ግጥም ብቻ 📘
67.3K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ዛሬ
እየዳነ ኼደ
የመፅሃፍ ምርቃት በዋልያ መፀሃፍ

@getem
👍143
ምሽት በረንዳ ላይ
(በእውቀቱ ስዩም)

አገር ምድሩ መሽቶ
ሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ
የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን
ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን
ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ
አጥብቄ ስፈልግ ፥የእለት ያይኔን ሲሳይ
የሌት አይኔን ሲሳይ

በኩርማን ገላዋ፤ እራፊ ደርባ
የራሷ ሻጭ ሆና ፤ለሸመታ ቀርባ
በሌት ይፋ ሆና፥ በቀን ልትደበቅ
ያልቀጠረችውን ፥የምትጠባበቅ
አንዲት ሴት እያየሁ
አሰላስላለሁ ፤

“ አብረዋት ያደጉ፤ ብጤዎቿ ሁሉ
በድሜና በውበት እሷን የሚያክሉ
ተድረው እንደ ሴት፥ ተከብረው እንደ ሰው
የባሎቻቸውን ደረት ተንተርሰው
ፍቅር ሲያጣጥሙ
ወይ በንቅልፍ ሲሰጥሙ
ይች ወገን አልባ
የሌሊት አበባ
በቀትር ተኝታ ለውድቅት የነቃች
የቱን ፍሬ በልታ ለዚህ ፍዳ በቃች ?”

እያልሁ አስባለሁ፥



ደሞ ከደጃፌ ትንሽ ማዶ ርቆ
የመሸበት ለማኝ ፤ መንገዱ ዳር ወድቆ

በግልጥ ይታየኛል
“ ረፍትን ላክልኝ ፥ወይ እንጎቻህን ጣል
በራብ እና በንቅልፍ ሰው እንዴት ይቀጣል"
የሚል ይመስለኛል ፤

በረንዳ ላይ ቆሜ፥ በሌሊት ስምሪት
ከመስኮት በወጣ፥ የብርሀን ቅሪት
አይቼ ማልዘልቀው
ያገሬ ጎዳና የት ላይ ነው የሚያልቀው
መከራና ውበት የሚያፈራርቀው::

@getem
@getem
@getem
105👍46🔥6😢6👎1
በሁለት ዋልታ ተከብቤ
ምረጥ አሉኝ
ከአንዱ እንዲያርፍ ልቤ
በሰሜን ትላንት
በደቡብ ነገ
አንዱላይ እንድገኝ
ለምን ተፈለገ?
ትላንት ትላንቴ ነው
ነገ ደሞ ምኞት
እኔን የናፈቀኝ
የዛሬ ህይወት!

              

   
Follow my IG & Tiktok @be_Olyon

       ✍️ Olyon
                       
           
              አስተያየት (@be_Olyon)


     @getem
                   @getem
                                  @getem
👍5310🔥5😁2
( አያሌው ሞኙ )
=============

ተቆጥሮ የማያልቅ
ለፍቅር ገዳሟ
እልፍ ነው መናኙ
ምን አገኝ ብለህ ነው
ዛሬም ተኮራምተህ
የምትጠብቃት .... ወይ አያሌው ሞኙ

"አለሷ እረፍት ምኔ"
ብለህ የደከምክላት
"አለሷ ዓለም ምኔ"
ብለህ የመነንክላት
በል እርምህን አውጣ

ያላንተ ዓለም አላት !

(እውነት እየሸሹ
አይመጣማ ንጋት...)

@kiyorna

@getem
@getem
@paappii
👍2926😁6🔥2🎉1
[የጅራፍ ጠበቃ]
_
እነ ተረት አዋቂ  ...
(እነ ጸጉር ሰንጣቂ....)
«ጅራፍ እራሱ ገርፎ ፥ እራሱ ይጮኻል»
(ይሉሃል....፤)
እንዲህ ሲነግሩህ — ምን ይሰማኻል?

አይተህ አይደል ወይ....!?
(ምስኪኑን ጅራፍ....)
ቁልቁል ከመሬት  እያላተመው
— እረኛው ጠልፎ ፤
እንዴት ይባላል...!?
«እራሱ ጮኸ — እራሱ ገርፎ » ?
²
(ጅራፉ ጥፋት የለበት....)
ሀሰት ነው —·· ውንጀላ ክሱ  ፤
(ገራፊ ካልሰነዘረው....)
መች ያውቃል —·· ገርፎ በራሱ!?
³
ሳትፈቅድ ተገፈህ
(ሳትወድ ተጠልፈህ...)
"ጅራፍ ሁነኝ" መባል....
(ለዱላ መታጨት....፤)
መግረፍ ነው? – መጋጨት?

(ግርፊያ በሚል ሰበብ..)
ጎርባጣ ጀርባ ላይ— ሄዶ በማረፉ ፤
ከበሬው ገላ እኩል — ያመዋል ጅራፉ ።

(ቢጮኽ አልፈርድበት......)
___
By @Bekalushumye

@getem
@getem
@paappii
👍24🔥103
የእግዜር ፍርድ


አንድት ቆንጆ
በእግዜር እጆች የተሳለች   ድንቅ ስራ
ቆዝማለች
ተክዛለች  ለብቻዋ  ከሰው መሆን ብትፈራ

እኔን የገረመኝ
የእሷ አይደለም  ይልቅስ የግዜሩ
የነፍስ ምግብ
አርጎ ፈጥሯት  ለማስከፋት መሞከሩ

እግዜር ጨካኝ  ፍርድ አያውቅም
ውበት የሰጠ   ደስታ አይነጥቅም
ከሀዘን ቢሰውራት እንጂ   ቢከልላት
ዋስ ቢሆናት እንጂ    ቢሰያስጠልላት
ውበትን ጎድቶ  ከሰው አያርቅም
እግዜርስ አንዳንዴ  ፍርድ አያውቅም

By kerim

@getem
@getem
@paappii
👍46👎4310😱5😁4🔥2😢2
የአቀባይ ተቀባይ ...በዔደን_ታደሰ
<unknown>
#የአቀባይ_ተቀባይ
ገጣሚ እና አንባቢ ፦ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
11🤩2👍1🔥1
መገረም
"""""""""
እንገረም እንጂ
የመገረም ዘመን
ሁሌ እያስደነቀን፤

ጀንበር ለሊት ወጥታ
ስታደምቀን ብትውል
ጨረቃ እኩለ ቀን...

ፈገግታዬ ጠልቆ
እየኮረኮረ
ሀዘኔም ቢያስቀኝ፤

የተስፋን መሰንቆ
እየገዘገዝኩኝ
ትዝታዬን ብቀኝ...

የሾምኩት ሲገፋኝ
የሻርኩትን ብመኝ
እያነቀኝ ሲቃ፤

ምን እፈይዳለሁ
በእቴ እሜቴ ሀገር
መገረም ነው በቃ...!

By Abrham F. Yekedas

@getem
@getem
@getem
👍2926
Audio
መቼ ትመጫለሽ??
በዔደን ታደሰ እና ኤልሻዳይ(ኤል ቶ)
ተፅፎ እንደቀረበ
@topazionnn
@getem
@getem
👍138👎1🔥1
እስኪ ምን ላርግልሽ

ካንቺ የተፀናወተኝ ማፍቀሬ እንዲገባሽ
ከአይኖችሽ የያዘኝ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ የኔ ዓለም እስኪ ምን ላርግልሽ
ከምድር እስከ ሰማይ ወጥቼ ወርጄ ስልጣን ተበድሬ
በዓለም ሚኖሩትን ሕዝቡን ሚገዙትን ነገስታትን ሽሬ
ለዘውድሽ እንድትሆን ከሰማየ ሰማይ ፀሐይን አውርጄ
ግርማሽ እንዲያስፈራ መጎናፀፍያሽን በእሳት ጋርጄ
ከሰው ሁሉ እንድትልቂ ተከብረሽ ተነግሰሽ
ዉበትሽ እንዲታይ እንዲጎላ መልክሽ
ጨረቃን አውርጄ ልሰራት ካንገትሽ
ኮከብ አዋቅሬ ልብስሽን ልስራልሽ
ከእሳት እና ከዉሃ  ዙፋን ልገንባልሽ
ስምሽ እንዳይረሳ ዓለም እንዲያስታውስ ትውልድ ሁሉ እንዲያውቀው
ቃላት እየመረጥኩ ግጥም እየፃፍኩኝ መልክሽ ልሳለው
ማፍቀሬ እንዲገባሽ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ ፍቅሬ ሆይ እስኪ ምን ላርግልሽ ?


                    ዘረ-ሠናይ
         
@Prince_Zeresenay

@getem
@getem
@getem
24👍23🔥6👎1😱1🤩1
በደረቅ ሌሊቱ
ሰው በሌለበቱ
ሲጋራ ለኩሼ
ህመም ተንተርሼ
ፍቅርን ሳስተነትን
በጭሱ መካከል አገኝሽ ይመስል
ስባትል ስኳትን
ያለፉ ሌሊቶች ፍቅርሽ የገዛቸው
እግዜር ይቁጠራቸው።


by kerim

@getem
@getem
@getem
🔥23👍188
[ለሻማ ሕይወቶች....]

🕯️
፩.

ሻማዬ ...ሞቆሻል አይደል?!
ላብሽ — ይንጠፈጠፋል ፤
እንዳላበርድሽ (ጨነቀኝ)
የቤቴ ብርሃን — ይጠፋል ።

["ይነጋል" ግን — አልልሽም...
አጉል ተስፋን— አልሰጥሽም ።]

አውቃለሁ በደጄ በራፍ·· —
የጠዋት ጮራ ይሰለፋል ፤
ያኔ ግን ከጨለማው ጋር —
ሕይወትሽም አብሮ ያልፋል ።

🕯️
፪.
(አንተም አንተም የኔ ወዳጅ....)
የሠው ልጅም በጨለማ....
ቢለኮስ – ቢቀልጥ – ቢቃጠል ፤
(እንባ ላቡ ቢንጠለጠል...)
"ይነጋል " አትበለው — እረፍ !
(ጀንበር 'በራሁ' — እስክትል...)
ማለቁ አይቀርም ሲሸረፍ ።

[ሰም ለበስ ነውና — ሠውም እንደ ሻማ እስከ ንጋት ድረስ — ያልቃል በጨለማ ።]

ከቻልክ "እፍ" በለው....
`ሳቱን አብርድለት ፤
ላንተ ብርሃን ተብሎ...
— ማለቅ አይወድለት ።
🕯️|
___
By @Bekalushumye

@getem
@getem
@getem
👍4326🔥3
ጠብም


አምላክ ሊታረቀ
ባንቺ ሊባርከኝ

ሊያመጣሽ ነው መሰል


ሰማዩ ዳመነ
ጨለማው ገነነ
ልክ አንደረተቱ
አይቀርም መንጋቱ
ቀኑ ሲጨላለልም
ብርሀን ሲጠልም
ሰማይ ሲደማምን
አላህን ልለምን
በስግደት በዱዓ
በፆም በጁምዓ
መሬት ተንበረከኩ
እናም አንቺን ለመንኩ

ለመንኩት ለመንኩት
ባንቺ አከበርኩት
አንቺን እንድሰጠኝ
አንድ አንቺን እንዲመፀወተኝ


ተረቱስ ተለለ
ጠብም ያለ የለ

ደመናው ለዝናብ
ጨለማው ለብርሀን
ቦታውን ለቀቀ
ተረቱም አለቀ

መስገዴ በከንቱ
ጠብም ያለ የለ
ካላህ በማውራቱ

አላህም እንዳንቺ
አላህም አንደሰው
ጨካኝነት ባሰው

ጨለማን  ሲያነግስ ጭካኔ
በግርማሽ  ሲፈራረስ  ወኔ
እኔም ጠፋሁ ከኔ ።


by kerim

@getem
@getem
@getem
👍44👎81
እስኪ ምን ላርግልሽ

ካንቺ የተፀናወተኝ ማፍቀሬ እንዲገባሽ
ከአይኖችሽ የያዘኝ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ የኔ ዓለም እስኪ ምን ላርግልሽ
ከምድር እስከ ሰማይ ወጥቼ ወርጄ ስልጣን ተበድሬ
በዓለም ሚኖሩትን ሕዝቡን ሚገዙትን ነገስታትን ሽሬ
ለዘውድሽ እንድትሆን ከሰማየ ሰማይ ፀሐይን አውርጄ
ግርማሽ እንዲያስፈራ መጎናፀፍያሽን በእሳት ጋርጄ
ከሰው ሁሉ እንድትልቂ ተከብረሽ ተነግሰሽ
ዉበትሽ እንዲታይ እንዲጎላ መልክሽ
ጨረቃን አውርጄ ልሰራት ካንገትሽ
ኮከብ አዋቅሬ ልብስሽን ልስራልሽ
ከእሳት እና ከዉሃ  ዙፋን ልገንባልሽ
ስምሽ እንዳይረሳ ዓለም እንዲያስታውስ ትውልድ ሁሉ እንዲያውቀው
ቃላት እየመረጥኩ ግጥም እየፃፍኩኝ መልክሽ ልሳለው
ማፍቀሬ እንዲገባሽ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ ፍቅሬ ሆይ እስኪ ምን ላርግልሽ ?


                    ዘረ-ሠናይ
         
@Prince_Zeresenay

@getem
@getem
@getem
39👍32😱2
አህያ

ጀርባው ይዞ ትልቅ ጭነት

አንገት ደፍቶ ሁሉ ሰው ፊት

አገልግሎት እንዳልሰጠ

በውጭ ገንዘብ ተለወጠ።

አንገቱ ላይ አርፎ ቢላ

ለእርድ ቀርቧል ነው እንዲበላ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝

       ✍️ @BEGITIMENAWGA

@getem
@getem
@getem
👍41🤩10😁72🔥2
🤔
.
.
ግራ መጋባቴ እንደዉ ግራ ገብቶኝ፤
ስቋጥር ስፈታ እጅጉን አሳስቦኝ፤

ባስብ ባሰላስል ከልቤ አጣሀት፤
ግራ የገባኝን ግራ ገብቶኝ ተዉኩት።
..........................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
👍66😁2611🤩5🔥1
አንዳንዴ ይታክታል
እልክ አስጨርሶ
ያዝኩ ያልከው ይርቃል
ካጠገብህ ደርሶ፤
ነገን ያስጠላኻል
የፊትህን እዳትኖር
እንዳከፍት አድርጎ
የተዘጋብህን በር፤
በምናብህ ይጭራል
የጨለማን ፅልመት
ያደላች እስኪመስልህ
የተወችክ እይወት፤
ጭንቅህን ሲያበዛው
አሳብህ ተዛብቶ
ክርናፍ ክርናፍ ይልሀል
የገዛኸው ሽቶ፤
ታዲያ ጊዜ ሲጠምብህ
እድል ካንተህ ስትርቅ
ከማንም አይደለም
ከራስህ ተታረቅ፤
         ያልፋል!!!#M.G
@getem
@getem
👍7216
ለማታዉቀኝ 1 ✍️በዔደን
<unknown>
ለማታዉቀኝ...
ገጣሚ እና አንባቢ ዔደን ታደሰ
ክፍል 2 ይቀጥላል...........
@topazionnn
@getem
@getem
7👍6
/በኔ ብሶ/,,
የተንከራተትኩት ፍዳዬን የበላው
መስሎኝ እንጂ ፍቅርን ካንቺ የማገኘው፤
ላንቺም የኔ ልፋት ምንም ያልመሰለሽ
ላትረጂኝ ነገር ለምን ልለምንሽ፤
ጥሬ የቻልኩትን መልስ ካንቺ ባጣ
ተውኩት መከጀሉን ወዳንቺ ልመጣ፤
እርሺው የኔን ስቃይ ይሁን አትዘኚልኝ
ድካሜም አይሰማሽ ከቶ አታስቢልኝ፤
ምናልባት አንድ ቀን ያንቺ ተራ ደርሶ
እንዳልገኝ ፍሪ ኃላ በኔ ብሶ
◈መሳይ ግርማ
@getem
@getem
👍368
በዚህ ሙቅ ከተማ
በዚህ ደማቅ መንገድ
ሺ አምፖል በበራበት
ፀሐይ ቀንና ሌት ፥ በማትጠልቅበት
ለሰው የማይታይ
አለ ብቸኝነት ።

አለ ብቸኝነት
በስንት እግሮች መሐል
ያደፈ ኮት ለብሶ
አይኑ ማዶ ፈዞ
የታክሲ ጥሩንባ የሚያደነቁረው
ሰው ገፍትሮት እንኳን
"ይቅርታ" የማይለው
ስሙ ፥ ማይነሳ
መኖሩ ፥ የተረሳ
ቢሞት ፥ ልብ የማይባል
አለ ብቸኝነት
እዚሁ ፥ እኛው መሐል ።

አለ ብቸኝነት
አንድ ጊዜ ተራምዶ
ብዙ ጊዜ የሚቆም
በፋሲካ በአል ፥ ብቻውን የሚጾም ።

አለ ብቸኝነት
ቢያውቀው ወይ ባያውቀው
የሚገላምጠው
(ወይ በመተያየት)
ፈገግታ 'ሚሰጠው
አንድ አይን የናፈቀው ።

አለ ብቸኝነት
ዕንባውን የዋጠ
ሳቁን የመጠጠ
ስሜቱን ያፈናት ፥ ልውጣ ባለች ቁጥር
ልቡ እንደ ድመት ሆድ ፥ ትር ትር የምትል ።

አለ ብቸኝነት
ወዴትም የማይሄድ ፥ ዝም ብሎ የሚራመድ
እንኳንስ ሰውና ፥ ልቡ ያልሆነው ዘመድ
ጭር ያለ ባይተዋር
በሰው ጎርፍ መሐል
ትንፋሹ የሚታየው
እርምጃ የሚመትር
ጠብታ የሚቆጥር
ወዴትም ሳንርቅ ፥ እዚሁ አፍንጫችን
እዚሁ ልባችን ስር
አለ ብቸኝነት ።

By HAB HD

@getem
@getem
@paappii
36👍24😢9