ግጥም ብቻ 📘
67.3K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
175 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
#አንድ_ያለኝን
:
ሀገሩን ከልሎ...
መግዛቱ ሳያንሰው ፣ ይሄ ዲያስፖራ
ሊቀማኝ ይጥራል ፣ የልብሽን ስፍራ

ሯ!


Ezana Mesfin

@getem
@getem
@lula_al_greeko
ከፍቅር በላይ
<unknown>
ርዕስ : ከ ፍቅር በላይ
ገጣሚ : ሄኖክ ብርሃኑ
አንባቢ : ሙሴ @moss1234567

@getem
@getem
ገደለ ሁሉ አቸናፊ ነው ወይ?
የተገደለውስ ተቸናፊ ነው ወይ?
ጊዜማ ከሰጠ
ቅል ድንጋ ይሰብራል
ቅቤ ጦር ይከላል
ኩበት ጋሻ ያልፋል
ሳር ሰይፍ ይመክታል
ጊዜማ ከሰጠ
በእልፍ ፈሪ መሀል አንድ ጀግና ካለ
ፈሪ ጎሽ ይባላል ጀግና እየገደለ፡፡
ግን ………………………….?
የገደለ ሁሉ አቸናፊ ነው ወይ?
የተገደለውስ ተቸናፊ ነው ወይ?
ፈሪማ ፈሪ ነው
ቁሞለት ነው እንጅ ጊዜ ለሱ ታጥቆ
ሙት እንኳን አያምንም ይቀብራል አርቆ
ፈሪማ ፈሪ ነው
ፈሪማ ከንቱ ነው
ፈሪማ ………………..
ፈሪማ …………………
በጀግና አባት ሀውልት ሰደድ እየተፋ
የሱን ስም ይፅፋል ታሪክ እያጠፋ፡፡

/ሃይሉ ካሳው አዳነ/
@getem
@getem
@lula_al_greeko
👍1
የአንድ ወር ተግባራዊ የህይወት መምሪያ ስልጠና።

-የህይወትን አላማ ማግኘት
-የስሜት ብልህነት
-ችግሮችን መፍታት
-ጭንቀትንና ፍርሀትን መቀነስ ማስወገድ እና ሌሎችም ስልጠናዎችን ያካተተ ነው።

ልምድ ባላቸው ሳይኮሎጂስቶችና የህይወት ክህሎት አሰልጣኞች ይምጡ ይሰልጥኑ።

ሁሉንም ስልጠናዎች ለተካፈለ በነፃ የንግግር ክህሎት ስልጠና ሰርተፊኬትን ጨምሮ ያገኛል።

ለበለጠ መረጃ
0946333951
0912664084 ይደውሉ።

ህዳር 20 ይጀምራል

👇👇👇👇
@temuabiy
@temuabiy
@temuabiy
በ2011 በ10ኛ ክፈል ማትሪክ 4 ነጥብ ወይንም በሁሉም ትምህርቶች " A " ያስመዘገበው ተማሪ የአንጒል ካንሰር ሰለባ ሆነ።
የ17 ዓመቱ ወጣት ተማሪ ናትናኤል አብርሀም ጊዒምሶ ባጋጠመው ህመም ምክንያት በአስቸኳይ ወደ ውጪ ሀገር እንዲሄድ ስለታዘዘ የህክምናው ወጪ ግዝፈት የተነሳ ቤተሰቦቹ ለማሳከም ስለማይችሉ ይህንን የነገ ሀገር ተረካቢ የሆነውን ወጣት ለማትረፍ በመላው ዓልም የሚገኙ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በፍጥነት ተረባርበን ከፈጣሪ በታች የተቻለንን በማድረግ እንታደገው።

#share 🙏መርዳት ለምትፈልጉ ስልክ ቁጥር የእናቱ +251984786575
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ : 1000187671907

ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው።
#ሳትመጪ_ነይ !

የጀመርሽው መንገድ ፥ ጉዞሽ እንዲቃና
በስሌት ተራመጅ ፥ ስሜቱን ተይና፣
ከልካይ የለም ብለሽ ፥ አቲጅ በመደዳው
ፈንጂ ወረዳ ነው ፥ የጨዋታ ሜዳው፣
ይልቅ ኳሷን ላኪያት ፥ ትሂድ ቃልሽን ሰምታ
ከነ ሙሉ አካልሽ ፥ ህልምሽ ግቡን ይምታ።
-----------------------//------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@lula_al_greeko
እኔ ብቻ ቀረሁ
( #ካፒቴን ናትናኤል ጌቱ )

ስንት ሐመሩ "ሐ" ዎች
በሐመር መኪና ፥ ተንደላቀው ሲያልፉ
ስንት ፎሌው "ሀ" ዎች
በወርቃማ ዋንጫ ፥ ውስኪ ሲጨልፉ
ስንት ንጉስ "ኃ" ዎች
ከመሬት ተነስተው ፥ ዙፋኑን ሲወርሱ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
በድሮ ልብና
በድሮ ሽክና ፥ ተከብቤ እንደቆምኩ
ጠላ ትዝታሽን
በፎሌ ተግቼ ፥ እየተንገዳገድኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! እኔ ብቻ ተከዝኩ!!
ያውና! … ያውና !
አለምነሽ ካሳነሽ
እንደተሳፈሩት ፥ የድሮ መኪና
ጭሱ ቦለል ይላል ፥ የቤቴ ኩሽና
አንቺኮ የለሽም ፥ ቤቴ ምን ነክቶታል ?
ብቸኛው ርስቴን ፥ በቃ አቃጥለውታል !!
እኔ ብቻ ቀረሁ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ሰባራ ፍቅርሽን ፥ እንደተመረኮዝኩ
ስንት ንጉስ "ሰ" ዎች
ንጉሱ "ኃ" ዎችን ፥ ሊጥሉ ሲነሱ
ስንት እሳቱ "ሰ"ዎች
አመፅ ለማስነሳት ፥ እሳት ሲለኩሱ
ስንት አለሙ "ዓ" ዎች
በደስታ ሲሰክሩ ፥ ቡጊ ሲደንሱ
አንገቴን ደፍቼ ፥ ከልቤ እያነባሁ
እኔ ብቻ ከፋኝ ፥ እኔ ብቻ ባባሁ!
ካንዲት ተራ ወንበር ፥ ቂጤ ተዘፍዝፎ
ጨቡዴና አማረ ፥ ካስተረፉት ገንፎ
እጄን እየሰደድኩ
በጎዳናው መሀል
ሺዎች ሲቀየሩ እየተመለከትኩ
እንጃ ማን እንደሆን ሽቶ የረጫቸው
ስንት ሐመሯ "ሐ" ዎች ሸክላ ከንፈራቸው
ሊፒስቲክ ተቀብቶ
ጫላ ጩቤ ጥሎ ፥ ዲሞፍተር አንስቶ
አድጎ ተመንድጎ ፥ ማሙሽ ምግብ በልቶ
እኔ ብቻ ከፋኝ
ትውስታሽ ተጠጋኝ ፥ ትዝታሽ ደረሰ
እሽሩሩ ፍቅር
እንባዬ እንደ ካሮት ፥ ቁልቁል ገሰገሰ
እኔ ብቻ ቀረሁ
የቡሄ በአልን ፥ ድፎ ሳላስደፋ
ራሴው ተደፍቼ
ሙስሊም ወንድሞቼ
ተምሩ በቅቷቸው ፥ ታምር ሲመገቡ
መካን ሊያዩ ወተው ፥ ዱባይ ሲያንጃብቡ
የረመዳን ጦሜን ፥ በውሀ እያፈጠርኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ያውና ያውና
ፊደል በሚመስል ፥ የህይወት ጎዳና
እነ ጸሎቱ "ጸ" ፥ ለስግደት ተደፍተው
ስለታቸው ሰምሮ ፥ ጭፈራ ቤት ከፍተው
ስንት አይናማው "ዐ" ዎች ፥ ባንድ አይናቸው ጠቅሰው
ከቆንጆ ተጣብሰው ፥ ቆንጆ ልጅ ወለዱ
እኔ ብቻ ጎደልኩ ፥ ከደስታ መንገዱ
እኔ ብቻ ዋተትኩ
እኔ ብቻ አዘንኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ
ፊደል ከሚመስለው ፥ የህይወት ገበታ
ነይ ታገኚኛለሽ
የዛሬ ሺ አመታት ፥ ካስቀመጥሺኝ ቦታ
እኔ ብቻ ቀረሁ…


@lula_al_greeko
@getem
@getem
👍1
#2 second round registration 😍😱 guys dont miss this opportunity only you have 11 days for this round read it carefully ** nadbis film production

ምንድነው ችሎታዎ? ?? ፀሐፊነት፣ገጣሚነት ፣ድምፃዊ ፣ ሰዓሊ ፣አቀናባሪ ፣ ሜካብ አርቲስት ፣ ቅርፃ ቅርፅ ፣ጋዜጠኝነት ፣ ዳንስ ፣ውዝዋዜ ፣ስዕል ፣ ግራፊክስ ዲዛይነር ፣ትወና ፣ ሞዴሊንግ ፣ ፎቶግራፍ ፣ አነቃቂ ንግግር.... ማንኛውም አይነት የጥበብ አቋም በጎ አድራጊያንን እናበረታታለን
ለአባልነት ምንፈልገው የትምህርት ማስረጃ እና መታወቂያ ብቻ ነው
ለበለጠ @kidusdan
0991739273
*-*ይፍጠኑ በነፃ ሰልጥነው ስራዎን በነፃ ሰርተን ከህልሞ ጋር እናገናኞት::
*ወጪዎን ሸፍነን በ አለም አቀፍ ደረጃ እናስተዋውቆ ስራዎም ተደራሽ ይሁን
*አሁንም ሰዓታት አሉ የራሳችሁን ራዕይ ያዙ ግባችሁን ለመምታት ናድቢስ ድልድይ ይሁናችሁ
inbox and register online @kidusdan
check our work @nadabis
ልቤና አዕምሮዬን ቦታ አቀያይሬ
በልቤ እያሰብኩኝ በአዕምሮዬ አፍቅሬ
ለፍቅር አዲስ ስሌት እራሴው ቀምሬ
ከሀሳቤ ጭን ስር አለው ተቀብሬ።

ከ yafet

@getem
@getem
* ባዶነት*

አምቄ በውሥጤ
ሺ ሀሜት
ሺ ቅናት
ሆኖብኝ መንገዴ
የ ርኩሠት
የ ዝሙት
ሥጨነቅ እየዋልኩ
ለሥጋ ለሆዴ
ሣልፆም አርብ እና እሮብ
ገና እና ሁዳዴ

ቄሥ ባገኘሁ ቁጥር
ይባርኩኝ እላለሁ
ብሩክ ሣይታሠብ
መባረክ የት አየሁ??


©marry

@getem
@getem
..........የስርቆሽ_ሱስ..........
.
ከሩቅ አሻግሬ ሰርቄ ሳያት ነው
ልቤን ደስ የሚላት
እባክህ አምላኬ የምወዳትን ልጅ
ጎረቤቴ ያግባት?!!

😁
-------------------------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@gebriel_19
" ንቦ...ተቀበይ"
--------//--------
በገዛ ቀዬዬ
......ከተክሌ ቀስመሽ፣
ደፋ ቀና ስትይ
.......ስታሴሪ ከርመሽ፣
በተስፋ እየኖርኩ
........ባንቺ ተማምኜ፣
ህልሜ ቅዠት ሲሆን
.......አመድ አፋሽ ሆኜ፣
ከሰው ድንበር ዉለሽ
........ ዘልቀሽ ከየቀፎ፣
አንቺ በቀሰምሺው
....መንጋው ሲያልቅ ተናድፎ፣
በስውር ክፋትሽ
........እጭሽ እየተላ፣
ካመረትሽው ግግር
........የግፍ ማር ወለላ፣
ጠዋት ያኖርሽውን
.........ስትልሽው ማታ፣
ለኖርሽበት ጎጆ
.........ላትከፍይ ውለታ፣
የንብ ወጉ ጠፍቶሽ
.........ከምትቀመጪ፣
ማርሽ ይቅር ወዲያ
........ቀፎዬን ግን አምጪ።
----------//---------
© ሚራጅ ጁሃር: 2010 ዓ.ም።

@getem
@getem
ምሪን ያልናት ጥንቸል ሄደች እኛን ጥላ
ኤሊም አልበጀንም ይዞን ቀረ ኀላ፣
ገራም ሰው ላክልን እንደ በቅሎ ሰጋር
ከጎናችን ሆኖ የሚጓዝ ከ'ኛ ጋር !!!!!
------------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@gebriel_19
ለምሽታችን
💚 ከወርቆቼ ገጣሚያን እና ግጥሙ ለምሽት ምርጥ ጀባታ እንካቹ


ከኒህ ሁለቱ መካከል
---------------------------
(ነቢይ መኮንን)
ያሸነፍን ሲመስለን
መሸነፍን እንረሳለን።
የተሸነፍን ሲመስለን
ማሸነፍ የእኛም አይመስለን።
አንድ ቀን ግዴላችሁም፣ ነገር በውል ሲገባን ግን
ከኒህ ሁለቱ መካከል፣ አንድ አዲስ ልጅ እንወልዳለን!!
(ለአሸናፊና ተሸናፊ ኢትዮዽያውያን)
-----------------------
ነሐሴ 24/1998

@getem
@getem
@balmbaras
👍1
Rediet Aseffa
.
.
ሟርተኛ ሳንሰኝ፥ ወይ ታሪክ ተራኪ
ወይ ሳንባል ነብይ፥ ወይ ዘገባ አርቃቂ
መች እንበል እግዚዖ? መች እንበል አያድርስ?
መካብ ሲጀምሩን፥ ወይስ ሲነካኩን? ወይስ ስንፈራርስ?
.
.
ሲጀምሩን መካብ?
ሲደላደልልን፥ ጫንቃቸው እንደእርካብ
ወይ ሲርገፈገፉ?
ያተሰመረውን፥ ድንበሩን ሲገፉ?
.
.
ወይስ ስንፈራርስ?
መች እንበል እግዚዖ? መች እንበል አያድርስ?

@getem
@getem
@gebriel_19
ጎጠኝነት ከቦኝ
ዘረኝነት ከቦኝ
ጥለሽኝ ስቴጂ፣
ያንቺን ፍቅር ነበር ተስፋ ያደረኩት
አንቺ ካድሽኝ እንጂ፣
ምናለ ስቴጂ፣
እያየሽ ሲከበኝ ግሳንግሱ ሁሉ፣
ባይነ ስጋ ባይታዩ መላዕክቶች አሉ፣
....ብለሽ ጠባቂ ሳትቀጥሪ፣
ፍርሃቴ በዝቷል
አንድ ሁለት ጠባቂ ያንሰኛል ጨምሪ፣

ሳሙኤል አለሙ
@Sazi5


@getem
@getem
……ህልሜን አደራ!
((በውቀቱ ስዩም))

ባይመረመሬ ፥ ጥበብ ተሽከርክሮ
ከወርቃማ ብርሃን ፥ ከብርማ ፀዳል
የተሰራ ሸማ ፥ ማግኘት ብችል ኖሮ
ከውብ እግሮችሽ ስር ፥ እዘረጋው ነበር
ግና ምንም የለኝ ፥ ከህልሞቼ በቀር፤
:
የኔ ውድ እንግዲህ
ህልሜን እግሮችሽ ስር ፥ ከዘረጋሁ ወዲህ
ዝግ ብለሽ እርገጪ ፥ ዝግ ብለሽ ሂጂ
ህልሜ ላይ ነውና ፥ የምትራመጂ።

°°°°°°° የማለዳ ድባብ °°°°°°°

@getem
@gebriel_19
ሸክም
ቀንበር ጭነውብኝ
የውሸት
የክህደት
እንዴት ደግ ላስብ
ጥሩነት ከየት ይምጣ
ሕይወት ራሷ መራ
ሆናብኝ ኮምጣጣ
ሸክሟ ራሱ ከብዶኝ
አቅቶኝ መሸከም
የነሱ ሲጨመር
ከበደኝ መቋቋም
ከታምሀዊ

@getem
@getem
ለጁምኣችን!
💚

በኅዳር ውስጥ እኔን
.....
ተወው
ቆሻሻህን ተወው
ከሳቱ ዳር እራቅ
ጭለማን ልበሰው
ጥቁር ካባ ደርብ
ዓይንህ ይጨልመው፡፡
ግዴለህም ተወው……
እቤትህ ግባና፤
ዓይንህን ጨፍነህ
ስላሳመምካቸው፣ስላቆሰልካቸው
ነፍሳት አስብና፤
ራስህን ክሰስ፤ራስህን ውቀስ
ራስህን አጥን
ተረማመድበት በንፁሀን ፋና፡፡
.....
ማጠን እራስን ነው!
መንፈስን ለማንጻት
ልቦናን ለማጽዳት
ቅዱስ ሰው ለመሆን
እኩይ ምኞቶችን ማቃጠል በእሳት፡፡
……..
የለበስነው ያልፈተልነው
የለቀምነው ያልዘራነው
የነቀልነው ያልተከልነው
አለ … አለ …አለ
ይኼንን ነው ማጽዳት
ይኼንን ነው ማንጻት፡፡
…..
(እንዳለጌታ ከበደ፤ልብ ሲበርደው)

ሸጋ ጁምኣ!💚

@getem
@getem
@getem