#ቀሽም_ብይን
ምሩቅ ጥበብ ሰሪ
የሸራ ቀበኛ ፥ የቀለም ቀማሪ
ጠቢባን ጠበብቶች
የቀለም አባቶች
የብሩሽ አርበኛ ፥ የኪነት ገማቾች
በዘመን የቆሙት
ከትውልዱ ወጥተው ፥ የሚተዛዘቡት
አልያ ....ዘመን አልፈው
በነጠረ ስራ....
ከኛ ጀምበር ጥላ ፥ በሞገስ የቆሙት
መናኛም.....ሆኑ ...ዝነኛ
ትሁትም ....ሆኑ ....ጉረኛ
እርቃን አፍቃሪዎች!
ምስል ደጋሚዎች!
ምጡቅ አሳቢዎች!
ብቻ.....ሰአሊ የሆኑ
ሸራ የወጠሩ ፥ ብሩሽ የዘገኑ
ሁለት ግዜ ነው.... የሚስሉ
ሁለት ግዜ ነው ....የሚያጤኑ
#አንድ...
በረጅም ግዜ ተመስጦ ...በጥቂት ግዜ መቃኘት
የሚፈለገውን ውበት ፥ ተኩሮ በማየት
በህሊና ችንካር ሸራ
ያኔ ነው ፥ የጥበብ ሽል ፥ ፅንሱ የሚዘራ
#ሁለት...
እንግዲህ በሀሳብ ፥ ምስሉ እንደታያቸው
በውን አለም ሸራ ...ይጫራል ንድፋቸው
አይን እና እጆቻቸው ፥ እኩል እስከቻሉ
የግል አይናቸውን ፥ ለሰው ይቸራሉ
ያዩትን ...ለማውረድ
ፅንፉን ለማዋደደ
ጣጥረው..
ጫጭረው...
ሞንጭረው...
የለቀለቁትን.... አቅመ ጥበብ ቅይጥ
ጋለሪ እያገባ ...ወዳጅ እንዲያቋምጥ
ሁለቴ ተረግዞ...ሁለቴ ይማጣል
አፍቃሪው በርትቶ....
ወላድ ለመጠየቅ ...አውደርይ ይወጣል
በዚህ ኩናቴ ውስጥ...
አንዳቹም ሰአሊ
ልጁን የሰቀለ ፥ በቤት በጋለሪ
እስኪያረጅ ...እስኪሸጥ
ማንጠልጠል ይወዳል ፥ ጭንቁን እንደ ትሪ
የብሩሹ አጣጣል ፥ ቀለም ስብጥሩ
የመልእክቱ ምጥቀት ፥ ብራና ሚስጥሩ
ገለፃው......ውብቱ
ጨረሩ ....ሙቀቱ
ሺህ ግዜ ፥ እልፍ አመት
እኛን ቢገርመንም...
ቢያጅበንም ...ደርሶ
የሁለቴ ምጥ ነው
ዘመን የሚሻገር ፥ በቀለማት ርሶ
አየሽልኝ ውዴ....
እንዲህ ያለውን ሰው
ወሮታው ሲዘከር ስላንጠለጠለ
በምናቤ ጓዳ...
የማይከስም ምስልን...ራሴ ላስጠለለ
አፍቃሪነት ዳሩ...
ከጠቢብም በላይ ...ጥበብ እንዳዘለ
ምስክሬ ነፍሴ
ባገኘው ወረቀ....አንቺን እንደሳለ
ምን ይሆን መስፈርቱ
ማነው የሚረዳ...
አይኔ በከደነ ፥ ገፅታሽ ሲቀዳ
ምስልሽ ሲንቀራወዝ ...በህልሜ ሰሌዳ
በውኔም በወረቀት ፥ ሲብስ በግድግዳ
የብዙ ብዙን ምጥ....አዕላፈ ውልጃ
ከሁለት ግልግል...ካንድ ተኩል ውርጃ
ለማመዛዘኛ....ቢጠፋ ብልሀቱ
ተደብቄ ኖርኩኝ ፥ የመልክሽ ሎሬቱ ።
✍ አብርሀም_ተክሉ ( መርዕድ)
@Abrham_teklu
@getem
@getem
ምሩቅ ጥበብ ሰሪ
የሸራ ቀበኛ ፥ የቀለም ቀማሪ
ጠቢባን ጠበብቶች
የቀለም አባቶች
የብሩሽ አርበኛ ፥ የኪነት ገማቾች
በዘመን የቆሙት
ከትውልዱ ወጥተው ፥ የሚተዛዘቡት
አልያ ....ዘመን አልፈው
በነጠረ ስራ....
ከኛ ጀምበር ጥላ ፥ በሞገስ የቆሙት
መናኛም.....ሆኑ ...ዝነኛ
ትሁትም ....ሆኑ ....ጉረኛ
እርቃን አፍቃሪዎች!
ምስል ደጋሚዎች!
ምጡቅ አሳቢዎች!
ብቻ.....ሰአሊ የሆኑ
ሸራ የወጠሩ ፥ ብሩሽ የዘገኑ
ሁለት ግዜ ነው.... የሚስሉ
ሁለት ግዜ ነው ....የሚያጤኑ
#አንድ...
በረጅም ግዜ ተመስጦ ...በጥቂት ግዜ መቃኘት
የሚፈለገውን ውበት ፥ ተኩሮ በማየት
በህሊና ችንካር ሸራ
ያኔ ነው ፥ የጥበብ ሽል ፥ ፅንሱ የሚዘራ
#ሁለት...
እንግዲህ በሀሳብ ፥ ምስሉ እንደታያቸው
በውን አለም ሸራ ...ይጫራል ንድፋቸው
አይን እና እጆቻቸው ፥ እኩል እስከቻሉ
የግል አይናቸውን ፥ ለሰው ይቸራሉ
ያዩትን ...ለማውረድ
ፅንፉን ለማዋደደ
ጣጥረው..
ጫጭረው...
ሞንጭረው...
የለቀለቁትን.... አቅመ ጥበብ ቅይጥ
ጋለሪ እያገባ ...ወዳጅ እንዲያቋምጥ
ሁለቴ ተረግዞ...ሁለቴ ይማጣል
አፍቃሪው በርትቶ....
ወላድ ለመጠየቅ ...አውደርይ ይወጣል
በዚህ ኩናቴ ውስጥ...
አንዳቹም ሰአሊ
ልጁን የሰቀለ ፥ በቤት በጋለሪ
እስኪያረጅ ...እስኪሸጥ
ማንጠልጠል ይወዳል ፥ ጭንቁን እንደ ትሪ
የብሩሹ አጣጣል ፥ ቀለም ስብጥሩ
የመልእክቱ ምጥቀት ፥ ብራና ሚስጥሩ
ገለፃው......ውብቱ
ጨረሩ ....ሙቀቱ
ሺህ ግዜ ፥ እልፍ አመት
እኛን ቢገርመንም...
ቢያጅበንም ...ደርሶ
የሁለቴ ምጥ ነው
ዘመን የሚሻገር ፥ በቀለማት ርሶ
አየሽልኝ ውዴ....
እንዲህ ያለውን ሰው
ወሮታው ሲዘከር ስላንጠለጠለ
በምናቤ ጓዳ...
የማይከስም ምስልን...ራሴ ላስጠለለ
አፍቃሪነት ዳሩ...
ከጠቢብም በላይ ...ጥበብ እንዳዘለ
ምስክሬ ነፍሴ
ባገኘው ወረቀ....አንቺን እንደሳለ
ምን ይሆን መስፈርቱ
ማነው የሚረዳ...
አይኔ በከደነ ፥ ገፅታሽ ሲቀዳ
ምስልሽ ሲንቀራወዝ ...በህልሜ ሰሌዳ
በውኔም በወረቀት ፥ ሲብስ በግድግዳ
የብዙ ብዙን ምጥ....አዕላፈ ውልጃ
ከሁለት ግልግል...ካንድ ተኩል ውርጃ
ለማመዛዘኛ....ቢጠፋ ብልሀቱ
ተደብቄ ኖርኩኝ ፥ የመልክሽ ሎሬቱ ።
✍ አብርሀም_ተክሉ ( መርዕድ)
@Abrham_teklu
@getem
@getem
❤1👍1