አ-ል-ገ-ጥ-ም-ም(ልዑል ሀይሌ)
እዪው ያን ገጣሚ
ጆሮው ስር እያለች ምትወደው ፍቅረኛ
ብዕሩን ወድሮ
ሩቅ ይማግጣል ጨረቃን ሊተኛ
.
ከዕለታት አንድ ቀን
ያ አፍቃሪ ገጣሚ ገጣሚ ነው ሲባል
በስንኙ ምስጠት
ባለቤቱን ፈትቶ ጨረቃን ያገባል
.
ከዕለታት አንድ ቀን
ያገባት ጨረቃ
በዕልፍ ገጣሚዎች ስንኝ ተወድሳ
ውበቷ የሁሉም መሆኑ ሲገባው
ጨረቃንም ፈታ መግጠሙንም ረሳ
.
ያ ምስኪን አፍቃሪ
ባበጃጀው ስንኝ
ባለቤቱን ትቶ በፍቺ ከተቀጣ
አ-ል-ገ-ጥ-ም-ም ካንቺ ጋር
ጨረቃን ልፈታ
01-08-10
@getem
@getem
@gebriel_19
እዪው ያን ገጣሚ
ጆሮው ስር እያለች ምትወደው ፍቅረኛ
ብዕሩን ወድሮ
ሩቅ ይማግጣል ጨረቃን ሊተኛ
.
ከዕለታት አንድ ቀን
ያ አፍቃሪ ገጣሚ ገጣሚ ነው ሲባል
በስንኙ ምስጠት
ባለቤቱን ፈትቶ ጨረቃን ያገባል
.
ከዕለታት አንድ ቀን
ያገባት ጨረቃ
በዕልፍ ገጣሚዎች ስንኝ ተወድሳ
ውበቷ የሁሉም መሆኑ ሲገባው
ጨረቃንም ፈታ መግጠሙንም ረሳ
.
ያ ምስኪን አፍቃሪ
ባበጃጀው ስንኝ
ባለቤቱን ትቶ በፍቺ ከተቀጣ
አ-ል-ገ-ጥ-ም-ም ካንቺ ጋር
ጨረቃን ልፈታ
01-08-10
@getem
@getem
@gebriel_19
«የ‘ናቴን ቤት ኪራይ»
:
:
አግባኝ አትበዪኝ ገና ከመውጣቴ
ስንት ዐመት ተምሬ ስራ ከማግኘቴ።
:
:
ሚጨበጥ ሳይኖረን ሚባል እዚግባ
ምን ሰምተሽ ነው ፍቅሬ ከጆሮሽ ምን ገባ።
:
:
እውነቱማ ይህ ነው...
... አጥንትሽ ካጥንቴ ካለው ቁርኝት
አምላክ ሁኚ ካለሽ አንቺን የኔ ሴት
ማንም ባንደበቱ ያሻውን ቢያወራ
መሆኔ ማይቀር ነው ያንቺው አባወራ።
:
:
እናምልሽ ውዴ ምማፀንሽ ቢኖር ...
... ምዬ በዚ ሰማይ
እሱ ከፃፈልን ስለማይቀር ደስታ...
...ስለማይቀር ሲሳይ
ስወድቅ ያነሱኝን ስዝል ያገዙኝን...
...ወገኖቼን እንዳይ
ባክሽን ታገሺኝ ባልጨርሰው እንኳ...
... እስክከፍል ድረስ የእናቴን ቤት ኪራይ።
✍ሄኖክ✍
@getem
@getem
:
:
አግባኝ አትበዪኝ ገና ከመውጣቴ
ስንት ዐመት ተምሬ ስራ ከማግኘቴ።
:
:
ሚጨበጥ ሳይኖረን ሚባል እዚግባ
ምን ሰምተሽ ነው ፍቅሬ ከጆሮሽ ምን ገባ።
:
:
እውነቱማ ይህ ነው...
... አጥንትሽ ካጥንቴ ካለው ቁርኝት
አምላክ ሁኚ ካለሽ አንቺን የኔ ሴት
ማንም ባንደበቱ ያሻውን ቢያወራ
መሆኔ ማይቀር ነው ያንቺው አባወራ።
:
:
እናምልሽ ውዴ ምማፀንሽ ቢኖር ...
... ምዬ በዚ ሰማይ
እሱ ከፃፈልን ስለማይቀር ደስታ...
...ስለማይቀር ሲሳይ
ስወድቅ ያነሱኝን ስዝል ያገዙኝን...
...ወገኖቼን እንዳይ
ባክሽን ታገሺኝ ባልጨርሰው እንኳ...
... እስክከፍል ድረስ የእናቴን ቤት ኪራይ።
✍ሄኖክ✍
@getem
@getem
#ትዝታ
ገጣሚ ፦ ኤፍሬም ስዩም
አቅራቢ ፦ ቶፊቅ
••●◉Join us share◉●••
╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗
@Nuenmamar
@getem
@McTof
╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝🌹
ገጣሚ ፦ ኤፍሬም ስዩም
አቅራቢ ፦ ቶፊቅ
••●◉Join us share◉●••
╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗
@Nuenmamar
@getem
@McTof
╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝🌹
ዝም ብዬ ላፍቅርሽ****
.
እኔና ዝምታ ስናወራ ብታይ
ጉድ ይላል ማዕበል ይደነቃል ሠማይ
ዝናም ይደመማል ግር ይላታል ፀሀይ
እውነት ነው የምልሽ
ማመን እስኪያቅትሽ
እኔና ዝምታ ስናወራ ብታይ
ድሮ ይለወጣል ይሆናል ዘመናይ
:
ዝምታን ቀዝፌ
እሽታን ታቅፌ
ጎርፉን እየታገልኩ ስመላለስ ካየሽ
ምን አስባ ይሆን? ከሚል ጉብታ ላይ ቁጭ ብዬ ካየሽ
አደራ ጥሻ እንዳጥሺ
ፍቅሬ የሚለውን አመፅሽን አትቀስቅሺ
ባላወራሺው ተረት አፌን አታብሺ
:
ግን እኔና ዝምታ ስናወራ ካየሽ
በድኔ ነው ያለው! በድኔን ነው ያየሽ!
በቡቃያው ዓለም ባሰስነው አዝመራ
ባቦካነው አፈር በረጨነው አቧራ
ጩኸት ብቻ ፍቅር
አዳማጭ ያጣ ህብር
:
ከክፋት ችግኝ ላይ ደስታ ሲሆን ዓረም
እንቦጭ ነቃይ ጠፍቶ ሲበቅል በኛ ዓለም
ነቅተሽ ሆኖ እንደሆን ተመኝተሽ ዋይታ
ትላንት ከናፈቀሽ ከገባሽ ዝምታ
ነይ አብረን ዝም እንበል እናውራ ትዝታ
:
ትላንት ግን ደክማለች አትስቅም ከቶ
ጥርሷ ዛሬ የለም ትላንቷ ላይ ወቶ
ነግሬሽ ከሰማሽ
እኔና ዝምታ ስናወራ ካየሽ
ከቶ እንዳይመስልሽ
በኔና አንቺ ፍቅር
እግሬ እሚተሳሰር
፡
ተይ ልንገርሽ ዝምታሽን ኑሪ
በህባሬ ቅኔ ድርሽን አትድሪ
ግን እውነት እውነት ስልሽ
እኔና ዝምታ ስናወራ ካየሽ
በጩወቴ ዘመን ጮኬ ያልነገርኩሽ
ያ ፍቅርሽ አውሎ ሠማይ ቅኔ
ምድር ጥልቀት ሠጥሞ በኔ
ዝብርቅርቃን ክስተት አውሎ በቀኔ
የሴት ሴቴ ሆነሽ ተላምጄሽ እኔ
፡
እንደ አካሌ ክፋይ
እንደ ልቤ ጉዳይ
ጉም እንደሚጋልብ እንደ ገነት ጉዳይ
ፍፁሜ ነበርሽ እንደሌለው ስህተት
ታሪኬ ነበርሽ እንደ ዕድሜዬ ርዝመት
፡
……ያኔ ስንጮኽ ያልነገርኩሽ!
ልቤ ላይ መቅኔ ቀስቃሽ
ውድ ፍቅር አለሽ
……ያኔ ስንጮኽ ያልነገርኩሽ!
ደፋ ቀና ብሎ ዝምታዬ የከለለሽ
ዝቅ ብዬ ከማፍር ቀና ብዬ የደበኩሽ
ውድ ፍቅር አለኝ ጊዜ ሄዶ ያልነገርኩሽ
:
ናናዬ የትላንቴ ጣፋጭ ከረሜላ
መጥጬሽ ልደሰት ጩኸቴ ይቀላ
ዝምታችን ያውራ
ይኑር ፍቅር እየሰራ
ውስጣችን ያፍቅር ውስጣችን ይናገር
ጩኸቱ ይቅርና ዝምታ ይፋቀር
:
:
:
አንቺም ዝም በይ ዝምታ ላልምድሽ
ዝምታ ሰብስቤ ዝም ብዬ ላፍቅርሽ
~~~~~~~~~~~~~~~~
:- አዲሱ ጉግሳ (ከሰባተኛ)
@getem
@getem
@gebriel19
.
እኔና ዝምታ ስናወራ ብታይ
ጉድ ይላል ማዕበል ይደነቃል ሠማይ
ዝናም ይደመማል ግር ይላታል ፀሀይ
እውነት ነው የምልሽ
ማመን እስኪያቅትሽ
እኔና ዝምታ ስናወራ ብታይ
ድሮ ይለወጣል ይሆናል ዘመናይ
:
ዝምታን ቀዝፌ
እሽታን ታቅፌ
ጎርፉን እየታገልኩ ስመላለስ ካየሽ
ምን አስባ ይሆን? ከሚል ጉብታ ላይ ቁጭ ብዬ ካየሽ
አደራ ጥሻ እንዳጥሺ
ፍቅሬ የሚለውን አመፅሽን አትቀስቅሺ
ባላወራሺው ተረት አፌን አታብሺ
:
ግን እኔና ዝምታ ስናወራ ካየሽ
በድኔ ነው ያለው! በድኔን ነው ያየሽ!
በቡቃያው ዓለም ባሰስነው አዝመራ
ባቦካነው አፈር በረጨነው አቧራ
ጩኸት ብቻ ፍቅር
አዳማጭ ያጣ ህብር
:
ከክፋት ችግኝ ላይ ደስታ ሲሆን ዓረም
እንቦጭ ነቃይ ጠፍቶ ሲበቅል በኛ ዓለም
ነቅተሽ ሆኖ እንደሆን ተመኝተሽ ዋይታ
ትላንት ከናፈቀሽ ከገባሽ ዝምታ
ነይ አብረን ዝም እንበል እናውራ ትዝታ
:
ትላንት ግን ደክማለች አትስቅም ከቶ
ጥርሷ ዛሬ የለም ትላንቷ ላይ ወቶ
ነግሬሽ ከሰማሽ
እኔና ዝምታ ስናወራ ካየሽ
ከቶ እንዳይመስልሽ
በኔና አንቺ ፍቅር
እግሬ እሚተሳሰር
፡
ተይ ልንገርሽ ዝምታሽን ኑሪ
በህባሬ ቅኔ ድርሽን አትድሪ
ግን እውነት እውነት ስልሽ
እኔና ዝምታ ስናወራ ካየሽ
በጩወቴ ዘመን ጮኬ ያልነገርኩሽ
ያ ፍቅርሽ አውሎ ሠማይ ቅኔ
ምድር ጥልቀት ሠጥሞ በኔ
ዝብርቅርቃን ክስተት አውሎ በቀኔ
የሴት ሴቴ ሆነሽ ተላምጄሽ እኔ
፡
እንደ አካሌ ክፋይ
እንደ ልቤ ጉዳይ
ጉም እንደሚጋልብ እንደ ገነት ጉዳይ
ፍፁሜ ነበርሽ እንደሌለው ስህተት
ታሪኬ ነበርሽ እንደ ዕድሜዬ ርዝመት
፡
……ያኔ ስንጮኽ ያልነገርኩሽ!
ልቤ ላይ መቅኔ ቀስቃሽ
ውድ ፍቅር አለሽ
……ያኔ ስንጮኽ ያልነገርኩሽ!
ደፋ ቀና ብሎ ዝምታዬ የከለለሽ
ዝቅ ብዬ ከማፍር ቀና ብዬ የደበኩሽ
ውድ ፍቅር አለኝ ጊዜ ሄዶ ያልነገርኩሽ
:
ናናዬ የትላንቴ ጣፋጭ ከረሜላ
መጥጬሽ ልደሰት ጩኸቴ ይቀላ
ዝምታችን ያውራ
ይኑር ፍቅር እየሰራ
ውስጣችን ያፍቅር ውስጣችን ይናገር
ጩኸቱ ይቅርና ዝምታ ይፋቀር
:
:
:
አንቺም ዝም በይ ዝምታ ላልምድሽ
ዝምታ ሰብስቤ ዝም ብዬ ላፍቅርሽ
~~~~~~~~~~~~~~~~
:- አዲሱ ጉግሳ (ከሰባተኛ)
@getem
@getem
@gebriel19
👍1
ለቅዳሚታችን
❤️
#የሆነ ቀን ነው ማታ ላይ............
ሀንግ ተደርጊያለው ብዬ ለማመልከት አቅራቢያዬ ወዳለው ፖሊስ ጣቢያ ሄድኩ ፣ቢሮውን
አንኳኳው ከውስጥ የሰለለ ድምፅ ይግቡ አለኝ።ገና ሳልቀመጥ ምን ልርዳህ አለኝ
ማዕረጉን እያስተካከለ፣ማታ ወደ ቤቴ ስገባ ዝርፊያ ተደርጎብኝ እሱን ለማመልከት
ነው።ስንት ሰአት ይሆናል? አለኝ በግምት ለአራት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ይመስለኛል አልኩት
ጨለማ ነበር አለኝ አይ ፀሀይ ወጥታ ነበር ማለት አማረኝ...ዝም ስለው መብራት ነበር
ወይ፣ሰዎቹን መለየት የምትችልበት ሁኔታ ነበር ወይ ለማለት ነው አለኝ።አይ መለየት
በሚያስችል ሁኔታ ብርሀን የለም ግን አንደኛው በጣም ስለተጠጋኝ በደምብ
አይቼዋለው...ምን ይዘህ ነበር ? የተወሰነ ገንዘብ ፣ስልክ እና ሀሳቦቼን። ሀሳቦቼን ማለት?
አለኝ ቀና ብሎ መስራት እና ማድረግ የምፈልጋቸውን ነገሮች አይምሮዬ ውስጥ ተሸክሜ
ነበር አደጋ አደረሱብኝ ወይ ሞትኩ ማለት እነሱም ጠፉ ማለት አይደል አልኩት እኔ ደሞ
ወንበሩ ላይ ለጠጥ ብዬ....ተኮሳተረ ሀሳብ ለፖሊስ ንብረት አይደለም ማለት ነው? ብዬ
ለራሴ አሰብኩ እያሾፍክ አይደለም አይደል አለኝ...ለምን አሾፋለው አልኩት ፈርጠም ብዬ
እሺ የብሩ መጠን ስንት ነበር አለኝ እኔንጃ በግምት ከአንድሺ አምስት መቶብር በታች
ከአንድሺ በላይ አልኩት፣ስልኩስ አለኝ ቴክኖ ነው ውስጡ ከመቶ ብር በላይ ካርድ እና
የተወሰነ የኢንተርኔት ፓኬጅ አለው አልኩት.....የምጠይቅህን ብቻ መልስ አለኝ
ቢቆጣም ባይቆጣም ድምፁ ተመሳሳይ የሰለለ ነው...እሺ ልጁ ምን አይነት ነው ?ይሄ
ሰውዬ ሁሉንም ጠይቆ ይዞት ሊካፈል ነው እንዴ ብዬ ማሰብ ጀመርኩ መልኩን አሳስቼ
ልንገረው? አይ በትክክል ልንገረው እና ይጠቀም አልኩ...ምነው ዝም አልክ መልኩ
ጠፋብህ አለኝ።አልጠፋብኝም ጠይም ፣መካከለኛ ቁመት፣ሰፊ ፊት ያለው፣የተንጨባረረ
ፂም እና ፀጉር ያለው እና ቀኝ እጁ ላይ ትልቅ ቀለበት አድርጓል አልኩት...በዚ ሰአት አንገቱን
እየነቀነቀ ነበር እኔ ግን ከእንቅልፌ ላብ በላብ ሆኜ ነቅቻለው።
.
.
.
.
ግጠም ያሉኝ ጊዜ!!!
እስቲ ቅኔ ልዝረፍ፤
ቅኔ ዛር አለብኝ፤ ደርሶ የሚነሳ፤
ና ግጠም የሚለኝ፤
ና ብረር የሚለኝ፤
ብድግ የሚልብኝ፤ ደርሶ እንደግሪሳ።
እኔም አያስችለኝ፤
መቼም አይሆንልኝ፤ የቅኔ ወግ ነገር፤
እየተዘረፉ፤
እየተዛረፉ፤
ደግሞ እየዘረፉ፤ በሚበሉት ሃገር፤
ጭቁን ምን ይዘርፋል፤
ከዘለላ ግጥም፤ ካንዲት ቅኔ በቀር።
((( ጃ ኖ )))💚💛❤️
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ !!!!!💚💛❤️
@balmbaras
@getem
@getem
❤️
#የሆነ ቀን ነው ማታ ላይ............
ሀንግ ተደርጊያለው ብዬ ለማመልከት አቅራቢያዬ ወዳለው ፖሊስ ጣቢያ ሄድኩ ፣ቢሮውን
አንኳኳው ከውስጥ የሰለለ ድምፅ ይግቡ አለኝ።ገና ሳልቀመጥ ምን ልርዳህ አለኝ
ማዕረጉን እያስተካከለ፣ማታ ወደ ቤቴ ስገባ ዝርፊያ ተደርጎብኝ እሱን ለማመልከት
ነው።ስንት ሰአት ይሆናል? አለኝ በግምት ለአራት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ይመስለኛል አልኩት
ጨለማ ነበር አለኝ አይ ፀሀይ ወጥታ ነበር ማለት አማረኝ...ዝም ስለው መብራት ነበር
ወይ፣ሰዎቹን መለየት የምትችልበት ሁኔታ ነበር ወይ ለማለት ነው አለኝ።አይ መለየት
በሚያስችል ሁኔታ ብርሀን የለም ግን አንደኛው በጣም ስለተጠጋኝ በደምብ
አይቼዋለው...ምን ይዘህ ነበር ? የተወሰነ ገንዘብ ፣ስልክ እና ሀሳቦቼን። ሀሳቦቼን ማለት?
አለኝ ቀና ብሎ መስራት እና ማድረግ የምፈልጋቸውን ነገሮች አይምሮዬ ውስጥ ተሸክሜ
ነበር አደጋ አደረሱብኝ ወይ ሞትኩ ማለት እነሱም ጠፉ ማለት አይደል አልኩት እኔ ደሞ
ወንበሩ ላይ ለጠጥ ብዬ....ተኮሳተረ ሀሳብ ለፖሊስ ንብረት አይደለም ማለት ነው? ብዬ
ለራሴ አሰብኩ እያሾፍክ አይደለም አይደል አለኝ...ለምን አሾፋለው አልኩት ፈርጠም ብዬ
እሺ የብሩ መጠን ስንት ነበር አለኝ እኔንጃ በግምት ከአንድሺ አምስት መቶብር በታች
ከአንድሺ በላይ አልኩት፣ስልኩስ አለኝ ቴክኖ ነው ውስጡ ከመቶ ብር በላይ ካርድ እና
የተወሰነ የኢንተርኔት ፓኬጅ አለው አልኩት.....የምጠይቅህን ብቻ መልስ አለኝ
ቢቆጣም ባይቆጣም ድምፁ ተመሳሳይ የሰለለ ነው...እሺ ልጁ ምን አይነት ነው ?ይሄ
ሰውዬ ሁሉንም ጠይቆ ይዞት ሊካፈል ነው እንዴ ብዬ ማሰብ ጀመርኩ መልኩን አሳስቼ
ልንገረው? አይ በትክክል ልንገረው እና ይጠቀም አልኩ...ምነው ዝም አልክ መልኩ
ጠፋብህ አለኝ።አልጠፋብኝም ጠይም ፣መካከለኛ ቁመት፣ሰፊ ፊት ያለው፣የተንጨባረረ
ፂም እና ፀጉር ያለው እና ቀኝ እጁ ላይ ትልቅ ቀለበት አድርጓል አልኩት...በዚ ሰአት አንገቱን
እየነቀነቀ ነበር እኔ ግን ከእንቅልፌ ላብ በላብ ሆኜ ነቅቻለው።
.
.
.
.
ግጠም ያሉኝ ጊዜ!!!
እስቲ ቅኔ ልዝረፍ፤
ቅኔ ዛር አለብኝ፤ ደርሶ የሚነሳ፤
ና ግጠም የሚለኝ፤
ና ብረር የሚለኝ፤
ብድግ የሚልብኝ፤ ደርሶ እንደግሪሳ።
እኔም አያስችለኝ፤
መቼም አይሆንልኝ፤ የቅኔ ወግ ነገር፤
እየተዘረፉ፤
እየተዛረፉ፤
ደግሞ እየዘረፉ፤ በሚበሉት ሃገር፤
ጭቁን ምን ይዘርፋል፤
ከዘለላ ግጥም፤ ካንዲት ቅኔ በቀር።
((( ጃ ኖ )))💚💛❤️
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ !!!!!💚💛❤️
@balmbaras
@getem
@getem
ቀሳፊ ምርቃት
/በ አሌክስ አብርሃም /
ሰማሁ ምርቃትሽን ….
ከእናት አንጀትሽ ቁልቁል ሲዥጎደጎድ
ታየኝ ምድረ መልዓክ …
ብራና ዘርግቶ ቃልሽን ሊከትብ ትከሻሽ ላይ ሲያረግድ
በረካሁንልኝ …ከፍ ያርግህ በሰው ፊት …
እድሜ ጥምቡን ይጣል ይቅና ማቱሳላ
እርጅና እጁ ይዛል አካላትህ ይስላ
ዝም !
እግርህን እንቅፋት ጎንህን ጋሬጣ
ጤናህን ድቅስቃስ የመንደር ሽውታ
አይንካብኝ ብለሽ የመረቅሽኝ ለታ
ዝም !
ዘርህ ዋርካ ይሁን ወንዝ ዳር ያበበ
ታሪክህ ዘላለም ባደባባይ ይድመቅ እየተነበበ
ደሆች ፊትክን አይተው በጥጋብ ይኑሩ
ልጆጅህ በስምህ ለዘላለም ይኩሩ
ብለሽ ስትመርቂኝ
ዝም !
ካ,ይንሽ የፍቅር እንባ ፊቴ እየረገፈ
ለእልፍ ምርቃትሽ እንቢ አለኝ ልሳኔ ‹‹አሚንታን ›› ነጠፈ
ዝምታየ አይክፋሽ ክፉ ፍራቴ ነው ልሳኔን የዘጋው
በምርቃትሽ ውስጥ የምርቃት መቅሰፍት ውስጤን እየወጋው
በክፉ የሚያይህን ጨለማ ያልብሰው
ክፉ ተራማጁን እግሩን ያልመስምሰው
ብለሽ አሚን ያልኩት ምርቃትሽ ያዘ
በክፉ የሚያየኝ አይኑ ታወረና
በጭፍን ሊፈጀኝ ጎራዴ መዘዘ
የህሊና እግሮቹ የሰለሉ ጠላት
ብረት ተመርኩዞ መንገዴ ላይ ቆመ
አሚን ካለሽ አፌ ‹‹እግዚኦታ›› ተመመ !
ግዴለሽም እማ …
ጠላቴ አይኑ ይብራ ይግደለኝ እያየ
ባቡሰጥ ብትሩ እኔን እየሳተ ወገን አሰቃየ
ጥላቴ እግሩ ይስላ ይቅደመኝ ከሮጠ
በለመሹ እግሮቹ መንገድ እየዘጋ
ከዘመን ሩጫ ትውልድ ተቋረጠ !
ግዴለሽም እማ …..
ጥላቴን መርቂው አይኑ ፀሃይ ይሁን ቦግ ብሎ ይብራ
ምናልባት ምናልባት እውነቱን ቢያሳየኝ
ወይ እውነቴን አይቶ ለልጅሽ ቢራራ ጥላቴ ዓይኑ ይብራ …
ያኔ ትሰሚያለሽ ድል ካረገ ልሳን የሃቅን ፉከራ !
እንጅ ባንድ ምድር ልጅ እየመረቁ ‹‹ጠላትን›› ቢገፉ
ርግማን ያወረው በደፈናው ጠላት ለልጅሽ ነው ደፉ !
አሚን ?
አሪፍ ቀን ቀሽቶቼ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
/በ አሌክስ አብርሃም /
ሰማሁ ምርቃትሽን ….
ከእናት አንጀትሽ ቁልቁል ሲዥጎደጎድ
ታየኝ ምድረ መልዓክ …
ብራና ዘርግቶ ቃልሽን ሊከትብ ትከሻሽ ላይ ሲያረግድ
በረካሁንልኝ …ከፍ ያርግህ በሰው ፊት …
እድሜ ጥምቡን ይጣል ይቅና ማቱሳላ
እርጅና እጁ ይዛል አካላትህ ይስላ
ዝም !
እግርህን እንቅፋት ጎንህን ጋሬጣ
ጤናህን ድቅስቃስ የመንደር ሽውታ
አይንካብኝ ብለሽ የመረቅሽኝ ለታ
ዝም !
ዘርህ ዋርካ ይሁን ወንዝ ዳር ያበበ
ታሪክህ ዘላለም ባደባባይ ይድመቅ እየተነበበ
ደሆች ፊትክን አይተው በጥጋብ ይኑሩ
ልጆጅህ በስምህ ለዘላለም ይኩሩ
ብለሽ ስትመርቂኝ
ዝም !
ካ,ይንሽ የፍቅር እንባ ፊቴ እየረገፈ
ለእልፍ ምርቃትሽ እንቢ አለኝ ልሳኔ ‹‹አሚንታን ›› ነጠፈ
ዝምታየ አይክፋሽ ክፉ ፍራቴ ነው ልሳኔን የዘጋው
በምርቃትሽ ውስጥ የምርቃት መቅሰፍት ውስጤን እየወጋው
በክፉ የሚያይህን ጨለማ ያልብሰው
ክፉ ተራማጁን እግሩን ያልመስምሰው
ብለሽ አሚን ያልኩት ምርቃትሽ ያዘ
በክፉ የሚያየኝ አይኑ ታወረና
በጭፍን ሊፈጀኝ ጎራዴ መዘዘ
የህሊና እግሮቹ የሰለሉ ጠላት
ብረት ተመርኩዞ መንገዴ ላይ ቆመ
አሚን ካለሽ አፌ ‹‹እግዚኦታ›› ተመመ !
ግዴለሽም እማ …
ጠላቴ አይኑ ይብራ ይግደለኝ እያየ
ባቡሰጥ ብትሩ እኔን እየሳተ ወገን አሰቃየ
ጥላቴ እግሩ ይስላ ይቅደመኝ ከሮጠ
በለመሹ እግሮቹ መንገድ እየዘጋ
ከዘመን ሩጫ ትውልድ ተቋረጠ !
ግዴለሽም እማ …..
ጥላቴን መርቂው አይኑ ፀሃይ ይሁን ቦግ ብሎ ይብራ
ምናልባት ምናልባት እውነቱን ቢያሳየኝ
ወይ እውነቴን አይቶ ለልጅሽ ቢራራ ጥላቴ ዓይኑ ይብራ …
ያኔ ትሰሚያለሽ ድል ካረገ ልሳን የሃቅን ፉከራ !
እንጅ ባንድ ምድር ልጅ እየመረቁ ‹‹ጠላትን›› ቢገፉ
ርግማን ያወረው በደፈናው ጠላት ለልጅሽ ነው ደፉ !
አሚን ?
አሪፍ ቀን ቀሽቶቼ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
👍1
*ህመም ፩***
በአንዲት ትንሽ ቅፅበት
በትንሽ መንደር ውሥጥ
ዙሪያየን ሥቃኘው
ይህ ነው የሚታየኝ.....
ሢጠጡ ያደሩ የጀዘቡ ነፍሶች
የተበታተኑ የቢራ ጠርሙሶች
ከበሩ ፊት ለፊት....
ሀገር የገነቡ ድንበር ያሥከበሩ
ጊዜ የጣላቸው ሠው ያላነሣቸው
ንፋሥ ላይ ተቀምጠው የሚራቡ ፊቶች
.....ትንሽ ዝቅ ብሎ...
ሁለት ልጅ ያዘለች
ከጡአት እሥከ ማታ ላፍታ ያላረፈች
የተጎሣቆለች ቆሎ ምትሸጥ እናት
ምንገድ ዳር ላይ ውላ ምንገድ የምታድር
..........................ማረፊያ የሌላት
ከዚህ አለፍ ብሎ...
ሽቶ ተርከፍክፈው ድሀ ተፀይፈው
የሚጉአዙ ጥንዶች..
ከነሡ ከፍ ብሎ
አየር ላይ ሚበሩ ጥንብ አንሣ ጭልፊቶች
..
ዱላ የጨበጠ ጋንጃ መቶ አዳሪ
ከቅርብ እርቀት ላይ..
እንዳላየ የሚያልፍ ሠላም አሥከባሪ
..
የተበታተኑ መፈክር የያዙ በጭሥ የታፈኑ
ሥራ አጥ ወጣቶች...
ከነሡ ፊት ለፊት...
ጥይት የታጠቁ እልፍ ወታደሮች
ከዚህ ሁሉ ጀርባ...
ግርማ የሌላቸው የፈረሡ ግንቦች።
#ኅይሌ
@getem
@getem
በአንዲት ትንሽ ቅፅበት
በትንሽ መንደር ውሥጥ
ዙሪያየን ሥቃኘው
ይህ ነው የሚታየኝ.....
ሢጠጡ ያደሩ የጀዘቡ ነፍሶች
የተበታተኑ የቢራ ጠርሙሶች
ከበሩ ፊት ለፊት....
ሀገር የገነቡ ድንበር ያሥከበሩ
ጊዜ የጣላቸው ሠው ያላነሣቸው
ንፋሥ ላይ ተቀምጠው የሚራቡ ፊቶች
.....ትንሽ ዝቅ ብሎ...
ሁለት ልጅ ያዘለች
ከጡአት እሥከ ማታ ላፍታ ያላረፈች
የተጎሣቆለች ቆሎ ምትሸጥ እናት
ምንገድ ዳር ላይ ውላ ምንገድ የምታድር
..........................ማረፊያ የሌላት
ከዚህ አለፍ ብሎ...
ሽቶ ተርከፍክፈው ድሀ ተፀይፈው
የሚጉአዙ ጥንዶች..
ከነሡ ከፍ ብሎ
አየር ላይ ሚበሩ ጥንብ አንሣ ጭልፊቶች
..
ዱላ የጨበጠ ጋንጃ መቶ አዳሪ
ከቅርብ እርቀት ላይ..
እንዳላየ የሚያልፍ ሠላም አሥከባሪ
..
የተበታተኑ መፈክር የያዙ በጭሥ የታፈኑ
ሥራ አጥ ወጣቶች...
ከነሡ ፊት ለፊት...
ጥይት የታጠቁ እልፍ ወታደሮች
ከዚህ ሁሉ ጀርባ...
ግርማ የሌላቸው የፈረሡ ግንቦች።
#ኅይሌ
@getem
@getem
👍1
"ደህና ነህ አትበይኝ"
ደህና መሆን ማለት
በጭንቀት ተራራ በናፍቆት ቁልቁለት
ድካም በበዛብት በብቸኝነት ቤት
መዳከር አይደለም....
ደህና መሆን ማለት....
ሣቅሽ በሌለበት በተቆጣ ሀገር
ደሥታ በቸገረው በሚያሣዝን ሠፈር
መንደርተኛ ተብሎ መቆጠር አይደለም
ደህና መሆን ማለት.....
ከተትረፈረፈው ከሚማርክ ገላ
ወይም ከሚያሠክረው ከጠላው አተላ
አንችን እያሠቡ መጎንጨት አይደለም
ደህና መሆን ማለት....
የትም በማያደርሥ መንገድ መመላለሥ
በማታውቂው ሥፍራ ትኖሪያለሽ ብሎ
...... ..........ሀገር ምድሩን ማሠሥ
መቅበዝበዝ አይደለም.....
ደህና መሆን ማለት
ከ ጫጫታ መሀል...
ፍዝዝ ብሎ ቁሞ ድምፅሽን መናፈቅ
አንቺን እያሠቡ...
ውብ ተፈጥሮን ትቶ ፈራሽ ጣኦት ማድነቅ
መሥለምለም አይደለም..
እናማ የኔአለም..
ደህና ነህ?? እያልሽኝ ትመጫለሽ እያልኩ
አንቺን እየጠበኩ...
አንቺን ያሣፈረ መርከብ የሌለበት
ዕልፍ አባይ ጎረፈ
ጠረንሽን ያልያዘ ዕልፍ አየር ነፈሠ
ዕልፍ ቀን አለፈ
ደህና ነህ?? እያልሽኝ አንቺን እየጠበኩ..
እርጉም መንግሥት ሂዶ
እንደመር የሚል እርጉም መንግሥት መጣ
የተደማሪ ነፍሥ ወደ ሠማይ ወጣ
.
.
እናም ቃሌን ሥሚ
ደህና ነህ እያልሽኝ ዝምምምም ከሆነ መልሤ
ዝምታየን ሥሚ...
ደህና ባልሆነ ሀገር..
መቅረትሽ ሢጨመር...
ደህና ነኝ እያለ
እንዴት ልቤ ዋሽቶ ምላሤ ይናገር!!
@Yasteseryall
@getem
@getelm
ደህና መሆን ማለት
በጭንቀት ተራራ በናፍቆት ቁልቁለት
ድካም በበዛብት በብቸኝነት ቤት
መዳከር አይደለም....
ደህና መሆን ማለት....
ሣቅሽ በሌለበት በተቆጣ ሀገር
ደሥታ በቸገረው በሚያሣዝን ሠፈር
መንደርተኛ ተብሎ መቆጠር አይደለም
ደህና መሆን ማለት.....
ከተትረፈረፈው ከሚማርክ ገላ
ወይም ከሚያሠክረው ከጠላው አተላ
አንችን እያሠቡ መጎንጨት አይደለም
ደህና መሆን ማለት....
የትም በማያደርሥ መንገድ መመላለሥ
በማታውቂው ሥፍራ ትኖሪያለሽ ብሎ
...... ..........ሀገር ምድሩን ማሠሥ
መቅበዝበዝ አይደለም.....
ደህና መሆን ማለት
ከ ጫጫታ መሀል...
ፍዝዝ ብሎ ቁሞ ድምፅሽን መናፈቅ
አንቺን እያሠቡ...
ውብ ተፈጥሮን ትቶ ፈራሽ ጣኦት ማድነቅ
መሥለምለም አይደለም..
እናማ የኔአለም..
ደህና ነህ?? እያልሽኝ ትመጫለሽ እያልኩ
አንቺን እየጠበኩ...
አንቺን ያሣፈረ መርከብ የሌለበት
ዕልፍ አባይ ጎረፈ
ጠረንሽን ያልያዘ ዕልፍ አየር ነፈሠ
ዕልፍ ቀን አለፈ
ደህና ነህ?? እያልሽኝ አንቺን እየጠበኩ..
እርጉም መንግሥት ሂዶ
እንደመር የሚል እርጉም መንግሥት መጣ
የተደማሪ ነፍሥ ወደ ሠማይ ወጣ
.
.
እናም ቃሌን ሥሚ
ደህና ነህ እያልሽኝ ዝምምምም ከሆነ መልሤ
ዝምታየን ሥሚ...
ደህና ባልሆነ ሀገር..
መቅረትሽ ሢጨመር...
ደህና ነኝ እያለ
እንዴት ልቤ ዋሽቶ ምላሤ ይናገር!!
@Yasteseryall
@getem
@getelm
❤1
አመውዴ(ልዑል ሀይሌ)
እናምልሽ ውዴ…
አንቺን በመውደዴ
በግ ማይጠፋው ቤት
ዶሮም አልታረደ
ዘይት ዋጋው ንሮ
እህል ተወደደ
ለነገሩ ይሁን
ቀን ነግቶ ይመሻል
እንኳን ኑሮ ቀርቶ
አንቺም ተወደሻል
………………………
እናምልሽ ውዴ…
አንቺን በመውደዴ
የቤታችን ቲቪ
ሪሞቱ ጠፍቶበት
የመኪናው መንገድ
አህያ ሄዶበት
ዕምነበረዳችን
ድንጋይ ተጠርቦበት
ያ ፅዱ ጎዳና
ተዝረክርኮልሻል
ለነገሩ ይሁን
አንቺም ሰው ጥለሻል
………………………
እናምልሽ ውዴ…
አንቺን በመውደዴ
በአውቶቡስ ፌርማታ
ባቡር ተጠበቀ
ሌባው እየኮራ
ፖሊስ ተደበቀ
ጥርስ ያለው አይስቅም
ድዳሙ እየሳቀ
ለነገሩ ይሁን
ቀን ነግቶ ይመሻል
እንኳን ሌላው ቀርቶ
አንቺም የኔዋ ጉድ
የኔን ልብ ሰርቀሻል
………………………
እናምልሽ ውዴ…
አንቺን በመውደዴ
በዝግ ቤት ውስጥ ሆኜ
ብጠብቅሽ እንኳ
..
.
ኳ
.
.
.
ኳ
.
.
.
....
በራችን ተንኳኳ!!
@getem
@getem
@getem
እናምልሽ ውዴ…
አንቺን በመውደዴ
በግ ማይጠፋው ቤት
ዶሮም አልታረደ
ዘይት ዋጋው ንሮ
እህል ተወደደ
ለነገሩ ይሁን
ቀን ነግቶ ይመሻል
እንኳን ኑሮ ቀርቶ
አንቺም ተወደሻል
………………………
እናምልሽ ውዴ…
አንቺን በመውደዴ
የቤታችን ቲቪ
ሪሞቱ ጠፍቶበት
የመኪናው መንገድ
አህያ ሄዶበት
ዕምነበረዳችን
ድንጋይ ተጠርቦበት
ያ ፅዱ ጎዳና
ተዝረክርኮልሻል
ለነገሩ ይሁን
አንቺም ሰው ጥለሻል
………………………
እናምልሽ ውዴ…
አንቺን በመውደዴ
በአውቶቡስ ፌርማታ
ባቡር ተጠበቀ
ሌባው እየኮራ
ፖሊስ ተደበቀ
ጥርስ ያለው አይስቅም
ድዳሙ እየሳቀ
ለነገሩ ይሁን
ቀን ነግቶ ይመሻል
እንኳን ሌላው ቀርቶ
አንቺም የኔዋ ጉድ
የኔን ልብ ሰርቀሻል
………………………
እናምልሽ ውዴ…
አንቺን በመውደዴ
በዝግ ቤት ውስጥ ሆኜ
ብጠብቅሽ እንኳ
..
.
ኳ
.
.
.
ኳ
.
.
.
....
በራችን ተንኳኳ!!
@getem
@getem
@getem
👍2
#የእናቴ_ልጅ_እቴን..... #አትበለኝ_እናቴ
( #አብርሀም_ተክሉ)
በብስጭቴ ልክ
የደበልኩት ፓርቲ
አንቺን እንድረሳ
በሴትነት ገላ ወንድ ግብር ያላት
ጠይም ደርባባ ሴት
መለያዬ ብሎ ፥ መፈክር አነሳ
#ይገርማል
ከሺህ ተፋቱ ባይ
ከልጅሽ ሊጋባ ከሚገባበዘው
ፍቅርና ተስፋ ፥ ከሚያቆረፍድ ሰው
እኩል ተገልብጦ ከሚርመሰመሰው
በምን ቃል አምኜ
የስጋዬን ዋጋ
ካንቺ ልቀንሰው ?
.
.
.
#አይ_ሰው.....
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@getem
( #አብርሀም_ተክሉ)
በብስጭቴ ልክ
የደበልኩት ፓርቲ
አንቺን እንድረሳ
በሴትነት ገላ ወንድ ግብር ያላት
ጠይም ደርባባ ሴት
መለያዬ ብሎ ፥ መፈክር አነሳ
#ይገርማል
ከሺህ ተፋቱ ባይ
ከልጅሽ ሊጋባ ከሚገባበዘው
ፍቅርና ተስፋ ፥ ከሚያቆረፍድ ሰው
እኩል ተገልብጦ ከሚርመሰመሰው
በምን ቃል አምኜ
የስጋዬን ዋጋ
ካንቺ ልቀንሰው ?
.
.
.
#አይ_ሰው.....
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@getem
የቸገራት
አንዳንድ ጠዋት አለ
ውበት ደፍቶብኝ ምንቃበት
እንደ ፀሀይዋ ማበራበት
እንደ ጤዛዋቹ ምጠራበት
ደግሞ በሌላ ቀን በሌላ ጠዋት
ቀጠሮ ኖሮኝ ፈልጌ ለመውጣት
ተቀብቼ ማልወዛበት
ተሽቀርቅሬ ማልደምቅበት
አለ የቀን ክፉ የቀን ልክፍት።
ኩሽና ስውል አሳምሮኝ
ልታይ ስል ሚደብቀኝ
የቀንማ ምቀኛ አለኝ።
ብሄድ እንኳን ችላ ብዪ
ምንው ጠቆርሽ ተጎሳቆልሽ
...........................ጎሽ!
ከቀኑ ማሽቃበጥ የነሱ ተዳምሮ
በዚጋ ወሬያቸው በዚያ የመልኬ ጉዳይ ናላዬን አዙሮ
መበሳጨት ጀምራለው
መስታወት ፊት እቆማለው
ኩሌን ሊፒስቲኬን ሁሉንም ጠርጋለው
ልብሴን እጥላለው
የኩሽና ልብሴን መልሼ ለብሳለው
በድጋሚ ሄጄ መስታወት አያለው
.............. አቤት ሳምር!
ለውበት አይደል ወይ ይህ ሁሉ መዳከር
በቃ ይቅራ ታድያ አልቀባ አልሽቀርቀር
ኩሽና ልቅጠርህ እባክህ እንዳትቀር።
✍hami
@getem
@getem
@getem
አንዳንድ ጠዋት አለ
ውበት ደፍቶብኝ ምንቃበት
እንደ ፀሀይዋ ማበራበት
እንደ ጤዛዋቹ ምጠራበት
ደግሞ በሌላ ቀን በሌላ ጠዋት
ቀጠሮ ኖሮኝ ፈልጌ ለመውጣት
ተቀብቼ ማልወዛበት
ተሽቀርቅሬ ማልደምቅበት
አለ የቀን ክፉ የቀን ልክፍት።
ኩሽና ስውል አሳምሮኝ
ልታይ ስል ሚደብቀኝ
የቀንማ ምቀኛ አለኝ።
ብሄድ እንኳን ችላ ብዪ
ምንው ጠቆርሽ ተጎሳቆልሽ
...........................ጎሽ!
ከቀኑ ማሽቃበጥ የነሱ ተዳምሮ
በዚጋ ወሬያቸው በዚያ የመልኬ ጉዳይ ናላዬን አዙሮ
መበሳጨት ጀምራለው
መስታወት ፊት እቆማለው
ኩሌን ሊፒስቲኬን ሁሉንም ጠርጋለው
ልብሴን እጥላለው
የኩሽና ልብሴን መልሼ ለብሳለው
በድጋሚ ሄጄ መስታወት አያለው
.............. አቤት ሳምር!
ለውበት አይደል ወይ ይህ ሁሉ መዳከር
በቃ ይቅራ ታድያ አልቀባ አልሽቀርቀር
ኩሽና ልቅጠርህ እባክህ እንዳትቀር።
✍hami
@getem
@getem
@getem
♡ ፨ ፧ « ምንነት » ፧ ፨ ♡
.
በ (ቾንድሮስ ) . A
.
አብረን በዋልንበት - በሄድንበት ሁሉ
ካንቺ ጋራ ያዩኝ - ያልገባቸው ውሉ
ምኗ ነው እያሉ - ሰው ይጠይቃሉ።
.
እናምልሽ ውዴ
.
ምኗ ነው እያሉ - ለሚጠራጠሩ
ስለኔ ምንነት - አውቀው እንዲኖሩ
ከቻልሽ አስረጃቸው - ገልፀሽ በአጭሩ።
.
እሱ ማለት ለኔ - ገና ከጅምሩ
በሰም የታጠረ - ቅኔ ነው ሚስጥሩ።
.
ቅኔ ማለት ደግሞ - የማይታይ ጌጡ
ተዘርፎ የማያልቅ - ወርቅ አለ በውስጡ
ለሱ ግን
.
ከሀብቱ የሚልቅ ሌላ በዚች አለም
ደስታ የሚፈጥር ምንም ይሁን ምንም
ከኔ ሳቅ የሚበልጥ አንዳች ነገር የለም።
.
መሳቅ ማለት ደስታ - ደስታ ማለት ደሞ
በልቡ ማሳ ላይ - የተዘራው ቀድሞ
የመንፈሱ ችግኝ - ስጋ ያበቀለው
የሚቀጥፈው መውደድ - ጊዜ ያበሰለው
ጣፍጦት የሚበላው የነፍሱ ፍሬ ነው።
ፍሬው ባስተሳሰብ - ዳግም የሚዘራ
የዘሩ ቅርንጫፍ - ከዕምነት የተጋራ
ፍቅር ያዳበረው - ወዳጅ የሚያፈራ
ጥሩ ጓደኛነት - በሚያጠላው ጥላ
እኔ ያስጠለለ - የሆነኝ ከለላ
አፍቅሮኝ የሚኖር - የማይመኝ ሌላ
ታማኝ ወዳጄ ነው - የዕምነቴ ኬላ።
ብለሽ አስረጃቸው
ስለኔ ምንነት - ማወቅ ተስኗቸው
ምኗ ነው ለሚሉ - ፍቅር ላልገባቸው።
@getem
@getem
@getem
.
በ (ቾንድሮስ ) . A
.
አብረን በዋልንበት - በሄድንበት ሁሉ
ካንቺ ጋራ ያዩኝ - ያልገባቸው ውሉ
ምኗ ነው እያሉ - ሰው ይጠይቃሉ።
.
እናምልሽ ውዴ
.
ምኗ ነው እያሉ - ለሚጠራጠሩ
ስለኔ ምንነት - አውቀው እንዲኖሩ
ከቻልሽ አስረጃቸው - ገልፀሽ በአጭሩ።
.
እሱ ማለት ለኔ - ገና ከጅምሩ
በሰም የታጠረ - ቅኔ ነው ሚስጥሩ።
.
ቅኔ ማለት ደግሞ - የማይታይ ጌጡ
ተዘርፎ የማያልቅ - ወርቅ አለ በውስጡ
ለሱ ግን
.
ከሀብቱ የሚልቅ ሌላ በዚች አለም
ደስታ የሚፈጥር ምንም ይሁን ምንም
ከኔ ሳቅ የሚበልጥ አንዳች ነገር የለም።
.
መሳቅ ማለት ደስታ - ደስታ ማለት ደሞ
በልቡ ማሳ ላይ - የተዘራው ቀድሞ
የመንፈሱ ችግኝ - ስጋ ያበቀለው
የሚቀጥፈው መውደድ - ጊዜ ያበሰለው
ጣፍጦት የሚበላው የነፍሱ ፍሬ ነው።
ፍሬው ባስተሳሰብ - ዳግም የሚዘራ
የዘሩ ቅርንጫፍ - ከዕምነት የተጋራ
ፍቅር ያዳበረው - ወዳጅ የሚያፈራ
ጥሩ ጓደኛነት - በሚያጠላው ጥላ
እኔ ያስጠለለ - የሆነኝ ከለላ
አፍቅሮኝ የሚኖር - የማይመኝ ሌላ
ታማኝ ወዳጄ ነው - የዕምነቴ ኬላ።
ብለሽ አስረጃቸው
ስለኔ ምንነት - ማወቅ ተስኗቸው
ምኗ ነው ለሚሉ - ፍቅር ላልገባቸው።
@getem
@getem
@getem
/////እየመቱህ ስራ/////
(ጉልላት አበበ)
.........
በህይወት ዘመንህ በስኬትህ መሀል
ለመነሳት መውደቅ ይጠበቅብሀል
ተቸገር ግድ የለም አይከፋ ልብህ
ከእንቅልፍህ ለመንቃት መተኛት አለብህ
ከፍ ብለህ ታይተህ እንድትኖር በኩራት
ይጠበቅብሀል ዝቅ ብሎ መስራት
......
ራሱን ዝቅ አድርጎ ችግር የሚፋለም
በግድ የሚሰራ እንደ ሚስማር የለም
በአናፂው ጉልበት በሀይል ተመትቶ
አይከፋም አንዴም ይሰራል ተጎድቶ
ውጤታማ እስክትሆን ፍሬ እስክታፈራ
አንተም እንደ ሚስማር እየመቱህ ስራ
(የታሰረው ልጅ)
@getem
@getem
@getem
(ጉልላት አበበ)
.........
በህይወት ዘመንህ በስኬትህ መሀል
ለመነሳት መውደቅ ይጠበቅብሀል
ተቸገር ግድ የለም አይከፋ ልብህ
ከእንቅልፍህ ለመንቃት መተኛት አለብህ
ከፍ ብለህ ታይተህ እንድትኖር በኩራት
ይጠበቅብሀል ዝቅ ብሎ መስራት
......
ራሱን ዝቅ አድርጎ ችግር የሚፋለም
በግድ የሚሰራ እንደ ሚስማር የለም
በአናፂው ጉልበት በሀይል ተመትቶ
አይከፋም አንዴም ይሰራል ተጎድቶ
ውጤታማ እስክትሆን ፍሬ እስክታፈራ
አንተም እንደ ሚስማር እየመቱህ ስራ
(የታሰረው ልጅ)
@getem
@getem
@getem
*ምንም አልል *
(ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን)
እሺ እንግዲህ በዝምታ
የልቤን ደም ሥር ትርታ
በደቂቃ ዕድሜን ትዝታ
ትር ስትል አፍታ ለአፍታ
እያዳመጥኩ እያስታመምኩ ጊዜዬን እያሰላሰልኩ
ሳልናገር ሳልጋገር፤ እየደገምኩ እያሰለሰልኩ
ሰልሰለች እየመላለስኩ ..........
እሺ እንግዲህ በጸጥታ
የልቤን ደም ሥር ትርታ
የእስትንፋሴን ቃል ጉምጉምታ
ትር ስትል አፍታ ለአፍታ
ሳልሰለቸ እየደጋገምኩ
በእግረ ሕልና እያደቀቅኩ
እየቋጠርኩ እየቆጠርኩ
እሺ እንግዲህ አልናገርም
በአንደበቴ አልተነፍስም
በልሳኔ አልመሰክርም
አልልም፡፡ ምንም አልልም
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም ዝም ............
የልቤ ደም ሥር ሲያቃጭል
ልሳኔን ሲያስነሳ ሲያስጥል
ቃላቴን ሲቃኝ ሲያጋግል
ትንፋሼን ሲያንር ሲያደውል
ክል ሲል ትር ድም ሲል
ማዳመጥ ማስታመም እንጅ ፤ ሌላ ምንም ምንም አልል
@getem
@getem
(ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን)
እሺ እንግዲህ በዝምታ
የልቤን ደም ሥር ትርታ
በደቂቃ ዕድሜን ትዝታ
ትር ስትል አፍታ ለአፍታ
እያዳመጥኩ እያስታመምኩ ጊዜዬን እያሰላሰልኩ
ሳልናገር ሳልጋገር፤ እየደገምኩ እያሰለሰልኩ
ሰልሰለች እየመላለስኩ ..........
እሺ እንግዲህ በጸጥታ
የልቤን ደም ሥር ትርታ
የእስትንፋሴን ቃል ጉምጉምታ
ትር ስትል አፍታ ለአፍታ
ሳልሰለቸ እየደጋገምኩ
በእግረ ሕልና እያደቀቅኩ
እየቋጠርኩ እየቆጠርኩ
እሺ እንግዲህ አልናገርም
በአንደበቴ አልተነፍስም
በልሳኔ አልመሰክርም
አልልም፡፡ ምንም አልልም
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም ዝም ............
የልቤ ደም ሥር ሲያቃጭል
ልሳኔን ሲያስነሳ ሲያስጥል
ቃላቴን ሲቃኝ ሲያጋግል
ትንፋሼን ሲያንር ሲያደውል
ክል ሲል ትር ድም ሲል
ማዳመጥ ማስታመም እንጅ ፤ ሌላ ምንም ምንም አልል
@getem
@getem