.................
ኣላወቅሽም እንጂ፤ኣስቤሽ ነበረ
ሚስክን ልቤ የፍጥኝ፤ባንቺ እንደታሰረ
ላዘን ለእንጉርጉሮ፤ካረቄ ቤት ገብቶ
ንዴቱን ማብረጃ፤ትንሽ ተጎንጭቶ
ገና እንደሰከረ፤ስምሽን እንደጠራ
ኣይኔን ህመም ሞልቶት፤በእንባ ላያባራ
እቅፍሽን ለምዶ፤ከትቦ ስር ሲያድር
ኣላወቅሽም እንጂ፤ብታውቂማ ፍቅር
እቅፍ ድግፍ ኣርገሽ፤ኣዝነሽ በመውደቄ
ትንባሆ ሲጃራ፤መጠጥ አና ኣረቄ
በህጻን ልጅ ኩርፊያ፤ንዴትና ቁጣ
እንደምትገዝቺኝ፤ዳግም እንዳልጠጣ
ኣቅ ነበር ብትወጂኝ፤ኣጨክኝም በኔ
ግና እንዳታይኝ፤ጋረደሽ ኩነኔ
ፍቅርዬ ውድዬ፤ምናምን ምናምን
ከእቅፌ አንዳትወጪ፤ስማጸን ስለምን
ኣንቺን ማባበያ፤እንቡጥ ጽገሬዳ
መኖሪያ እንኳን የለኝ፤የማድረው ከሜዳ
የምሰጠው ባይኖር፤ሀብት እንኳ ቢጎለኝ
ከኔ ጋራ ሁኚ፤ለ ነገ አምላክ ኣለኝ
ብዬ ተማልጄ፤ችዬ እንዳላስቀራት
የማታውቀው ነገ፤ዛሬዋን ደለላት
.
..
...
ኣላወቅሽም እንጂ
አንቺን ኣጣው ብዬ፤ሳለቅስ ሳላዝን
ምን ጎሎኝ ነው ብዬ፤እራሴን ስመዝን
ከትቦ ስር ሀኜ፤የማየው ኣዲስ ጀንበር
ላንቺ የሚታይሽ፤ለካስ እሱ ነበር
ከትቦ ስር ሆኖ፤ማን ውበት ያደንቃል
ለተራበ ኣንጀት፤ጀንበር ሸከሰም እንጂ
መች ጌጥ ሆኖ ያቃል
ፍቅራችን ቢማርክ፤እንደ እንቡጥ ኣበባ
ቋንቋችን ኣይገጥም፤በምን እንግባባ
ከጎዳና ወድቃ፤ለምትማቅቅ ነፍሴ
ምን ያለ ምስጋና፤የፍቅር ውዳሴ
ቁስሌን ላያድነው፤ጠባሳዬን ላይሽር
ኣንቺን ኣጣሁ ብዬ፤እድሌን ሳማርር
ደርሶ ላያድነኝ፤ቁስሌን ላይፈውሰው
ከንፈር መጠጠልኝ፤ሳለቅስ የሚያየኝ ሰው
.
..
...
ኣላወቅሽም እንጂ፤ብታቂም ባታቂም
መኖሬ ኣስጨንቆሽ፤ስለኔ ኣጠይቂም
መውደቅ የለመደ፤መነሳት ይፈራል
ተጎዝ ያፈቀረ፤ሲከተል ይኖራል
ከመኖር ላይ ጎሎ፤የድራሻውን ያጣ
በውሲኪ በታጠብ፤ኣሬቄ ቢጠጣ
መውደዴን ታይ ብሎ፤ከደጇ ቢወድቅም
የሰካራም ፍቅር፤በመጠጥ ኣይለቅም
@Mad12titan
@getem
@getem
@getem
ኣላወቅሽም እንጂ፤ኣስቤሽ ነበረ
ሚስክን ልቤ የፍጥኝ፤ባንቺ እንደታሰረ
ላዘን ለእንጉርጉሮ፤ካረቄ ቤት ገብቶ
ንዴቱን ማብረጃ፤ትንሽ ተጎንጭቶ
ገና እንደሰከረ፤ስምሽን እንደጠራ
ኣይኔን ህመም ሞልቶት፤በእንባ ላያባራ
እቅፍሽን ለምዶ፤ከትቦ ስር ሲያድር
ኣላወቅሽም እንጂ፤ብታውቂማ ፍቅር
እቅፍ ድግፍ ኣርገሽ፤ኣዝነሽ በመውደቄ
ትንባሆ ሲጃራ፤መጠጥ አና ኣረቄ
በህጻን ልጅ ኩርፊያ፤ንዴትና ቁጣ
እንደምትገዝቺኝ፤ዳግም እንዳልጠጣ
ኣቅ ነበር ብትወጂኝ፤ኣጨክኝም በኔ
ግና እንዳታይኝ፤ጋረደሽ ኩነኔ
ፍቅርዬ ውድዬ፤ምናምን ምናምን
ከእቅፌ አንዳትወጪ፤ስማጸን ስለምን
ኣንቺን ማባበያ፤እንቡጥ ጽገሬዳ
መኖሪያ እንኳን የለኝ፤የማድረው ከሜዳ
የምሰጠው ባይኖር፤ሀብት እንኳ ቢጎለኝ
ከኔ ጋራ ሁኚ፤ለ ነገ አምላክ ኣለኝ
ብዬ ተማልጄ፤ችዬ እንዳላስቀራት
የማታውቀው ነገ፤ዛሬዋን ደለላት
.
..
...
ኣላወቅሽም እንጂ
አንቺን ኣጣው ብዬ፤ሳለቅስ ሳላዝን
ምን ጎሎኝ ነው ብዬ፤እራሴን ስመዝን
ከትቦ ስር ሀኜ፤የማየው ኣዲስ ጀንበር
ላንቺ የሚታይሽ፤ለካስ እሱ ነበር
ከትቦ ስር ሆኖ፤ማን ውበት ያደንቃል
ለተራበ ኣንጀት፤ጀንበር ሸከሰም እንጂ
መች ጌጥ ሆኖ ያቃል
ፍቅራችን ቢማርክ፤እንደ እንቡጥ ኣበባ
ቋንቋችን ኣይገጥም፤በምን እንግባባ
ከጎዳና ወድቃ፤ለምትማቅቅ ነፍሴ
ምን ያለ ምስጋና፤የፍቅር ውዳሴ
ቁስሌን ላያድነው፤ጠባሳዬን ላይሽር
ኣንቺን ኣጣሁ ብዬ፤እድሌን ሳማርር
ደርሶ ላያድነኝ፤ቁስሌን ላይፈውሰው
ከንፈር መጠጠልኝ፤ሳለቅስ የሚያየኝ ሰው
.
..
...
ኣላወቅሽም እንጂ፤ብታቂም ባታቂም
መኖሬ ኣስጨንቆሽ፤ስለኔ ኣጠይቂም
መውደቅ የለመደ፤መነሳት ይፈራል
ተጎዝ ያፈቀረ፤ሲከተል ይኖራል
ከመኖር ላይ ጎሎ፤የድራሻውን ያጣ
በውሲኪ በታጠብ፤ኣሬቄ ቢጠጣ
መውደዴን ታይ ብሎ፤ከደጇ ቢወድቅም
የሰካራም ፍቅር፤በመጠጥ ኣይለቅም
@Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍41❤11🔥11😢1
..............
የጸነሽው ባይወለድ
ያዳፈንሽው ጭሶ ባይነድ
ውጥናችን ባይሳካ
ሞት ደጃችን ሲያመሰኳ
ህይወት ሸክሞ ሲቀልልን
የዘራነው ሳይበቅልልን
ሲራገፍ ስጋ ከገላሽ
በስብሰሽ ምስጥ ሲበላሸ
የት እንደምቴጅ ባላቅም
ወደድኩሽ በሙታን ኣቅም
የሚኖር ማፍቀር ኣልሻም፤የማይቀልጥ የምድር ሻማ
ቢኩላት ኣያምርባትም፤ብጥስጣሽ ጨርቅና ሸማ
ኣፈር ነው የሷ ገላ ጌጥ፤ኣታቅም ተውባ በኩል
ኣትሻም ማድመቂያ ብረት፤ካንገቷ ከጆቿ በኩል
ጭንጋፍ ነው ቢሉም፤ተያቸው ለሷ ሞትን ተመኘ
ስታለቅስ ሳያስታምማት፤ስተለይ ጎኗ ተገኘ
ባቀው ነው የሀዘንሽን ጥግ፤በቃላት ኣይታበስም
ምን ያህል እንባ ቢፈስስ፤በጊዜ ኣይታፈስም
ቢገባኝ ነው መጠኑ፤ማቅሽን ብመቀምቀው
ልትሞት ነው ሲሉ የምስቀው
ውጥናችን ባይሳካ፤የጸነሽው ጭነጋፍ ሲቀር
ነገ ከሞትሽ እንዳራ፤ነገ ከሞትሽ እንፋቀር
@Mad12titan
@getem
@getem
@getem
የጸነሽው ባይወለድ
ያዳፈንሽው ጭሶ ባይነድ
ውጥናችን ባይሳካ
ሞት ደጃችን ሲያመሰኳ
ህይወት ሸክሞ ሲቀልልን
የዘራነው ሳይበቅልልን
ሲራገፍ ስጋ ከገላሽ
በስብሰሽ ምስጥ ሲበላሸ
የት እንደምቴጅ ባላቅም
ወደድኩሽ በሙታን ኣቅም
የሚኖር ማፍቀር ኣልሻም፤የማይቀልጥ የምድር ሻማ
ቢኩላት ኣያምርባትም፤ብጥስጣሽ ጨርቅና ሸማ
ኣፈር ነው የሷ ገላ ጌጥ፤ኣታቅም ተውባ በኩል
ኣትሻም ማድመቂያ ብረት፤ካንገቷ ከጆቿ በኩል
ጭንጋፍ ነው ቢሉም፤ተያቸው ለሷ ሞትን ተመኘ
ስታለቅስ ሳያስታምማት፤ስተለይ ጎኗ ተገኘ
ባቀው ነው የሀዘንሽን ጥግ፤በቃላት ኣይታበስም
ምን ያህል እንባ ቢፈስስ፤በጊዜ ኣይታፈስም
ቢገባኝ ነው መጠኑ፤ማቅሽን ብመቀምቀው
ልትሞት ነው ሲሉ የምስቀው
ውጥናችን ባይሳካ፤የጸነሽው ጭነጋፍ ሲቀር
ነገ ከሞትሽ እንዳራ፤ነገ ከሞትሽ እንፋቀር
@Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍18❤11🔥1
¹
ገና ወጣት ንፁህ ነበር .....
ያለ ግብሩ ወነጀሉት ፤
ይግባኝ ቢልም አልገባቸው
ግራ ቀኝ ሳይሉ ገ ደ ሉት ።
ከመሬት አጋድመው
አፈ ሙዝ ደግነው እየፎከሩበት
እሳት ያዘለ እርሳስ አርከፈከፉበት ።
²
የእሱስ ይሁን አንዴ ሄደ
እንደ ንፋስ ....ነፍሶ (ደርሶ)
አተረፈው ከሕይወቱ
(ከስቃይ አዳነው ሞቱ !)
ይብላኝ ለኗሪ እናቱ ።
³
ያኔ ፊትለፊቷ....
ልጇን በመስቀል ላይ የቸነከሩት ለት
ያሰረችበትን የወላድ አንጀቷን
አላቀበለቻት ማርያም መቀነቷን ።
ውስጥ ውስጡን ተከፍታ በሀዘን ዝላለች
ስዕሏ ፊት ቆማ እንዲህ ትላታለች
“ለደረሰበት ምኑ ሊነገር ?
ታውቂው የለም ወይ የልጅን ነገር !?
የልጅን ነገር ታውቂው የለም ወይ ?
አይተሽ የለም ወይ?
ወስደው ሲያዳፉት
አስረው ሲገርፉት
በምስማር ፊትሽ ሲቸነክሩት
አካል ገላውን በደም ሲነክሩት
አይተሽ የለም ወይ?
ታመሽ የለም ወይ?
.
.
.
«ያንቺስ ተነስቷል በሦስት ቀኑ
የኔ ግን ይሄው ስንት ዘመኑ
በአካል በስጋ መች ይገለጣል
ትዝታው ብቻ በሌት ይመጣል ።
እስኪ ንገሪኝ ?
እነዛ አይሁዶች አንቺን
እንደ
ድግስ ሲጠሩ
ትታደማለች ፤
እንደ ተፅናና ፈገግ ትላለች ።
ሀዘኗ ሳይሽር አውልቃው ማቋን ፤
ዕምባ ዕምባ ይላል ቢቀምሱት ሳቋን ።
እየዋሸች ነው እያስመሰለች
"እንደ ሚኖሩት ልኑር" እያለች ።
(አልተፅናናችም )
⁶
ተፅናናች እንዴ?
ፀኣዳ ቢሆን ከላይ ቀሚሷ
የሀዘን ማቋን ካልጣለች ነፍሷ
ውስጧ እንዳዘነ....
ልቧ ተከፍቶ ዘቅዝቆ ጥለት
‘ሞቶ መኖር’ ነው ....
“መፅናናት” ማለት ?
------
@Bekalushumye
ነሃሴ 23 — 2016 ዓም
@getem
@getem
@getem
ገና ወጣት ንፁህ ነበር .....
ያለ ግብሩ ወነጀሉት ፤
ይግባኝ ቢልም አልገባቸው
ግራ ቀኝ ሳይሉ ገ ደ ሉት ።
ከመሬት አጋድመው
አፈ ሙዝ ደግነው እየፎከሩበት
እሳት ያዘለ እርሳስ አርከፈከፉበት ።
²
የእሱስ ይሁን አንዴ ሄደ
እንደ ንፋስ ....ነፍሶ (ደርሶ)
አተረፈው ከሕይወቱ
(ከስቃይ አዳነው ሞቱ !)
ይብላኝ ለኗሪ እናቱ ።
³
ያኔ ፊትለፊቷ....
ልጇን በመስቀል ላይ የቸነከሩት ለት
ያሰረችበትን የወላድ አንጀቷን
አላቀበለቻት ማርያም መቀነቷን ።
ውስጥ ውስጡን ተከፍታ በሀዘን ዝላለች
ስዕሏ ፊት ቆማ እንዲህ ትላታለች
“ለደረሰበት ምኑ ሊነገር ?
ታውቂው የለም ወይ የልጅን ነገር !?
የልጅን ነገር ታውቂው የለም ወይ ?
አይተሽ የለም ወይ?
ወስደው ሲያዳፉት
አስረው ሲገርፉት
በምስማር ፊትሽ ሲቸነክሩት
አካል ገላውን በደም ሲነክሩት
አይተሽ የለም ወይ?
ታመሽ የለም ወይ?
.
.
.
«ያንቺስ ተነስቷል በሦስት ቀኑ
የኔ ግን ይሄው ስንት ዘመኑ
በአካል በስጋ መች ይገለጣል
ትዝታው ብቻ በሌት ይመጣል ።
እስኪ ንገሪኝ ?
እነዛ አይሁዶች አንቺን
እንደ
ኔ በድለውሻል?
ልጅሽን ገድለው
አታልቅሽ ብለው
ከልክለውሻል?»
⁴
የታወቀ ነው.....
ደስታ ቢታሰር በሳቅ ያመልጣል
ሀዘን ፈንቅሎ በእንባ ይወጣል
(እሷ ትላለች ....)
«አልበቃ ብሎ ልጄን የነሱኝ
ባዋጅ በሕጉ እየመለሱኝ
እንደው በወጉ አላስለቀሱኝ »
⁵
ብዙ ቀን ሄዶ....ብዙ ቀን አልፎ
ከሕይወት ዛፍ ላይ ዘመን ረግፎ
ጎረቤቶቿ አብረው ሚኖሩ
በየሰርጉ ዳስ በየማ
በሩ ድግስ ሲጠሩ
ትታደማለች ፤
እንደ ተፅናና ፈገግ ትላለች ።
ሀዘኗ ሳይሽር አውልቃው ማቋን ፤
ዕምባ ዕምባ ይላል ቢቀምሱት ሳቋን ።
እየዋሸች ነው እያስመሰለች
"እንደ ሚኖሩት ልኑር" እያለች ።
(አልተፅናናችም )
⁶
ተፅናናች እንዴ?
ፀኣዳ ቢሆን ከላይ ቀሚሷ
የሀዘን ማቋን ካልጣለች ነፍሷ
ውስጧ እንዳዘነ....
ልቧ ተከፍቶ ዘቅዝቆ ጥለት
‘ሞቶ መኖር’ ነው ....
“መፅናናት” ማለት ?
------
@Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
👍35❤22😢15🔥3🎉1
ተቁነጥንጣ ቀረበችኝ
ተቻኮለች እንዳፈቅራት ፣
ተጨነቀች ወዲያው ደሞ
ተቻኩየ ስላቀፍኳት ፣
ትፈጥናለች ለማግኜት
ልቤን አርጋው የቀበሌ ፣
ታምር አርጋ ቆጠረችው
በእሷ ፍቅር መቸኮሌ ፣
መቸኮልን አስለምዳኝ
ተጣድፎ ዝግታየን
አቻኩላ አገባችኝ
እይ ስትል እድሜየን ፣
ተቻኩላ አስለምዳኝ
ረጋ ያለ አረማመድ ፣
ተቻኩየ ጥያት ሄድኩኝ
ቀድማ ከእኔ እንዳትራመድ ፣
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@getem
ተቻኮለች እንዳፈቅራት ፣
ተጨነቀች ወዲያው ደሞ
ተቻኩየ ስላቀፍኳት ፣
ትፈጥናለች ለማግኜት
ልቤን አርጋው የቀበሌ ፣
ታምር አርጋ ቆጠረችው
በእሷ ፍቅር መቸኮሌ ፣
መቸኮልን አስለምዳኝ
ተጣድፎ ዝግታየን
አቻኩላ አገባችኝ
እይ ስትል እድሜየን ፣
ተቻኩላ አስለምዳኝ
ረጋ ያለ አረማመድ ፣
ተቻኩየ ጥያት ሄድኩኝ
ቀድማ ከእኔ እንዳትራመድ ፣
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@getem
❤34👍18😱3👎2🎉1
ይመስለኝ ነበር
ፍቅር አዳልጦት ውድቀት ያነቀው
መቼም የማይስቅ ሞትም ቢንቀው
ይመስለኝ ነበር
ሚወደውን ያጣ ትንፋሹ የሚርቅ
እንባ ሲቀለብ ማግኘትን 'ሚንቅ
ይመስለኝ ነበር
ዳግም ማያብብ አንዴ የረገፈ
እምነት ተስፋውን ቆሞ ያሰየፈ
ተሳስቻለሁ
ተጸጽቻለሁ
መምሰል መሆን ላይሆን ባ'ጉል ስጋት ቀንበር
መክሰምን ፍራቻ ወድቄ ለካ ነበር
ይለይልኝ ዘንድ
ትተሽኝ ስትቀዝፊ
ጥለሽኝ ስትከንፊ
፧
ጽልመት ሳቅ አንጣፊ
ፍም እንባ አርጋፊ
እልህ ዘር አብቃይ
ሰው ሸሽቶ ጣይ
ልሆን ለዘላለም ራሴን ሳሰለጥን
አንሽዬ አንሺ ላከ ውድቀቴን የሚጥል
ተነሳሁ ተራግፌ
ተስፋን ታቅፌ
እንኳን ተውሽኝ እንኳን ጣልሽኝ
ጥሩ እጅ ላይ ገፍተሽ አኖርሽኝ
#ኤልዳን
tiktok ... ldan291
@getem
@getem
@getem
ፍቅር አዳልጦት ውድቀት ያነቀው
መቼም የማይስቅ ሞትም ቢንቀው
ይመስለኝ ነበር
ሚወደውን ያጣ ትንፋሹ የሚርቅ
እንባ ሲቀለብ ማግኘትን 'ሚንቅ
ይመስለኝ ነበር
ዳግም ማያብብ አንዴ የረገፈ
እምነት ተስፋውን ቆሞ ያሰየፈ
ተሳስቻለሁ
ተጸጽቻለሁ
መምሰል መሆን ላይሆን ባ'ጉል ስጋት ቀንበር
መክሰምን ፍራቻ ወድቄ ለካ ነበር
ይለይልኝ ዘንድ
ትተሽኝ ስትቀዝፊ
ጥለሽኝ ስትከንፊ
፧
ጽልመት ሳቅ አንጣፊ
ፍም እንባ አርጋፊ
እልህ ዘር አብቃይ
ሰው ሸሽቶ ጣይ
ልሆን ለዘላለም ራሴን ሳሰለጥን
አንሽዬ አንሺ ላከ ውድቀቴን የሚጥል
ተነሳሁ ተራግፌ
ተስፋን ታቅፌ
እንኳን ተውሽኝ እንኳን ጣልሽኝ
ጥሩ እጅ ላይ ገፍተሽ አኖርሽኝ
#ኤልዳን
tiktok ... ldan291
@getem
@getem
@getem
❤19👍8🔥1🤩1
እሺ ብያለሁኝ
ትዳር ለመመስረት አምኜህ አምነኸኝ
መርጠኸኝ ከሌላ እኔን ስትጠይቀኝ
የወግ ማዕረጉን የባህል ስርአቱን
ጠብቀህ ጠይቀህ ቤትህ ልታስገባኝ
ሚስትህ ልታደርገኝ አንተ ስጠይቀኝ
እኔም በተራዬ እሺ ብያለሁኝ
ተቀብያለሁኝ
@getem
@getem
@getem
@Eltene937
ትዳር ለመመስረት አምኜህ አምነኸኝ
መርጠኸኝ ከሌላ እኔን ስትጠይቀኝ
የወግ ማዕረጉን የባህል ስርአቱን
ጠብቀህ ጠይቀህ ቤትህ ልታስገባኝ
ሚስትህ ልታደርገኝ አንተ ስጠይቀኝ
እኔም በተራዬ እሺ ብያለሁኝ
ተቀብያለሁኝ
@getem
@getem
@getem
@Eltene937
👍27❤11🔥2🎉2
..............
ሠማዩም መዝገብ ነው፤ምድርም ብርሀና
ገልጦ ላነበበው፤በኣይነ ልቦና
መዝገብ ነው ሠማይ፤ያልተነበበ
በፈራጅ ሚዛን የተከተበ
ብርሀና ነው ምድር
ንፁህ የበግ ቆዳ፤የተፈጥሮ ጽፈት
ስርዝ ድልዝ ያለው
ፍጹም ልክ ያልሆነ፤ፍጹምም ስህተት
ንባብ ነው መብረቁ፤የእንስሳቱ ድምፀት
የባህር የሸለቆው፤የኣዋፋቱ ዜማ
ለምጽ የሚፈው
ልብ የሚሰረስር፤በነፍስ የሚሰማ
የሚፈካው ኣበባ፤ደርቆ የጠወለገው
ስንዴ እንክርዳዱ
እንደ ኣዲስ ሊወለድ፤ወድቆ የበሰበሰው
የሀይቁ ፀጥታ፤የማዕበል ጩኀት
ቅንጣት እምነትና
ተራራን ያሰረው፤የተፈጥሮ እውነት
የዛፍ የቅጠሉ
የእሳት ነበልባሉ
መዝገብ ነው ይሄ ሁሉ
ፅህፈት ነው ይሄ ሁሉ
ገልጦ ላለበበው፤በኣይነ ልቦና
ሠማይም መዝገብ ነው
ምድርም ብርሀና
.
....
መጸሀፍ ነው ኑሮ፤መጸሀፍ ነው ህይወት
ነዋሪዋች በደም፤ጽፈው የከተቡት
በመስፈሪያው መዝገብ፤በህቡ የተፃፈ
ከትእዛዝህ ኣልፎ፤ሚዛን ያተረፈ
መፀሀፍ ነው ህይወት፤መፀሀፍ ነው ኑሮ
ንባብ ነው ፈገግታው፤ንባብ ነው እሮሮ
የሚስቀው ጥርስ፤ደም ተጎንጭቶ
የሚነባው ኣይን፤በሀዘን ታክቶ
ይህ ሁሉ ንባብ፤ይሄም ጽህፈት ነው
ይህ ሁሉ ኑሮ፤ይሄም ህይወት ነው
ያልደረስንበት እረቂቅ ምስጢር
ስውር ጽህፈት
ኑሮ ነው መጸሀፍ፤ህይወት ነው ህርመት
.
....
ግና ግና ግና
ይሄን ሁሉ ጽህፈት፤ገብቶት ያነበበ
ኣንዳች ጠቢብ ቢኖር፤በእውቀት ያበበ
እንዲ ነበር ቃሉ፤የሚል የሚናገር
መስፈርያ ሆኛለው፤ከሰፋሪዋች ሀገር
የመለስከው ሰይፍ፤ከሰገባው ኣምልጦ
ዲዳ ህዝብ ኣፍርቷል፤መኣት ጆሮ ቆርጦ
ታፈልገናለህ ተወለድ ከንደገና
የእዳ ደብዳቤያችን፤እጅግ በዝቷልና
እግዚኦ እግዚኦ
አድን ህዝበከ
ወባርክ ርስተከ
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
ሠማዩም መዝገብ ነው፤ምድርም ብርሀና
ገልጦ ላነበበው፤በኣይነ ልቦና
መዝገብ ነው ሠማይ፤ያልተነበበ
በፈራጅ ሚዛን የተከተበ
ብርሀና ነው ምድር
ንፁህ የበግ ቆዳ፤የተፈጥሮ ጽፈት
ስርዝ ድልዝ ያለው
ፍጹም ልክ ያልሆነ፤ፍጹምም ስህተት
ንባብ ነው መብረቁ፤የእንስሳቱ ድምፀት
የባህር የሸለቆው፤የኣዋፋቱ ዜማ
ለምጽ የሚፈው
ልብ የሚሰረስር፤በነፍስ የሚሰማ
የሚፈካው ኣበባ፤ደርቆ የጠወለገው
ስንዴ እንክርዳዱ
እንደ ኣዲስ ሊወለድ፤ወድቆ የበሰበሰው
የሀይቁ ፀጥታ፤የማዕበል ጩኀት
ቅንጣት እምነትና
ተራራን ያሰረው፤የተፈጥሮ እውነት
የዛፍ የቅጠሉ
የእሳት ነበልባሉ
መዝገብ ነው ይሄ ሁሉ
ፅህፈት ነው ይሄ ሁሉ
ገልጦ ላለበበው፤በኣይነ ልቦና
ሠማይም መዝገብ ነው
ምድርም ብርሀና
.
....
መጸሀፍ ነው ኑሮ፤መጸሀፍ ነው ህይወት
ነዋሪዋች በደም፤ጽፈው የከተቡት
በመስፈሪያው መዝገብ፤በህቡ የተፃፈ
ከትእዛዝህ ኣልፎ፤ሚዛን ያተረፈ
መፀሀፍ ነው ህይወት፤መፀሀፍ ነው ኑሮ
ንባብ ነው ፈገግታው፤ንባብ ነው እሮሮ
የሚስቀው ጥርስ፤ደም ተጎንጭቶ
የሚነባው ኣይን፤በሀዘን ታክቶ
ይህ ሁሉ ንባብ፤ይሄም ጽህፈት ነው
ይህ ሁሉ ኑሮ፤ይሄም ህይወት ነው
ያልደረስንበት እረቂቅ ምስጢር
ስውር ጽህፈት
ኑሮ ነው መጸሀፍ፤ህይወት ነው ህርመት
.
....
ግና ግና ግና
ይሄን ሁሉ ጽህፈት፤ገብቶት ያነበበ
ኣንዳች ጠቢብ ቢኖር፤በእውቀት ያበበ
እንዲ ነበር ቃሉ፤የሚል የሚናገር
መስፈርያ ሆኛለው፤ከሰፋሪዋች ሀገር
የመለስከው ሰይፍ፤ከሰገባው ኣምልጦ
ዲዳ ህዝብ ኣፍርቷል፤መኣት ጆሮ ቆርጦ
ታፈልገናለህ ተወለድ ከንደገና
የእዳ ደብዳቤያችን፤እጅግ በዝቷልና
እግዚኦ እግዚኦ
አድን ህዝበከ
ወባርክ ርስተከ
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍12🔥11❤6
................
ኣኩኩሉ ሲባል
እንደበቅ ደሞ
ሰው ከማይደርስበት፤መርጠን ስውር ቦታ
ከኑሮ እንቆቅልሽ፤ከፊደል ገበታ
ገሽሽ ግሳንግሱን፤የህይወትን እድፍ
ቀን ኣልፎ ከገላሽ፤ጠባሳ ለሚጽፍ
ኣልነጋም እያልን፤ባይጠይቁን እንኳን
መደበቂያ እንፈልግ፤መሸሸጊያ ድንኳን
መፈለግ ሲረክስ፤ፈላጊ ሲረሳ
ከተሸሸገበት ወድቆ ባይነሳ
ኣልነጋም ይለዋል፤በምስጋና ቅኔ
ደጅህ ተደብቆ፤ከኣለም ምናኔ
ሌትን ተቆራምተን፤ንቀነው ንጋቱን
ማስታመሚያ ሆነሽ፤ያኩኩሉ ህይወቱን
ይዞሽ ለመደበቅ፤ጭዋታ መረጠ
ኣልነጋም እያለ፤ሊሸሸግ እሮጠ
በቀንሽ ተዳራ፤ለሊትሽ ቢመስል
ቀለም ኣልባ ብእር፤ሌጣ እንደሚስል
ጨለማን ያማጠ፤ብርሀን አይወልድም
ንጋቷን የጠላ፤ተስፋዋን ኣይወድም
የኣኩኩሉ ትውልድ፤ያልነጋም ኣፍቃሪ
ነግቶ ላትፈልገው፤ከደጅህ ኣዳሪ
ጭዋታ ነው ብሎ፤በእንባው እየሳቀ
ኣልነጋም እያለ፤ደጅህ ተደበቀ
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
ኣኩኩሉ ሲባል
እንደበቅ ደሞ
ሰው ከማይደርስበት፤መርጠን ስውር ቦታ
ከኑሮ እንቆቅልሽ፤ከፊደል ገበታ
ገሽሽ ግሳንግሱን፤የህይወትን እድፍ
ቀን ኣልፎ ከገላሽ፤ጠባሳ ለሚጽፍ
ኣልነጋም እያልን፤ባይጠይቁን እንኳን
መደበቂያ እንፈልግ፤መሸሸጊያ ድንኳን
መፈለግ ሲረክስ፤ፈላጊ ሲረሳ
ከተሸሸገበት ወድቆ ባይነሳ
ኣልነጋም ይለዋል፤በምስጋና ቅኔ
ደጅህ ተደብቆ፤ከኣለም ምናኔ
ሌትን ተቆራምተን፤ንቀነው ንጋቱን
ማስታመሚያ ሆነሽ፤ያኩኩሉ ህይወቱን
ይዞሽ ለመደበቅ፤ጭዋታ መረጠ
ኣልነጋም እያለ፤ሊሸሸግ እሮጠ
በቀንሽ ተዳራ፤ለሊትሽ ቢመስል
ቀለም ኣልባ ብእር፤ሌጣ እንደሚስል
ጨለማን ያማጠ፤ብርሀን አይወልድም
ንጋቷን የጠላ፤ተስፋዋን ኣይወድም
የኣኩኩሉ ትውልድ፤ያልነጋም ኣፍቃሪ
ነግቶ ላትፈልገው፤ከደጅህ ኣዳሪ
ጭዋታ ነው ብሎ፤በእንባው እየሳቀ
ኣልነጋም እያለ፤ደጅህ ተደበቀ
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍15❤13
ቋጠሮሽ
ዞሮ ዞሮ ከሀገር ዞሬ ዞሬ ካንቺ
ካንቺ ሚስበኝን ቋጠሮሽን ፍቺ
ከተሰደዱበት ሀገር ቢመለሱ
እንደው ተጓዙ እንጂ ድሮስ መች ደረሱ
እንደ አፈሯ ሽታ እትብቴ ከተቀበረባት እኩል
እረቄ ከሄድኩት ትጎትተኛለች በትዝታ በኩል
ሀገርስ እናት ነች ብወድቅ ባላገግም
አልጋ ባትሰጠኝ በረንዳን አትነፍግም
ያንቺ ግን ጥላ ነው ወደ ፀሀይ ስዞር
ከኋላ ይወድቃል
ተፈጥሮው ነውና ስርቀው ይቀርባል
ስቀርበው ይርቃል
የኔ ፍላጎቴ መራቅ ብቻ ካንቺ
በቃ ልሂድበት ቋጠሮሽን ፍቺ
የታመመን ትናንት ዛሬ ባማርርም
መድረስ ከሌለበት ነገን አልገብርም
by kerim
@poem2513
@getem
@getem
@getem
ዞሮ ዞሮ ከሀገር ዞሬ ዞሬ ካንቺ
ካንቺ ሚስበኝን ቋጠሮሽን ፍቺ
ከተሰደዱበት ሀገር ቢመለሱ
እንደው ተጓዙ እንጂ ድሮስ መች ደረሱ
እንደ አፈሯ ሽታ እትብቴ ከተቀበረባት እኩል
እረቄ ከሄድኩት ትጎትተኛለች በትዝታ በኩል
ሀገርስ እናት ነች ብወድቅ ባላገግም
አልጋ ባትሰጠኝ በረንዳን አትነፍግም
ያንቺ ግን ጥላ ነው ወደ ፀሀይ ስዞር
ከኋላ ይወድቃል
ተፈጥሮው ነውና ስርቀው ይቀርባል
ስቀርበው ይርቃል
የኔ ፍላጎቴ መራቅ ብቻ ካንቺ
በቃ ልሂድበት ቋጠሮሽን ፍቺ
የታመመን ትናንት ዛሬ ባማርርም
መድረስ ከሌለበት ነገን አልገብርም
by kerim
@poem2513
@getem
@getem
@getem
❤26👍26😱1🎉1
-----------ፍቅር------------
እንዲያውቀው
መውደዴ ጥግ የለው፣ ሁሌ ናፍቃለሁ
ቀን በሀሳቤ ፣ሌሊት ደሞ በህልሜ እሱን አስባለሁ
ሱስ ሆኖብኝ፣ መላ አጥቻለሁ
እያሉ መጃጃል፣ በቅርቡ ትቻለሁ
አለ አይደል...
ቢተውት የማይተው፣ ቢርቁት የማይርቅ
ፍቅር ሚባል ልክፍት፣ ከሰዎች እሚያርቅ
ትቼዋለሁ፣ ፍቅራችን አብቅቷል
እያልኩ ስወስን፣ ደሞ ሳብሰለስል
ይህ ጅሉ ልቤ ፣እንዲ ይሟገታል
ያፈቅርሻል ብሎ ፣ሊያሞኘኝ ይቃጣል።
ስማኝ ልቤ አፍቃሪማ..
ቢሸሹት የማይሸሽ ፣ቢተውት የማይተው፣
የፍቅር ዋጋ፣ በእርግጥም የገባው፣
ንጭንጭ ንትርክ ፣ክፋት እማይመስለው፣
ለደስታ ስኬትህ ፣እራሱን ለጋስ ነው።
ሳምሪ የዝኑ ልጅ
@getem
@getem
@getem
እንዲያውቀው
መውደዴ ጥግ የለው፣ ሁሌ ናፍቃለሁ
ቀን በሀሳቤ ፣ሌሊት ደሞ በህልሜ እሱን አስባለሁ
ሱስ ሆኖብኝ፣ መላ አጥቻለሁ
እያሉ መጃጃል፣ በቅርቡ ትቻለሁ
አለ አይደል...
ቢተውት የማይተው፣ ቢርቁት የማይርቅ
ፍቅር ሚባል ልክፍት፣ ከሰዎች እሚያርቅ
ትቼዋለሁ፣ ፍቅራችን አብቅቷል
እያልኩ ስወስን፣ ደሞ ሳብሰለስል
ይህ ጅሉ ልቤ ፣እንዲ ይሟገታል
ያፈቅርሻል ብሎ ፣ሊያሞኘኝ ይቃጣል።
ስማኝ ልቤ አፍቃሪማ..
ቢሸሹት የማይሸሽ ፣ቢተውት የማይተው፣
የፍቅር ዋጋ፣ በእርግጥም የገባው፣
ንጭንጭ ንትርክ ፣ክፋት እማይመስለው፣
ለደስታ ስኬትህ ፣እራሱን ለጋስ ነው።
ሳምሪ የዝኑ ልጅ
@getem
@getem
@getem
❤33👍15🔥3🤩2
..............
ከማበዴ በፊት፤ኣንድ ቃል ልንገርሽ
ላንቺ ብዬ ኣይደለም፤ጨርቅ የምቀድልሽ
ስለተውሺኝ ብዬ
መራቅ መገፋቴን፤መቻል ስላቃተኝ
ፍቅርሽ እንደ ቅዘት፤ስለሚያቃትተኝ
ከምቀደው ልብሴ፤ከገላዬ ካለው
ትዝታሽ ብቻ ነው፤በውብ የተሳለው
ጠረንሽ ነው ያለ፤ከገላ ከጨርቄ
የሄድሽ ቀን ጣልኩት፤ሀፍረቴን ኣውልቄ
ከማበዴ በፊት
ኣንድ ቃል ለናገር፤ፍቅርዬ ባንቺ ፊት
ኡ ኡ ብዬ ብጮህ
እንዳትጠብቂ ከጬኀቴ መሀል
ከቶም ስምሽ የለም
የኔ ውድ የኔ ኣለም
ለኔ ኣይነቱ ኣፍቃሪ
እብደት ጤንነት ነው ከእስሩ መፈቻ
ኣንቺን አንቺን ብቻ
ማለቱን እረስቶ
ፍቅርን እንደጨርቅ፤ከገላው ለይቶ
ከገረባው መሀል
ተግቶ ሊፈልጋት፤የጠፋችው ፍቅሩን
ቅጠሏ ኣመርቅኖ
ግንዷ የበከለ ሰማይና ምድሩን
ቅጠሏ ፍቅር ነው፤ሙትን የሚባብል
ግንዷ ደሞ ግፍሽ፤በቁም የሚገድል
ለዚህ ይሆን ? እብድ ሁሉ
ገረባ የሚያነሳ፤ገረባ የሚጥለው
የጠፋችው ፍቅሩን፤ስለምትመስለው
እናም ፍቅርዬ
ላብድ ስለሆነ እንዳትጸጸቺ
ኣንቺን ፍለጋ ነው፤የማበዴ ፍቺ
ከሰው መሀል ባጣሽ፤ካትሮንስ ባትገኚ
ኣብጄ ፈለኩሽ፤ገረባ ስትሆኚ
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
ከማበዴ በፊት፤ኣንድ ቃል ልንገርሽ
ላንቺ ብዬ ኣይደለም፤ጨርቅ የምቀድልሽ
ስለተውሺኝ ብዬ
መራቅ መገፋቴን፤መቻል ስላቃተኝ
ፍቅርሽ እንደ ቅዘት፤ስለሚያቃትተኝ
ከምቀደው ልብሴ፤ከገላዬ ካለው
ትዝታሽ ብቻ ነው፤በውብ የተሳለው
ጠረንሽ ነው ያለ፤ከገላ ከጨርቄ
የሄድሽ ቀን ጣልኩት፤ሀፍረቴን ኣውልቄ
ከማበዴ በፊት
ኣንድ ቃል ለናገር፤ፍቅርዬ ባንቺ ፊት
ኡ ኡ ብዬ ብጮህ
እንዳትጠብቂ ከጬኀቴ መሀል
ከቶም ስምሽ የለም
የኔ ውድ የኔ ኣለም
ለኔ ኣይነቱ ኣፍቃሪ
እብደት ጤንነት ነው ከእስሩ መፈቻ
ኣንቺን አንቺን ብቻ
ማለቱን እረስቶ
ፍቅርን እንደጨርቅ፤ከገላው ለይቶ
ከገረባው መሀል
ተግቶ ሊፈልጋት፤የጠፋችው ፍቅሩን
ቅጠሏ ኣመርቅኖ
ግንዷ የበከለ ሰማይና ምድሩን
ቅጠሏ ፍቅር ነው፤ሙትን የሚባብል
ግንዷ ደሞ ግፍሽ፤በቁም የሚገድል
ለዚህ ይሆን ? እብድ ሁሉ
ገረባ የሚያነሳ፤ገረባ የሚጥለው
የጠፋችው ፍቅሩን፤ስለምትመስለው
እናም ፍቅርዬ
ላብድ ስለሆነ እንዳትጸጸቺ
ኣንቺን ፍለጋ ነው፤የማበዴ ፍቺ
ከሰው መሀል ባጣሽ፤ካትሮንስ ባትገኚ
ኣብጄ ፈለኩሽ፤ገረባ ስትሆኚ
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
❤30👍24😢8👎6🤩3🔥2
የቱ ፍቅሬ ስቦህ እንደምንፈታኸኝ
እኔኮ ብኩንነኝ
አንተ ስትሰቀል ከዐይሁድ ጋር የምገኝ
እኔኮ ምንም ነኝ ተራ የህመም ሰው
ጌታዬ እንድትምረኝ ምክንያትህ ምንድነው ?
በከሀሊነትህ ብቆምም የኔ አሳር
ከደግነት ደጅህ የቆረጥኩኝ ምሳር
ብቶደኝ ብትምረኝ እኔ ምን ታድዬ
ከሰቀሉህ ጋር ልስቀልህ ጌታዬ
እንዲህ ነኝ መፃጉ ውለታ ምረሳ
ስወድህ እንድኖር ህመሜን አትፈውስ
ቀንበሬን አታንሳ ።
ስንኩር ነው የኔ እግር ለሀሰት ያጋደለ
ጠማማ ነው ልቤ ፍቅርህን የጣለ
ቀጤማ ነው እጄ ክፋት ያቃጠለው
ያዙት ያን ክርስቶስ ብሎ ሚጠቁመው
እውር ነው ብሌኔ እያየ ሚከዳ
ከደግነት ኩሬ መዐት የሚቀዳ
እዳ ነኝ ለራሴ እዳ ነኝ ለአለም
ሲጀመር ነው የካድኩህ ሲፈፀም አይደለም
አልጋን ተሸከሚ ስትለኝ የኔ አባት
ልቤን አናተበው የመራመድ ክፋት
አትማረኝ መዳኑ አትማረኝ ጌታዬ
አልጋን መሸከሜ ለኔ መጥፋት
እንጂ መፈወስ አይደለም
እጆቼ ላንቺ ነው ትለኝም አነበረም
እናማ
ይቅር በለኝ እና ከመቅደስህ ልፅና
እጆችህን ስጠኝ ብርታት ሁነኝና።
By bline asefa
@getem
@getem
@getem
እኔኮ ብኩንነኝ
አንተ ስትሰቀል ከዐይሁድ ጋር የምገኝ
እኔኮ ምንም ነኝ ተራ የህመም ሰው
ጌታዬ እንድትምረኝ ምክንያትህ ምንድነው ?
በከሀሊነትህ ብቆምም የኔ አሳር
ከደግነት ደጅህ የቆረጥኩኝ ምሳር
ብቶደኝ ብትምረኝ እኔ ምን ታድዬ
ከሰቀሉህ ጋር ልስቀልህ ጌታዬ
እንዲህ ነኝ መፃጉ ውለታ ምረሳ
ስወድህ እንድኖር ህመሜን አትፈውስ
ቀንበሬን አታንሳ ።
ስንኩር ነው የኔ እግር ለሀሰት ያጋደለ
ጠማማ ነው ልቤ ፍቅርህን የጣለ
ቀጤማ ነው እጄ ክፋት ያቃጠለው
ያዙት ያን ክርስቶስ ብሎ ሚጠቁመው
እውር ነው ብሌኔ እያየ ሚከዳ
ከደግነት ኩሬ መዐት የሚቀዳ
እዳ ነኝ ለራሴ እዳ ነኝ ለአለም
ሲጀመር ነው የካድኩህ ሲፈፀም አይደለም
አልጋን ተሸከሚ ስትለኝ የኔ አባት
ልቤን አናተበው የመራመድ ክፋት
አትማረኝ መዳኑ አትማረኝ ጌታዬ
አልጋን መሸከሜ ለኔ መጥፋት
እንጂ መፈወስ አይደለም
እጆቼ ላንቺ ነው ትለኝም አነበረም
እናማ
ይቅር በለኝ እና ከመቅደስህ ልፅና
እጆችህን ስጠኝ ብርታት ሁነኝና።
By bline asefa
@getem
@getem
@getem
❤45👍26🔥3🎉2👎1🤩1
............
መለያየት ሞት ነው፤ብላኝ እንዳልነበር
ይኀው ተለያየን፤ሞታ ስትቀበር
አፈር ስትለብስ፤መሬት ሲደብቃት
የኣዳም ዘር እዳ፤ከቅፌ ሲነጥቃት
ጩኀት ለቅሶ ዋይታ፤ኣጅቧት ስጠፋ
ነፍስ ይማር የሚል ቃል፤ጆሮ ላይ ሲከፋ
ሞታ ስትቀበር
መለያየት ሞት ነው
ሞት መለያየት ነው
ብላኝ እንዳልነበር
ይኀው ተለየቺኝ፤ኣፈር ስትለብስ
እንባም ኣይበቃኝም፤ላንቺ በምን ላልቅስ
የቀብርሽ እለት
በልብሰተ ክህኖ፤ገጡን ያሳመረ
ጠይም ደርባባ ቄስ፤
ስለ ሞትሽ ትርጉም፤እንዲ ተናገረ
ተው ኣይለቀስም
ምን ሰራህ ተብሎ እግዜር ይወቀሳል
ኣፈር የተጫማ
ሊበሰብስ እንጂ፤ተጉዞ የት ይደርሳል
ህይው ልትሆን እንጂ
ከፈራሽ ገላዋ፤ነፍሷን የነጠቀ
ያልሞተ ኣያፈራም፤ዘር ሆኖ ያልወደቀ
ትድን እደሆነ
ተዝካሯን ኣውጡላት፤ነድያን መግቡ
እሱ እንደው ሩህሩህ፤ኣይጨክንም ልቡ
ብለው ቢናገሩ
ከበደኝ ቀብሩ
ኣንቺስ ፍቅርዬ
መለያየት ሞት ነው፤ብለሺኝ ኣልነበር
በመሞት ከሆነ፤ህይወት የሚጀመር
ውልደትሽ ምን ነበር?
ከኔ ተለይተሽ
ገነት ብትገቢ፤ብትቆሚ በቀኙ
ያንቺን እጣ ማግኘት፤ሙታን እዲመኙ
ውይ ሲኦል ተጥለሽ፤እልፍ ብትቀጪ
ለየለት ሀጥያትሽ፤ፀፀት ብታምጪ
ከልብሽ ላይ ችለው፤እኔን ላያወጡ
ስፍር ኣልባ ጋኔል፤ባንቺ ላይ ቢቆጡ
ብታማትቢ እንኳ
የማይጠፋ ሴጣን፤ከሲኦል ቢገጥምሽ
ኣውቃለሁ ፍቅርዬ
የሀጥያት ሰንሰለት፤እንደማይገድብሽ
ስለዚህ ለኣንቺ
ፍጹም እንቀይረው፤የመሞትን ፍቺ
ኣንቺ እንደነገርሺኝ፤እኔም እንደማቀው
ካሀዘናቸው ብዛት፤ባይቀብሩሽም ስቀው
ስለመለየትሽ እንባ አሰያፈሰሱ
መኣት ለቀስተኞች፤ከለቅሶሽ ደረሱ
እኔም ከንቱ ኣፍቃሪሽ
ሞት ህያውነት ነው፤ብዬ እያመንኩኝ
ህያው ሆኜ እንኳ፤ካንቺ የተነጠልኩኝ
ሳስስ ስፈልገው፤የሞትሽን ትርጉም
ከእንባ ላይ ኣየሁት፤የሚተን እንደ ጉም
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
መለያየት ሞት ነው፤ብላኝ እንዳልነበር
ይኀው ተለያየን፤ሞታ ስትቀበር
አፈር ስትለብስ፤መሬት ሲደብቃት
የኣዳም ዘር እዳ፤ከቅፌ ሲነጥቃት
ጩኀት ለቅሶ ዋይታ፤ኣጅቧት ስጠፋ
ነፍስ ይማር የሚል ቃል፤ጆሮ ላይ ሲከፋ
ሞታ ስትቀበር
መለያየት ሞት ነው
ሞት መለያየት ነው
ብላኝ እንዳልነበር
ይኀው ተለየቺኝ፤ኣፈር ስትለብስ
እንባም ኣይበቃኝም፤ላንቺ በምን ላልቅስ
የቀብርሽ እለት
በልብሰተ ክህኖ፤ገጡን ያሳመረ
ጠይም ደርባባ ቄስ፤
ስለ ሞትሽ ትርጉም፤እንዲ ተናገረ
ተው ኣይለቀስም
ምን ሰራህ ተብሎ እግዜር ይወቀሳል
ኣፈር የተጫማ
ሊበሰብስ እንጂ፤ተጉዞ የት ይደርሳል
ህይው ልትሆን እንጂ
ከፈራሽ ገላዋ፤ነፍሷን የነጠቀ
ያልሞተ ኣያፈራም፤ዘር ሆኖ ያልወደቀ
ትድን እደሆነ
ተዝካሯን ኣውጡላት፤ነድያን መግቡ
እሱ እንደው ሩህሩህ፤ኣይጨክንም ልቡ
ብለው ቢናገሩ
ከበደኝ ቀብሩ
ኣንቺስ ፍቅርዬ
መለያየት ሞት ነው፤ብለሺኝ ኣልነበር
በመሞት ከሆነ፤ህይወት የሚጀመር
ውልደትሽ ምን ነበር?
ከኔ ተለይተሽ
ገነት ብትገቢ፤ብትቆሚ በቀኙ
ያንቺን እጣ ማግኘት፤ሙታን እዲመኙ
ውይ ሲኦል ተጥለሽ፤እልፍ ብትቀጪ
ለየለት ሀጥያትሽ፤ፀፀት ብታምጪ
ከልብሽ ላይ ችለው፤እኔን ላያወጡ
ስፍር ኣልባ ጋኔል፤ባንቺ ላይ ቢቆጡ
ብታማትቢ እንኳ
የማይጠፋ ሴጣን፤ከሲኦል ቢገጥምሽ
ኣውቃለሁ ፍቅርዬ
የሀጥያት ሰንሰለት፤እንደማይገድብሽ
ስለዚህ ለኣንቺ
ፍጹም እንቀይረው፤የመሞትን ፍቺ
ኣንቺ እንደነገርሺኝ፤እኔም እንደማቀው
ካሀዘናቸው ብዛት፤ባይቀብሩሽም ስቀው
ስለመለየትሽ እንባ አሰያፈሰሱ
መኣት ለቀስተኞች፤ከለቅሶሽ ደረሱ
እኔም ከንቱ ኣፍቃሪሽ
ሞት ህያውነት ነው፤ብዬ እያመንኩኝ
ህያው ሆኜ እንኳ፤ካንቺ የተነጠልኩኝ
ሳስስ ስፈልገው፤የሞትሽን ትርጉም
ከእንባ ላይ ኣየሁት፤የሚተን እንደ ጉም
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍38❤23😢7🔥3🎉2
እልልታ
ጭብጨባ
ከአውደ ምህረቱ ተነስቶ ይነፍሳል፤
የሰማእቷ ታ'ምር እንደ ጉድ ይወሳል።
"ሰምታኛለች እናቴ..."
"ታውቃለች አርሴማ..."
ክብሯን የሚመጥን
ይገባል ስለት - ጧፍ፣ ጥላ፣ ብር፣ ሻማ።
ሰው ይጸልያል
ሰው ይለምናል ክፍተቱን አይቶ፣
እኔ ከንቱ ግን
የጎደለኝን አላውቅም ከቶ፤
ብቻ እመጣለሁ
ብቻ አይሻለሁ፣
ደጅሽን ስረግጥ እታደሳለሁ።
እዪኣት ያቺን ሴት
ከአትሮንሱ ጀርባ የምትዘምረው
ስምሽን ደጋግማ የምታነሳው፤
እኔ እስከማውቃት
ፊደል የሚያንቃት
ኩልትፍ አንደበት - ነው የነበራት።
ምን ጸልያ ነው አፏ የተፈታ?
ምን ብላሽ ይሆን
ቃል አቅሙን አጥቶ ለእሷ የተረታ?
የእኔማ ምላስ አግድም ለፋፊ
ለ'ንቶ ፈንቶ እንጂ ለጸሎት ታጣፊ።
እይው ያንን ሰው
ኑሮ የደቆሰው
የደስታን እንባ ሞልቶ ሚያፈሰው፤
እኔ እስከማውቀው
ሞት 'ሚናፍቀው
ማጣት በዝቶበት ገዳይ ሚፈልግ
ተስፋን ተነጥቆ
አለመኖርን የሚያነበንብ።
ምን ሰጥተሽው ነው ፊቱ የፈካ?
ምን አግኝቶ ነው
የደስታው መጠን ጣሪያ የነካ?
እኔ ሳቅ አላውቅ እንባም አይገደኝ
መኖርም መሞት ትርጉም አይሰጠኝ፤
ብቻ እመጣለሁ
ብቻ አይሻለሁ፤
ደጅሽን ስረግጥ ነፍስ እገዛለሁ።
#ኤልዳን
tiktok - ldan291
@getem
@getem
@getem
ጭብጨባ
ከአውደ ምህረቱ ተነስቶ ይነፍሳል፤
የሰማእቷ ታ'ምር እንደ ጉድ ይወሳል።
"ሰምታኛለች እናቴ..."
"ታውቃለች አርሴማ..."
ክብሯን የሚመጥን
ይገባል ስለት - ጧፍ፣ ጥላ፣ ብር፣ ሻማ።
ሰው ይጸልያል
ሰው ይለምናል ክፍተቱን አይቶ፣
እኔ ከንቱ ግን
የጎደለኝን አላውቅም ከቶ፤
ብቻ እመጣለሁ
ብቻ አይሻለሁ፣
ደጅሽን ስረግጥ እታደሳለሁ።
እዪኣት ያቺን ሴት
ከአትሮንሱ ጀርባ የምትዘምረው
ስምሽን ደጋግማ የምታነሳው፤
እኔ እስከማውቃት
ፊደል የሚያንቃት
ኩልትፍ አንደበት - ነው የነበራት።
ምን ጸልያ ነው አፏ የተፈታ?
ምን ብላሽ ይሆን
ቃል አቅሙን አጥቶ ለእሷ የተረታ?
የእኔማ ምላስ አግድም ለፋፊ
ለ'ንቶ ፈንቶ እንጂ ለጸሎት ታጣፊ።
እይው ያንን ሰው
ኑሮ የደቆሰው
የደስታን እንባ ሞልቶ ሚያፈሰው፤
እኔ እስከማውቀው
ሞት 'ሚናፍቀው
ማጣት በዝቶበት ገዳይ ሚፈልግ
ተስፋን ተነጥቆ
አለመኖርን የሚያነበንብ።
ምን ሰጥተሽው ነው ፊቱ የፈካ?
ምን አግኝቶ ነው
የደስታው መጠን ጣሪያ የነካ?
እኔ ሳቅ አላውቅ እንባም አይገደኝ
መኖርም መሞት ትርጉም አይሰጠኝ፤
ብቻ እመጣለሁ
ብቻ አይሻለሁ፤
ደጅሽን ስረግጥ ነፍስ እገዛለሁ።
#ኤልዳን
tiktok - ldan291
@getem
@getem
@getem
❤54👍34🔥3
መቼስ ልብ የለኝም
ልብ እንዳለው ስሆን
መቼስ ነፍስ የለኝም
ነፍስ እንዳለው ስሆን
መቼስ ህዝብ የለኝም
የጥንድ አልቃሽ ምሆን
እና ምኑ ይገርማል
እየኖርኩኝ እንኳ
እንዳልኖርኩኝ ስሆን
በትንንሽ ድምፆች አምላኬ በሚሉት
ሶቆቃ ብቻ ነው ምእመን ሚያሰሙት
በጨቅላ ህፃናት ቆመው በሚሰግዱት
ጫንቃቸው ሞትን ነው ነጠላ ያረጉት
ይሄ ሁሉ ምእመን
ለአምላክ የሚነግረው
ኑሮን አቅል ነው
ወይ መሪን ቀንሰው
እኔ ግን ደስታ ነው
ላንተ የማቀርበው
እኔ ስለት አለኝ
ልሞት ስለሆነ
ጥላ አለኝ ማስገባው
ኑሮ በሚያስፈራው
ዋይታ በደፈረው
በጭንቅ ለቅሶ ድምፅ
ዝምታ ይበላል
ያለምንም ፍትህ
ከኖረ እንደምስፅ
አለም ትንሽ ገብታኝ
ሀገር በደንብ ገብታኝ
እኛሳ ስላልናት
ስትጋረፍ አየሁ
በምእመን ልጇ
ጨካኝ ሁና እናት
እናት በጨከነች አባት በደበቃት
በግራ እግር ሀገር
ሞት ቀጠሮ ማወቅ
ደስታ ሆኖ ቀረ ተሳቆ ከማደር
እናማ ጌታዬ በዚህ ሺህ ምእመን
የጭንቅ መሃል ለቅሶ
አንዲት ነፍስ አለች
ደስታ ያፈነዳት የሞት ክሬም ልሶ
ኗሪው በሚፈራት
መሪው በሚንቃት
በግራ እግር ሀገር፣
ሞት ቀጠሮ ማወቅ
ደስታ ሆኖ ቀረ
ተሳቆ ከማደር ፣
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@paappii
ልብ እንዳለው ስሆን
መቼስ ነፍስ የለኝም
ነፍስ እንዳለው ስሆን
መቼስ ህዝብ የለኝም
የጥንድ አልቃሽ ምሆን
እና ምኑ ይገርማል
እየኖርኩኝ እንኳ
እንዳልኖርኩኝ ስሆን
በትንንሽ ድምፆች አምላኬ በሚሉት
ሶቆቃ ብቻ ነው ምእመን ሚያሰሙት
በጨቅላ ህፃናት ቆመው በሚሰግዱት
ጫንቃቸው ሞትን ነው ነጠላ ያረጉት
ይሄ ሁሉ ምእመን
ለአምላክ የሚነግረው
ኑሮን አቅል ነው
ወይ መሪን ቀንሰው
እኔ ግን ደስታ ነው
ላንተ የማቀርበው
እኔ ስለት አለኝ
ልሞት ስለሆነ
ጥላ አለኝ ማስገባው
ኑሮ በሚያስፈራው
ዋይታ በደፈረው
በጭንቅ ለቅሶ ድምፅ
ዝምታ ይበላል
ያለምንም ፍትህ
ከኖረ እንደምስፅ
አለም ትንሽ ገብታኝ
ሀገር በደንብ ገብታኝ
እኛሳ ስላልናት
ስትጋረፍ አየሁ
በምእመን ልጇ
ጨካኝ ሁና እናት
እናት በጨከነች አባት በደበቃት
በግራ እግር ሀገር
ሞት ቀጠሮ ማወቅ
ደስታ ሆኖ ቀረ ተሳቆ ከማደር
እናማ ጌታዬ በዚህ ሺህ ምእመን
የጭንቅ መሃል ለቅሶ
አንዲት ነፍስ አለች
ደስታ ያፈነዳት የሞት ክሬም ልሶ
ኗሪው በሚፈራት
መሪው በሚንቃት
በግራ እግር ሀገር፣
ሞት ቀጠሮ ማወቅ
ደስታ ሆኖ ቀረ
ተሳቆ ከማደር ፣
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@paappii
👍41❤14😢2🔥1
ማን ልበልህ አንተስ እሺ ዛሬ ኮስተር ነገ ፈገግ በቃ ይሄው ነው የኔ አቅም አንተስ እሺ እኔ ልበል ላንተ ፍግም ። ይሻልሀል እያወከው የኔን አቅም ወይስ ልራቅህ እንድረሳው የአንተን አቅም አላውቅም በምን ይሆን መፈወሻህ ገዳም ፀበል ይዤህ ልሂድ መጥፎው ነገር ጥሎህ እንዲሄድ ። ምን ላድርግልህ....... ለኔስ ይሁን ክርክርህ ሱስ ይዞኛል እንዳርቅህ ። በጨዋታ እያዋዛህ አደረከኝ እንድወድህ የኔ ፍቅር ....... ማን ልበልህ ቃላት ጠፋኝ በምን ልጥራህ ስሱን ጎኔን እየነካህ እያስለቀስክ እያዋዛህ ተራ ህመም አደረከው አስጠፋኸው የኔን ለዛ ።
By bline asefa
@getem
@getem
@getem
By bline asefa
@getem
@getem
@getem
❤23👍10🔥5