተራጭተን አንድ አፈር አቡክተን
ቃታ ስንሳሳብ
እሺ ላይለው ልብህ ደስ ላይለው ልቤን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
እኔና አንተ እኮ
ያንድ እናት ልጆች
ወንድምና እህቶች
ያንድ አፈር አፈሮች
እናም ወንድም ስማኝ ልስማህ
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ጸብ ሲያቃባ
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ
በመሞትህ ደስ ላይለኝ ውስጥ ልቤ እዥ ሊያነባ
የናቱ ልጅ ልጅህ ገድሎ ላያሰማ ጉሮ ወሸባ
ፍቅር እንጂ ግድባችን ወሰን አይኑር የደም ካባ
ይልቅስ ልንገርህ
ኩራቴ ኩራትህ
ታሪኬ ታሪክህ
የሚያመጻድቀኝ የሚያመጻድቅህ
የኔም ያባቴ ነው ያንተም የአባትህ
ከቢዘን ባስቀድስ ከግሸን ብትሰልስ
በአክሱም ብትኮራ
ብሸልል በአስመራ
ያንተ አባት አባቴ አባቴ አባትህ
የሚያመያጻድቀኝ የሚያጻድቀኝ ታሪኬ ታሪክህ
መሆኑን ስናውቀው መሆኑን ስታውቁት
በደምና ባጥንት በስጋ በጅማት በታሪክ በትውፊት
መንታ ናቸው ሲሉን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
በብቀላ ጸጸት በቀር ወንድም ጥሎ ላይፎክር
ጀግና ተብሎ ሜዳይ ላይኖር
በናቴ ልጅ በመጨከን እሺ ላይለኝ የልቤ በር
ወንድ ልጄን ግዳይ ጥለህ ላይፈታ የደምህ ስር
ካንድ ደብር አድገን በአንድ አስቀድሰን አንድ ዳዊት ደግመን
ካንድ መስጊድ ኖረን ባንድ ሰላት አድገን አንድ ቁርዓን ቀርተን
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን
ለጉዳትህ ተሰዉቼ
ላንተ ክብር ብዙ ሞቼ
ስላንተ ነጻነት ካገርህ ደሜ አለ
በናቕፋ ተራሮች እቅፍ የታዘለ
መጎዳቴን እምቢ ብለህ
ስለ ክብሬ ተሰውተህ
የሰጠኸኝ ክቡር ደምህ
ያንተም አጽም ዓድዋ አለ
ለጦቢያ ነጻነት ስለኔ የዋለ
መንታ ናቸው ሲሉን
ፍቅር ናቸው ሲሉን
እያወቁት ልቦናችን
ሁለት ክልል ላይመጥነን
ድንበር ወሰን ላይገድበን
መገዳደል ፍት' ላይሆነን
በሽንፈትህ ስንዘምር "በለው" ያሉን ሊታዘቡን
ነጭ ሴራ ወጣው ሊሉን
ስጋ ክንድህ ሲደማብህ ልቦናችን ሊያዝብን
ባለም ዜና ድላችንን ደም ጥማት ነው ብለው ሊሉን
ልጅህ በጄ ለምን ይሙት
ልጄስ በእጅህ ለምን ይሙት
ስማኝ ወገን
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ጸብ ሲያቃባ
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ
ርስት አፈሩማ
ይቅርም ከወደዚህ ይሂድም ወደዚያ
ያው ነው የኢትዮጵያ ያንድ አፈር መጠሪያ
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ ወዲህ ካለው የእስካሁኗ
እናም በሞቱት ሞት
እኔና አንተ አንሙት
እኔና አንተማ
የአንድ እናት ልጆች
ወንድምና እህቶች
ያንድ አፈር አፈሮች
•
©ገጣሚ #ኤፍሬም_ስዩም
@getem
@getem
ስንብት
#ኤፍሬም_ስዩም
አሁን
በጣም ከባድ ዝናብ መዝነቡን ጀምሯል
አየሩ ይከብዳል
ትንሽ በረድ ይላል።
በይ እንደልማድሽ
በርሽን ቆልፈሽ. . . ጋቢ ደረብ አርገሽ
መስኮትሽን ዘግተሽ ሳሎን ከሶፋው ላይ ትንሽ አረፍ በይ
ከዚያም ግድግዳው ላይ
የተሰቀለውን ፎቶሽን ልብ በይ
በዚህ ዕድሜሽ ነበር. . . ?
አፍቅሬሽ የነበር።
በዚህ ዕድሜሽ ነበር. . . ትተሽኝ የነበር
በዚህ ጊዜ ነበር . . .
ፍቅር እዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር. . .
የሚል ውብ ግጥሜን ፅፌልሽ የነበር።
በዚህ ዕድሜሽ ነበር።
-
አሁን
አሁን ግና
እስከ አሁን ድረስ ከነገርኩሽ ይልቅ ያልነገርኩሽ ነገር
ልብ ያላልሽው ምስጢር
ጊዜ አስረጅቶት
የግድግዳሽ ሰዓት መስራት እንዳቆመ እርሱን ብቻ ነበር።
ምንም ወዳጄ ሆይ. . . በይ እንግዲህ ቻዎ! ! !
ቻዎ!
@getem
@getem
@getem
#ኤፍሬም_ስዩም
አሁን
በጣም ከባድ ዝናብ መዝነቡን ጀምሯል
አየሩ ይከብዳል
ትንሽ በረድ ይላል።
በይ እንደልማድሽ
በርሽን ቆልፈሽ. . . ጋቢ ደረብ አርገሽ
መስኮትሽን ዘግተሽ ሳሎን ከሶፋው ላይ ትንሽ አረፍ በይ
ከዚያም ግድግዳው ላይ
የተሰቀለውን ፎቶሽን ልብ በይ
በዚህ ዕድሜሽ ነበር. . . ?
አፍቅሬሽ የነበር።
በዚህ ዕድሜሽ ነበር. . . ትተሽኝ የነበር
በዚህ ጊዜ ነበር . . .
ፍቅር እዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር. . .
የሚል ውብ ግጥሜን ፅፌልሽ የነበር።
በዚህ ዕድሜሽ ነበር።
-
አሁን
አሁን ግና
እስከ አሁን ድረስ ከነገርኩሽ ይልቅ ያልነገርኩሽ ነገር
ልብ ያላልሽው ምስጢር
ጊዜ አስረጅቶት
የግድግዳሽ ሰዓት መስራት እንዳቆመ እርሱን ብቻ ነበር።
ምንም ወዳጄ ሆይ. . . በይ እንግዲህ ቻዎ! ! !
ቻዎ!
@getem
@getem
@getem
(ኤፍሬም ስዩም)
:- እውነት ወደ ኋላ
ገንዘብ ካለው ጋራ
ፍቅር አይኖርም ወይ ብለሽ ጠይቀሻል!?
እኔ ያንቺን እንጂ
የሌላን አላልኩም እጅግ ተሳስተሻል
አይኖርም አላልኩም...አይጠፋም ይኖራል
ይኖራል
ይኖራል
ግን?...
ከባለሐብት ጋር
ተፋቅራ 'ምናያት የቷም አይነት እንስት...
'ምን ' ትሁንም ' ምንም '
የሕይወት ታሪኳን ወደኋላ ሄደን ....ጥቂት ብንገመግም
አንድ ቡና ለሁለት ....
አብራ የጠጣችው አንድ አፍቃሪ አታጣም ።
#ኤፍሬም ስዩም
@getem
@getem
@beckyalexander
:- እውነት ወደ ኋላ
ገንዘብ ካለው ጋራ
ፍቅር አይኖርም ወይ ብለሽ ጠይቀሻል!?
እኔ ያንቺን እንጂ
የሌላን አላልኩም እጅግ ተሳስተሻል
አይኖርም አላልኩም...አይጠፋም ይኖራል
ይኖራል
ይኖራል
ግን?...
ከባለሐብት ጋር
ተፋቅራ 'ምናያት የቷም አይነት እንስት...
'ምን ' ትሁንም ' ምንም '
የሕይወት ታሪኳን ወደኋላ ሄደን ....ጥቂት ብንገመግም
አንድ ቡና ለሁለት ....
አብራ የጠጣችው አንድ አፍቃሪ አታጣም ።
#ኤፍሬም ስዩም
@getem
@getem
@beckyalexander
ይሁዳ
(#ኤፍሬም ስዩም)
እኚያ ጓደኞችህ ጴጥሮስ ወይ ዮሀንስ
ናትናኤል ፊሊጶስ
ቀራጩ ማቲዎስ
ሌሎቹም በሙሉ
ጌታ ሆይ እኔ እሆን? እኔ እሆን? ሲሉ
አይደለም ሲባሉ
የእነሱ እናቶች በደስታ ሲዘሉ
ምናለች እናትህ አንተን ሲጠቁምህ
ከደሙ ላይ ነክሮ ምልክት ሲያደርግህ
ዐይኗ ምን አነባ ልቧ ምን ታዘበ
ከናንተ አንደኛው ዲያቢሎስ ነው ሲልህ እግር እያጠበ
ከየት ነው ትዕግስቷ
የእናትህ አንጀቷ
የመቻል ፅናቷ
ምናለች ? ይሁዳ ምናለች እናትህ? አንተን ሲጠቁምህ?
ምልክት ሲያደርግህ
እንደ ማሪያም አለቀሰች?
ለኔ ስትል ብላ ወድቃ ተማፀነች?
ወይንስ ለልጇ ያንተ እናት ጨካኝ ነች?
ምናለች እናትህ ታማኝ ነው ስትል ይሁዳ ያለችህ
የሰው ልጅ ይሰቅሉታል
ሰቅለው ይገድሉታል
ቢገድሉት ይነሳል
ግና ላሰቀለው
ግና ላስገደለው
ወዮለት ለዛ ሰው
ብሎ ሲናገርህ
ምናለች እናትህ አንተን ሲጠቁምህ
ከደሙ ላይ ነክሮ ምልክት ሲያደርግህ
እናትህ መለሰች
እንዲህ ተናገረች?
እውነት ነው ጌታ ሆይ ባይወለድ በተሻለው
ግና እንድወልደው እናቱ እንድሰኝ ማሕፀኔን ብትፈታው
በአርኣያ በአምሳልህ ሰው አርገህ ብትሰራው
የወለድኩስ እኔ የፈጠረው ማነው
ብላለት መለሰች
ወይንስ ምን አለች
ምን አለች እናትህ?
አንተን ሲጠቁምህ
ምልክት ሲያረግህ!!
@getem
@getem
@beckyalexander
(#ኤፍሬም ስዩም)
እኚያ ጓደኞችህ ጴጥሮስ ወይ ዮሀንስ
ናትናኤል ፊሊጶስ
ቀራጩ ማቲዎስ
ሌሎቹም በሙሉ
ጌታ ሆይ እኔ እሆን? እኔ እሆን? ሲሉ
አይደለም ሲባሉ
የእነሱ እናቶች በደስታ ሲዘሉ
ምናለች እናትህ አንተን ሲጠቁምህ
ከደሙ ላይ ነክሮ ምልክት ሲያደርግህ
ዐይኗ ምን አነባ ልቧ ምን ታዘበ
ከናንተ አንደኛው ዲያቢሎስ ነው ሲልህ እግር እያጠበ
ከየት ነው ትዕግስቷ
የእናትህ አንጀቷ
የመቻል ፅናቷ
ምናለች ? ይሁዳ ምናለች እናትህ? አንተን ሲጠቁምህ?
ምልክት ሲያደርግህ
እንደ ማሪያም አለቀሰች?
ለኔ ስትል ብላ ወድቃ ተማፀነች?
ወይንስ ለልጇ ያንተ እናት ጨካኝ ነች?
ምናለች እናትህ ታማኝ ነው ስትል ይሁዳ ያለችህ
የሰው ልጅ ይሰቅሉታል
ሰቅለው ይገድሉታል
ቢገድሉት ይነሳል
ግና ላሰቀለው
ግና ላስገደለው
ወዮለት ለዛ ሰው
ብሎ ሲናገርህ
ምናለች እናትህ አንተን ሲጠቁምህ
ከደሙ ላይ ነክሮ ምልክት ሲያደርግህ
እናትህ መለሰች
እንዲህ ተናገረች?
እውነት ነው ጌታ ሆይ ባይወለድ በተሻለው
ግና እንድወልደው እናቱ እንድሰኝ ማሕፀኔን ብትፈታው
በአርኣያ በአምሳልህ ሰው አርገህ ብትሰራው
የወለድኩስ እኔ የፈጠረው ማነው
ብላለት መለሰች
ወይንስ ምን አለች
ምን አለች እናትህ?
አንተን ሲጠቁምህ
ምልክት ሲያረግህ!!
@getem
@getem
@beckyalexander