#የጡንቸኞች_ዓለም
.
ፍትሕ ዓይን የላትም ፡ አይታ እንዳታደላ
በጫንቃችን ቆመች ፡ መንገድ ምሩኝ ብላ!
-
ኧረ አሁንስ ፈራን ...
እንቅልፍ ያዛት መሰል ፡ ሚዛኑ እንዳይወድቃት
አትወርድም አትፈርድም ፡ ብናይ ብንጠብቃት፨
---------------------------//-------------------------
(በርናባስ ከበደ)
-
(In Picture; a Sculpture titled 'Survival of the Fattest' , Created by Gens Galschiot)
@getem
@getem
@getem
.
ፍትሕ ዓይን የላትም ፡ አይታ እንዳታደላ
በጫንቃችን ቆመች ፡ መንገድ ምሩኝ ብላ!
-
ኧረ አሁንስ ፈራን ...
እንቅልፍ ያዛት መሰል ፡ ሚዛኑ እንዳይወድቃት
አትወርድም አትፈርድም ፡ ብናይ ብንጠብቃት፨
---------------------------//-------------------------
(በርናባስ ከበደ)
-
(In Picture; a Sculpture titled 'Survival of the Fattest' , Created by Gens Galschiot)
@getem
@getem
@getem
ግጥም ብቻ 📘
Photo
"ዘምባባ ዛሬ በገበያ ላይ ውላለች "
ምንም ይሁን ማንም ዘምባባን የማይጠብቃት አይኖርም። እርግጥ ነው ምግባርን የማታውቁት ልትኖሩ ትችላላችሁ። ወደ ፊት ግን ታውቁታላችሁ፣ ታደንቁታላችሁ፣ ትደነቁበታላችሁ፤ ትደሰቱበታላችሁ፣ ትናፍቂታላችሁም ጭምር። እሱ ከዚህም በላይ ነው። አሁን የበኩር ድክ ድኩን ዛሬ ጀባ ብሎናል ተሰልፈን እንሻማት። አንብባችሁ የምትወዱትና ደጋግማችሁ የምታነቧት መፅሐፍ እንደምትሆን አንጠራጠርም።
#ዘምባባ
አዲስ መፅሐፍ
በምግባር ሲራጅ
@getem
@getem
@getem
ምንም ይሁን ማንም ዘምባባን የማይጠብቃት አይኖርም። እርግጥ ነው ምግባርን የማታውቁት ልትኖሩ ትችላላችሁ። ወደ ፊት ግን ታውቁታላችሁ፣ ታደንቁታላችሁ፣ ትደነቁበታላችሁ፤ ትደሰቱበታላችሁ፣ ትናፍቂታላችሁም ጭምር። እሱ ከዚህም በላይ ነው። አሁን የበኩር ድክ ድኩን ዛሬ ጀባ ብሎናል ተሰልፈን እንሻማት። አንብባችሁ የምትወዱትና ደጋግማችሁ የምታነቧት መፅሐፍ እንደምትሆን አንጠራጠርም።
#ዘምባባ
አዲስ መፅሐፍ
በምግባር ሲራጅ
@getem
@getem
@getem
ተፈወሽ🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ግን እማማዬ፣
በፊት እንዴት ነበርሽ?
ከኖህ ጊዜ አንስቶ እስከ ሙሴ ድረስ፣
ዘመናትን ነጉዶ፣
ከነ አክሱም ጥበብ አድዋ እስከ
መድረስ።
እንዴት ነበርሽ ያኔ?
ዮሐንስ መተማ ላይ አንገቱን ሲሰጥሽ፣
ቴዎድሮስ መቅደላ ላይ፣
ራሱን በራሱ ሰውቶ ሲለይሽ።
እንዴት ነበርሽ ያኔ?
በእንስቶች ተምሳሌት በጣይቱ
ዘመን፣
የጥቁር ህዝብ ደም በአኩሪ ድል
ሲተመን፣
እስቲ ልጠይቅሽ....
አሁን ያለው እሳት ያኔ ከነበረ፣
ከአንድ ማህጸን የወጡ ልጆችን
ሲያፋጅ ከኖረ፣
ዳግም ልጠይቅሽ...
ፍቅር የሚሉት ግን ያኔ ምን ነበረ?
ከ 'መዋደድ' ትርጉም
መባላት ወደ ሚል መቼ ተቀየረ?
አሁን ግን እምዬ ለትንሳኤሽ ኑሪ፣
ኢትዮጵያ ተብለሽ በስም ብቻ አትቅሪ፣
ባለሽበት ቆመሽ...
ታናሽ ሞት በሆነው በእንቅልፍ
አትፍዘዢ!
ግብሽን ለመምታት...
የጥላቻ ሳይሆን የፍቅር ቀስት ያዢ፣
ይህን ግን አስቢ...
የተበከለ እርሾ ከጎንሽ እንዳለ፣
የዘር ፍቅር እሳት...
በፀደቁ አበቦች መሐል የበቀለ፣
ደግመሽም ተመልከች...
በሁለት ዛፎሽ መሐል ተተክለሽ
እንደቆምሽ፣
አንዱ ዛፍ ብልህ ነው...
ለስኬቱ ማማ ሽቅብ ሚመለከት፣
አንዱ ግን እሾህ ነው...
አንቆ የሚያስቀርሽ ከጸጋሽ በረከት
መንታ ልቦች ይዘሽ...
ደግነት ከክፋት ተፈራረቁብሽ፣
አሁን ደግሞ ብሶ...
ክፋት ከበደና ሚዛኑን ደፋብሽ።
አንዲት ምስኪን ዶሮ...
እንቁላሏን ልትጥል ቦታዋ
ጠፍቶባት፣
ቦታ ብታገኝም...
ሳትጥለው ቀረች ትንሽ አቅም
አንሷት፣
ዶሮዋ አንቺው ነሽ
እንቁላሏ ደግሞ ያሰብሻት ራእይሽ
ሽቅብ ከደረሱት
ከዘመኑት ተርታ የምታሰልፍሽ...
ቦታ ያልኩሽ ደግሞ..
ጥቂቶች ሚያምኑበት የስራው
ባህል ነው፣
ጥሪት አስገኝቶ....
ከስኬት ማማ ላይ ከፍ አርጎ
የሚያቆመው፣
ነገር ግን ይህ ሁሉ...
ትንሽ አቅም ያልኩት ፍቅርን ተነፈገ
'ታጥቦ ጭቃ' ተረበት
ፍቅርን በተራብሽው በአንቺ ላይ
ሰረገ።
ስለዚህ እምዬ...
ከጸጋሽ ተገፈሽ ባዶ እንዳትቀሪ
ጨለማው ተገፎ
ጸሐይ እንድትወጣ
የፍቅር እህል ዝሪ..
ሞትሽን አላይም...
በዘር ፍቅር እሳት መጠበስሽ ይብቃ፣
ቁስልሽን ላክመው ..
ካሰረኝ እንቅልፌ ከሰመመን ልንቃ፣
ይብቃሽ እማማዬ
የሀዘን ጠባሳሽ ወደ እኔ ይገልበጥ
እስቲ አንቺ ቀና በይ...
በጭንቀት ባህር ውስጥ እኔ
ቁልቁል ልስመጥ፣
መራቆትሽ ይብቃ!!!
የፍቅርን ሸማ ደራርበሽ ልበሺ፣
ዳገቱ መሐል ላይ..
እኔ ልውደቅና እስቲ አንቺ ጨርሺ፣
የተስፋ ጸሐይሽ...
ዳግም እንድትወጣ አምላክን ለምኚ፣
እኔ ይጨልምብኝ አንቺ ግን
አግኚ፣
በዚህ በአዲስ ዘመን...
አንድ የሚያደርግሽን ብሩህ ፍቅር
ይስጥሽ
እኔ መውደድ ልጣ አንቺን ግን
አይራብሽ
በእግሮችሽ መሐል...
ቆልፎ ያስቀረሽ የክፋት መርዝ
ይውጣ፣
የፍቅር ዶፍ ይዝነብ
አንቺ እፎይ ብለሽ እኔ ሰላም ልጣ፣
መንገዳገድ ይብቃ
በሰላም ምርኩዝሽ በሁለት እግርሽ ሂጂ
እኔ አንካሳ ልሁን መጓዝ የናፈቀሽ
አንቺ ተራመጂ..
ይብቃሽ እማማዬ🇪🇹
ብርሀን ተመልከች ይሄ ድቅድቅ
አልፎ፣
አንቺ ፈገግ በይ የእኔ ጥርስ ረግፎ፣
የረገፈው ጸጉርሽ...
ዳግም እንዲበቅል ያግዘው
ይህ ፍቅር፣
መክሳትሽም ይብቃ
ስጋዬን ውሰጂና የእኔ አጥንት
ይቅር...
«ኢትዮጵያ ታበጽሕ
ዕደዊሀ ሀበ እግዚአብሔር»
✍ዮሐንስ ገርማሜ
@getem
@getem
@getem
ግን እማማዬ፣
በፊት እንዴት ነበርሽ?
ከኖህ ጊዜ አንስቶ እስከ ሙሴ ድረስ፣
ዘመናትን ነጉዶ፣
ከነ አክሱም ጥበብ አድዋ እስከ
መድረስ።
እንዴት ነበርሽ ያኔ?
ዮሐንስ መተማ ላይ አንገቱን ሲሰጥሽ፣
ቴዎድሮስ መቅደላ ላይ፣
ራሱን በራሱ ሰውቶ ሲለይሽ።
እንዴት ነበርሽ ያኔ?
በእንስቶች ተምሳሌት በጣይቱ
ዘመን፣
የጥቁር ህዝብ ደም በአኩሪ ድል
ሲተመን፣
እስቲ ልጠይቅሽ....
አሁን ያለው እሳት ያኔ ከነበረ፣
ከአንድ ማህጸን የወጡ ልጆችን
ሲያፋጅ ከኖረ፣
ዳግም ልጠይቅሽ...
ፍቅር የሚሉት ግን ያኔ ምን ነበረ?
ከ 'መዋደድ' ትርጉም
መባላት ወደ ሚል መቼ ተቀየረ?
አሁን ግን እምዬ ለትንሳኤሽ ኑሪ፣
ኢትዮጵያ ተብለሽ በስም ብቻ አትቅሪ፣
ባለሽበት ቆመሽ...
ታናሽ ሞት በሆነው በእንቅልፍ
አትፍዘዢ!
ግብሽን ለመምታት...
የጥላቻ ሳይሆን የፍቅር ቀስት ያዢ፣
ይህን ግን አስቢ...
የተበከለ እርሾ ከጎንሽ እንዳለ፣
የዘር ፍቅር እሳት...
በፀደቁ አበቦች መሐል የበቀለ፣
ደግመሽም ተመልከች...
በሁለት ዛፎሽ መሐል ተተክለሽ
እንደቆምሽ፣
አንዱ ዛፍ ብልህ ነው...
ለስኬቱ ማማ ሽቅብ ሚመለከት፣
አንዱ ግን እሾህ ነው...
አንቆ የሚያስቀርሽ ከጸጋሽ በረከት
መንታ ልቦች ይዘሽ...
ደግነት ከክፋት ተፈራረቁብሽ፣
አሁን ደግሞ ብሶ...
ክፋት ከበደና ሚዛኑን ደፋብሽ።
አንዲት ምስኪን ዶሮ...
እንቁላሏን ልትጥል ቦታዋ
ጠፍቶባት፣
ቦታ ብታገኝም...
ሳትጥለው ቀረች ትንሽ አቅም
አንሷት፣
ዶሮዋ አንቺው ነሽ
እንቁላሏ ደግሞ ያሰብሻት ራእይሽ
ሽቅብ ከደረሱት
ከዘመኑት ተርታ የምታሰልፍሽ...
ቦታ ያልኩሽ ደግሞ..
ጥቂቶች ሚያምኑበት የስራው
ባህል ነው፣
ጥሪት አስገኝቶ....
ከስኬት ማማ ላይ ከፍ አርጎ
የሚያቆመው፣
ነገር ግን ይህ ሁሉ...
ትንሽ አቅም ያልኩት ፍቅርን ተነፈገ
'ታጥቦ ጭቃ' ተረበት
ፍቅርን በተራብሽው በአንቺ ላይ
ሰረገ።
ስለዚህ እምዬ...
ከጸጋሽ ተገፈሽ ባዶ እንዳትቀሪ
ጨለማው ተገፎ
ጸሐይ እንድትወጣ
የፍቅር እህል ዝሪ..
ሞትሽን አላይም...
በዘር ፍቅር እሳት መጠበስሽ ይብቃ፣
ቁስልሽን ላክመው ..
ካሰረኝ እንቅልፌ ከሰመመን ልንቃ፣
ይብቃሽ እማማዬ
የሀዘን ጠባሳሽ ወደ እኔ ይገልበጥ
እስቲ አንቺ ቀና በይ...
በጭንቀት ባህር ውስጥ እኔ
ቁልቁል ልስመጥ፣
መራቆትሽ ይብቃ!!!
የፍቅርን ሸማ ደራርበሽ ልበሺ፣
ዳገቱ መሐል ላይ..
እኔ ልውደቅና እስቲ አንቺ ጨርሺ፣
የተስፋ ጸሐይሽ...
ዳግም እንድትወጣ አምላክን ለምኚ፣
እኔ ይጨልምብኝ አንቺ ግን
አግኚ፣
በዚህ በአዲስ ዘመን...
አንድ የሚያደርግሽን ብሩህ ፍቅር
ይስጥሽ
እኔ መውደድ ልጣ አንቺን ግን
አይራብሽ
በእግሮችሽ መሐል...
ቆልፎ ያስቀረሽ የክፋት መርዝ
ይውጣ፣
የፍቅር ዶፍ ይዝነብ
አንቺ እፎይ ብለሽ እኔ ሰላም ልጣ፣
መንገዳገድ ይብቃ
በሰላም ምርኩዝሽ በሁለት እግርሽ ሂጂ
እኔ አንካሳ ልሁን መጓዝ የናፈቀሽ
አንቺ ተራመጂ..
ይብቃሽ እማማዬ🇪🇹
ብርሀን ተመልከች ይሄ ድቅድቅ
አልፎ፣
አንቺ ፈገግ በይ የእኔ ጥርስ ረግፎ፣
የረገፈው ጸጉርሽ...
ዳግም እንዲበቅል ያግዘው
ይህ ፍቅር፣
መክሳትሽም ይብቃ
ስጋዬን ውሰጂና የእኔ አጥንት
ይቅር...
«ኢትዮጵያ ታበጽሕ
ዕደዊሀ ሀበ እግዚአብሔር»
✍ዮሐንስ ገርማሜ
@getem
@getem
@getem
❤1👍1
''ለማያውቅሽ ታጠኚ''
————//————
.
አወይ እንዴት ያምራል አቋምሽ አለሜ
እንደ ጣና ደንገል
ተክነሽው የለ ፥ .....የተክሌን ዝማሜ
.
ከነገስታት እልፍኝ ፥ ከማጀትሽ ጓዳ
ሙገሳሽ ከአፄው ፥ ባንኳላ ቢቀዳ
ለማያቅሽ ጉብል…
ልዩ ነው ዘረፋሽ ፥ ቅኔሽም አንግዳ
.
እልፍ እያሰለፈ
....…እየደጋገፈ
ያ ወርቁ መቋሚያ ፥ የንጉሥ ግድግዳ
አስቸገረን እንጂ…
ላንቺ ምርኩዝ ሆኖ ፥ …እኛን እየከዳ
.
አንቺ እንደልቡ
የከፍታሽ ነገር ፥ የዙፋንሽ ደርቡ
የለበጥሽው መዳብ ወርቅ አርገሽ በዕቡ'
የጉባዬ ቃናው ፥ ..የቅኔሽ ድባቡ
ገመገም ነውና…
ፈቺ ስላልጠፋ ፥ ገብቶናል ሀሳቡ
.
እንደ ተ'ኩላት ጥሎሽ
እንደ ሰማይ ጭሬ ፥ ያየር ምልልስሽ
ጠቦት በበዛበት ፥ የማንጃበብ ውልሽ
ሥጋ ለማጋዝ ነው…
በክሽን አጀንዳ ፥ በመልካም ወጣትሽ
.
ስራሽንም አውቆ
ፊደልን ጠንቅቆ
ስውር ስፍ ሙያሽን ፥ ለጠየቀ ርቆ
በነብዩ አፍሽ ፥ ተጠቅመሽ ላመሉ
የቅናት መንፈስ ነው ፥ ትይኛለሽ አሉ
.
አሁን ለሸመታ
እንዳዘነ ኩታ
ላላወቀ ታጥነሽ ፥ ድርቡን ለብሰሽው
በጆንያ ፊልተር ፥ ..ጅሉን አስክረሽው
ሚስጥር ሳታወርጂ ፥ እንዳሻ ፈተሽው
ሰሙን በመናገር…
ታግዢያለሽ አሉ ፥ ወርቁን ደብቀሽው
.
«ሚኪ እንዳለ»
@getem
@getem
@getem
@mmiku
————//————
.
አወይ እንዴት ያምራል አቋምሽ አለሜ
እንደ ጣና ደንገል
ተክነሽው የለ ፥ .....የተክሌን ዝማሜ
.
ከነገስታት እልፍኝ ፥ ከማጀትሽ ጓዳ
ሙገሳሽ ከአፄው ፥ ባንኳላ ቢቀዳ
ለማያቅሽ ጉብል…
ልዩ ነው ዘረፋሽ ፥ ቅኔሽም አንግዳ
.
እልፍ እያሰለፈ
....…እየደጋገፈ
ያ ወርቁ መቋሚያ ፥ የንጉሥ ግድግዳ
አስቸገረን እንጂ…
ላንቺ ምርኩዝ ሆኖ ፥ …እኛን እየከዳ
.
አንቺ እንደልቡ
የከፍታሽ ነገር ፥ የዙፋንሽ ደርቡ
የለበጥሽው መዳብ ወርቅ አርገሽ በዕቡ'
የጉባዬ ቃናው ፥ ..የቅኔሽ ድባቡ
ገመገም ነውና…
ፈቺ ስላልጠፋ ፥ ገብቶናል ሀሳቡ
.
እንደ ተ'ኩላት ጥሎሽ
እንደ ሰማይ ጭሬ ፥ ያየር ምልልስሽ
ጠቦት በበዛበት ፥ የማንጃበብ ውልሽ
ሥጋ ለማጋዝ ነው…
በክሽን አጀንዳ ፥ በመልካም ወጣትሽ
.
ስራሽንም አውቆ
ፊደልን ጠንቅቆ
ስውር ስፍ ሙያሽን ፥ ለጠየቀ ርቆ
በነብዩ አፍሽ ፥ ተጠቅመሽ ላመሉ
የቅናት መንፈስ ነው ፥ ትይኛለሽ አሉ
.
አሁን ለሸመታ
እንዳዘነ ኩታ
ላላወቀ ታጥነሽ ፥ ድርቡን ለብሰሽው
በጆንያ ፊልተር ፥ ..ጅሉን አስክረሽው
ሚስጥር ሳታወርጂ ፥ እንዳሻ ፈተሽው
ሰሙን በመናገር…
ታግዢያለሽ አሉ ፥ ወርቁን ደብቀሽው
.
«ሚኪ እንዳለ»
@getem
@getem
@getem
@mmiku
ያለ አቅሜ አልንጠራራም!!!
_====_________
ከእለታት ባንድ ቀን አይጥና ዝሆን
አብረው እየተጓዙ፣
ወንዝ ለማቋረጥ ካንድ ትልቅ
ድልድይ አጠገብ ደረሱ፣
ከዚያም ወዲያውኑ...
አይጥ ከፊት ለፊት ዝሆን ሁዋላ
ሆነው፣
መሻገር ጀመሩ ይህን ግዙፍ ድልድይ መተማመኛ አርገው።
ትንሽ እንደሄዱ...
ያ ያመኑት ድልድይ ድንገት
ነቅነቅ ብሎ
ዝሆን ወዲያው ቆመ...
ፍርሀት ተሰምቶት ለአፍታ
ቀልቡን ጥሎ
አቅሟን ሳትገድብ...
አይጥ እንዲህ አለች አይታ
የታቹን ገደል፣
«አያ ዝሆንዬ እንዴት ሚገርም ነው
ነቀነቅነው አይደል!»
✍ዮሐንስ ገርማሜ
#john
@getem
@getem
@getem
_====_________
ከእለታት ባንድ ቀን አይጥና ዝሆን
አብረው እየተጓዙ፣
ወንዝ ለማቋረጥ ካንድ ትልቅ
ድልድይ አጠገብ ደረሱ፣
ከዚያም ወዲያውኑ...
አይጥ ከፊት ለፊት ዝሆን ሁዋላ
ሆነው፣
መሻገር ጀመሩ ይህን ግዙፍ ድልድይ መተማመኛ አርገው።
ትንሽ እንደሄዱ...
ያ ያመኑት ድልድይ ድንገት
ነቅነቅ ብሎ
ዝሆን ወዲያው ቆመ...
ፍርሀት ተሰምቶት ለአፍታ
ቀልቡን ጥሎ
አቅሟን ሳትገድብ...
አይጥ እንዲህ አለች አይታ
የታቹን ገደል፣
«አያ ዝሆንዬ እንዴት ሚገርም ነው
ነቀነቅነው አይደል!»
✍ዮሐንስ ገርማሜ
#john
@getem
@getem
@getem
ፍጭው!!!!
እቴ ቸግሮኛል፤
የኔ ሃገር ዋዘኞች ወዲህና ወዲያ እየተዛመዱ፤
እንዳይሆን እንዳይሆን፤
እብቅና አዝመራው እየተላመዱ፤
ቁርጥ ነው ዘንድሮ፤
መጅሺን ያዥና፤
ፍጭውና ይለይ አሰርና ግርዱ።
((( ጃ ኖ ))💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
እቴ ቸግሮኛል፤
የኔ ሃገር ዋዘኞች ወዲህና ወዲያ እየተዛመዱ፤
እንዳይሆን እንዳይሆን፤
እብቅና አዝመራው እየተላመዱ፤
ቁርጥ ነው ዘንድሮ፤
መጅሺን ያዥና፤
ፍጭውና ይለይ አሰርና ግርዱ።
((( ጃ ኖ ))💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
👍1
"…ግን ግን… ብላቴናዎቹ ምን በደሉ?
የማንን አደራ በልተው… የማንን አማና አጎደሉ?
እምብርታቸው ያላረረ… አጥንተቸው ያልከረረ
ሰማይ በቀል እንቋጠረ… እጣቸውን እየመነጠረ
መንገዳቸው እያጠረ
እንደ ደራሽ ውሃ አግተልትሎ
በራብ አኮርማጅ ተልትሎ
ከእናት እቅፍ በግፍ ነጥቆ
ምላሱ ሊቃመስ ተባጥቆ
ሲሰለፍብን በአጭር ታጥቆ
እያየህ ዝም ካልክማ…?
እውነት…እውነት ከመንበርህ የለህማ!…"
((( ሙሉጌታ ተስፋዬ ))💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
የማንን አደራ በልተው… የማንን አማና አጎደሉ?
እምብርታቸው ያላረረ… አጥንተቸው ያልከረረ
ሰማይ በቀል እንቋጠረ… እጣቸውን እየመነጠረ
መንገዳቸው እያጠረ
እንደ ደራሽ ውሃ አግተልትሎ
በራብ አኮርማጅ ተልትሎ
ከእናት እቅፍ በግፍ ነጥቆ
ምላሱ ሊቃመስ ተባጥቆ
ሲሰለፍብን በአጭር ታጥቆ
እያየህ ዝም ካልክማ…?
እውነት…እውነት ከመንበርህ የለህማ!…"
((( ሙሉጌታ ተስፋዬ ))💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
ሲፈቀር የሚባል...
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
"ፈገግ ስትዪ...
ጥርስሽ ምስራቅ ሆነኝ ፣ የፀሐይ መውጫ በር
ከሳቅሽ ሰማይ ላይ ...
ንጋቴን አያለሁ ፣ ተሰቅላ እንደጀንበር።
አንቺ ስትስቂ...
የጨረቃ ገላ ፣ እስኪያልቅ ይሸረፋል
"ሙሉ"
"ግማሽ"
"ሩብ"
እያለ ይጠፋል
ኮከብ እንደ ቅጠል ፣ እግሬ ስር ይረግፋል።"
ብዬሽም አልነበር?
..................................
"ስታኮርፊ ደሞ
ነፍስሽ ምእራብ ነች ፣ መውጫ ለጨለማ
ከኩርፊያሽ ሰማይ ላይ...
ምሽቴን አያለሁ ፣ ንጋቴን ስቀማ።
አንቺ ስታኮርፊ...
ሳቅሽ ሚያደርቃቸው ፣
"ኮከብ ነን" ባይ ሁላ ፣ ይድናል ከመርገፍ
ጨረቃም ሙሉ ነች...
ዳግም ስትስቂ አይታ ፣ ገላዋ እስኪሸረፍ
እስከዚያው ድረስ ግን....
ምን ጨለማ ቢገዝፍ፣
ትንሽ ብርሀንን ፣ አይችልም ማሸነፍ!!"
ብዬሽም አልነበር?
...................................
"ስትስሚኝ ደግሞ...
መለኮት ከንፈርሽ ፣ ከንፈሬን ሲያጠምቀው
ምኔ እንደተነካ ፣ሳይገባኝ ሳላውቀው
ከገነት ደጃፍ ነው ፣ ደርሼ ምወድቀው።
ሲኦል ከቆመ ነፍስ ፣ ገነት የወደቀ አይደል የሚፀድቀው!!?"
ብዬሽም አልነበር?
ግን በቃ አትመኚኝ!!
ይሄን ሁሉ ያልሁሽ...
ስለጠፋብኝ ነው ፣ ልልሽ ያልሁት ነገር!!!
.....................................
አሁን ግን የምልሽ...
"ልቤና አንደበቴ ፣ አይተዋወቅም
አፍቃሪና እውነት....
ሩቅ ለ ሩቅ ናቸው!
ሰማይ ከምድር ላይ ፣ ያን ያህል አይርቅም
ሳፈቅርሽ እንዲህ ነኝ...
የምልሽ ሲጠፋኝ ፣ ያልሁትን አላውቅም!!!
ግን አፈቅርሻለሁ።"
እያልሁሽ አልነበር?
የማይባል የለም! ፣ ይባላል ሲፈቀር!!!!
@getem
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
"ፈገግ ስትዪ...
ጥርስሽ ምስራቅ ሆነኝ ፣ የፀሐይ መውጫ በር
ከሳቅሽ ሰማይ ላይ ...
ንጋቴን አያለሁ ፣ ተሰቅላ እንደጀንበር።
አንቺ ስትስቂ...
የጨረቃ ገላ ፣ እስኪያልቅ ይሸረፋል
"ሙሉ"
"ግማሽ"
"ሩብ"
እያለ ይጠፋል
ኮከብ እንደ ቅጠል ፣ እግሬ ስር ይረግፋል።"
ብዬሽም አልነበር?
..................................
"ስታኮርፊ ደሞ
ነፍስሽ ምእራብ ነች ፣ መውጫ ለጨለማ
ከኩርፊያሽ ሰማይ ላይ...
ምሽቴን አያለሁ ፣ ንጋቴን ስቀማ።
አንቺ ስታኮርፊ...
ሳቅሽ ሚያደርቃቸው ፣
"ኮከብ ነን" ባይ ሁላ ፣ ይድናል ከመርገፍ
ጨረቃም ሙሉ ነች...
ዳግም ስትስቂ አይታ ፣ ገላዋ እስኪሸረፍ
እስከዚያው ድረስ ግን....
ምን ጨለማ ቢገዝፍ፣
ትንሽ ብርሀንን ፣ አይችልም ማሸነፍ!!"
ብዬሽም አልነበር?
...................................
"ስትስሚኝ ደግሞ...
መለኮት ከንፈርሽ ፣ ከንፈሬን ሲያጠምቀው
ምኔ እንደተነካ ፣ሳይገባኝ ሳላውቀው
ከገነት ደጃፍ ነው ፣ ደርሼ ምወድቀው።
ሲኦል ከቆመ ነፍስ ፣ ገነት የወደቀ አይደል የሚፀድቀው!!?"
ብዬሽም አልነበር?
ግን በቃ አትመኚኝ!!
ይሄን ሁሉ ያልሁሽ...
ስለጠፋብኝ ነው ፣ ልልሽ ያልሁት ነገር!!!
.....................................
አሁን ግን የምልሽ...
"ልቤና አንደበቴ ፣ አይተዋወቅም
አፍቃሪና እውነት....
ሩቅ ለ ሩቅ ናቸው!
ሰማይ ከምድር ላይ ፣ ያን ያህል አይርቅም
ሳፈቅርሽ እንዲህ ነኝ...
የምልሽ ሲጠፋኝ ፣ ያልሁትን አላውቅም!!!
ግን አፈቅርሻለሁ።"
እያልሁሽ አልነበር?
የማይባል የለም! ፣ ይባላል ሲፈቀር!!!!
@getem
@getem
@getem
👍1
#እስኪ.....
(ቤዛዊት ከበደ)
ይስቃሉ በሀሣቤ
ይስቃሉ በጉልበቴ
ይስቃሉ በጥረቴ
.
.
ይበላሉ ከማጀቴ
ይጠጣሉ ከማጀቴ
ከእጄ ፍሬ ከደም ላቤ
ይቆርሣሉ ከስኬቴ
.
.
ያደንቃሉ ያን ሀሣቤን
ያደንቃሉ ያን ጉልበቴን
ያደንቃሉ ሙሉ ቤቴን
.
.
እንዲህ እንደዚ እያሉ
ይኖራሉ ከቤቴ ጎን አጥር ጋርደው
ወይ ለወሬ
ወይ ለስርቆት
ወይ ለፅድቅ እንዲመቻቸው::
.
.
እኔም አለሁ
እስኪፀዳ ማድጋዬ
እስኪከዳኝ ቀኝ ጉልበቴ
እስኪጎድል ሙሉ ቀኔ
.
.
ይሀው አለሁ
..
እኔም አለሁ
.
.
ምርቃቴን ይዤ
እርግማኔን ትቼ!!
@getem
@getem
@getem
(ቤዛዊት ከበደ)
ይስቃሉ በሀሣቤ
ይስቃሉ በጉልበቴ
ይስቃሉ በጥረቴ
.
.
ይበላሉ ከማጀቴ
ይጠጣሉ ከማጀቴ
ከእጄ ፍሬ ከደም ላቤ
ይቆርሣሉ ከስኬቴ
.
.
ያደንቃሉ ያን ሀሣቤን
ያደንቃሉ ያን ጉልበቴን
ያደንቃሉ ሙሉ ቤቴን
.
.
እንዲህ እንደዚ እያሉ
ይኖራሉ ከቤቴ ጎን አጥር ጋርደው
ወይ ለወሬ
ወይ ለስርቆት
ወይ ለፅድቅ እንዲመቻቸው::
.
.
እኔም አለሁ
እስኪፀዳ ማድጋዬ
እስኪከዳኝ ቀኝ ጉልበቴ
እስኪጎድል ሙሉ ቀኔ
.
.
ይሀው አለሁ
..
እኔም አለሁ
.
.
ምርቃቴን ይዤ
እርግማኔን ትቼ!!
@getem
@getem
@getem
ለኢትዮጵያ!!!
(በላይ በቀለ ወያ)
,
,
ይብላኝለት እንጂ...
በዘር ተከፋፍሎ ፣ ለሚታመስ ቤቷ
ይብላኝለት እንጂ...
ተሸርፎ ተሸርፎ ፣ ላለቀ መሬቷ
ይብላኝለት እንጂ...
ደረቷን ስትደቃ ፣ ለወረደው ጡቷ
ይብላኝለት እንጂ...
ባዘን ፀጉሯን ስትነጭ ፣ ለገጠበ አናቷ
ይብላኝለት እንጂ..
ቁንጅናውን ላጣ ፣ ማድያታም ፊቷ...
፡፡፡፡፡፡፡
ከዚ ሁሉ ኋላም
የዘመን ጥላሸት ፣ መልኳን ተለቅልቃ
ቁንጅናዋ ርቋት ፣ ፉንጋነትን ታጥቃ
ልንጠላት አንችልም ፣ ውብ ሀገር ነች በቃ!!!
@getem
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
,
,
ይብላኝለት እንጂ...
በዘር ተከፋፍሎ ፣ ለሚታመስ ቤቷ
ይብላኝለት እንጂ...
ተሸርፎ ተሸርፎ ፣ ላለቀ መሬቷ
ይብላኝለት እንጂ...
ደረቷን ስትደቃ ፣ ለወረደው ጡቷ
ይብላኝለት እንጂ...
ባዘን ፀጉሯን ስትነጭ ፣ ለገጠበ አናቷ
ይብላኝለት እንጂ..
ቁንጅናውን ላጣ ፣ ማድያታም ፊቷ...
፡፡፡፡፡፡፡
ከዚ ሁሉ ኋላም
የዘመን ጥላሸት ፣ መልኳን ተለቅልቃ
ቁንጅናዋ ርቋት ፣ ፉንጋነትን ታጥቃ
ልንጠላት አንችልም ፣ ውብ ሀገር ነች በቃ!!!
@getem
@getem
@getem
ዝክረ _ኸሚስ
ልጅት ሳይሞቅ ፈላ
************
ባለ ሁለት ጆሮ ……ገንቦየን አንግቼ
በዋርማ በፎሌ…… ከሚንጩ ቀድቼ
ዳለች እና ቦራን ……ከወንዙ አጠጥቼ
ከጅረቱ አጠገብ… ካለችው አከያ እንጠላጠላለሁ
ከለምለሙ ዛፍ ላይ …… እመለምላለሁ
ለቤታችን ጉዝጓዝ ……ቅጠል እቆርጣለሁ።
ከዛፉ ላይ ሁኘ ዝቅዝቅ ስመለከት የበለጠ አያለሁ
በእየ ቀንዘሉ ላይ ጢብ ጢብ ብየ እታች እዳፋለሁ
ከጅረቱ በታች ወዳለችው ገደል እጄን እሰዳለሁ
ቄጠማ ጠጄ ሳር …… አደሱን አጭዳለሁ።
ለማለሙን ሁሉ ……ባንድነት ሸክፌ
ገንቦየን አዝየ ……ጉዝጓዜን ታቅፌ
ዳለች እና ቦራን…… ከፊት እየነዳሁ
ለአንድየ ምነግረው …… ዱአ እያሰናዳሁ
ስሄድ ስገሰግስ
ከቀየየ ስደርስ
አባባ እና አየዋ …… ጃኖ ተሸፋፍነው
ማዶ ማዶ እያዩ ……ከቀልባቸው ሁነው
አውዱማው አጠገብ …… ወግ እያወጉ ነው
እንዴት ነሁ አይወይ…… አማን ነው መንደሩ?
ሸጋ ነወይ አጥቢያው ……እንዴት ውሏል ዱሩ?
ብየ እጅ ነሳሁኝ………እንዳባት አደሩ
አየዋም ጭራዎን ……ከግራ ወደቀኝ እየነሰነሱ
«አማን ሁኚ!» ብለው ……ነገያ መለሱ።
እኔም እየጠደፍኩ…… ወደ ቤቴ አቅንቼ
ገንቦና ዋርማየን …… ኸማጄት ከትቼ
እቅፍ ሙሉ ለምለም…… ለእማማ ሰጥቼ፤
እናት አለም ሆዴ …
ያወዱድ ያወዱድ …… ያወዱድ እያለች
የቀልብ የሙራዷን …… እያንጎራጎረች
ከመደብ እስከ ዘብጥ…… ትጎዘጉዛለች
እታለም ከምድጃው…… ወይራ ታጬሳለች።
ሰማይ ሲጨላልም…… አዱኒያን በበረት
ፍየሎቹን በጋጥ …… ደጃፉን በብረት
ሸክፎ ቢገባ …… አባታለም ክንዴ
የቤታችን ድባብ ……መለወጡ ባንዴ፤
ግር አለው ሁናቴው ……ገረመው በጠና
ቀኑ ሀሙስ መሆኑን …… ዘንግቶታልና፤
ከቀጠላው አናት…… እየተሰየመ
በወይራ በአድሩሱ ……እየተደመመ
ከጭሱ ጋር ስበን ……ቃል ሳይናገረኝ
ቀልብ የሚገዛውን……ፈገግታዉን ቸረኝ ።
ፈዋሽ ልዝብ እጆቹን……ሰዶ ወደ አናቴ
«ጎሽሽ!» ሲል አባባ …… «አበጀሽ እናቴ!»
ከነበረው በእጥፍእመረቅናለሁ …ይብሳል ፍጥነቴ
አይ ነብስ አለማወቅ…… አወይ ልጅነቴ!
በፋኖስ ታጅቦ … እንጀራው በሞሰብ ወጡ በሰታቴ
ከቀረበ ወድያ…… ብሉ እየተባለ ጠጡልኝ በሞቴ
በሳቅ በፍስሀ …… እንደተጎራረስን ይነሳል ገበታ
እምድጃውን ከበን…ቡና እየተቆላ ይደራል ጫወታ
እኔ ሀድራ ወዳጅ…
ልጅት ሳይሞቅ ፈላ…
ማጨዱ ሳይበቃኝ ……ቀጤማ እና አሪቲ
አደስና ከሴ ……ጠጀሳር አሽኩቲ
መጎዝጎዝ ሳያንሰኝ…… ጓሳ እና ሉባንጃ
ኸሚስ አመሻሹን ያቅበጠብጠኛል የነካኝን እንጃ
ጥፍጥሬ ማህል ልጅ ……ምርቃት ለምጄ
«አወል ጀባ!» እላለሁ …… ጀበና ጨምድጄ
የቤታችን አውራ የምኞትሽ ይሁን ብሎ ቢመርቀኝ
«በአሚን»ተቀብየው…… ቀይ ባህር ዘፈቀኝ
ይሄው በዛን ዘመን ……ምኞት አጣምሜ
በስደት አለቀ …… ተጋመሰ አለሜ !
ምፅ!ምፅፅ!
ውዶቼ
የምኞታችሁ አይሁን ይልቅስ የሚበጃችሁ ይሁን!
አላሁመ ሰሊ ወሰሊም አላ ሰይድና ወሀቢበና ሙሀመድ ወአላ አሊሂ ወአስሀቢሂ አጅመኢን!!
ሸጋ ኸሚስ ሸጎቼ!
@getem
@getem
@balmbaras
ልጅት ሳይሞቅ ፈላ
************
ባለ ሁለት ጆሮ ……ገንቦየን አንግቼ
በዋርማ በፎሌ…… ከሚንጩ ቀድቼ
ዳለች እና ቦራን ……ከወንዙ አጠጥቼ
ከጅረቱ አጠገብ… ካለችው አከያ እንጠላጠላለሁ
ከለምለሙ ዛፍ ላይ …… እመለምላለሁ
ለቤታችን ጉዝጓዝ ……ቅጠል እቆርጣለሁ።
ከዛፉ ላይ ሁኘ ዝቅዝቅ ስመለከት የበለጠ አያለሁ
በእየ ቀንዘሉ ላይ ጢብ ጢብ ብየ እታች እዳፋለሁ
ከጅረቱ በታች ወዳለችው ገደል እጄን እሰዳለሁ
ቄጠማ ጠጄ ሳር …… አደሱን አጭዳለሁ።
ለማለሙን ሁሉ ……ባንድነት ሸክፌ
ገንቦየን አዝየ ……ጉዝጓዜን ታቅፌ
ዳለች እና ቦራን…… ከፊት እየነዳሁ
ለአንድየ ምነግረው …… ዱአ እያሰናዳሁ
ስሄድ ስገሰግስ
ከቀየየ ስደርስ
አባባ እና አየዋ …… ጃኖ ተሸፋፍነው
ማዶ ማዶ እያዩ ……ከቀልባቸው ሁነው
አውዱማው አጠገብ …… ወግ እያወጉ ነው
እንዴት ነሁ አይወይ…… አማን ነው መንደሩ?
ሸጋ ነወይ አጥቢያው ……እንዴት ውሏል ዱሩ?
ብየ እጅ ነሳሁኝ………እንዳባት አደሩ
አየዋም ጭራዎን ……ከግራ ወደቀኝ እየነሰነሱ
«አማን ሁኚ!» ብለው ……ነገያ መለሱ።
እኔም እየጠደፍኩ…… ወደ ቤቴ አቅንቼ
ገንቦና ዋርማየን …… ኸማጄት ከትቼ
እቅፍ ሙሉ ለምለም…… ለእማማ ሰጥቼ፤
እናት አለም ሆዴ …
ያወዱድ ያወዱድ …… ያወዱድ እያለች
የቀልብ የሙራዷን …… እያንጎራጎረች
ከመደብ እስከ ዘብጥ…… ትጎዘጉዛለች
እታለም ከምድጃው…… ወይራ ታጬሳለች።
ሰማይ ሲጨላልም…… አዱኒያን በበረት
ፍየሎቹን በጋጥ …… ደጃፉን በብረት
ሸክፎ ቢገባ …… አባታለም ክንዴ
የቤታችን ድባብ ……መለወጡ ባንዴ፤
ግር አለው ሁናቴው ……ገረመው በጠና
ቀኑ ሀሙስ መሆኑን …… ዘንግቶታልና፤
ከቀጠላው አናት…… እየተሰየመ
በወይራ በአድሩሱ ……እየተደመመ
ከጭሱ ጋር ስበን ……ቃል ሳይናገረኝ
ቀልብ የሚገዛውን……ፈገግታዉን ቸረኝ ።
ፈዋሽ ልዝብ እጆቹን……ሰዶ ወደ አናቴ
«ጎሽሽ!» ሲል አባባ …… «አበጀሽ እናቴ!»
ከነበረው በእጥፍእመረቅናለሁ …ይብሳል ፍጥነቴ
አይ ነብስ አለማወቅ…… አወይ ልጅነቴ!
በፋኖስ ታጅቦ … እንጀራው በሞሰብ ወጡ በሰታቴ
ከቀረበ ወድያ…… ብሉ እየተባለ ጠጡልኝ በሞቴ
በሳቅ በፍስሀ …… እንደተጎራረስን ይነሳል ገበታ
እምድጃውን ከበን…ቡና እየተቆላ ይደራል ጫወታ
እኔ ሀድራ ወዳጅ…
ልጅት ሳይሞቅ ፈላ…
ማጨዱ ሳይበቃኝ ……ቀጤማ እና አሪቲ
አደስና ከሴ ……ጠጀሳር አሽኩቲ
መጎዝጎዝ ሳያንሰኝ…… ጓሳ እና ሉባንጃ
ኸሚስ አመሻሹን ያቅበጠብጠኛል የነካኝን እንጃ
ጥፍጥሬ ማህል ልጅ ……ምርቃት ለምጄ
«አወል ጀባ!» እላለሁ …… ጀበና ጨምድጄ
የቤታችን አውራ የምኞትሽ ይሁን ብሎ ቢመርቀኝ
«በአሚን»ተቀብየው…… ቀይ ባህር ዘፈቀኝ
ይሄው በዛን ዘመን ……ምኞት አጣምሜ
በስደት አለቀ …… ተጋመሰ አለሜ !
ምፅ!ምፅፅ!
ውዶቼ
የምኞታችሁ አይሁን ይልቅስ የሚበጃችሁ ይሁን!
አላሁመ ሰሊ ወሰሊም አላ ሰይድና ወሀቢበና ሙሀመድ ወአላ አሊሂ ወአስሀቢሂ አጅመኢን!!
ሸጋ ኸሚስ ሸጎቼ!
@getem
@getem
@balmbaras
👍2