.............
በምን ሀቅ ጠየከኝ
በዕጣ ፋንታ ጽፈህ፤ከትከሻህ መስቀል
መዳን ያላቃተው፥ቃልህን ለመስቀል
ፈቅደህ ለሰየምከው፤ላኖርኩብህ ችንካር
በምን ሀቅ ጠይቀህ፤አጨኀኝ ለአሳር
ወዳ የተኛችና፤ፈቅዶ የዘሞተ
መዳን እየቻለ፤ለማዳን የሞተ
ደፈረኝ አትልም፤ቀሚሴን ገፈፈ
ገደለኝ ጥሰት ነው፤መሞቱን ለጻፈ
በዝሙት ሞግተኝ
ለረከሰች ነፍሴ፤ልማጸንህ ምላሽ
ፈቅዶ ለሚሰቀል፤ማን ሊሆነው ደራሽ
ይክደኛል ብለህ፤መዝነህ እምነቴን
ውሸቴን እያወክ፤ለሸሸህ እውነቴን
ሞቱኩ ብለህ አድነህ
ገለህኛል ብለህ፤የሰየምከኝ ሸንጎ
በምን ቃል ለሟገት
ከመስቀልህ ጀርባ፤ሀቄ ተሸሽጎ
በምን ልብ ልማልድህ፤በየቱ ልማጸን
ገዱ ለተጻፈ ገና ከማህጸን
ሳይወልዱት ለማይድን
ተወልዶ ለሚያድን
የተሰዋ ሀቄን፤የከተቡት እድል
በምን ሀቅ ጠየከኝ፤እዲያው ምን ብበድል
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
በምን ሀቅ ጠየከኝ
በዕጣ ፋንታ ጽፈህ፤ከትከሻህ መስቀል
መዳን ያላቃተው፥ቃልህን ለመስቀል
ፈቅደህ ለሰየምከው፤ላኖርኩብህ ችንካር
በምን ሀቅ ጠይቀህ፤አጨኀኝ ለአሳር
ወዳ የተኛችና፤ፈቅዶ የዘሞተ
መዳን እየቻለ፤ለማዳን የሞተ
ደፈረኝ አትልም፤ቀሚሴን ገፈፈ
ገደለኝ ጥሰት ነው፤መሞቱን ለጻፈ
በዝሙት ሞግተኝ
ለረከሰች ነፍሴ፤ልማጸንህ ምላሽ
ፈቅዶ ለሚሰቀል፤ማን ሊሆነው ደራሽ
ይክደኛል ብለህ፤መዝነህ እምነቴን
ውሸቴን እያወክ፤ለሸሸህ እውነቴን
ሞቱኩ ብለህ አድነህ
ገለህኛል ብለህ፤የሰየምከኝ ሸንጎ
በምን ቃል ለሟገት
ከመስቀልህ ጀርባ፤ሀቄ ተሸሽጎ
በምን ልብ ልማልድህ፤በየቱ ልማጸን
ገዱ ለተጻፈ ገና ከማህጸን
ሳይወልዱት ለማይድን
ተወልዶ ለሚያድን
የተሰዋ ሀቄን፤የከተቡት እድል
በምን ሀቅ ጠየከኝ፤እዲያው ምን ብበድል
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
❤19👍11🔥3
ለምን ፣ ለምን ፣ ለምን?
(ሚካኤል አ)
(ጠዋት)
እኔ ያንቺ ባካኝ
ብርድ ፣ ቁር ሳይረታኝ
ወረቀት ሳይበቃኝ
ሳልሰስት ለቀለም
በፍቅርሽ ስታመም
እንዴት እንደከረምኩ
አንቺን ለማስረዳት
ግጥም መፃፍ ጀመርኩ።
ጻፍኩኝ ብዙ ፣ ብዙ
“ ስለ ዓይንሽ መዘዙ
ስለ ትንሽ ጣትሽ
ልክ እኔ ሳፈቅርሽ
ነክሳሽ ነበር ቢንቢ
ከጥፍርሽ ግርጌ…
ሰው መሆኔን ጠላሁ
ቢንቢነት ፈልጌ ።
ደግሞ ካንገትሽ ስር
ማርያም የሳመችሽ
ጥቁር ፣ አንድ … ነጥብ
በማርያም ቀናሁኝ
አንቺን መሳም ሳስብ።
ዝቅ አልኩኝ ለጥቆ
ሎሚ ተረከዝሽ
እንሶስላ ሞቆ
በነጠላ ጫማ
ባየው አሸብርቆ
ጫማ መሆን ፈለ’ኩ
ብረገጥ ከእግርሽ ስር
:
ሰው መሆን ሲደብር ! “
የሚል ስንኝ ቃላት
ጀምሬ በጠዋት
እንዲህ እንዲያ እያልኩኝ
በብዙ ብፅፍም
(ማት አመሻሽ ላይ )
“ግጥም አትወድም “
ብላ ነገረችኝ ፣ ጓደኛሽ በሀዘን
ከቅፅበት በኋላ
ባዶ ሆነ ፍቅርሽ ፣ ከልቤ ሲመዘን ።
ለምን ጠላሽ ቅኔ?
ለምን ጠላሽ ግጥም?
:
አንቺን አልፈልግም።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አ)
(ጠዋት)
እኔ ያንቺ ባካኝ
ብርድ ፣ ቁር ሳይረታኝ
ወረቀት ሳይበቃኝ
ሳልሰስት ለቀለም
በፍቅርሽ ስታመም
እንዴት እንደከረምኩ
አንቺን ለማስረዳት
ግጥም መፃፍ ጀመርኩ።
ጻፍኩኝ ብዙ ፣ ብዙ
“ ስለ ዓይንሽ መዘዙ
ስለ ትንሽ ጣትሽ
ልክ እኔ ሳፈቅርሽ
ነክሳሽ ነበር ቢንቢ
ከጥፍርሽ ግርጌ…
ሰው መሆኔን ጠላሁ
ቢንቢነት ፈልጌ ።
ደግሞ ካንገትሽ ስር
ማርያም የሳመችሽ
ጥቁር ፣ አንድ … ነጥብ
በማርያም ቀናሁኝ
አንቺን መሳም ሳስብ።
ዝቅ አልኩኝ ለጥቆ
ሎሚ ተረከዝሽ
እንሶስላ ሞቆ
በነጠላ ጫማ
ባየው አሸብርቆ
ጫማ መሆን ፈለ’ኩ
ብረገጥ ከእግርሽ ስር
:
ሰው መሆን ሲደብር ! “
የሚል ስንኝ ቃላት
ጀምሬ በጠዋት
እንዲህ እንዲያ እያልኩኝ
በብዙ ብፅፍም
(ማት አመሻሽ ላይ )
“ግጥም አትወድም “
ብላ ነገረችኝ ፣ ጓደኛሽ በሀዘን
ከቅፅበት በኋላ
ባዶ ሆነ ፍቅርሽ ፣ ከልቤ ሲመዘን ።
ለምን ጠላሽ ቅኔ?
ለምን ጠላሽ ግጥም?
:
አንቺን አልፈልግም።
@getem
@getem
@getem
👍44😁21❤19🤩1
❤50👍11🔥3😢3
\ ዱ ባባ /
ሁለት ሰው ነበሩ...
በገንገን ወንዝ ዳር
በዱባባ ገጠር ፣
አንዱ እንዲፈቀር
ላንዱ የሚፈጠር ፣
አንዱ እንዲቆጠር
አንዱ የሚሰበር ፣
አንዱ እንዲራመድ
አንዱ ነፍስ የሚበር፣
ደሞ አንዱ አለ...
አንዱን ለመሆን
ከአንድ የሚሰፋ ፣
ሻማውን አቅልጦ
በስንጥር ክብሪት
በሰከንድ ሚጠፋ ፣
ላያወጣው ነገር
የሻርኩ ጉንጭ ላይ
ምራቅ የሚተፋ ፣
አንደኛዋ አለች
እናት ምትባል
ወላድ የምትባል ፣
በጉምዝ አንቀልባ
ልጇን ከወንዝ ሰዳ
እሷ እየሳቀች
ባሏ ቤት ያነባል ፣
እነሱ እያሉ
ማች ልጇ ይረባል ፣
ዱ ባባ ብትልም
ልጇን ደራሽ ወስዶ
ከውሃ ስትጠማ ፣
ቀን ከፈረደ
በህፃን ትጠራለች
የአንዲት ገጠር ስሟ፣
ዳስ ቢሆንም ከቶ
ያገሩ ኩራቱ
ከአንድ እጅ ቢበልጥም ፣
ሁለት አለኝ ተብሎ
ተአምር ቢፈጠር
ልጅ ሞቱን አይሰጥም ፣
እዳ እና እፍርቱ
በጉምዟ ሲናሻ
በዱ'ባባ መሃል ፣
አንድ ህፃን አለ
ከገንገን ወንዝ ላይ
ሬሳው ይጮኻል፣
በቀጭን ታሪክ ስር
የሚጠና ስም ላይ
ገጠር እንዲባል ፣
መቀንጨር ነው መልሱ
ላልተወለደ ልጅ
መኖርም ያባባል፣
ሁለት ሚባል የለም
ሞትም አንድ ነው ስሙ፣
በገዛ ከንፈር የገዛ ጉንጭን
እንዴት ነው ምትስሙ
ለዚህች እናት ታዝኖ
በህፃኗ ሞት ላይ
ሁለት ስሜት የለም
ወይ አልቅስ ለስቃይ
ወይ ገርሞህ ሳቅ ይታይ
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት 🦘
@getem
@getem
@getem
ሁለት ሰው ነበሩ...
በገንገን ወንዝ ዳር
በዱባባ ገጠር ፣
አንዱ እንዲፈቀር
ላንዱ የሚፈጠር ፣
አንዱ እንዲቆጠር
አንዱ የሚሰበር ፣
አንዱ እንዲራመድ
አንዱ ነፍስ የሚበር፣
ደሞ አንዱ አለ...
አንዱን ለመሆን
ከአንድ የሚሰፋ ፣
ሻማውን አቅልጦ
በስንጥር ክብሪት
በሰከንድ ሚጠፋ ፣
ላያወጣው ነገር
የሻርኩ ጉንጭ ላይ
ምራቅ የሚተፋ ፣
አንደኛዋ አለች
እናት ምትባል
ወላድ የምትባል ፣
በጉምዝ አንቀልባ
ልጇን ከወንዝ ሰዳ
እሷ እየሳቀች
ባሏ ቤት ያነባል ፣
እነሱ እያሉ
ማች ልጇ ይረባል ፣
ዱ ባባ ብትልም
ልጇን ደራሽ ወስዶ
ከውሃ ስትጠማ ፣
ቀን ከፈረደ
በህፃን ትጠራለች
የአንዲት ገጠር ስሟ፣
ዳስ ቢሆንም ከቶ
ያገሩ ኩራቱ
ከአንድ እጅ ቢበልጥም ፣
ሁለት አለኝ ተብሎ
ተአምር ቢፈጠር
ልጅ ሞቱን አይሰጥም ፣
እዳ እና እፍርቱ
በጉምዟ ሲናሻ
በዱ'ባባ መሃል ፣
አንድ ህፃን አለ
ከገንገን ወንዝ ላይ
ሬሳው ይጮኻል፣
በቀጭን ታሪክ ስር
የሚጠና ስም ላይ
ገጠር እንዲባል ፣
መቀንጨር ነው መልሱ
ላልተወለደ ልጅ
መኖርም ያባባል፣
ሁለት ሚባል የለም
ሞትም አንድ ነው ስሙ፣
በገዛ ከንፈር የገዛ ጉንጭን
እንዴት ነው ምትስሙ
ለዚህች እናት ታዝኖ
በህፃኗ ሞት ላይ
ሁለት ስሜት የለም
ወይ አልቅስ ለስቃይ
ወይ ገርሞህ ሳቅ ይታይ
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት 🦘
@getem
@getem
@getem
👍39❤8😱2
ይቅርታዬ
ምን ቢሰማኝ ሰላም ወይ ጥል ምን ብኳትን ያለው ሊሆን ምን ብታመም ለማገግም ምን ብሰቃይ ዳግም ልስቅ ይታየኛል ፋኖሶቹ ከዐይኔ ሳይርቅ ይታየኛል ሙሉ ተስፋው እኔን ሊያደምቅ፤ ይታየኛል ከስሬ ነው ከልቤ ስር አድማስ ያለው፤ ከእግሮቹ ነኝ ከመዳፉ መቼም አርቅ ከበራፉ፤ እሱን ይዤ ያጣሁበት እሱን ብዬ ያፈርኩበት፤ ቀን አላውቅም ብጠይቁኝ ግን .......... ምስክር ነኝ ላመንኩበት ልንገራችሁ እጁን ያዙት ችላ ቢልም አትልቀቁት፤ ምክንያት አለው ሲፈትንም እያዳነኝ ዝም አልልም ።
By bline asefa
@getem
@getem
@getem
ምን ቢሰማኝ ሰላም ወይ ጥል ምን ብኳትን ያለው ሊሆን ምን ብታመም ለማገግም ምን ብሰቃይ ዳግም ልስቅ ይታየኛል ፋኖሶቹ ከዐይኔ ሳይርቅ ይታየኛል ሙሉ ተስፋው እኔን ሊያደምቅ፤ ይታየኛል ከስሬ ነው ከልቤ ስር አድማስ ያለው፤ ከእግሮቹ ነኝ ከመዳፉ መቼም አርቅ ከበራፉ፤ እሱን ይዤ ያጣሁበት እሱን ብዬ ያፈርኩበት፤ ቀን አላውቅም ብጠይቁኝ ግን .......... ምስክር ነኝ ላመንኩበት ልንገራችሁ እጁን ያዙት ችላ ቢልም አትልቀቁት፤ ምክንያት አለው ሲፈትንም እያዳነኝ ዝም አልልም ።
By bline asefa
@getem
@getem
@getem
❤63👍26🤩3
Forwarded from վohaŋŋes Lawgaw
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤21👍8🔥3🎉3😱2🤩1
Forwarded from Sami Alemu
ጣዕሙን የሚያውቀው
(ሳሙኤል አለሙ)
እንደ ሌላው
እንደ ሌላው፤
ሰርክ...
ጉንጭሽ ጋ አይደረስም
ረ------ጅም ነው ኬላው።
እያዩት...
ያስውላል።
ዕሮብ ለት
እያዩት...
ያፆማል።
አርብ ዕለት
እንደ እኛው
እንደ እኛው፤
አንቺ...
ከቶ አልተፈጠርሽም
በቀን ስድስተኛው።
ለምን...?
አይባልም።
አይጠየቅም።
እንዴት...?
አትለውም።
አትከራከርም።
ከአፈሩም ፣ ከውኃውም
ከእስትንፋሱም ፣ ሌላም
አለው... ሌላም...ሌላም
ሌላም አለው ያከለበት፤
ወተቱን እንዳ---
ፈሰሰ---
---በት
ጉንጭሽን የሳመው።
ጣዕሙን የሚያቀው።
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@getem
@getem
(ሳሙኤል አለሙ)
እንደ ሌላው
እንደ ሌላው፤
ሰርክ...
ጉንጭሽ ጋ አይደረስም
ረ------ጅም ነው ኬላው።
እያዩት...
ያስውላል።
ዕሮብ ለት
እያዩት...
ያፆማል።
አርብ ዕለት
እንደ እኛው
እንደ እኛው፤
አንቺ...
ከቶ አልተፈጠርሽም
በቀን ስድስተኛው።
ለምን...?
አይባልም።
አይጠየቅም።
እንዴት...?
አትለውም።
አትከራከርም።
ከአፈሩም ፣ ከውኃውም
ከእስትንፋሱም ፣ ሌላም
አለው... ሌላም...ሌላም
ሌላም አለው ያከለበት፤
ወተቱን እንዳ---
ፈሰሰ---
---በት
ጉንጭሽን የሳመው።
ጣዕሙን የሚያቀው።
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@getem
@getem
👍39❤19🔥1🤩1
...........
ኢትዮጵያዬ ልጄን ውለጅ
አንደወጣ ቀረ ከደጅ
አፈር ምሶ የቀበረ
ውለጅ ይላል እያረረ
ከገጠሩ
ከመንደሩ
ከጎዳና ከድንበሩ
ለዘላለም ለማይደላው
ለምን ? ልጄን ልጅሽ በላው!
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
ኢትዮጵያዬ ልጄን ውለጅ
አንደወጣ ቀረ ከደጅ
አፈር ምሶ የቀበረ
ውለጅ ይላል እያረረ
ከገጠሩ
ከመንደሩ
ከጎዳና ከድንበሩ
ለዘላለም ለማይደላው
ለምን ? ልጄን ልጅሽ በላው!
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍47😢25❤12🔥2
ህይወት ሞልታ አትሞላም
ወይ ጎላ አትጎድል
ቁልፉ ስኬት ሲሆን
ውድቀት ዋነኛው ድል
ስቃይ እና ደስታ...ድሎት እና ችግር
ምን ቢሆን ጣዕሙ
ሁሉም እርግፍ ይላል
ባንቺ ከተሳሙ
"ደስታ ምንም ነው
ስቃይ አይታሰብም
ለእንደኔ እና እንዳንቺ
ብቻ ሳሚኝ አንቺ"
ብዬ ነበር ብዬ ነበር
ሆኖ አንገትሽ ሌላ ዘንዳ
እያየሁት ዛሬ ባይኔ
አትረሳህም እለዋለው
ለተጎዳው ባንቺ ጎኔ
የቀን ሳቄን ከሳቅሽ ጋር
እንዳልሳቅነው ተያይዘን
ሲመሽ ሲጠልቅ ሁሉም ነገር
ስንቱ ቀናት ደበዘዘን
አይኔ ይበቃል ለመረዳት
ባላወጣው የፍቅሬን ቃል
እንደወደድኩሽ ነው...
ድፍን ሐገር ያውቃል
ውድቀት ቢሆን ሲመሽ ጊዜው
ይበቃኛል ለቀኑ ዕድል
ህይወት እንደዚህ ነች
ወይ ሞልታ አትሞላም
ወይ ጎላ አትጎድል።
አሳየሽኝ ስቃይ ድሉን
ከዚም ከዛም እያጣቀሽ
ተኮሳትረሽ ያው ወርቅ ነሽ
ትገያለሽ ደግሞ ስቀሽ
አስረዳሁሽ በአይን ወሬ
ልብሽ ከቶ ምኑን ነቃ
አንቺም ሂጂ ይለይልኝ
እኔም ደግሞ ልርሳሽ በቃ።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ወይ ጎላ አትጎድል
ቁልፉ ስኬት ሲሆን
ውድቀት ዋነኛው ድል
ስቃይ እና ደስታ...ድሎት እና ችግር
ምን ቢሆን ጣዕሙ
ሁሉም እርግፍ ይላል
ባንቺ ከተሳሙ
"ደስታ ምንም ነው
ስቃይ አይታሰብም
ለእንደኔ እና እንዳንቺ
ብቻ ሳሚኝ አንቺ"
ብዬ ነበር ብዬ ነበር
ሆኖ አንገትሽ ሌላ ዘንዳ
እያየሁት ዛሬ ባይኔ
አትረሳህም እለዋለው
ለተጎዳው ባንቺ ጎኔ
የቀን ሳቄን ከሳቅሽ ጋር
እንዳልሳቅነው ተያይዘን
ሲመሽ ሲጠልቅ ሁሉም ነገር
ስንቱ ቀናት ደበዘዘን
አይኔ ይበቃል ለመረዳት
ባላወጣው የፍቅሬን ቃል
እንደወደድኩሽ ነው...
ድፍን ሐገር ያውቃል
ውድቀት ቢሆን ሲመሽ ጊዜው
ይበቃኛል ለቀኑ ዕድል
ህይወት እንደዚህ ነች
ወይ ሞልታ አትሞላም
ወይ ጎላ አትጎድል።
አሳየሽኝ ስቃይ ድሉን
ከዚም ከዛም እያጣቀሽ
ተኮሳትረሽ ያው ወርቅ ነሽ
ትገያለሽ ደግሞ ስቀሽ
አስረዳሁሽ በአይን ወሬ
ልብሽ ከቶ ምኑን ነቃ
አንቺም ሂጂ ይለይልኝ
እኔም ደግሞ ልርሳሽ በቃ።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
👍31❤6😢3🤩2
የደስታ ሰማይ - በር መክፈቻ፣
ይገኛል መስሎሽ - በመብረር ብቻ፣
በተዋስሽው ክንፍ - ሽቅብ ስትመጥቂ፣
የደመና ሆድ ስትሰነጥቂ ፣
(ድንገት ከአየር ላይ)
በባለ ክንፉ - ስትነጠቂ፥
በማይገመት - በማይጠበቅ ፣
በእድል ጨፈቃ - በጊዜ ለበቅ፣
በጊዜ ለበቅ - በማይመከት፣
ስትገረፊ -
ደንግጠን ሽቅብ - ስንመለከት፣
ስንመለከት የማታ ማታ፥
ያዘልሽው ላባ -
የአንቺ እንዳልሆነ - ትዝ ያለሽ ለታ፥
ወዮ የዛን 'ለት - ለመንደራችን፤
ወዮ ለመሬት፥
ወዮ ለጆሮ - ወዮ ለዐይናችን፤
By Michael Minassie
@getem
@getem
@paappii
ይገኛል መስሎሽ - በመብረር ብቻ፣
በተዋስሽው ክንፍ - ሽቅብ ስትመጥቂ፣
የደመና ሆድ ስትሰነጥቂ ፣
(ድንገት ከአየር ላይ)
በባለ ክንፉ - ስትነጠቂ፥
በማይገመት - በማይጠበቅ ፣
በእድል ጨፈቃ - በጊዜ ለበቅ፣
በጊዜ ለበቅ - በማይመከት፣
ስትገረፊ -
ደንግጠን ሽቅብ - ስንመለከት፣
ስንመለከት የማታ ማታ፥
ያዘልሽው ላባ -
የአንቺ እንዳልሆነ - ትዝ ያለሽ ለታ፥
ወዮ የዛን 'ለት - ለመንደራችን፤
ወዮ ለመሬት፥
ወዮ ለጆሮ - ወዮ ለዐይናችን፤
By Michael Minassie
@getem
@getem
@paappii
👍20❤18🔥2
..........
በመዳፌ ጠፈር ዳሳሽ
በኣይኖቼ ህዋን አሳሽ
አፈር ድንጋዩን መርማሪ
ፀሀይን በጥፊ ኣብራሪ
ጨረቃን በኩርኩም ቀባሪ
በውርቅያኖስ የምግሞጠሞጥ
ከንፋስ እጥፍ የምሮጥ
ጉም ዘጋኝ በመዳፌ
በኖህ መርከብ ቀዝፌ
ከጥፋት ውሀ ተርፌ
ቅንጥብ ዘንባባ ቀጥፌ
ኣዲስ ምዕራፍ የማበስር
ብኩርናዬን የማልሸጥ በምስር
በኮከብ ወደም ምጫወት
የማድር ከኣብርሀም ቤት
እንግዳ ያልሆንኩኝ እንግዳ
የሩቅ ዘመድ የቅርብ ባዳ
ከጲላጦስ ሸንጎ የምፋረድ
በደመና ይምራመድ
ከሰባሰገሎች ኣንዱ
ወርቅ እጣን ከርቤ የገበረ
ንጉሱን ከበረት ኣይቶ እረኛውን ያከበረ
ከድንጋይ ከህጻናት ጋር
ሆሳእና ብሎ የዘመረ
እኔ ነኝ ብኩኑ ባሪያህ የጥበብህ ማሳያ
የሀዲስ ኪዳን ነብይ የኦሪት ሀዋርያ
በሀሳቤ እሩቅ ተጎዝ
ባካሌ ከቅርብ የማድር
ቅንጣት እምነት የጎደለኝ
የሚነቅል የተራራን ስር
እንኳንስ በደመና ላይ
በጠፈር ሰማይ ምድሩ
ሸክም ሆኖ የከበደኝ
የኣካሌ ክፋይ ኣፈሩ
ጉም መጨበጥ የምመኝ
የእጄን መና ለቅቄ
በሀሳብ ከኣብርሀም ያደርኩ
ከመንገድ መሀል ወድቄ
በኮከብ ወደሙ ቀርቶ
ጠጠር ማንሳት ያቃተኝ
ፍቅር መስቀል ይመስል
በየቀን የሚያቃትተኝ
አንድ ቀን ጠግቦ ለማደር
ብኩርናዬን የምሰዋ
ባገሬ መኖር ያቃተኝ
እንኳን በጠፈር ህዋ
ኣንድ ጉንጭ ውሀ የምለምን
ውርቂያኖስ መሉ ተፍቼ
ከሰገባ የማድር
ከስልክ እንጨት ስር ተኝቼ
ከጥፋት ውሀ ታዳሚ
ወይ ኣልድን ወይ ሰጥሜ ኣልሞት
እስትንፋስ አልባ የሆነ
የምኖሮ ትርጉም ኣልባ ህይወት
የኖህም መርከብ የራቀኝ
ለምግብ ጥንብ ኣንሳ የነቀኝ
መሲህ ፍለጋ ወጥቼ
ነብይ ይዜ የተመለስኩ
ሰባሰገል ተብዬ
ከሄሮድስ ጭፍሮች ያበርኩ
እንኳንስ ፀሀይ በጥፊ
ውቧን ጨረቃ በኩርኩም
ዝንብ ሽ ማለት ያቃተኝ
ሀሳቤ ብናኝ እንደ ጉም
እኔ ነኝ ብኩኑ ፍጡርህ
በህልሜ ሁሌ ከደጅህ
ስነቃ ከተራራው ስር
ደራሽ በሌለበት ምድር
በሲቃ ድምጽ የምጣራ
ከመብረቅም በሚያስፈራ
የቅንጣት እምነቴ ተራራ ኣነቅል ቢለኝ
ተራራ ያሸከመኝ
ከገነት ያላደርኩ ከሲኦል ያልገባው
መሲሁን ጠቋሚ ኣንድ ኮከብ ያጣው
ወይ ድኜ ኣልድን ከስሜ አልጠፋ
ከፈራጅ ችሎት ዳኛ የማስከፋ
እኔ ነኝ ብኩኑ ፍጡርህ
ወድቄ ያለው ከግርህ
ፍቅርህን የምሻ ልቤን ኣሽችቼ
ልክ እንደ ኣይሁድ ጎኑን ወግቼ
ከእቅፍህ ውስጥ ማደር የምመኝ
ብኩኑ ልጅህ
ባሪያህ እኔ ነኝ
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
በመዳፌ ጠፈር ዳሳሽ
በኣይኖቼ ህዋን አሳሽ
አፈር ድንጋዩን መርማሪ
ፀሀይን በጥፊ ኣብራሪ
ጨረቃን በኩርኩም ቀባሪ
በውርቅያኖስ የምግሞጠሞጥ
ከንፋስ እጥፍ የምሮጥ
ጉም ዘጋኝ በመዳፌ
በኖህ መርከብ ቀዝፌ
ከጥፋት ውሀ ተርፌ
ቅንጥብ ዘንባባ ቀጥፌ
ኣዲስ ምዕራፍ የማበስር
ብኩርናዬን የማልሸጥ በምስር
በኮከብ ወደም ምጫወት
የማድር ከኣብርሀም ቤት
እንግዳ ያልሆንኩኝ እንግዳ
የሩቅ ዘመድ የቅርብ ባዳ
ከጲላጦስ ሸንጎ የምፋረድ
በደመና ይምራመድ
ከሰባሰገሎች ኣንዱ
ወርቅ እጣን ከርቤ የገበረ
ንጉሱን ከበረት ኣይቶ እረኛውን ያከበረ
ከድንጋይ ከህጻናት ጋር
ሆሳእና ብሎ የዘመረ
እኔ ነኝ ብኩኑ ባሪያህ የጥበብህ ማሳያ
የሀዲስ ኪዳን ነብይ የኦሪት ሀዋርያ
በሀሳቤ እሩቅ ተጎዝ
ባካሌ ከቅርብ የማድር
ቅንጣት እምነት የጎደለኝ
የሚነቅል የተራራን ስር
እንኳንስ በደመና ላይ
በጠፈር ሰማይ ምድሩ
ሸክም ሆኖ የከበደኝ
የኣካሌ ክፋይ ኣፈሩ
ጉም መጨበጥ የምመኝ
የእጄን መና ለቅቄ
በሀሳብ ከኣብርሀም ያደርኩ
ከመንገድ መሀል ወድቄ
በኮከብ ወደሙ ቀርቶ
ጠጠር ማንሳት ያቃተኝ
ፍቅር መስቀል ይመስል
በየቀን የሚያቃትተኝ
አንድ ቀን ጠግቦ ለማደር
ብኩርናዬን የምሰዋ
ባገሬ መኖር ያቃተኝ
እንኳን በጠፈር ህዋ
ኣንድ ጉንጭ ውሀ የምለምን
ውርቂያኖስ መሉ ተፍቼ
ከሰገባ የማድር
ከስልክ እንጨት ስር ተኝቼ
ከጥፋት ውሀ ታዳሚ
ወይ ኣልድን ወይ ሰጥሜ ኣልሞት
እስትንፋስ አልባ የሆነ
የምኖሮ ትርጉም ኣልባ ህይወት
የኖህም መርከብ የራቀኝ
ለምግብ ጥንብ ኣንሳ የነቀኝ
መሲህ ፍለጋ ወጥቼ
ነብይ ይዜ የተመለስኩ
ሰባሰገል ተብዬ
ከሄሮድስ ጭፍሮች ያበርኩ
እንኳንስ ፀሀይ በጥፊ
ውቧን ጨረቃ በኩርኩም
ዝንብ ሽ ማለት ያቃተኝ
ሀሳቤ ብናኝ እንደ ጉም
እኔ ነኝ ብኩኑ ፍጡርህ
በህልሜ ሁሌ ከደጅህ
ስነቃ ከተራራው ስር
ደራሽ በሌለበት ምድር
በሲቃ ድምጽ የምጣራ
ከመብረቅም በሚያስፈራ
የቅንጣት እምነቴ ተራራ ኣነቅል ቢለኝ
ተራራ ያሸከመኝ
ከገነት ያላደርኩ ከሲኦል ያልገባው
መሲሁን ጠቋሚ ኣንድ ኮከብ ያጣው
ወይ ድኜ ኣልድን ከስሜ አልጠፋ
ከፈራጅ ችሎት ዳኛ የማስከፋ
እኔ ነኝ ብኩኑ ፍጡርህ
ወድቄ ያለው ከግርህ
ፍቅርህን የምሻ ልቤን ኣሽችቼ
ልክ እንደ ኣይሁድ ጎኑን ወግቼ
ከእቅፍህ ውስጥ ማደር የምመኝ
ብኩኑ ልጅህ
ባሪያህ እኔ ነኝ
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍32❤16😱5🔥3