ዐውደ ምሕረት
3.67K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
ኢኦተቤ02_05.amr
605.6 KB
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን_ታሪክ

#ክፍል አሥራ አራት

#በመምህር #ማርቆስ አለማየሁ

#ይዘት
👉 የእስልምና መነሳት፣ የእስላም ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ መግባትና ቤተ ክርስቲያን ላይ ያመጣው ተጽዕኖ
👉 የዮዲት ጉዲት ቤተ ክርስቲያን ላይ ያደረሰችው ጥፋት

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ኢኦተቤ02_06.amr
690.3 KB
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን_ታሪክ

#ክፍል አሥራ አምስት

#በመምህር #ማርቆስ አለማየሁ

#ይዘት
👉 የመራ ተክለሃይማኖት (ዛግዌ) መነሳት ጠጠውድም ጃንስዩምና ግርማ ስዩም
👉 አራቱ ቅዱሳን ነገሥት

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ኢኦተቤ02_09.amr
809.2 KB
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን_ታሪክ

#ክፍል አሥራ ስምንት

#በመምህር #ማርቆስ አለማየሁ

#ይዘት
👉 ቤተ ክርስቲያን በአጼ አምደ ጽዮን ዘመን አባ ኤዮስጣጥዮስ፣ አባ መድኃኒነ እግዚእ እና አባ በጸሎተ ሚካኤል

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ኢኦተቤ04_1.mp3
791.3 KB
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን_ታሪክ

#ክፍል ሀያ ሁለት

#በመምህር #ማርቆስ አለማየሁ

#ይዘት
👉ምዕራፍ አራት
የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከአጼናዖድ በኋላ (በ፰ኛው ሺህ)
ቤተክርስቲያን በዘመነ አጼ ልብነ ድንግል የቤተክርስቲያን ታላቅ ፈተና (የግራኝ ወረራ)


#ከትምህርቱ የተወጣጡ ጥያቄዎች

1 የግራኝ ወረራ ቤተ ክርስቲያናችን ላይ ያደረሰው ተጽዕኖ ምን ነበር?
2 አጼ ልብነ ድንግል ለቤተክርስቲያን ያደረጉት አስተዋጽኦ ምን ነበር?

መልሶቻችሁን እና አስተያየታችሁን
@Abenma እና @Midyam ላይ ያድርሱን።

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ኢኦተቤ04_2.mp3
1.3 MB
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን_ታሪክ

#ክፍል ሀያ ሦስት

#በመምህር #ማርቆስ አለማየሁ

#ይዘት
👉 ቤተ ክርስቲያን ከአጼ ገላውዴዎስ እስከ አጼ ፋሲል


#ከትምህርቱ የተወጣጡ ጥያቄዎች

1 ቤተ ክርስቲያን በዘመነ አጼ ገላውዴዎስ የገጠማት ችግር ምንድን ነበር?
2 አጼ ፋሲል ለቤተክርስቲያን ያደረጉት አስተዋጽኦ ምን ነበር?

መልሶቻችሁን እና አስተያየታችሁን
@Abenma እና @Midyam ላይ ያድርሱን።

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
Audio
#ዓውደ_ስብከት

#በመምህር #ቢትወደድ_ወርቁ

"መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል።" 1ኛ ጢሞ 6:12

ገድልን ለሚቃወሙ ሰዎች የተሰጠ ትምህርትና መልስ።

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
Audio
#ዓውደ_ስብከት

#በመምህር #ቢትወደድ_ወርቁ

"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው።" ምሳ 10:7

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ገድላትን መንቀፍ መጽሐፍ ቅዱስን መንቀፍ ነው!!

ስለ ቅዱሳት መጻሕፍት አለማወቅ ጥልቅ ወደ ሆነ የክህደትና ስህተት ዐዘቅት ውስጥ ይጥላል፡፡ ጌታችን በወንጌል ‹መጻህፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ›
ማቴ 22፤29 እንዳለ፡፡ የአበው ቅዱሳንን ተጋድሎ የሚነግሩን
አዋልድ መጻሕፍት አሥራው መጻሕፍትን (መጽሐፍ ቅዱስን) ያብራራሉ ይተረጉማሉ፡፡
ለአንዳንዶች እንደሚመስላቸው ገድላት ወደ ገደል አይከቱም
ከገደል ያወጣሉ እንጂ፡፡ ገድላት የእግዚአብሔርን ቃል ለመፈጸም
እንደ ቃሉ ለመመላለስ ያግዙናል፡፡ ‹የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩዋችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሩዋቸውንም ፍሬ
እየተመለከታችሁ በእምነታችሁ ምሰሉዋቸው› ዕብ 13፤7
‹እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ› ኤፌ 5፤1
‹በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን
አስቡ› ዕብ 12 ፤ 2-5፡፡
በማለት ቅዱሳንን እንድንከተል
የሚያዙንን የልዑል ቃላት የቅዱሳኑን ታሪክ ተጋድሎ ሕይወት የሚተርክልንን ገድላቸውን ሳናነብ እንዴት መፈጸም አንችላለን?
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ፈጣሪነት ጌትነት ኃያልነት
እንደሚነግረን የቅዱሳንንም ተጋድሎ ታሪክ ተአምር በሁለት
መንገድ ይነግረናል፡፡

1ኛ ከሌሎች ታሪኮች ጋር አሰናስሎ አያይዞ ምሳሌ በዘፍጥረት የአብርሃም የይስኃቅ የሔኖክና የሌሎች ቅዱሳን ታሪክ በዘጸዐት የሙሴ የኢያሱ የካሌብ በመሳፍንት የጌድዮን የዮፍታሔ
በሐዋርያት ሥራ የሐዋርያትን የሳሙኤልን፤ የኤልሳዕን፤ የኤልያስን ፤የናቡቴን፤ የዳዊትን ፤ የሰለሞንን ታሪኮች በመጽሐፈ ነገሥት እና መጽሐፈ ሳሙኤል መጻሕፍት እናገኛለን፡፡

2ኛ የቅዱሳኑን ታሪክ ለብቻው ምሳሌ መጽሐፈ አስቴር የአስቴርን ታሪክ፤ መጽሐፈ ኢዮብ የኢዮብን ታሪክ ፤ መጽሐፈ ሩት የሩትን ታሪክ ፤ መጽሐፈ ጦቢት የጦቢትን ታሪክ ይነግረናል:: መጽሐፍ ቅዱስ የቅዱሳንን ታሪክ እንድናነብ አዋልድ መጻሕፍትን
አንድንመለከት ይጋብዘናል። ለዚህ አስረጂ የሚሆኑን ጥቂት ኃይለ ቃላትትን ለማየት
‹የቀረውም የሰለሞንን ነገር ያደረገውም ሁሉ ጥበቡም እነሆ በሰሎሞን ታሪክ መጽሐፍ ተጽፎዋል።› 1 ነገ 11፤41 ከዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል የሚከተሉትን ቁምነገሮች መረዳት እነችላለን

2.1 የነገረ ቅዱሳን ትምህርት መነሻው መጽሐፍ ቅዱስ ነው ፡፡
ነገረ ማርያም ፤ ነገረ ቅዱሳን እንደምንል ነገረ ሰለሞን አለን።

2.2 የእግዚአብሔር ቅዱሳን ድንቅ ድንቅ ተአምራት መፈጸም
ይችላሉ "ሰለሞን" ያደረገውም እንዲል። ይኽውም ጌታችን
አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ‹በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን እርሱ ደግሞ ያደርጋል ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል› ዮሐ 14 ፤ 12 ያረጋግጥልናል። ልበ
አምላክ ቅዱስ ዳዊትም በመዝሙሩ "እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው" መዝ 67÷35 እያለ ይዘምራል፡፡በተጨማሪም ቅዱሳኑ ፀሐይን እንዳቆሙ ኢያሱ 10÷12 በሥጋ ከሞቱ በኃላ በአጥንታቸው ሙት እንዳስነሱ 2 ነገ 13፤20 በጨርቃቸው በበትራቸው ባሕር እንደከፈሉ ዘጸ 14÷16 2ነገ 2÷8 ክፉዎች መናፍስትን አንዳወጡ የሐዋ 19÷11 በሰውነታቸው ጥላ (Shadow) ድውያንን እነደፈወሱ አጋንንትን አንዳወጡ ተአምራትን እንዳደረጉ የሐዋ 5÷15 መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክራል፡፡ ታድያ ገድላት ይህን ሲመሰክሩ ለምን ይተቻሉ?

2.3 ጠቢቡ ሰለሞን በመጽሀፍ ቅዱስ ከተተረክው ታሪኩ
በተጨማሪ የራሱን ታሪክ ጥበብ ሕይወት የሚተርክ መጽሐፍ
አለው፡፡ "በሰለሞን ታሪክ መጽሐፍ" አንዲል ገድለ ሰለሞን ማለት ነው ፡፡ ታዲያ ሰለሞን ስለራሱ ታሪክና ስለሰራቸው ሥራዎች የሚተርክ መጽሐፍ ካለው ያንንም እንድናነብ መጽሐፍ ቅዱስ ከጋበዘን የሌሎችን ቅዱሳን ታሪክ ለማንበብና ለመቀበል ሰዎች
ለምን ይቸገራሉ? በሌላም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል
"የንጉሡም የዳዊት የፊተኛውና
የኃለኛው ነገር እነሆ በባለ ራዕዩ በሳሙኤል ታሪክ በነቢዩም
በናታን ታሪክ በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ተጽፏል።" 1ዜና 29÷29 ተብሎ ተጽፋል ፡፡ በዚህ ክፍል ሶስት የቅዱሳን የገድል መጻሕፍት ተጠቅሰውልናል።

1ኛ የሳሙኤል
2ኛ የናታን
3ኛ የጋድ
መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ቅዱሳን የታሪክ መጻሕፍት ይመራናል ሰዎቹ "አታንብቡ" ይሉናል ማንን እንቀበል? ማስተዋሉን ያድለን አሜን!!

#በመምህር #ቢትወደድ_ወርቁ

✟ለአዕዛኒከ

ሰላም : ለአዕዛኒከ : እለ : ያጸምዓ : ምሳሌ : ዘሐዋርያት : ቡሩካን : ወዘነቢያት : ሰብአ ኩፋሌ ፤ ተክለ ሃይማኖት ምድራዊ ወመልአክ : ዘሉዓሌ ።
ምሥጠኒ : ውስተ ቤትከ : ዘአረፈቲሀሃ : ቢረሌ ። ከመ : አዕርፍ : ባቲ : እምብካይ : ወወይሌ ።

ትርጉም :- ✟ ለአዕዛኒከ ( ለጆሮሆችህ )

ተክለሃይማኖት ሆይ ፤ በክቡራን ነቢያት የተነገረውን በክቡራን ሐዋርያት የተሰበከውን መልካሙን ምሣሌ ነገር ለሚያደምጡ አዕዛኖችህ ሰላም እላለሁ ።
ቅዱስ አባቴ ሆይ በተፈጥሮ ጠባይህ ምድራዊ ሰው ስትሆን ፤ በሥነ ምግባርህ ሰማያዊ መልአክ ነህኮን ።
ከለቅሶና ከዋይታው በእርሷ ዐርፍ ዘንድ በወርቅና በዕንቁ በተሠራችው በሉዓላዊት ቤትህ
በዚያ ወስደህ አስቀምጠኝ

📜 መልክአ ተክለሃይማኖት

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ኢኦተቤ04_2.mp3
1.3 MB
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን_ታሪክ

#ክፍል ሀያ ሦስት

#በመምህር #ማርቆስ አለማየሁ

#ይዘት
👉 ቤተ ክርስቲያን ከአጼ ገላውዴዎስ እስከ አጼ ፋሲል


#ከትምህርቱ የተወጣጡ ጥያቄዎች

1 ቤተ ክርስቲያን በዘመነ አጼ ገላውዴዎስ የገጠማት ችግር ምንድን ነበር?
2 አጼ ፋሲል ለቤተክርስቲያን ያደረጉት አስተዋጽኦ ምን ነበር?

መልሶቻችሁን እና አስተያየታችሁን
@Abenma እና @Midyam ላይ ያድርሱን።

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ኢኦተቤ04_3.amr
776.1 KB
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን_ታሪክ

#ክፍል ሀያ አራት

#በመምህር #ማርቆስ አለማየሁ

#ይዘት
👉 ቤተ ክርስቲያን በቅብዐት እና ጸጋ ኑፋቄዎች የደረሰባት ፈተናዎች

አስተያየታችሁን
@Midyam ላይ ያድርሱን።

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ገድላትን መንቀፍ መጽሐፍ ቅዱስን መንቀፍ ነው!!

ስለ ቅዱሳት መጻሕፍት አለማወቅ ጥልቅ ወደ ሆነ የክህደትና ስህተት ዐዘቅት ውስጥ ይጥላል፡፡ ጌታችን በወንጌል ‹መጻህፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ›
ማቴ 22፤29 እንዳለ፡፡ የአበው ቅዱሳንን ተጋድሎ የሚነግሩን
አዋልድ መጻሕፍት አሥራው መጻሕፍትን (መጽሐፍ ቅዱስን) ያብራራሉ ይተረጉማሉ፡፡
ለአንዳንዶች እንደሚመስላቸው ገድላት ወደ ገደል አይከቱም
ከገደል ያወጣሉ እንጂ፡፡ ገድላት የእግዚአብሔርን ቃል ለመፈጸም
እንደ ቃሉ ለመመላለስ ያግዙናል፡፡ ‹የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩዋችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሩዋቸውንም ፍሬ
እየተመለከታችሁ በእምነታችሁ ምሰሉዋቸው› ዕብ 13፤7
‹እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ› ኤፌ 5፤1
‹በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን
አስቡ› ዕብ 12 ፤ 2-5፡፡
በማለት ቅዱሳንን እንድንከተል
የሚያዙንን የልዑል ቃላት የቅዱሳኑን ታሪክ ተጋድሎ ሕይወት የሚተርክልንን ገድላቸውን ሳናነብ እንዴት መፈጸም አንችላለን?
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ፈጣሪነት ጌትነት ኃያልነት
እንደሚነግረን የቅዱሳንንም ተጋድሎ ታሪክ ተአምር በሁለት
መንገድ ይነግረናል፡፡

1ኛ ከሌሎች ታሪኮች ጋር አሰናስሎ አያይዞ ምሳሌ በዘፍጥረት የአብርሃም የይስኃቅ የሔኖክና የሌሎች ቅዱሳን ታሪክ በዘጸዐት የሙሴ የኢያሱ የካሌብ በመሳፍንት የጌድዮን የዮፍታሔ
በሐዋርያት ሥራ የሐዋርያትን የሳሙኤልን፤ የኤልሳዕን፤ የኤልያስን ፤የናቡቴን፤ የዳዊትን ፤ የሰለሞንን ታሪኮች በመጽሐፈ ነገሥት እና መጽሐፈ ሳሙኤል መጻሕፍት እናገኛለን፡፡

2ኛ የቅዱሳኑን ታሪክ ለብቻው ምሳሌ መጽሐፈ አስቴር የአስቴርን ታሪክ፤ መጽሐፈ ኢዮብ የኢዮብን ታሪክ ፤ መጽሐፈ ሩት የሩትን ታሪክ ፤ መጽሐፈ ጦቢት የጦቢትን ታሪክ ይነግረናል:: መጽሐፍ ቅዱስ የቅዱሳንን ታሪክ እንድናነብ አዋልድ መጻሕፍትን
አንድንመለከት ይጋብዘናል። ለዚህ አስረጂ የሚሆኑን ጥቂት ኃይለ ቃላትትን ለማየት
‹የቀረውም የሰለሞንን ነገር ያደረገውም ሁሉ ጥበቡም እነሆ በሰሎሞን ታሪክ መጽሐፍ ተጽፎዋል።› 1 ነገ 11፤41 ከዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል የሚከተሉትን ቁምነገሮች መረዳት እነችላለን

2.1 የነገረ ቅዱሳን ትምህርት መነሻው መጽሐፍ ቅዱስ ነው ፡፡
ነገረ ማርያም ፤ ነገረ ቅዱሳን እንደምንል ነገረ ሰለሞን አለን።

2.2 የእግዚአብሔር ቅዱሳን ድንቅ ድንቅ ተአምራት መፈጸም
ይችላሉ "ሰለሞን" ያደረገውም እንዲል። ይኽውም ጌታችን
አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ‹በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን እርሱ ደግሞ ያደርጋል ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል› ዮሐ 14 ፤ 12 ያረጋግጥልናል። ልበ
አምላክ ቅዱስ ዳዊትም በመዝሙሩ "እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው" መዝ 67÷35 እያለ ይዘምራል፡፡በተጨማሪም ቅዱሳኑ ፀሐይን እንዳቆሙ ኢያሱ 10÷12 በሥጋ ከሞቱ በኃላ በአጥንታቸው ሙት እንዳስነሱ 2 ነገ 13፤20 በጨርቃቸው በበትራቸው ባሕር እንደከፈሉ ዘጸ 14÷16 2ነገ 2÷8 ክፉዎች መናፍስትን አንዳወጡ የሐዋ 19÷11 በሰውነታቸው ጥላ (Shadow) ድውያንን እነደፈወሱ አጋንንትን አንዳወጡ ተአምራትን እንዳደረጉ የሐዋ 5÷15 መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክራል፡፡ ታድያ ገድላት ይህን ሲመሰክሩ ለምን ይተቻሉ?

2.3 ጠቢቡ ሰለሞን በመጽሀፍ ቅዱስ ከተተረክው ታሪኩ
በተጨማሪ የራሱን ታሪክ ጥበብ ሕይወት የሚተርክ መጽሐፍ
አለው፡፡ "በሰለሞን ታሪክ መጽሐፍ" አንዲል ገድለ ሰለሞን ማለት ነው ፡፡ ታዲያ ሰለሞን ስለራሱ ታሪክና ስለሰራቸው ሥራዎች የሚተርክ መጽሐፍ ካለው ያንንም እንድናነብ መጽሐፍ ቅዱስ ከጋበዘን የሌሎችን ቅዱሳን ታሪክ ለማንበብና ለመቀበል ሰዎች
ለምን ይቸገራሉ? በሌላም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል
"የንጉሡም የዳዊት የፊተኛውና
የኃለኛው ነገር እነሆ በባለ ራዕዩ በሳሙኤል ታሪክ በነቢዩም
በናታን ታሪክ በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ተጽፏል።" 1ዜና 29÷29 ተብሎ ተጽፋል ፡፡ በዚህ ክፍል ሶስት የቅዱሳን የገድል መጻሕፍት ተጠቅሰውልናል።

1ኛ የሳሙኤል
2ኛ የናታን
3ኛ የጋድ
መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ቅዱሳን የታሪክ መጻሕፍት ይመራናል ሰዎቹ "አታንብቡ" ይሉናል ማንን እንቀበል? ማስተዋሉን ያድለን አሜን!!

#በመምህር #ቢትወደድ_ወርቁ

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
Audio
20220615_112539.aac
24.8 MB
#በመምህር ኢዮብ ክንፈ ሊደመጥ የሚገባው ጥዑም ወቅታዊ ትምህርት እነሆ