#እምወድሽዋ!❤ ቅዳሜዋ!❤ ሸጋዬዋ!
..ዛሬ ደርባባዋ ቅዳሚት ነች....ለክብሯ ሲባል አንድ ሸላይ የሆነ ግጥም ነው ነው የምንገባበዘው....ስለ ግጥሙ ሀሳብ እና ስለ ግጥሙ የቃላት ውበት ላወራ ነበር ግን....እናንተው አንብባችሁት ተደመሙበት #ቅዳሚታቹን ግጥሙን ደጋግሞ በማንበብ እና ለወዳጆቻቹ በመጋበዝ ተገማሸሩበት....#ለኔም በአሪፍ ድምፅ ተነቦ ቢላክልኝ አልጠላም..☺ መቼም ምን አይነት ግጥም ቢሆነው እንዲህ በጠዋቱ ተነስቶ ሚሸልልብን ማለታቹ አይቀርም....እንግድያው ፍረዱኝ...ይኸው እንካቹ...❤
"ስራህ ?"ስባል
እንዲህ እመልሳለሁ
ሀዘንን ማባበል
ለሚያለቅሱ ነፍሶች በገና ማቀበል
" ስራ ?" ህ ስባል
ከደስታ መቃጠር
ለሰዓሊ ሸራ ዘርግቶ መወጠር
" ስራህ ? " ስባል
መቃ መጠራረብ
ላንድ ገጣሚ ነፍስ መድ ከፊት ማቅረብ
ከየት ስባል
ምን እመልሳለሁ
እንዴት ስባል ብቻ መናገረ አውቃለሁ
ብኩን ሰው ነበርኩኝ - ተሰበርኩ እንደ ገል
የማለውቀውን ነፍስ ጀመርኩኝ ማገልገል
ነፍሴንም
ገደልኳት
ሰውቼ አቀርብኳት
የቀላይ መታሪ - ታንኳ ሁኚ አልኳት
ያኔም ነው እንደ አረሆ- እንደኮከብ ጧሪ
ከፍ ብሎ ቋሚ - ናፍቆት አጋፋሪ
ብቻዬን የሆንኩት
እንደ እልፍኝ አስከልካይ ዘብ ሆኜ የቆምኩት
ጮራ የበተንኩት
ነፍስ ያገለገልኩት
አየህ አይገለፅም ማደሪያው
የወዲያ ወዲያው
ቅፅር ካለፈረሱ
ሀዘን ካልሰፈሩ
ያን እግረ ሙቅ ገንቦ - ደፍረው ካልሰበሩ
አይነገር
በቃል አይጋገር
ለተራ ተርታ ሰው - አለው ማደናገር
ይሄው ነው
በገናውን በስልት
ቀሰሙንም በስልት
ዋሽንቱንም በስልት
ሳቀርብ እያየህኝ
እኔ ነኝ የምፅፍ
እኔ ነኝ የማዜም
በዋሽንት የማፏጭ - በተብሳ መቃ
ብልህ እንዳትለኝ - አንትንገረኝ በቃ
እኔው እያጋፍርኩ
መሪ - ጌታ እያለኝ የጥበብ አለቃ ::
📝ሰለሀዲን አሊ
ደመቅመቅ ያለ ቅዳሜ ጀባታ!❤
@getem
@getem
@Nagayta
..ዛሬ ደርባባዋ ቅዳሚት ነች....ለክብሯ ሲባል አንድ ሸላይ የሆነ ግጥም ነው ነው የምንገባበዘው....ስለ ግጥሙ ሀሳብ እና ስለ ግጥሙ የቃላት ውበት ላወራ ነበር ግን....እናንተው አንብባችሁት ተደመሙበት #ቅዳሚታቹን ግጥሙን ደጋግሞ በማንበብ እና ለወዳጆቻቹ በመጋበዝ ተገማሸሩበት....#ለኔም በአሪፍ ድምፅ ተነቦ ቢላክልኝ አልጠላም..☺ መቼም ምን አይነት ግጥም ቢሆነው እንዲህ በጠዋቱ ተነስቶ ሚሸልልብን ማለታቹ አይቀርም....እንግድያው ፍረዱኝ...ይኸው እንካቹ...❤
"ስራህ ?"ስባል
እንዲህ እመልሳለሁ
ሀዘንን ማባበል
ለሚያለቅሱ ነፍሶች በገና ማቀበል
" ስራ ?" ህ ስባል
ከደስታ መቃጠር
ለሰዓሊ ሸራ ዘርግቶ መወጠር
" ስራህ ? " ስባል
መቃ መጠራረብ
ላንድ ገጣሚ ነፍስ መድ ከፊት ማቅረብ
ከየት ስባል
ምን እመልሳለሁ
እንዴት ስባል ብቻ መናገረ አውቃለሁ
ብኩን ሰው ነበርኩኝ - ተሰበርኩ እንደ ገል
የማለውቀውን ነፍስ ጀመርኩኝ ማገልገል
ነፍሴንም
ገደልኳት
ሰውቼ አቀርብኳት
የቀላይ መታሪ - ታንኳ ሁኚ አልኳት
ያኔም ነው እንደ አረሆ- እንደኮከብ ጧሪ
ከፍ ብሎ ቋሚ - ናፍቆት አጋፋሪ
ብቻዬን የሆንኩት
እንደ እልፍኝ አስከልካይ ዘብ ሆኜ የቆምኩት
ጮራ የበተንኩት
ነፍስ ያገለገልኩት
አየህ አይገለፅም ማደሪያው
የወዲያ ወዲያው
ቅፅር ካለፈረሱ
ሀዘን ካልሰፈሩ
ያን እግረ ሙቅ ገንቦ - ደፍረው ካልሰበሩ
አይነገር
በቃል አይጋገር
ለተራ ተርታ ሰው - አለው ማደናገር
ይሄው ነው
በገናውን በስልት
ቀሰሙንም በስልት
ዋሽንቱንም በስልት
ሳቀርብ እያየህኝ
እኔ ነኝ የምፅፍ
እኔ ነኝ የማዜም
በዋሽንት የማፏጭ - በተብሳ መቃ
ብልህ እንዳትለኝ - አንትንገረኝ በቃ
እኔው እያጋፍርኩ
መሪ - ጌታ እያለኝ የጥበብ አለቃ ::
📝ሰለሀዲን አሊ
ደመቅመቅ ያለ ቅዳሜ ጀባታ!❤
@getem
@getem
@Nagayta
👍2