ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
ዕብ 13፥7 "ዋኖቻችሁን አስቡ"

ይህን ኃይለቃል ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በመንፈስቅዱስ ተቃኝቶ በረድኤተ እግዚአብሔር ተጎብኝቶ ተናግሮታል። አስቀድሞም "የጸኑትን አስቡ" በማለት መክሮናል(ዕብ 12፥3)። ስለምን ማሰብ ማንንስ ማሰብ እንዳለብን ግራ ለገባን ለእኛ ይህን መልእክት ጽፎልናል። ኃጢአት ከሚሠራባቸው መንገዶች አንዱ ሀሳብ ነው። ለዚህ ነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ለቀደሙት አትግደል እንደተባለ ሰምታችኅል እኔ ግን እላችኅለሁ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" በማለት ወደ መግደል የሚወስደውንና በሀሳብ ሊሠራ የሚችለውን ቁጣ የተባለ ኃጢአት የከለከለው(ማቴ 5፥22)። ዋኖችን(ቅዱሳንን) ማሰብ እኩይ ሀሳብን በማሰብ ከመባከን ያድናል። ቅዱስ ጳውሎስን በድንቅ አጠራሩ የጠራ ጌታችን ራሱ በመዋዕለ ስብከቱ "ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀመዝሙሬ ስም የሚያጠጣ ዋጋው አይጠፋበትም" (ማቴ10፥42) ብሎ የተናገረው ደቀመዛሙርትን (ቅዱሳንን) ማሰብ እንደሚገባን ሲያስረዳን ነው። ሀሳብ ለጽድቅም ለኃጢአትም መነሻ መሆኑን በሚገባ ማስተዋል ያስፈልጋል።" መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል ክፉም ሰው ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣል.የተባለውም ለዚሁ ነው(ማቴ12፥35)። ቅዱሳንን በማሰብ ብቻ ግን መዳን አይቻልም። አስቦ በሃይማኖት በምግባር በመምሰል እንጂ።

#ለምን ቅዱሳንን አስቡ ተባልን?

፨በምኞት ተስበን በኃጢአት እንዳንወድቅ። ቅዱሳንን በማሰብ የተጠመደ አእምሮ ያልተገባ ጉዳይን ለማሰብ ጊዜ አይኖረውምና።
፨እንድንመስላቸው። "የኑሯቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው" ዕብ 13፥7።
፨ከቃልኪዳናቸው ለመጠቀም። "ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃልኪዳኔን አደረግሁ።" መዝ 88፥3
፨እግዚአብሔርን እንድናስብና እንድናደንቅ። "እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው" መዝ 67፥35።
፨ቅዱሳኑ ለእግዚአብሔር ያሳዩትን ፍጹም ፍቅርና መገዛት ተመልክተን በጥቂቱ ለእግዚአብሔር መገዛት ያልቻለ እኛነታችንን ወቅሰን በንስሐ እንድንመለስ። "ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ።" ኢሳ 51፥2
፨በባዶነታችን የምንታበይ እኛ ትሕትናን እንድንማር። አበ ብዙኃን ሥርወ ሃይማኖት የተባለ አብርሃም አመድና ትቢያ ነኝ ካለ፤ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እኔ ግን ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም ካለ፤ ቅዱስ ጳውሎስ ጭንጋፍ ነኝ ካለ (ዘፍ 18፥27፤መዝ 21፥6 ፤1ኛ ቆሮ 15፥8) እኛ ማንነን እንበል?

#ቅዱሳንን እንዴት እናስብ?

፨በሚከብሩበት ዕለት ታቦታቸውን በማንገሥ።
፨ገድላቸውን፣ተአምራታቸውን በማንበብ።
፨በስማቸው ነዳያንን በመመጽወት።
፨በስማቸው በታነጸው ቤተክርስቲያን መባ (ዕጣን፣ጣፍ፣ዘቢብ፣ዣንጥላ፣መጋረጃ) በመስጠት።
፨በመንፈሳዊ ዝማሬ ቅዱሳንን አስበን፣ መስለን ስሙን ለመቀደስ መንግሥቱን ለመውረስ ልዑል አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን።

አሜን።

በወንድችማን #ኢዮብ ክንፍ

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ዕብ 13፥7 "ዋኖቻችሁን አስቡ"

ይህን ኃይለቃል ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በመንፈስቅዱስ ተቃኝቶ በረድኤተ እግዚአብሔር ተጎብኝቶ ተናግሮታል። አስቀድሞም "የጸኑትን አስቡ" በማለት መክሮናል(ዕብ 12፥3)። ስለምን ማሰብ ማንንስ ማሰብ እንዳለብን ግራ ለገባን ለእኛ ይህን መልእክት ጽፎልናል። ኃጢአት ከሚሠራባቸው መንገዶች አንዱ ሀሳብ ነው። ለዚህ ነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ለቀደሙት አትግደል እንደተባለ ሰምታችኅል እኔ ግን እላችኅለሁ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" በማለት ወደ መግደል የሚወስደውንና በሀሳብ ሊሠራ የሚችለውን ቁጣ የተባለ ኃጢአት የከለከለው(ማቴ 5፥22)። ዋኖችን(ቅዱሳንን) ማሰብ እኩይ ሀሳብን በማሰብ ከመባከን ያድናል። ቅዱስ ጳውሎስን በድንቅ አጠራሩ የጠራ ጌታችን ራሱ በመዋዕለ ስብከቱ "ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀመዝሙሬ ስም የሚያጠጣ ዋጋው አይጠፋበትም" (ማቴ10፥42) ብሎ የተናገረው ደቀመዛሙርትን (ቅዱሳንን) ማሰብ እንደሚገባን ሲያስረዳን ነው። ሀሳብ ለጽድቅም ለኃጢአትም መነሻ መሆኑን በሚገባ ማስተዋል ያስፈልጋል።" መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል ክፉም ሰው ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣል.የተባለውም ለዚሁ ነው(ማቴ12፥35)። ቅዱሳንን በማሰብ ብቻ ግን መዳን አይቻልም። አስቦ በሃይማኖት በምግባር በመምሰል እንጂ።

#ለምን ቅዱሳንን አስቡ ተባልን?

፨በምኞት ተስበን በኃጢአት እንዳንወድቅ። ቅዱሳንን በማሰብ የተጠመደ አእምሮ ያልተገባ ጉዳይን ለማሰብ ጊዜ አይኖረውምና።
፨እንድንመስላቸው። "የኑሯቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው" ዕብ 13፥7።
፨ከቃልኪዳናቸው ለመጠቀም። "ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃልኪዳኔን አደረግሁ።" መዝ 88፥3
፨እግዚአብሔርን እንድናስብና እንድናደንቅ። "እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው" መዝ 67፥35።
፨ቅዱሳኑ ለእግዚአብሔር ያሳዩትን ፍጹም ፍቅርና መገዛት ተመልክተን በጥቂቱ ለእግዚአብሔር መገዛት ያልቻለ እኛነታችንን ወቅሰን በንስሐ እንድንመለስ። "ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ።" ኢሳ 51፥2
፨በባዶነታችን የምንታበይ እኛ ትሕትናን እንድንማር። አበ ብዙኃን ሥርወ ሃይማኖት የተባለ አብርሃም አመድና ትቢያ ነኝ ካለ፤ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እኔ ግን ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም ካለ፤ ቅዱስ ጳውሎስ ጭንጋፍ ነኝ ካለ (ዘፍ 18፥27፤መዝ 21፥6 ፤1ኛ ቆሮ 15፥8) እኛ ማንነን እንበል?

#ቅዱሳንን እንዴት እናስብ?

፨በሚከብሩበት ዕለት ታቦታቸውን በማንገሥ።
፨ገድላቸውን፣ተአምራታቸውን በማንበብ።
፨በስማቸው ነዳያንን በመመጽወት።
፨በስማቸው በታነጸው ቤተክርስቲያን መባ (ዕጣን፣ጣፍ፣ዘቢብ፣ዣንጥላ፣መጋረጃ) በመስጠት።
፨በመንፈሳዊ ዝማሬ ቅዱሳንን አስበን፣ መስለን ስሙን ለመቀደስ መንግሥቱን ለመውረስ ልዑል አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን።

አሜን።

በወንድችማን #ኢዮብ ክንፍ

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ዕብ 13፥7 "ዋኖቻችሁን አስቡ"

ይህን ኃይለቃል ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በመንፈስቅዱስ ተቃኝቶ በረድኤተ እግዚአብሔር ተጎብኝቶ ተናግሮታል። አስቀድሞም "የጸኑትን አስቡ" በማለት መክሮናል(ዕብ 12፥3)። ስለምን ማሰብ ማንንስ ማሰብ እንዳለብን ግራ ለገባን ለእኛ ይህን መልእክት ጽፎልናል። ኃጢአት ከሚሠራባቸው መንገዶች አንዱ ሀሳብ ነው። ለዚህ ነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ለቀደሙት አትግደል እንደተባለ ሰምታችኅል እኔ ግን እላችኅለሁ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" በማለት ወደ መግደል የሚወስደውንና በሀሳብ ሊሠራ የሚችለውን ቁጣ የተባለ ኃጢአት የከለከለው(ማቴ 5፥22)። ዋኖችን(ቅዱሳንን) ማሰብ እኩይ ሀሳብን በማሰብ ከመባከን ያድናል። ቅዱስ ጳውሎስን በድንቅ አጠራሩ የጠራ ጌታችን ራሱ በመዋዕለ ስብከቱ "ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀመዝሙሬ ስም የሚያጠጣ ዋጋው አይጠፋበትም" (ማቴ10፥42) ብሎ የተናገረው ደቀመዛሙርትን (ቅዱሳንን) ማሰብ እንደሚገባን ሲያስረዳን ነው። ሀሳብ ለጽድቅም ለኃጢአትም መነሻ መሆኑን በሚገባ ማስተዋል ያስፈልጋል።" መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል ክፉም ሰው ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣል.የተባለውም ለዚሁ ነው(ማቴ12፥35)። ቅዱሳንን በማሰብ ብቻ ግን መዳን አይቻልም። አስቦ በሃይማኖት በምግባር በመምሰል እንጂ።

#ለምን ቅዱሳንን አስቡ ተባልን?

፨በምኞት ተስበን በኃጢአት እንዳንወድቅ። ቅዱሳንን በማሰብ የተጠመደ አእምሮ ያልተገባ ጉዳይን ለማሰብ ጊዜ አይኖረውምና።
፨እንድንመስላቸው። "የኑሯቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው" ዕብ 13፥7።
፨ከቃልኪዳናቸው ለመጠቀም። "ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃልኪዳኔን አደረግሁ።" መዝ 88፥3
፨እግዚአብሔርን እንድናስብና እንድናደንቅ። "እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው" መዝ 67፥35።
፨ቅዱሳኑ ለእግዚአብሔር ያሳዩትን ፍጹም ፍቅርና መገዛት ተመልክተን በጥቂቱ ለእግዚአብሔር መገዛት ያልቻለ እኛነታችንን ወቅሰን በንስሐ እንድንመለስ። "ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ።" ኢሳ 51፥2
፨በባዶነታችን የምንታበይ እኛ ትሕትናን እንድንማር። አበ ብዙኃን ሥርወ ሃይማኖት የተባለ አብርሃም አመድና ትቢያ ነኝ ካለ፤ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እኔ ግን ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም ካለ፤ ቅዱስ ጳውሎስ ጭንጋፍ ነኝ ካለ (ዘፍ 18፥27፤መዝ 21፥6 ፤1ኛ ቆሮ 15፥8) እኛ ማንነን እንበል?

#ቅዱሳንን እንዴት እናስብ?

፨በሚከብሩበት ዕለት ታቦታቸውን በማንገሥ።
፨ገድላቸውን፣ተአምራታቸውን በማንበብ።
፨በስማቸው ነዳያንን በመመጽወት።
፨በስማቸው በታነጸው ቤተክርስቲያን መባ (ዕጣን፣ጣፍ፣ዘቢብ፣ዣንጥላ፣መጋረጃ) በመስጠት።
፨በመንፈሳዊ ዝማሬ ቅዱሳንን አስበን፣ መስለን ስሙን ለመቀደስ መንግሥቱን ለመውረስ ልዑል አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን።

አሜን።

በወንድችማን #ኢዮብ ክንፍ

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit