ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#ልትድን ትወዳለህን?"
#ዮሐ ፭÷፮
የዐቢይ ጾም አራተኛው ሰንበት “መጻጉዕ” ይባላል፡፡ መጻጉዕ ማለት “በሽተኛ” ማለት ነው፡
በዚህ ዕለት ጌታችን በቤተ ስዳ መጻጉዕን ማዳኑን ቤተክርስቲያን ትሰብካለች፡፡ ለ ፴ ፰
ዓመታት ያህል የፈውስ ተስፈኛ ሆኖ በመጠመቂያው አጠገብ የኖረ መጻጉዕን በአልጋው
ተኝቶ ሳለ ደዌው እንደጠናበት ፈውስ እንደዘገየበት አይቶ ‹‹አዎን›› እንደሚለው እያወቀ
መጻጉዕን ‹‹ልትድን ትወዳለህን?” አለው።
#መጻጉዕም ‹‹ሰው የለኝም›› በማለት የመዳን ጉጉቱን ከወዳጅ አልባነቱ ጋር ገለጠ።
ጌታም ‹‹ተንስና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ” አለው፡፡ ወዲያው አፈፍ ብሎ በፍጥነት ያን ሁሉ
ዘመን የተሸከመችውን ጠንካራ አልጋ ተሸክሟት ሄደ (ዮሐ ፭÷፩ -፭)።
ጌታችን መጻጉዕን ‹‹ ተነስተህ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ›› ያለው ስለ ሁለት ነገር ነው፡፡
አንደኛው ቅዱስ ኤስድሮስ እንዳለው አልጋው ጠንካራ የብረት አልጋ ነበረና ጽንዓ
ተአምራቱን ለማሳየት ነው፡፡ ሁለተኛው ‹‹ታዲያ ቢያድነኝ በከንቱ መች ሆነና የገዛ አልጋዬን
ትቼለት የመጣሁ ለመዳኔ ዋጋ የከፈልኩበት አይደለምን?›› እንዳይል መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ‹‹ያለህን ይዘህ ሂድ እኔ ከአንተ አንዳች አልሻም›› ባሰኘ ቃል ‹‹አልጋህን
ተሸክመህ ሂድ›› ብሎታል።
# ይህ_ሰንበት የሕሙማን ፈውስ መታሰቢያ ዕለት ነው። የሰንበቱም ስያሜ በዕለቱ
የሚነበቡትን የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢርና የጾመ ድጓውን ይትበሀል ተከትሎ የተሰየመ
ነው፡፡ በመልእክታቱ የሚነበቡት (ገላ ፭÷፩ እና ያዕ ፭÷፡፲ ፬) ስለ ድውያን መፈወስ
የሚያወሱ ናቸው፡፡ ከሐዋርያት ሥራ የሚነበውም እንዲሁ (ሐዋ ፫÷፩)፡፡ የዕለቱ ምስባክ
እንዲሁ የድውያንን መፈወስ የሚሰብክ ሲሆን “እግዚአብሔር በደዌው አልጋ ላይ ሳለ
ይረዳዋል፤ መኝታውንም ሁሉ ከበሽታው የተነሳ ይለውጥለታል፡፡ እኔስ “አቤቱ ይቅር በለኝ፤
አንተን በድያለሁና ለነፍሴ አስተስርይላት” አልሁ፡፡” ይላል (መዝ ፴ ፱(፵)÷፫)
መጻጉዕ ማለት ድዊ፣ ሕመምተኛ፣በሽተኛ ማለት ነውና በቤተ ሳይዳ ፴ ፰ ዓመት በአልጋ
ቁራኛ በደዌ ዳኛ ተይዞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ የፈወሰው ሰው ስም ብቻ
አይደለም የዚያ ሰው ስም "ስምዖን" ነው። ሕመምተኞች ሁሉ መጻጉዕ ተብለው ሊጠሩ
ይችላሉ ።ስለሆነም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህን የዐቢይ ጾም አራተኛ ሳምንት መጻጉዕ
ብላ ስታስብ ሕሙማነ ነፍስን እሙማነ ሥጋን ሁሉ ፈውሰ ነፍስ ፈውሰ ሥጋ እንዲያገኙ
ታስባቸዋለች ማለት ነው ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመዋለ ስብከቱ
እሙማነ ነፍሳትን በትምህርቱ እሙማነ ሥጋን በተአምራቱ እንደፈወሳቸውም
ታዘክርበታለች።
#ሕማማ ወይም ደዌ በ ፭ ዓይነት መንገድ ሊመጣ ይችላል። እነርሱም
፩, ደዌ ዘንጽሕ(በንጽሕና የሚመጣ በሽታ) ለአብነትም እንደ ጢሞቲዎስ በአገልግሎት
ምክንያት የሚመጡ ::እንደ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት።
፪, ደዌ ዘእሴት (ለዋጋ የሚመጣ በሽታ) እንደ ጻድቁ ኢዮብ
፫, ደዌ ዘተአምራት( የእግዚአብሔር ተአምራት እንዲገለጥ የሚመጡ በሽታዎች) እንደ
ዘውር ተወልደ
፬, ደዌ ዘመቅሰፍት(በቅጣት የሚመጣ በሽታ)
እንደ ፈርዖን ዘመን ያሉ በሽታዎችና አባር ቸነፈሮች በዘመናችን ኮረና
፭,ደዌ ዘኃጢያት (በኃጢያት ምክንያት የሚመጣ) አንደ መጻጉዕ ፣ እንደ ባለ ሽቶዋ
ማርያም፣ በድንጋይ ልትወገር እንደነበረችው አመንዝራ ሴት
#ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ድኅነትን በ፭ መንገድ ይፈጽምላቸው
ነበር።ይህውም
፩,በኃልዮ (በሀሳቡ) ማር ፩፥፳ ፭
፪,በነቢብ(በንግሩ) ማቴ፲ ፭፥፳ ፰፣ ዮሐ ፭÷፰
፫,በገሲስ(በመዳሰስ) ማቴ፰፥፫ ፣ማቴ ፰፥፩ ፭
፬,በዘፈራ ልብስ (በልሱ ዘርፍ) ሉቃስ ፰፥፵ ፬
፭,በወሪቀ ምሪቅ (ምራቅን እንትፍ በማለት)“ ዮሐ ፱፥፮
ለድኅነት የሰው በጎ ፍቃድና ፍላጎት እጅግ አስፈላጊ ነው።መጻጉን ልትድን ትወዳለህን ብሎ
የመጠየቁም ምጢር ይህ ነበር ሰው ነጻ ፍቃዱ ሊነፍገው አይሻምና ። ሰው ለመዳን ወይም
ሌላውንም ለማዳን ብርቱ ጥረትን ሊያደርግ ይገባዋል
መጽሐፍ ቅዱስ አራት ሰዎች አንድ ሕመምተኛ ለማዳን የተጠቀሙትን ብርቱ ጥረት እንዲ
በግሩም ተርኮልን እናነባለን።
" #አራት_ሰዎችም የተሸከሙትን ሽባ አመጡለት። ስለ ሕዝቡም ብዛት ወደ እርሱ ማቅረብ
ቢያቅታቸው እርሱ ያለበትን የቤቱን ጣራ አነሡ፥ ነድለውም ሽባው የተኛበትን አልጋ
አወረዱ። # ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፦ አንተ ልጅ፥
ኃጢአትህ ተሰረየችልህ አለው። ማር ፪ ÷፫-፭
.............ይቆየን.......
ግብሐት :-የዮሐንስ ወንጌል ም፭ ትርጓሜው
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፲ ፱ ቀን/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም