እኔ ብቻ ቀረሁ
( #ካፒቴን ናትናኤል ጌቱ )
…
ስንት ሐመሩ "ሐ" ዎች
በሐመር መኪና ፥ ተንደላቀው ሲያልፉ
ስንት ፎሌው "ሀ" ዎች
በወርቃማ ዋንጫ ፥ ውስኪ ሲጨልፉ
ስንት ንጉስ "ኃ" ዎች
ከመሬት ተነስተው ፥ ዙፋኑን ሲወርሱ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
በድሮ ልብና
በድሮ ሽክና ፥ ተከብቤ እንደቆምኩ
ጠላ ትዝታሽን
በፎሌ ተግቼ ፥ እየተንገዳገድኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! እኔ ብቻ ተከዝኩ!!
ያውና! … ያውና !
አለምነሽ ካሳነሽ
እንደተሳፈሩት ፥ የድሮ መኪና
ጭሱ ቦለል ይላል ፥ የቤቴ ኩሽና
አንቺኮ የለሽም ፥ ቤቴ ምን ነክቶታል ?
ብቸኛው ርስቴን ፥ በቃ አቃጥለውታል !!
እኔ ብቻ ቀረሁ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ሰባራ ፍቅርሽን ፥ እንደተመረኮዝኩ
ስንት ንጉስ "ሰ" ዎች
ንጉሱ "ኃ" ዎችን ፥ ሊጥሉ ሲነሱ
ስንት እሳቱ "ሰ"ዎች
አመፅ ለማስነሳት ፥ እሳት ሲለኩሱ
ስንት አለሙ "ዓ" ዎች
በደስታ ሲሰክሩ ፥ ቡጊ ሲደንሱ
አንገቴን ደፍቼ ፥ ከልቤ እያነባሁ
እኔ ብቻ ከፋኝ ፥ እኔ ብቻ ባባሁ!
ካንዲት ተራ ወንበር ፥ ቂጤ ተዘፍዝፎ
ጨቡዴና አማረ ፥ ካስተረፉት ገንፎ
እጄን እየሰደድኩ
በጎዳናው መሀል
ሺዎች ሲቀየሩ እየተመለከትኩ
እንጃ ማን እንደሆን ሽቶ የረጫቸው
ስንት ሐመሯ "ሐ" ዎች ሸክላ ከንፈራቸው
ሊፒስቲክ ተቀብቶ
ጫላ ጩቤ ጥሎ ፥ ዲሞፍተር አንስቶ
አድጎ ተመንድጎ ፥ ማሙሽ ምግብ በልቶ
እኔ ብቻ ከፋኝ
ትውስታሽ ተጠጋኝ ፥ ትዝታሽ ደረሰ
እሽሩሩ ፍቅር
እንባዬ እንደ ካሮት ፥ ቁልቁል ገሰገሰ
እኔ ብቻ ቀረሁ
የቡሄ በአልን ፥ ድፎ ሳላስደፋ
ራሴው ተደፍቼ
ሙስሊም ወንድሞቼ
ተምሩ በቅቷቸው ፥ ታምር ሲመገቡ
መካን ሊያዩ ወተው ፥ ዱባይ ሲያንጃብቡ
የረመዳን ጦሜን ፥ በውሀ እያፈጠርኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ያውና ያውና
ፊደል በሚመስል ፥ የህይወት ጎዳና
እነ ጸሎቱ "ጸ" ፥ ለስግደት ተደፍተው
ስለታቸው ሰምሮ ፥ ጭፈራ ቤት ከፍተው
ስንት አይናማው "ዐ" ዎች ፥ ባንድ አይናቸው ጠቅሰው
ከቆንጆ ተጣብሰው ፥ ቆንጆ ልጅ ወለዱ
እኔ ብቻ ጎደልኩ ፥ ከደስታ መንገዱ
እኔ ብቻ ዋተትኩ
እኔ ብቻ አዘንኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ
ፊደል ከሚመስለው ፥ የህይወት ገበታ
ነይ ታገኚኛለሽ
የዛሬ ሺ አመታት ፥ ካስቀመጥሺኝ ቦታ
እኔ ብቻ ቀረሁ…
@getemsource
@getem
@getem
( #ካፒቴን ናትናኤል ጌቱ )
…
ስንት ሐመሩ "ሐ" ዎች
በሐመር መኪና ፥ ተንደላቀው ሲያልፉ
ስንት ፎሌው "ሀ" ዎች
በወርቃማ ዋንጫ ፥ ውስኪ ሲጨልፉ
ስንት ንጉስ "ኃ" ዎች
ከመሬት ተነስተው ፥ ዙፋኑን ሲወርሱ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
በድሮ ልብና
በድሮ ሽክና ፥ ተከብቤ እንደቆምኩ
ጠላ ትዝታሽን
በፎሌ ተግቼ ፥ እየተንገዳገድኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! እኔ ብቻ ተከዝኩ!!
ያውና! … ያውና !
አለምነሽ ካሳነሽ
እንደተሳፈሩት ፥ የድሮ መኪና
ጭሱ ቦለል ይላል ፥ የቤቴ ኩሽና
አንቺኮ የለሽም ፥ ቤቴ ምን ነክቶታል ?
ብቸኛው ርስቴን ፥ በቃ አቃጥለውታል !!
እኔ ብቻ ቀረሁ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ሰባራ ፍቅርሽን ፥ እንደተመረኮዝኩ
ስንት ንጉስ "ሰ" ዎች
ንጉሱ "ኃ" ዎችን ፥ ሊጥሉ ሲነሱ
ስንት እሳቱ "ሰ"ዎች
አመፅ ለማስነሳት ፥ እሳት ሲለኩሱ
ስንት አለሙ "ዓ" ዎች
በደስታ ሲሰክሩ ፥ ቡጊ ሲደንሱ
አንገቴን ደፍቼ ፥ ከልቤ እያነባሁ
እኔ ብቻ ከፋኝ ፥ እኔ ብቻ ባባሁ!
ካንዲት ተራ ወንበር ፥ ቂጤ ተዘፍዝፎ
ጨቡዴና አማረ ፥ ካስተረፉት ገንፎ
እጄን እየሰደድኩ
በጎዳናው መሀል
ሺዎች ሲቀየሩ እየተመለከትኩ
እንጃ ማን እንደሆን ሽቶ የረጫቸው
ስንት ሐመሯ "ሐ" ዎች ሸክላ ከንፈራቸው
ሊፒስቲክ ተቀብቶ
ጫላ ጩቤ ጥሎ ፥ ዲሞፍተር አንስቶ
አድጎ ተመንድጎ ፥ ማሙሽ ምግብ በልቶ
እኔ ብቻ ከፋኝ
ትውስታሽ ተጠጋኝ ፥ ትዝታሽ ደረሰ
እሽሩሩ ፍቅር
እንባዬ እንደ ካሮት ፥ ቁልቁል ገሰገሰ
እኔ ብቻ ቀረሁ
የቡሄ በአልን ፥ ድፎ ሳላስደፋ
ራሴው ተደፍቼ
ሙስሊም ወንድሞቼ
ተምሩ በቅቷቸው ፥ ታምር ሲመገቡ
መካን ሊያዩ ወተው ፥ ዱባይ ሲያንጃብቡ
የረመዳን ጦሜን ፥ በውሀ እያፈጠርኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ያውና ያውና
ፊደል በሚመስል ፥ የህይወት ጎዳና
እነ ጸሎቱ "ጸ" ፥ ለስግደት ተደፍተው
ስለታቸው ሰምሮ ፥ ጭፈራ ቤት ከፍተው
ስንት አይናማው "ዐ" ዎች ፥ ባንድ አይናቸው ጠቅሰው
ከቆንጆ ተጣብሰው ፥ ቆንጆ ልጅ ወለዱ
እኔ ብቻ ጎደልኩ ፥ ከደስታ መንገዱ
እኔ ብቻ ዋተትኩ
እኔ ብቻ አዘንኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ
ፊደል ከሚመስለው ፥ የህይወት ገበታ
ነይ ታገኚኛለሽ
የዛሬ ሺ አመታት ፥ ካስቀመጥሺኝ ቦታ
እኔ ብቻ ቀረሁ…
@getemsource
@getem
@getem
እኔ ብቻ ቀረሁ
( #ካፒቴን ናትናኤል ጌቱ )
…
ስንት ሐመሩ "ሐ" ዎች
በሐመር መኪና ፥ ተንደላቀው ሲያልፉ
ስንት ፎሌው "ሀ" ዎች
በወርቃማ ዋንጫ ፥ ውስኪ ሲጨልፉ
ስንት ንጉስ "ኃ" ዎች
ከመሬት ተነስተው ፥ ዙፋኑን ሲወርሱ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
በድሮ ልብና
በድሮ ሽክና ፥ ተከብቤ እንደቆምኩ
ጠላ ትዝታሽን
በፎሌ ተግቼ ፥ እየተንገዳገድኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! እኔ ብቻ ተከዝኩ!!
ያውና! … ያውና !
አለምነሽ ካሳነሽ
እንደተሳፈሩት ፥ የድሮ መኪና
ጭሱ ቦለል ይላል ፥ የቤቴ ኩሽና
አንቺኮ የለሽም ፥ ቤቴ ምን ነክቶታል ?
ብቸኛው ርስቴን ፥ በቃ አቃጥለውታል !!
እኔ ብቻ ቀረሁ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ሰባራ ፍቅርሽን ፥ እንደተመረኮዝኩ
ስንት ንጉስ "ሰ" ዎች
ንጉሱ "ኃ" ዎችን ፥ ሊጥሉ ሲነሱ
ስንት እሳቱ "ሰ"ዎች
አመፅ ለማስነሳት ፥ እሳት ሲለኩሱ
ስንት አለሙ "ዓ" ዎች
በደስታ ሲሰክሩ ፥ ቡጊ ሲደንሱ
አንገቴን ደፍቼ ፥ ከልቤ እያነባሁ
እኔ ብቻ ከፋኝ ፥ እኔ ብቻ ባባሁ!
ካንዲት ተራ ወንበር ፥ ቂጤ ተዘፍዝፎ
ጨቡዴና አማረ ፥ ካስተረፉት ገንፎ
እጄን እየሰደድኩ
በጎዳናው መሀል
ሺዎች ሲቀየሩ እየተመለከትኩ
እንጃ ማን እንደሆን ሽቶ የረጫቸው
ስንት ሐመሯ "ሐ" ዎች ሸክላ ከንፈራቸው
ሊፒስቲክ ተቀብቶ
ጫላ ጩቤ ጥሎ ፥ ዲሞፍተር አንስቶ
አድጎ ተመንድጎ ፥ ማሙሽ ምግብ በልቶ
እኔ ብቻ ከፋኝ
ትውስታሽ ተጠጋኝ ፥ ትዝታሽ ደረሰ
እሽሩሩ ፍቅር
እንባዬ እንደ ካሮት ፥ ቁልቁል ገሰገሰ
እኔ ብቻ ቀረሁ
የቡሄ በአልን ፥ ድፎ ሳላስደፋ
ራሴው ተደፍቼ
ሙስሊም ወንድሞቼ
ተምሩ በቅቷቸው ፥ ታምር ሲመገቡ
መካን ሊያዩ ወተው ፥ ዱባይ ሲያንጃብቡ
የረመዳን ጦሜን ፥ በውሀ እያፈጠርኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ያውና ያውና
ፊደል በሚመስል ፥ የህይወት ጎዳና
እነ ጸሎቱ "ጸ" ፥ ለስግደት ተደፍተው
ስለታቸው ሰምሮ ፥ ጭፈራ ቤት ከፍተው
ስንት አይናማው "ዐ" ዎች ፥ ባንድ አይናቸው ጠቅሰው
ከቆንጆ ተጣብሰው ፥ ቆንጆ ልጅ ወለዱ
እኔ ብቻ ጎደልኩ ፥ ከደስታ መንገዱ
እኔ ብቻ ዋተትኩ
እኔ ብቻ አዘንኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ
ፊደል ከሚመስለው ፥ የህይወት ገበታ
ነይ ታገኚኛለሽ
የዛሬ ሺ አመታት ፥ ካስቀመጥሺኝ ቦታ
እኔ ብቻ ቀረሁ…
@lula_al_greeko
@getem
@getem
( #ካፒቴን ናትናኤል ጌቱ )
…
ስንት ሐመሩ "ሐ" ዎች
በሐመር መኪና ፥ ተንደላቀው ሲያልፉ
ስንት ፎሌው "ሀ" ዎች
በወርቃማ ዋንጫ ፥ ውስኪ ሲጨልፉ
ስንት ንጉስ "ኃ" ዎች
ከመሬት ተነስተው ፥ ዙፋኑን ሲወርሱ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
በድሮ ልብና
በድሮ ሽክና ፥ ተከብቤ እንደቆምኩ
ጠላ ትዝታሽን
በፎሌ ተግቼ ፥ እየተንገዳገድኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! እኔ ብቻ ተከዝኩ!!
ያውና! … ያውና !
አለምነሽ ካሳነሽ
እንደተሳፈሩት ፥ የድሮ መኪና
ጭሱ ቦለል ይላል ፥ የቤቴ ኩሽና
አንቺኮ የለሽም ፥ ቤቴ ምን ነክቶታል ?
ብቸኛው ርስቴን ፥ በቃ አቃጥለውታል !!
እኔ ብቻ ቀረሁ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ሰባራ ፍቅርሽን ፥ እንደተመረኮዝኩ
ስንት ንጉስ "ሰ" ዎች
ንጉሱ "ኃ" ዎችን ፥ ሊጥሉ ሲነሱ
ስንት እሳቱ "ሰ"ዎች
አመፅ ለማስነሳት ፥ እሳት ሲለኩሱ
ስንት አለሙ "ዓ" ዎች
በደስታ ሲሰክሩ ፥ ቡጊ ሲደንሱ
አንገቴን ደፍቼ ፥ ከልቤ እያነባሁ
እኔ ብቻ ከፋኝ ፥ እኔ ብቻ ባባሁ!
ካንዲት ተራ ወንበር ፥ ቂጤ ተዘፍዝፎ
ጨቡዴና አማረ ፥ ካስተረፉት ገንፎ
እጄን እየሰደድኩ
በጎዳናው መሀል
ሺዎች ሲቀየሩ እየተመለከትኩ
እንጃ ማን እንደሆን ሽቶ የረጫቸው
ስንት ሐመሯ "ሐ" ዎች ሸክላ ከንፈራቸው
ሊፒስቲክ ተቀብቶ
ጫላ ጩቤ ጥሎ ፥ ዲሞፍተር አንስቶ
አድጎ ተመንድጎ ፥ ማሙሽ ምግብ በልቶ
እኔ ብቻ ከፋኝ
ትውስታሽ ተጠጋኝ ፥ ትዝታሽ ደረሰ
እሽሩሩ ፍቅር
እንባዬ እንደ ካሮት ፥ ቁልቁል ገሰገሰ
እኔ ብቻ ቀረሁ
የቡሄ በአልን ፥ ድፎ ሳላስደፋ
ራሴው ተደፍቼ
ሙስሊም ወንድሞቼ
ተምሩ በቅቷቸው ፥ ታምር ሲመገቡ
መካን ሊያዩ ወተው ፥ ዱባይ ሲያንጃብቡ
የረመዳን ጦሜን ፥ በውሀ እያፈጠርኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ያውና ያውና
ፊደል በሚመስል ፥ የህይወት ጎዳና
እነ ጸሎቱ "ጸ" ፥ ለስግደት ተደፍተው
ስለታቸው ሰምሮ ፥ ጭፈራ ቤት ከፍተው
ስንት አይናማው "ዐ" ዎች ፥ ባንድ አይናቸው ጠቅሰው
ከቆንጆ ተጣብሰው ፥ ቆንጆ ልጅ ወለዱ
እኔ ብቻ ጎደልኩ ፥ ከደስታ መንገዱ
እኔ ብቻ ዋተትኩ
እኔ ብቻ አዘንኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ
ፊደል ከሚመስለው ፥ የህይወት ገበታ
ነይ ታገኚኛለሽ
የዛሬ ሺ አመታት ፥ ካስቀመጥሺኝ ቦታ
እኔ ብቻ ቀረሁ…
@lula_al_greeko
@getem
@getem
👍1