#ሰማያዊት_ቅኔ
፡
በመለኮት ፈትል
ሸማኔ ፈጣሪ ጥበብሽን ቋጭቶ
በሰማይ ሸራ ላይ
ጥለት ሰንደቅሽን እንዲታይ ዘርግቶ
ከህያው መንበሩ
በገዘፈ ክብር ደርሶ ቢያነግስሽም
ባ'ለም ቋንቋ ፍቺ
ከኀላ ተቀምጠሽ ማንም አላየሽም፡፡
፡
ነገሩ እውነት ነው፡፡
፡
የገዛ ልጆችሽ
ውበታም ፊትሽ ላይ ምራቅ እየተፋን
እኛው ጭርታም አርገን
ጭርታም ናት እያልን ስናማሽ ካልከፋን
ሌላው እየናቀሽ
ክብርሽን ቢያወርደው ከቶ ምን ይገርማል
ቢገባን እውነቱ
ትልቅ ሆነው መቅለል ከሞት በላይ ያማል፡፡
፡
አይገርምሽም አይደል?
፡
በባዶ ማንነት
የኛ መዘላበድ እንዲህ መተናነስ
ባልተጨበጠ ውል
በገዛ ግብራችን ከስመን መፈራረስ?
፡
ለምን ይገርምሻል!!
፡
አንቺ እንደው አንቺ ነሽ
በዘመን መለወጥ የማትለወጪ የፈጣሪ ዙፋን
እኛ ነን ሞኞቹ
ያ ሰፊው ጎዳናሽ ጠቦን የሚያጋፋን፡፡
ምናለ በደፋን!!!
#ልብ_አልባው_ገጣሚ
@getem
@getem
፡
በመለኮት ፈትል
ሸማኔ ፈጣሪ ጥበብሽን ቋጭቶ
በሰማይ ሸራ ላይ
ጥለት ሰንደቅሽን እንዲታይ ዘርግቶ
ከህያው መንበሩ
በገዘፈ ክብር ደርሶ ቢያነግስሽም
ባ'ለም ቋንቋ ፍቺ
ከኀላ ተቀምጠሽ ማንም አላየሽም፡፡
፡
ነገሩ እውነት ነው፡፡
፡
የገዛ ልጆችሽ
ውበታም ፊትሽ ላይ ምራቅ እየተፋን
እኛው ጭርታም አርገን
ጭርታም ናት እያልን ስናማሽ ካልከፋን
ሌላው እየናቀሽ
ክብርሽን ቢያወርደው ከቶ ምን ይገርማል
ቢገባን እውነቱ
ትልቅ ሆነው መቅለል ከሞት በላይ ያማል፡፡
፡
አይገርምሽም አይደል?
፡
በባዶ ማንነት
የኛ መዘላበድ እንዲህ መተናነስ
ባልተጨበጠ ውል
በገዛ ግብራችን ከስመን መፈራረስ?
፡
ለምን ይገርምሻል!!
፡
አንቺ እንደው አንቺ ነሽ
በዘመን መለወጥ የማትለወጪ የፈጣሪ ዙፋን
እኛ ነን ሞኞቹ
ያ ሰፊው ጎዳናሽ ጠቦን የሚያጋፋን፡፡
ምናለ በደፋን!!!
#ልብ_አልባው_ገጣሚ
@getem
@getem
❤1