ለአባቴ
(ቡሩክ ካሳሁን)
ከጥንት ጀምሮ ከወንድ የዘር ግንዱ
ሀያላን ነበሩ ተራራ ’ሚንዱ
ጠቢቦች ነበሩ ጥበብ የሚወዱ
ምን ያደርጋል ታዲያ
አንተን የሚመስሉ መቼ ተወለዱ?
ባልሆን ሙታን ቀስቃሽ
ወደኋላ ገስጋሽ በእውነት ታሪክ ጋሪ
ባልሆን እንኳን ነቢይ ትንቢት ተናጋሪ
በቁንፅሏ እድሜዬ የተገለጠልኝ ያወቅኩት ሀቂቃ
ለራሴ ብነግረው
ምንም ’ማይሰለቸኝ ብደጋግመውም በየሩብ ደቂቃ
አንዳ’ንተ አይነቱ የተመረጠ አባት ህሩየ ህሩያን
ካንተ ኋላ የለ ወደፊት አይመጣ ልክ እንደ ሰለሞን*።
* ጠቢቡ ሰለሞን ከሱ በፊትም ሆነ ከሱ በኋላ እንደሱ ያለ ጠቢብ እንደሌለ፤ እንደማይኖርም፡፡
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል @burukassahunC
@getem
@getem
(ቡሩክ ካሳሁን)
ከጥንት ጀምሮ ከወንድ የዘር ግንዱ
ሀያላን ነበሩ ተራራ ’ሚንዱ
ጠቢቦች ነበሩ ጥበብ የሚወዱ
ምን ያደርጋል ታዲያ
አንተን የሚመስሉ መቼ ተወለዱ?
ባልሆን ሙታን ቀስቃሽ
ወደኋላ ገስጋሽ በእውነት ታሪክ ጋሪ
ባልሆን እንኳን ነቢይ ትንቢት ተናጋሪ
በቁንፅሏ እድሜዬ የተገለጠልኝ ያወቅኩት ሀቂቃ
ለራሴ ብነግረው
ምንም ’ማይሰለቸኝ ብደጋግመውም በየሩብ ደቂቃ
አንዳ’ንተ አይነቱ የተመረጠ አባት ህሩየ ህሩያን
ካንተ ኋላ የለ ወደፊት አይመጣ ልክ እንደ ሰለሞን*።
* ጠቢቡ ሰለሞን ከሱ በፊትም ሆነ ከሱ በኋላ እንደሱ ያለ ጠቢብ እንደሌለ፤ እንደማይኖርም፡፡
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል @burukassahunC
@getem
@getem
👍1
🏃♀ሸሸው እንጂ አልራኩም💏
በትዝታህ ገመድ የዋሊት ጠፍረህ
የፊጢኝ አስረኸኝ በግዞትህ አኑረህ
የራኩኝ ቢመስለኝ የሄድኩኝ ካንተ ዘንድ
አሁንም አብሬህ ነኝ በትዝታ መንገድ፡፡
በእምነት ላይ ፀንቶ የቆመው ፍቅራችን
ፅልመትን ለበሰ ተከፍሎ ሀሳባችን፡፡
ውስጤም ተሰበረ ልቤም ያው ወሰነ
መላው እኔነቴ ባንተ ላይ ጨከነ
ከዚያማ ተነሳው ልርቅህ አስቤ
ግና አስመሠልኩኝ ተሸወደ ልቤ
ጥቂት ሸሸው እንጂ መች ራኩኝ ከቀልቤ፡
ዛሬን ነገን መኖር ጭራሽ አቁሜአለው
ኑሬዬ በሙሉ በትዝታ አለም ነው ፤
አኩርፌ ዞር ስል ፈገግታን ችረኸኝ
ከፍቶኝ ያየኸኝ ለት ቀርበህ ምታፅናናኝ
ለዛ ያለው ቀልድህ ተወዳጁ ሳቅህ
ገዳዩ እርምጃህ ሸበላው አቋምህ
አይኖቼን ምታየው በፍቅር አይኖችህ
እጄን ምትዳስሰው በአለንጋ ጣቶችህ
ያ ሸጋው አመልህ ቁም ነገር የበዛው
በፍፁም አልቻልኩም ላፍታ እንኳን ልረሳው ፤
እኔ መቼ ራኩክ አንተን መቼ ተውኩኝ
ብሶብኝ ትዝታህ በፅኑ ታመምኩኝ
ፍቅርህን ፍለጋ በምናብ ባዘንኩኝ
ብዙ ተቅበዘበዝኩ አንተን እያሰብኩኝ፤
ግና ላልመለስ አንዴ ወጥቻለው
የናፍቆቱን እሳት ባልችልም ችላለው
በቃ ወስኛለሁ ላልመለስ ምዬ
ባልርቅም መሸሹ ይሻለኛል ብዬ፡፡
ተፃፈ-በሠላም ሻኪሶ
@getem
@getem
@gebriel_19
በትዝታህ ገመድ የዋሊት ጠፍረህ
የፊጢኝ አስረኸኝ በግዞትህ አኑረህ
የራኩኝ ቢመስለኝ የሄድኩኝ ካንተ ዘንድ
አሁንም አብሬህ ነኝ በትዝታ መንገድ፡፡
በእምነት ላይ ፀንቶ የቆመው ፍቅራችን
ፅልመትን ለበሰ ተከፍሎ ሀሳባችን፡፡
ውስጤም ተሰበረ ልቤም ያው ወሰነ
መላው እኔነቴ ባንተ ላይ ጨከነ
ከዚያማ ተነሳው ልርቅህ አስቤ
ግና አስመሠልኩኝ ተሸወደ ልቤ
ጥቂት ሸሸው እንጂ መች ራኩኝ ከቀልቤ፡
ዛሬን ነገን መኖር ጭራሽ አቁሜአለው
ኑሬዬ በሙሉ በትዝታ አለም ነው ፤
አኩርፌ ዞር ስል ፈገግታን ችረኸኝ
ከፍቶኝ ያየኸኝ ለት ቀርበህ ምታፅናናኝ
ለዛ ያለው ቀልድህ ተወዳጁ ሳቅህ
ገዳዩ እርምጃህ ሸበላው አቋምህ
አይኖቼን ምታየው በፍቅር አይኖችህ
እጄን ምትዳስሰው በአለንጋ ጣቶችህ
ያ ሸጋው አመልህ ቁም ነገር የበዛው
በፍፁም አልቻልኩም ላፍታ እንኳን ልረሳው ፤
እኔ መቼ ራኩክ አንተን መቼ ተውኩኝ
ብሶብኝ ትዝታህ በፅኑ ታመምኩኝ
ፍቅርህን ፍለጋ በምናብ ባዘንኩኝ
ብዙ ተቅበዘበዝኩ አንተን እያሰብኩኝ፤
ግና ላልመለስ አንዴ ወጥቻለው
የናፍቆቱን እሳት ባልችልም ችላለው
በቃ ወስኛለሁ ላልመለስ ምዬ
ባልርቅም መሸሹ ይሻለኛል ብዬ፡፡
ተፃፈ-በሠላም ሻኪሶ
@getem
@getem
@gebriel_19
።።።። ዋ! ።።።።
(በረከት በላይነህ)
አይኔ ወደደሽ ስልሽ፣
አይኑን አጥፋው ብለሽ ገባሽ አሉ ስለት
ምኞትሽ ሰመረ
አይኖቼ ጠፉልሽ ይኸው አንደዘበት።
ግን መች ተውሻለው
በልቤ ብሩህ አይን ዛሬም አይሻለው።
ደሞ አንደዚ ስልሽ አትወጅኝምና
ልቡንም አጥፋልኝ ብለሽ ትሳይና
ፀሎት ያልቅብሻል እሞትብሽና።
@lula_al_greeko
@getem
@getem
(በረከት በላይነህ)
አይኔ ወደደሽ ስልሽ፣
አይኑን አጥፋው ብለሽ ገባሽ አሉ ስለት
ምኞትሽ ሰመረ
አይኖቼ ጠፉልሽ ይኸው አንደዘበት።
ግን መች ተውሻለው
በልቤ ብሩህ አይን ዛሬም አይሻለው።
ደሞ አንደዚ ስልሽ አትወጅኝምና
ልቡንም አጥፋልኝ ብለሽ ትሳይና
ፀሎት ያልቅብሻል እሞትብሽና።
@lula_al_greeko
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
ከለታት አንድ ቀን
ከማጣህ ከምሞት? ፣ የሚል ምርጫ አቅርባ
የራሷን ጥያቄ ፣ በእንባዋ አጅባ
ብሞት ይሻለኛል ፣ ብላ ነገረችኝ
ስትነግረኝ አመንኳት
እፈትናት ብዬ ፣ እንድትሞት ራኳት ፣ ሳትፈልግ አጣችኝ
።።።
ከእለታት ሁለት ቀን ፣
እሷ ዋሽታ አታውቅም ፣ ለቃሏ ታማኝ ነች
እንዳጣችኝ አውቃ ፣ ይሔኔ ሞታለች
በማለት አስቤ ፣
ለቀብሯ ስዘጋጅ ፣ እሷ ትኖራለች
።።።
ከእለታት ብዙ ቀን ፣
እንዴት አልሞተችም ?
የሚል የእምነት እዳ ፣ መች አብሰለሰለኝ?
አጥታኝ ስትኖር ባያት
እየኖረች መሞት ፣ ምታውቅ መሠለኝ
አምናታለሁና
እሷ አትዋሽምና
@getem
@getem
@gebriel_19
ከለታት አንድ ቀን
ከማጣህ ከምሞት? ፣ የሚል ምርጫ አቅርባ
የራሷን ጥያቄ ፣ በእንባዋ አጅባ
ብሞት ይሻለኛል ፣ ብላ ነገረችኝ
ስትነግረኝ አመንኳት
እፈትናት ብዬ ፣ እንድትሞት ራኳት ፣ ሳትፈልግ አጣችኝ
።።።
ከእለታት ሁለት ቀን ፣
እሷ ዋሽታ አታውቅም ፣ ለቃሏ ታማኝ ነች
እንዳጣችኝ አውቃ ፣ ይሔኔ ሞታለች
በማለት አስቤ ፣
ለቀብሯ ስዘጋጅ ፣ እሷ ትኖራለች
።።።
ከእለታት ብዙ ቀን ፣
እንዴት አልሞተችም ?
የሚል የእምነት እዳ ፣ መች አብሰለሰለኝ?
አጥታኝ ስትኖር ባያት
እየኖረች መሞት ፣ ምታውቅ መሠለኝ
አምናታለሁና
እሷ አትዋሽምና
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
ጨረቃ ሆይ!
((እዮብ ሰብስቤ))
፡
የፍለጋን አቅም
የማግኘትን ጣዕም
የሚያውቅ ይጀግናል፤
የፈራ ግን ልቡ
ጨረቃን ለማየት
ፀሐይ ይለምናል፡፡
እናም ይሁን!
በቀን ተደበቂ በቀን ተሰወሪ
ሲመሽ ግን ይህን አውሪ፡፡
መሻገር ስትፈልግ አዲስ ነገር ማየት
ከለውጥ መጠጋት
ሁሌም ያስፈልጋል ምቾቴ ነው ካልከው
ዓለምህ መዋጋት፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
((እዮብ ሰብስቤ))
፡
የፍለጋን አቅም
የማግኘትን ጣዕም
የሚያውቅ ይጀግናል፤
የፈራ ግን ልቡ
ጨረቃን ለማየት
ፀሐይ ይለምናል፡፡
እናም ይሁን!
በቀን ተደበቂ በቀን ተሰወሪ
ሲመሽ ግን ይህን አውሪ፡፡
መሻገር ስትፈልግ አዲስ ነገር ማየት
ከለውጥ መጠጋት
ሁሌም ያስፈልጋል ምቾቴ ነው ካልከው
ዓለምህ መዋጋት፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
ግድብ እና ገደብ
....ፀጉር ቤት
ተመላጭ እያለ መብራት ከነ የለም አትገረም ወንድም ይሄ ብዙ አይደንቅም
ለምን.....ብትል
መብራት ሀይል.. ኤልፓችን እራሱ
በቂ ግድብ የለም እጄ አጠረ ሆኖአል ተዘውታሪ ክሱ.
ግድብማ ሞልቶአል ገደብ እንጂ የጠፋው
ከእለታት ባንዱ ቀን.. ባንዱ ቀን ተነስተው
ግድብ ልንሰራ ነው ጨለማን ሚያጠፋ
ብለው ሰጥተው ተስፋ
እኛም ተስፈኞቹ ከልብ አምነናቸው
እነሱም ሆ ብለው ተሰፋችንን በልተው
ቦጥቡጠው ቦጥቡጠው በ ማን አለብኝነት የ ተስፈኛን ተሰፋ አረጉት እንክትክት
.....አባይ እንኩዋን በ አቅሙ
ማደሪያ የሌለው ግንድ ይዞ ሚዞረው
ግንዱን አስቀምጦ ጭንቅላቱን ይዞ አጃኢብ ነዉ ያለው
...እናም የኔ መልክት
ከሁሉ አስቀድሞ ከ ግድቡ ሁሉ በፊት
ገደብን እንወቅ እንኑር በ ለከት
ጋጠወጥ አንሁን ይኑረን ሰርአት.🙏
በ...ቢንያም ኤሊያስ
@ben_am
@getem
@getem
@gebriel_19
....ፀጉር ቤት
ተመላጭ እያለ መብራት ከነ የለም አትገረም ወንድም ይሄ ብዙ አይደንቅም
ለምን.....ብትል
መብራት ሀይል.. ኤልፓችን እራሱ
በቂ ግድብ የለም እጄ አጠረ ሆኖአል ተዘውታሪ ክሱ.
ግድብማ ሞልቶአል ገደብ እንጂ የጠፋው
ከእለታት ባንዱ ቀን.. ባንዱ ቀን ተነስተው
ግድብ ልንሰራ ነው ጨለማን ሚያጠፋ
ብለው ሰጥተው ተስፋ
እኛም ተስፈኞቹ ከልብ አምነናቸው
እነሱም ሆ ብለው ተሰፋችንን በልተው
ቦጥቡጠው ቦጥቡጠው በ ማን አለብኝነት የ ተስፈኛን ተሰፋ አረጉት እንክትክት
.....አባይ እንኩዋን በ አቅሙ
ማደሪያ የሌለው ግንድ ይዞ ሚዞረው
ግንዱን አስቀምጦ ጭንቅላቱን ይዞ አጃኢብ ነዉ ያለው
...እናም የኔ መልክት
ከሁሉ አስቀድሞ ከ ግድቡ ሁሉ በፊት
ገደብን እንወቅ እንኑር በ ለከት
ጋጠወጥ አንሁን ይኑረን ሰርአት.🙏
በ...ቢንያም ኤሊያስ
@ben_am
@getem
@getem
@gebriel_19
" #የሞራል_ብቃት ?"
-
መቼም ሰው ይስታል ፣ ዋናው መታረሙ
ህመም ሁሉ አይገልም፣ ዋናው መታከሙ፣
በሚል የሞራል ሕግ፣ የወል አስተሳሰብ
ያለማቆላለፍ ፣ ያለማወሳሰብ፣
ስለ አቋሙ ዝንፈት
ስለ ርምጃው ሽፈት
በተረዳኝ አቅም ባሽሙር ሳላነውር
ኮሶ ሁኖ ሚያሽር ሃሳብ ብወረውር፣
አለኝ ትንፍሽ አትበል ጩሆ በድንፋታ
ጫማዬን ሳታጠልቅ ሳትቆም በኔ ቦታ!
ወፈፍ አደረገው ...
ሊሰፍርብኝ ቃጣው ነቅንቆ ሊጥለኝ
ምናል ብረሳበት እግር እንደሌለኝ ፨
------------------///--------------
[በርናባስ ከበደ]
@getem
@getem
@gebrielAQL
-
መቼም ሰው ይስታል ፣ ዋናው መታረሙ
ህመም ሁሉ አይገልም፣ ዋናው መታከሙ፣
በሚል የሞራል ሕግ፣ የወል አስተሳሰብ
ያለማቆላለፍ ፣ ያለማወሳሰብ፣
ስለ አቋሙ ዝንፈት
ስለ ርምጃው ሽፈት
በተረዳኝ አቅም ባሽሙር ሳላነውር
ኮሶ ሁኖ ሚያሽር ሃሳብ ብወረውር፣
አለኝ ትንፍሽ አትበል ጩሆ በድንፋታ
ጫማዬን ሳታጠልቅ ሳትቆም በኔ ቦታ!
ወፈፍ አደረገው ...
ሊሰፍርብኝ ቃጣው ነቅንቆ ሊጥለኝ
ምናል ብረሳበት እግር እንደሌለኝ ፨
------------------///--------------
[በርናባስ ከበደ]
@getem
@getem
@gebrielAQL
ግብረ ቴስቲ ሶያ
(ቡሩክ ካሳሁን)
ከአዳም ምቹ ህይወት ከገነት ቆይታ
መጾም መስገድ እንጂ መች ተረፈን ደስታ
ከህጉ ሳይወጡ ተድላን ሚፈልጉ
አኩሪ አተርን ፈጭተው ስጋ አደረጉ
ቴስቲ ሶያ ቢባል ቢበላ እንደ ስጋ
ግብሩ ጎዶሎ ነው ከጠረጴዛ አልፎ መች ይሆናል ለአልጋ?
ህግ መጣስ አንሽም አንት የፈጠራ አባት የጥበብ ማሳያ
እባክህ አምጣልን ግብረ ቴስቲ ሶያ፡፡
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል
@burukassahunC
@getem
@getem
@gebriel_19
(ቡሩክ ካሳሁን)
ከአዳም ምቹ ህይወት ከገነት ቆይታ
መጾም መስገድ እንጂ መች ተረፈን ደስታ
ከህጉ ሳይወጡ ተድላን ሚፈልጉ
አኩሪ አተርን ፈጭተው ስጋ አደረጉ
ቴስቲ ሶያ ቢባል ቢበላ እንደ ስጋ
ግብሩ ጎዶሎ ነው ከጠረጴዛ አልፎ መች ይሆናል ለአልጋ?
ህግ መጣስ አንሽም አንት የፈጠራ አባት የጥበብ ማሳያ
እባክህ አምጣልን ግብረ ቴስቲ ሶያ፡፡
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል
@burukassahunC
@getem
@getem
@gebriel_19
ረድኤት አሰፋ
ቅዱሳን ቢደርሱት፥ ጻድቃን ቢጸልዩት
ሾላ በድፍን ነው፥
ጸሎትን ፈልፍለው፥ እንደራስ ካልበሉት፤
እጸድቃለሁ ብለሽ፥
ከገዛ ራስሽ ጋር፥ እንዳትካካጂ
ለጸሎት ስትቆሚ፥
'እክህደከ ሰይጣን'፥ ብለሽ አታውጂ።
@getem
@getem
@gebriel_19
ቅዱሳን ቢደርሱት፥ ጻድቃን ቢጸልዩት
ሾላ በድፍን ነው፥
ጸሎትን ፈልፍለው፥ እንደራስ ካልበሉት፤
እጸድቃለሁ ብለሽ፥
ከገዛ ራስሽ ጋር፥ እንዳትካካጂ
ለጸሎት ስትቆሚ፥
'እክህደከ ሰይጣን'፥ ብለሽ አታውጂ።
@getem
@getem
@gebriel_19
ለምን ይመስልሻል
ጥላኝ ሔደች ብዬ ፣ የማልጨነቀው?
መንገድ ስለሆንኩኝ
መሔድሽን አይታ
የምትመጣ እንዳለች ፣ ቀድሜ ነው ማውቀው። (ርእሱ ነው )
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
።።።
ስንት አመታት ሙሉ...
በመጋባት ናፍቆት ፣ ልቤን አንጠልጥለሽ
የኔፍሴን ህያው መልስ ፣ ጥያቄ ላይ ጥለሽ
ቅድሚያ ለእግረኛ
ትሰጫለሽ እያልኩ
መኪና ሲመጣ ፣ ሔድሽ ተንጠልጥለሽ
፡፡፡፡፡፡፡
ስለ ቬሎሽ አይነት...
ስላዳራሽ ኪራይ ፣
ሳወራሽ ከርሜ ፣ ስታወሪኝ ኖረሽ
ተንጠልጥሎ መሔድ ፣ ስለምን አማረሽ?
።።።።
ምንም ጋልቦ ባይሔድ ፣ ባልሞላበት ነዳጅ
እኔም መኪና አለኝ ፣ ምሰፋበት ቅዳጅ
ነይ ልብ እሰፋለሁ ፣ የሚሸሽ ከወዳጅ!!"
።።።
@getem
@getem
@getem
ጥላኝ ሔደች ብዬ ፣ የማልጨነቀው?
መንገድ ስለሆንኩኝ
መሔድሽን አይታ
የምትመጣ እንዳለች ፣ ቀድሜ ነው ማውቀው። (ርእሱ ነው )
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
።።።
ስንት አመታት ሙሉ...
በመጋባት ናፍቆት ፣ ልቤን አንጠልጥለሽ
የኔፍሴን ህያው መልስ ፣ ጥያቄ ላይ ጥለሽ
ቅድሚያ ለእግረኛ
ትሰጫለሽ እያልኩ
መኪና ሲመጣ ፣ ሔድሽ ተንጠልጥለሽ
፡፡፡፡፡፡፡
ስለ ቬሎሽ አይነት...
ስላዳራሽ ኪራይ ፣
ሳወራሽ ከርሜ ፣ ስታወሪኝ ኖረሽ
ተንጠልጥሎ መሔድ ፣ ስለምን አማረሽ?
።።።።
ምንም ጋልቦ ባይሔድ ፣ ባልሞላበት ነዳጅ
እኔም መኪና አለኝ ፣ ምሰፋበት ቅዳጅ
ነይ ልብ እሰፋለሁ ፣ የሚሸሽ ከወዳጅ!!"
።።።
@getem
@getem
@getem
።።ጠያቂ ፀረ ሰላም ነው።።
በኔ ሀገር ስኖር
ህዝብ ቸግሮት ሲያድር
እሚቀምሰው አጥቶ
ጥም እራብ በርትቶ
ሰቆቃው በርክቶ መኖር ተሰልችቶ
ሰላም አለ ሲባል ውስጥህ ሰላም አጥቶ
ትርጉሙ ጠፍቶብህ
ሰላም የታል ብለህ
ሲታወክ ሰላምህ
ሰሚ ሰው ፈልገህ
በሰላም ብትጠይቅ ሲፀናብህ ጥምህ
በጠኔ ተንጣነህ
ወሃ ብለህ ብጮህ
በነሱ አሰማም ያኔ ነው ስህተትህ
ያኔ ሰላም የለም
ሀገርም ታምሷል
ጥላቻ ታውጇል
....
.....
ምክንያቱም ወዳጀ ጠምቶህ ዝም አላልክም
ልተንፍስ ብለሀል ከፍቶህ አልታፈንክም
ያንተ የውሀ ጥያቄም ሆኗል ፀረ ሰላም
እናማ አትድከም
የሰላም ትርጉሙም ዝምታ ነውና
ሰላም እነዲሰፍን ዝምታን እናፅና ።
እስጢፋኖስ ተስፋየ
woldia university
@getem
@getem
@gebriel_19
በኔ ሀገር ስኖር
ህዝብ ቸግሮት ሲያድር
እሚቀምሰው አጥቶ
ጥም እራብ በርትቶ
ሰቆቃው በርክቶ መኖር ተሰልችቶ
ሰላም አለ ሲባል ውስጥህ ሰላም አጥቶ
ትርጉሙ ጠፍቶብህ
ሰላም የታል ብለህ
ሲታወክ ሰላምህ
ሰሚ ሰው ፈልገህ
በሰላም ብትጠይቅ ሲፀናብህ ጥምህ
በጠኔ ተንጣነህ
ወሃ ብለህ ብጮህ
በነሱ አሰማም ያኔ ነው ስህተትህ
ያኔ ሰላም የለም
ሀገርም ታምሷል
ጥላቻ ታውጇል
....
.....
ምክንያቱም ወዳጀ ጠምቶህ ዝም አላልክም
ልተንፍስ ብለሀል ከፍቶህ አልታፈንክም
ያንተ የውሀ ጥያቄም ሆኗል ፀረ ሰላም
እናማ አትድከም
የሰላም ትርጉሙም ዝምታ ነውና
ሰላም እነዲሰፍን ዝምታን እናፅና ።
እስጢፋኖስ ተስፋየ
woldia university
@getem
@getem
@gebriel_19
©©ሳይፀልዩ ማደር☜☜
የተራበነብር ከሩቅተመልክታ
ሚዳቋዋፀለየች አውጣኝ አውጣኝ አለች ለፈጠራት ጌታ
ነብሩም ተርቦ ወደአምላኩቀርቦ
አንጀቱከሆዱ እንደተጣበቀ ሚዳቋዋን አይቶ
ፈቅዶ እንዲሰጠው አምላኩን ጠየቀ
የሁለቱም አምላክ የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውን ሠማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምፁ ሚዳቆዋንአላት
እሩጠሽ አምልጪ ከበረታጠላት
ነብሩንም አለው እሩጥ ተከተላት ምግብአርገክ ብላት
ሚዳቆዋም ስትሮጥ ከነብሩ ለማምለጥ
ነብሩም ሢከተላት ሆዱን ሊሞላባት
ቋጥኙን ስትዘል እግሯተሥፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛከርከሮ
ከንቅልፉሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየውነብር
አውጣኝያለው ወቶ አበላኝያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ ተበላ
☞☞☞☞ በረከት በላይነህ☜☜☜☜
@lula_al_greeko
@getem
@getem
የተራበነብር ከሩቅተመልክታ
ሚዳቋዋፀለየች አውጣኝ አውጣኝ አለች ለፈጠራት ጌታ
ነብሩም ተርቦ ወደአምላኩቀርቦ
አንጀቱከሆዱ እንደተጣበቀ ሚዳቋዋን አይቶ
ፈቅዶ እንዲሰጠው አምላኩን ጠየቀ
የሁለቱም አምላክ የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውን ሠማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምፁ ሚዳቆዋንአላት
እሩጠሽ አምልጪ ከበረታጠላት
ነብሩንም አለው እሩጥ ተከተላት ምግብአርገክ ብላት
ሚዳቆዋም ስትሮጥ ከነብሩ ለማምለጥ
ነብሩም ሢከተላት ሆዱን ሊሞላባት
ቋጥኙን ስትዘል እግሯተሥፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛከርከሮ
ከንቅልፉሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየውነብር
አውጣኝያለው ወቶ አበላኝያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ ተበላ
☞☞☞☞ በረከት በላይነህ☜☜☜☜
@lula_al_greeko
@getem
@getem
ከንፈር ልሶ ማደር
———//————
መለየቱ ሲያምርሽ ፥ ከላዬ'ላይ መብረር
ከኔ ጉያ ርቀሽ ፣ ከዛኛው ለማደር
በለመድኳት ም'ኛት እንዲ ትይኝ ነበር
''በጊዜ ካልገባው፥ይቆጣኛል ፋዘር!!''
ግና ከኔ ርቀሽ
ሳደርሺ ካባትሽ
እንደ መንገድ እሸት፥የወይን ዘለላ
ይቆርጥሽ ነበር...
ከመንገድ ላይ ቆሞ፣የለመድሽው ገላ
እኔም በባዶዬ፥ጾሜን ላለማደር
አንቺን ተከትዬ፥ከደስታቹ መንደር
የሐሴት ግርፋት፥ሲወርድብሽ በትር
ሲቃሽን ላደምጥው፥እቆማለው ከበር
ልማዴ ነውና…
ጩህትሽን ሰምቶ፥ከንፈር ልሶ ማደር
ሚኪ endale
@MMIKU
@getem
@getem
———//————
መለየቱ ሲያምርሽ ፥ ከላዬ'ላይ መብረር
ከኔ ጉያ ርቀሽ ፣ ከዛኛው ለማደር
በለመድኳት ም'ኛት እንዲ ትይኝ ነበር
''በጊዜ ካልገባው፥ይቆጣኛል ፋዘር!!''
ግና ከኔ ርቀሽ
ሳደርሺ ካባትሽ
እንደ መንገድ እሸት፥የወይን ዘለላ
ይቆርጥሽ ነበር...
ከመንገድ ላይ ቆሞ፣የለመድሽው ገላ
እኔም በባዶዬ፥ጾሜን ላለማደር
አንቺን ተከትዬ፥ከደስታቹ መንደር
የሐሴት ግርፋት፥ሲወርድብሽ በትር
ሲቃሽን ላደምጥው፥እቆማለው ከበር
ልማዴ ነውና…
ጩህትሽን ሰምቶ፥ከንፈር ልሶ ማደር
ሚኪ endale
@MMIKU
@getem
@getem
(#ፋሲል_ስዩም)
©
...
ከላይ...
ከወደ ሰማይ...
ለአፍታ ማይጨፈን የፈጣሪ አይን፣
ከውብ ሽፋሽፍቱ የምትምዘገዘግ የስስት እይታ፣
ለፈጠረው ምድር፣እንደ ልብ ትርታ፣
(የዐይኑ ብልጭታ)
.
(ከታች)
ከእኔ ካንቺ መንደር...
ፈጣሪን የሚያሙ ማይዘጉ አፎች፣
እሳት የፀነሱ...እሳት የሚወልዱ...እልፋን አንደበቶች፣
(ክፍት አፎች፣)
.
(ከመሃሉ)
ቀይ ክር ያለበት የታሰረ ስጋ
ነክሶ የሚበርር
ጥምብ አንሳ አሞራ፣
ከነፋስ ጋር ምትዞር አንዲት የርግብ ላባ፣
ከምድር ተነጥቃ ከነፋስ ያበረች
ፅጌ-ሬዳ አበባ፣
(ትንሽ ከፍ ብሎ)
በደመና ስዕላት፣የተቀላለመ፣
የውብ ቆንጆ ስዕል፣
የሆነ መልክም አልባ፣
የሆነ ደምም አልባ፣
የሆነ ገላም አልባ፣
የደመቀ ምስል፣
፡
(እኔ)
ከመንደሬ ካለች ወንዝ ዳር ቁጭ ብዬ፣
ምናቤን፣
ከበላይ...ከመሃል...ከበታች
ደግሞም ካንቺ ጥዬ፣
በትንሽ ዛፍ ጥላ 'ራሴን ጠልዬ፣
(ግጥም እፅፋለሁ)
)ስንኝ እጥፋለሁ(
፡
ከወንዙ ባሻገር፣
ለጋነት ያነቃት፣አንዲት ልጃገረድ፣
ከጋለ አለት ላይ፣ለመብረድ ተቀምጣ፣
እግሮቿን ተከፍተው፣ቀሚሷ ተገልቦ፣
አዳፋ ብጫቂ፣ውራጅ ጨርቅ ታጥባለች፣
.
ቀና ስል ካየሁት፣ዝቅ ስል አጥቼ፣መሃል ላይ ካዋልኩት፣
የውበት ገፅታ፣
እኔን የማረከኝ፣
ብዕሬን ቀጥ አርጎ፣
ግጣም አሳይቶ፣
መግጠምን ያስረሳኝ፣
ከባሻገሬ ላይ፣
ከክፍት ቀሚስ መሃል፣
ተከፍቶ ያየሁት፣የውድዬ ሲሳይ፣!
(ከላይ)
(ፈጣሪ እንዳያይ)
፡
፡
...///...
ዲላ
@getem
@getem
@gebriel_19
©
...
ከላይ...
ከወደ ሰማይ...
ለአፍታ ማይጨፈን የፈጣሪ አይን፣
ከውብ ሽፋሽፍቱ የምትምዘገዘግ የስስት እይታ፣
ለፈጠረው ምድር፣እንደ ልብ ትርታ፣
(የዐይኑ ብልጭታ)
.
(ከታች)
ከእኔ ካንቺ መንደር...
ፈጣሪን የሚያሙ ማይዘጉ አፎች፣
እሳት የፀነሱ...እሳት የሚወልዱ...እልፋን አንደበቶች፣
(ክፍት አፎች፣)
.
(ከመሃሉ)
ቀይ ክር ያለበት የታሰረ ስጋ
ነክሶ የሚበርር
ጥምብ አንሳ አሞራ፣
ከነፋስ ጋር ምትዞር አንዲት የርግብ ላባ፣
ከምድር ተነጥቃ ከነፋስ ያበረች
ፅጌ-ሬዳ አበባ፣
(ትንሽ ከፍ ብሎ)
በደመና ስዕላት፣የተቀላለመ፣
የውብ ቆንጆ ስዕል፣
የሆነ መልክም አልባ፣
የሆነ ደምም አልባ፣
የሆነ ገላም አልባ፣
የደመቀ ምስል፣
፡
(እኔ)
ከመንደሬ ካለች ወንዝ ዳር ቁጭ ብዬ፣
ምናቤን፣
ከበላይ...ከመሃል...ከበታች
ደግሞም ካንቺ ጥዬ፣
በትንሽ ዛፍ ጥላ 'ራሴን ጠልዬ፣
(ግጥም እፅፋለሁ)
)ስንኝ እጥፋለሁ(
፡
ከወንዙ ባሻገር፣
ለጋነት ያነቃት፣አንዲት ልጃገረድ፣
ከጋለ አለት ላይ፣ለመብረድ ተቀምጣ፣
እግሮቿን ተከፍተው፣ቀሚሷ ተገልቦ፣
አዳፋ ብጫቂ፣ውራጅ ጨርቅ ታጥባለች፣
.
ቀና ስል ካየሁት፣ዝቅ ስል አጥቼ፣መሃል ላይ ካዋልኩት፣
የውበት ገፅታ፣
እኔን የማረከኝ፣
ብዕሬን ቀጥ አርጎ፣
ግጣም አሳይቶ፣
መግጠምን ያስረሳኝ፣
ከባሻገሬ ላይ፣
ከክፍት ቀሚስ መሃል፣
ተከፍቶ ያየሁት፣የውድዬ ሲሳይ፣!
(ከላይ)
(ፈጣሪ እንዳያይ)
፡
፡
...///...
ዲላ
@getem
@getem
@gebriel_19
"ትክክል? /ስህተት? "
( በአምባዬ ጌታነህ )
ልክ ነበርሽ አንቺ
ልክ ነበርኩ ያኔ፣
የእኔ በአንቺ መሄድ
መማገጠሽ በእኔ።
የለገመ ወስፌ
ቅቤ የማይወጋው፣
የኔና አንቺን ናፍቆት፣
የበረሀ ጋመን
በጧት ያቃጠለው፣
ከመውደድ ከመጥላት
የተሰላቸነው፣
ከትላንት ወዲያ ነው።
ምፅአት ቢመጣ እንኳ
ከእንግዲህ ህልም እልም፣
በድጋሚ አንድ ላይ
እኔ እና አንቺ አንሆንም።
ከድሮውም ቢሆን፣
የኔና የአንቺ ፍቅር
የማስመሰል ጥበብ
የላይ ብቻ ነበር።
ከእኔ መለየቱ ስኬትሽ ከሆነ፣
እኔም የስንት ጊዜ ህልሜ እውን ሆነ።
07/09/2011 ጠዋት 12:14
@amba88 የቻናሉ ቤተሰብ ለመሆን
@getem
@getem
@getem
( በአምባዬ ጌታነህ )
ልክ ነበርሽ አንቺ
ልክ ነበርኩ ያኔ፣
የእኔ በአንቺ መሄድ
መማገጠሽ በእኔ።
የለገመ ወስፌ
ቅቤ የማይወጋው፣
የኔና አንቺን ናፍቆት፣
የበረሀ ጋመን
በጧት ያቃጠለው፣
ከመውደድ ከመጥላት
የተሰላቸነው፣
ከትላንት ወዲያ ነው።
ምፅአት ቢመጣ እንኳ
ከእንግዲህ ህልም እልም፣
በድጋሚ አንድ ላይ
እኔ እና አንቺ አንሆንም።
ከድሮውም ቢሆን፣
የኔና የአንቺ ፍቅር
የማስመሰል ጥበብ
የላይ ብቻ ነበር።
ከእኔ መለየቱ ስኬትሽ ከሆነ፣
እኔም የስንት ጊዜ ህልሜ እውን ሆነ።
07/09/2011 ጠዋት 12:14
@amba88 የቻናሉ ቤተሰብ ለመሆን
@getem
@getem
@getem