#የአልጋ_ላይ_ዱካ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
ትላንት ማታ ክፉ ነገር ተፈጠረ፡፡
መልከ መልካሙና ገራገሩ እጮኛዬ ላይ ማገጥኩበት፡፡
ያች በልጣጣ ጓደኛዬ ትዕግስት ናት፣ እዚህ ሁሉ ጣጣ ውስጥ የከተተችኝ።
ሁሌም ለሰኔ ሚካኤል ቤቷ ድል ያለ ድግስ ታዘጋጃለች፡፡ የምታውቀውን ሰው ሁሉ ትጋብዛለች፡፡ ከልክ በላይ
ታበላለች፡፡ ከመጠን በላይ ታጠጣለች፡፡ አንድ ውስኪ ለሦስት ሰው እየቀረበ፣ በረዶ አንሷል እየተባለ ውስኪ እንደተፈጠረ በጉሮሮ ሲንቆረቆር፣ ሰዉ ሁሉ ከማያውቀው ሰው እንደ አብሮ አደግ ይሣሣቃል፣ ያሽካካል፡፡ ምስጢር ይጋራል፡፡ ይሟዘዛል፡፡ የትዕግስት
ፓርቲ እንዲህ ነው፡፡ ነጠላ
ሆኖ የመጣን፣ ጥንድ አድርጎ
ይሸኛል፡፡ አይተው ከማያውቁት ሰው አደጋግፎ፤ አስተቃቅፎ፣አልጋ ድረስ ያጓትታል፡፡
ውስኪዋ ውስጥ ትንሽ ቅንዝር ጠብ፣ ብዙ የፍትወት ፍላጎትና የመማገጥ ዓላማ ሙጅር ታደርግበት ይመስል፤ በየዓመቱ የሚወራ የወሲብ ገድል መነሻ ይሆናል፡፡
ለስድስት ዓመታት ይሄንን የተቀበረ የመጠጥ ፈንጂ አልፌ፤ ዘንድሮው ግን ረገጥኩት፡፡
እርግጥ አድርጌ ብ......ው......
አደረግኩት፡፡ አጀማመሩ እንዲህ ነበር፡፡
ጥሬና ጥብሱን ሥጋ፣ ከዚህ በኋላ ለሳምንት አትበሉም የተባልን ያህል ተስገብግበን ጎስረን፣ ጎስረን፣ “እሰቲ አወራርዱት... እስቲ ጥረጉት” እያለች የምታስተናብረውን ትዕግስት እየሰማን፣ ሁለት ጠርሙስ ውስኪያችንን በጉሮሯችን እያንቆረቆርን ስድስት ሆነን
አንድ ጠረጴዛ ላይ ተሰይመናል፡፡
ከለብታ አልፎ ሞቅታ፣ ከሞቅታ አልፎ ስካር ሲጀማምረኝ ትዕግስት
ወደ ጠረጴዛችን መጥታ፣ “አወራርዱት” ባለች ቁጥር፤ የሞት ሞቴን የብርጭቆዬን አፍ በእጆቼ ለመክደን ብሞክርም፣ ልክ ትንኝ እንደምታባርር ሁሌ እጄን ጧ እያደረገች ታስከፍተኝና በውስኪ
ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ቺርስ ባሉ ቁጥር እጠጣለሁ፡፡
“አትጨምሪልኝ... በቃኝ” እያልኩ በእጄ ብርጭቆውን ለመዝጋት እሞክራለሁ፡፡
እጄን ጧ አድርጋ፣ ብርጭቆዬን አስከፍታኝ ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ቺርስ ባሉ ቁጥር እጠጣለሁ፡፡
እንደገና “አትጨምሪልኝ... በቃኝ” እያልኩ በእጄ ብርጭቆውን ለመዝጋት እሞክራለሁ፡፡
እጄን ጧ አድርጋ፣ ብርጭቆዬን አስከፍታኝ ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ይሄ አዙሪት ለዐሥራ ምናምን ጊዜ እንደቆየ ሳሙኤል ከፊቴ ተከሰተ፡፡ ያንን ሰንደቅ የሚያስቅል ቁመቱን፤ የቀይ ዳማ የደስ ደሳም ፊቱን፣ ቦርጭ አልባ ሰውነቱን ይዞ፣ ሳሙኤል ከፊቱ ተከሰተ፡፡ ያውም አንዴ ሁለት፣ አንዴ አራት፣ አንዴ ስድስት
ሆኖ... ሞቅታዬ አብዝቶት፣ ስካሬ አባዝቶት የቀድሞ ፍቅረኛዬ ሳሙኤል ከፊቴ ተከሰተ።
ሲቀመጥ ትዝ አይለኝም፡፡ እጆቼን ሲያሻሸኝ ግን ትዝ ይለኛል፡፡
መጀመሪያ ሲስመኝ ትዝ አይለኝም፡፡ አፌን አፉ ውስጥ ሳገኘው ግን ትዝ ይለኛል።
መኪናው ላይ ስሳፈር አላስታውስም፡፡ አልጋው ውስጥ መግባቴ ግን ውል ይለኛል፡፡ ልብሳችንን ስናወልቅ ትዝ
አይለኝም፡፡ ዕራቁት ሰውነቱን በስሜት ስቧጭር ግን በደንብ ትዝ ይለኛል።
ከንፈር እየተሻማን ስንቃበጥ፣ አንገቴን ሲልስም፣ ሲስምም፤ ኋላም ሴትነቴን በወፍራም ወንድነቱ ሲከድን፣ መሀሉ መሀሉ ጭለማ በገባበት ሁኔታ ትዝ ይለኛል፡፡
ይሄው ነው፡፡
ጠዋት ላይ፣ አልጋው ውስጥ አናት ከሚፈልጥ ራስ ምታት ጋር
ስነቃ፣ ትላልቅ ድፍርስ ዐይኖቹ ተቀበሉኝ፡፡
ራሴን በሁለት እጆቼ ካልደገፍኩ ቷ ብሎ የሚፈነዳ ስለመሰለኝ፣በቀኝም በግራም እጆቼ ጭንቅላቴን ይዤ፣ ከወገቤ በላይ ብድግ አልኩና፣
“ምንድነው ...! ምንድነው ያደረግነው?” ብዬ ጮኽኩ፡፡ ሳሙኤል
ትላልቅ ዐይኖቹን ፊቱ ላይ እያንጎማለለ ሲያየኝ፣ የራሴ ጩኸት ራስ ምታቴን እያባሰው ከወገቤ በታች ዐየሁ፡፡ እንደፈጠረኝ ነኝ፡፡
“ሳሙኤል... እዚሀ እንዴት መጣሁ...? ምንድነው ያደረገገው...?”አልኩ በአንሶላው ተጠቅልዬ ከአልጋው የመሸሽ ያህል እየወጣሁ:ከአልጋው ፈንጠር ብሎ ወጣ፡፡ ቁምጣ ከሚያህል ቡራቡሬ የውስጥ ሱሪ ሌላ ምንም አላደረገም፡፡
“ሆሆሆ! ምንድነው ያደረግነው? ካርታ ስንጫወት ነዋ ያደርነው”አለኝ፣ እየሣቀ፡፡ ጥርስህ ይርገፍ፡፡
ዝም ብዬው ልብሶቼን ፍለጋ ጀመርኩ፡፡
ሮዝ ጡት ማስያዣዬን አልጋው ግርጌ፣ ጥብቅ ያለው ቀይ የድግስ ቀሚሴን ከአልጋው በስተቀኝ መሬት ላይ አግኝቼ፣ በሰማያዊው ለስላሳ አንሶላ እንደተጠመጠምኩ ወደ ማውቀው መታጠቢያ ቤት ገብቼ ፊቴን ሳልታጠብ መስታወቱ ፊት ቆምኩ፡፡
ምንድነው የሠራሁት?
ምን ነካኝ?
እሺ ለብ ይበለኝ፡፡ እሺ ሞቅ ይበለኝ፡፡ እሺ ልስከር፡፡ እሺ እጄን እንዲይዝ ልፍቀድለት፡፡ እሺ ሲስመኝ ልሳመው፡፡ እሺ ትንሽ ልቃበጥ፡፡ ግን ምንስ ያህል ብጠጣ ከትዕግስት ቤት ወጥቼ፣
መኪናው ውስጥ ገብቼ፣ ከብስራተ ገብርኤል ሰሚት ድረስ ንፋስ እየመታኝ መጥቼ፣ እቤቱ ሄጄ፣ መኝታ ቤቱ ገብቼ፣ አልጋው ጋር ሄጄ፣ አልጋው ውስጥ ገብቼ፣ ልብሴን አውልቄ፣ ራቁቴን ሆኜ፣
እጮኛ (ያውም የሰው ጥግ) እያለኝ፤ ከቀድሞ ፍቀረኛዬ ጋር ስዳራ
ማደሬ ልክ ነው?
ለመልአክ ሩብ ጉዳይ በሆነ እጮኛዬ ላይ
መልከስከሴ ግፍ አይደለም?
ቢሰማ አያብድም?
ቢያውቅ ራሱን አያጠፋም?
ፊቴን በቅጡ ሳልታጠብ፣ ከመታጠቢያ ቤቱ ወጥቼ በጥድፊያ ጫማዬን አድርጌ፣ ቦርሳዬን አነገብኩና... “ስሚኝ...” ምናምን...የሚለኝን ሳሙኤል ሙሉ በሙሉ ዘግቼ እግሬ በፈቀደልኝ ፍጥነት
ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ፡፡
የኮንዶሚኒየሙን ደረጃ እየወረድኩ ስልኬን አወጣሁ፡፡
.
ዐሥራ ዘጠኝ ያመለጡኝ ጥሪዎች፡፡ ሰባት የጽሑፍ መልዕክቶች፡፡ከፈትኩት፡፡
ዐሥራ ስድስቱ የእጮኛዬ ጥሪ ነው፡፡ ስማግጥ ያልመለስኳቸው 16
ጥሪዎች፡፡ እርምጃዬን አቁሜ እጄ እየተንቀጠቀጠ መልዕእክቶቹን
ከፈትኳቸው፡፡ ሁሉም ከእሱ ናቸው፡፡
“ማሬ ስልክ አታነሺም” ... “በሰላም ነው...?”... “ኧረ ተጨነቅኩ”...
.
“በደህናሽ ነው?”... “እባክሽ ደውይልኝ... “ትዕግስትም አላነሳ አለችኝ ... “በናትሽ ደውይልኝ” ....
ኮንዶሚኒየሙ ጣራ ላይ ወጥቼ መፈጥፈጥ አማረኝ፡፡
ልደውልለት ግን ጉልበት አጣሁ፡፡ እሱን ትቼ ትዕግስት ጋር ደወልኩ፡፡ በሁለተኛው ዙር ከአራት ጥሪ በኋላ አነሳች፡፡
ሰላምም ሳልላት፣ “አንቺ ማታ ምንድነው የተፈጠረው?” ብዬ ጮኽኩባት፡፡
“እንዴ እኔ ምናባሽ አውቅልሻለሁ... የት ሆነሽ ነው...?” አለችኝ።ድምፅዋ፣ ቤተክርስትያን ሲያስቀድስ አድሮ የመጣ ሰላማዊ ሰው እንጂ፤ አሸሼ ገዳሜ ሲል ያደረ አይመስልም፡፡
“ምን የት ነሽ?” ትይኛለሽ... ሳሚ ጋር ነበርኩ... እንዴት እንዲህ
ዓይነት ነገር ሲደረግ... እዚህ ሲያመጣኝ ዝም ትያለሽ?” አልኩ፣ ቱግ ብዬ እርምጃዬን እያፈጠንኩ፡፡
“እንዴ... ኧረ ቀስ...! አንቺ አይደለሽ ስንት ሆነን ስንለምንሽ፣ ከእሱ በስተቀር ከማንም ጋር አልሄድም እያልሽ፤ እንደ
እባብ ስትጠመጠሚበት ያመሸሽው?” አለችኝ ቆጣ ብላ፡፡
ወሬውን በስልክ መቀጠል ስላልፈለግኩ፣ ቤት መሆኗን አረጋግጬ ራይድ ጠራሁና ስበር ቤቷ ደረስኩ፡፡
በስልክ የጀመረችልኝን አጠናክራ፣ ለያዥ ለገናዥ ማስቸገሬን፤ ያየኝ ሰው ሁሉ ሲሥቅ እንደነበር፤ መጨረሻ ላይ እንደፈለጋት ትሁን ብለው እንደተዉኝ በሚያም ዝርዝር ነገረችኝ፡፡
ያቀረበችልኝን ቁርስ ሳልነካ ሻዩን ብቻ እየማግኩ፣
“ቲጂ...” አልኳት፡፡
“ወይ...” አለች፣ ዐይን ዐይኔን እያየች፡፡
“ደሬ የሚሰማ ይመስልሻል...? ማለቴ ሰው ቢነግረውስ?” አልኳት፡፡
“እ...ህ አይመስለኝም... ደግነቱ እንደዛ ስታብጂ የነበረው አብዛኛው ሰው ከሄደ በኋላ ነው...ማሐቴ ሳሙኤል ካልተናገረ" አለችኝ።
ሳሙኤል ካልተናገረ!
በተቀመጥኩበት መርዶ እንደተረዳ ሰው
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
ትላንት ማታ ክፉ ነገር ተፈጠረ፡፡
መልከ መልካሙና ገራገሩ እጮኛዬ ላይ ማገጥኩበት፡፡
ያች በልጣጣ ጓደኛዬ ትዕግስት ናት፣ እዚህ ሁሉ ጣጣ ውስጥ የከተተችኝ።
ሁሌም ለሰኔ ሚካኤል ቤቷ ድል ያለ ድግስ ታዘጋጃለች፡፡ የምታውቀውን ሰው ሁሉ ትጋብዛለች፡፡ ከልክ በላይ
ታበላለች፡፡ ከመጠን በላይ ታጠጣለች፡፡ አንድ ውስኪ ለሦስት ሰው እየቀረበ፣ በረዶ አንሷል እየተባለ ውስኪ እንደተፈጠረ በጉሮሮ ሲንቆረቆር፣ ሰዉ ሁሉ ከማያውቀው ሰው እንደ አብሮ አደግ ይሣሣቃል፣ ያሽካካል፡፡ ምስጢር ይጋራል፡፡ ይሟዘዛል፡፡ የትዕግስት
ፓርቲ እንዲህ ነው፡፡ ነጠላ
ሆኖ የመጣን፣ ጥንድ አድርጎ
ይሸኛል፡፡ አይተው ከማያውቁት ሰው አደጋግፎ፤ አስተቃቅፎ፣አልጋ ድረስ ያጓትታል፡፡
ውስኪዋ ውስጥ ትንሽ ቅንዝር ጠብ፣ ብዙ የፍትወት ፍላጎትና የመማገጥ ዓላማ ሙጅር ታደርግበት ይመስል፤ በየዓመቱ የሚወራ የወሲብ ገድል መነሻ ይሆናል፡፡
ለስድስት ዓመታት ይሄንን የተቀበረ የመጠጥ ፈንጂ አልፌ፤ ዘንድሮው ግን ረገጥኩት፡፡
እርግጥ አድርጌ ብ......ው......
አደረግኩት፡፡ አጀማመሩ እንዲህ ነበር፡፡
ጥሬና ጥብሱን ሥጋ፣ ከዚህ በኋላ ለሳምንት አትበሉም የተባልን ያህል ተስገብግበን ጎስረን፣ ጎስረን፣ “እሰቲ አወራርዱት... እስቲ ጥረጉት” እያለች የምታስተናብረውን ትዕግስት እየሰማን፣ ሁለት ጠርሙስ ውስኪያችንን በጉሮሯችን እያንቆረቆርን ስድስት ሆነን
አንድ ጠረጴዛ ላይ ተሰይመናል፡፡
ከለብታ አልፎ ሞቅታ፣ ከሞቅታ አልፎ ስካር ሲጀማምረኝ ትዕግስት
ወደ ጠረጴዛችን መጥታ፣ “አወራርዱት” ባለች ቁጥር፤ የሞት ሞቴን የብርጭቆዬን አፍ በእጆቼ ለመክደን ብሞክርም፣ ልክ ትንኝ እንደምታባርር ሁሌ እጄን ጧ እያደረገች ታስከፍተኝና በውስኪ
ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ቺርስ ባሉ ቁጥር እጠጣለሁ፡፡
“አትጨምሪልኝ... በቃኝ” እያልኩ በእጄ ብርጭቆውን ለመዝጋት እሞክራለሁ፡፡
እጄን ጧ አድርጋ፣ ብርጭቆዬን አስከፍታኝ ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ቺርስ ባሉ ቁጥር እጠጣለሁ፡፡
እንደገና “አትጨምሪልኝ... በቃኝ” እያልኩ በእጄ ብርጭቆውን ለመዝጋት እሞክራለሁ፡፡
እጄን ጧ አድርጋ፣ ብርጭቆዬን አስከፍታኝ ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ይሄ አዙሪት ለዐሥራ ምናምን ጊዜ እንደቆየ ሳሙኤል ከፊቴ ተከሰተ፡፡ ያንን ሰንደቅ የሚያስቅል ቁመቱን፤ የቀይ ዳማ የደስ ደሳም ፊቱን፣ ቦርጭ አልባ ሰውነቱን ይዞ፣ ሳሙኤል ከፊቱ ተከሰተ፡፡ ያውም አንዴ ሁለት፣ አንዴ አራት፣ አንዴ ስድስት
ሆኖ... ሞቅታዬ አብዝቶት፣ ስካሬ አባዝቶት የቀድሞ ፍቅረኛዬ ሳሙኤል ከፊቴ ተከሰተ።
ሲቀመጥ ትዝ አይለኝም፡፡ እጆቼን ሲያሻሸኝ ግን ትዝ ይለኛል፡፡
መጀመሪያ ሲስመኝ ትዝ አይለኝም፡፡ አፌን አፉ ውስጥ ሳገኘው ግን ትዝ ይለኛል።
መኪናው ላይ ስሳፈር አላስታውስም፡፡ አልጋው ውስጥ መግባቴ ግን ውል ይለኛል፡፡ ልብሳችንን ስናወልቅ ትዝ
አይለኝም፡፡ ዕራቁት ሰውነቱን በስሜት ስቧጭር ግን በደንብ ትዝ ይለኛል።
ከንፈር እየተሻማን ስንቃበጥ፣ አንገቴን ሲልስም፣ ሲስምም፤ ኋላም ሴትነቴን በወፍራም ወንድነቱ ሲከድን፣ መሀሉ መሀሉ ጭለማ በገባበት ሁኔታ ትዝ ይለኛል፡፡
ይሄው ነው፡፡
ጠዋት ላይ፣ አልጋው ውስጥ አናት ከሚፈልጥ ራስ ምታት ጋር
ስነቃ፣ ትላልቅ ድፍርስ ዐይኖቹ ተቀበሉኝ፡፡
ራሴን በሁለት እጆቼ ካልደገፍኩ ቷ ብሎ የሚፈነዳ ስለመሰለኝ፣በቀኝም በግራም እጆቼ ጭንቅላቴን ይዤ፣ ከወገቤ በላይ ብድግ አልኩና፣
“ምንድነው ...! ምንድነው ያደረግነው?” ብዬ ጮኽኩ፡፡ ሳሙኤል
ትላልቅ ዐይኖቹን ፊቱ ላይ እያንጎማለለ ሲያየኝ፣ የራሴ ጩኸት ራስ ምታቴን እያባሰው ከወገቤ በታች ዐየሁ፡፡ እንደፈጠረኝ ነኝ፡፡
“ሳሙኤል... እዚሀ እንዴት መጣሁ...? ምንድነው ያደረገገው...?”አልኩ በአንሶላው ተጠቅልዬ ከአልጋው የመሸሽ ያህል እየወጣሁ:ከአልጋው ፈንጠር ብሎ ወጣ፡፡ ቁምጣ ከሚያህል ቡራቡሬ የውስጥ ሱሪ ሌላ ምንም አላደረገም፡፡
“ሆሆሆ! ምንድነው ያደረግነው? ካርታ ስንጫወት ነዋ ያደርነው”አለኝ፣ እየሣቀ፡፡ ጥርስህ ይርገፍ፡፡
ዝም ብዬው ልብሶቼን ፍለጋ ጀመርኩ፡፡
ሮዝ ጡት ማስያዣዬን አልጋው ግርጌ፣ ጥብቅ ያለው ቀይ የድግስ ቀሚሴን ከአልጋው በስተቀኝ መሬት ላይ አግኝቼ፣ በሰማያዊው ለስላሳ አንሶላ እንደተጠመጠምኩ ወደ ማውቀው መታጠቢያ ቤት ገብቼ ፊቴን ሳልታጠብ መስታወቱ ፊት ቆምኩ፡፡
ምንድነው የሠራሁት?
ምን ነካኝ?
እሺ ለብ ይበለኝ፡፡ እሺ ሞቅ ይበለኝ፡፡ እሺ ልስከር፡፡ እሺ እጄን እንዲይዝ ልፍቀድለት፡፡ እሺ ሲስመኝ ልሳመው፡፡ እሺ ትንሽ ልቃበጥ፡፡ ግን ምንስ ያህል ብጠጣ ከትዕግስት ቤት ወጥቼ፣
መኪናው ውስጥ ገብቼ፣ ከብስራተ ገብርኤል ሰሚት ድረስ ንፋስ እየመታኝ መጥቼ፣ እቤቱ ሄጄ፣ መኝታ ቤቱ ገብቼ፣ አልጋው ጋር ሄጄ፣ አልጋው ውስጥ ገብቼ፣ ልብሴን አውልቄ፣ ራቁቴን ሆኜ፣
እጮኛ (ያውም የሰው ጥግ) እያለኝ፤ ከቀድሞ ፍቀረኛዬ ጋር ስዳራ
ማደሬ ልክ ነው?
ለመልአክ ሩብ ጉዳይ በሆነ እጮኛዬ ላይ
መልከስከሴ ግፍ አይደለም?
ቢሰማ አያብድም?
ቢያውቅ ራሱን አያጠፋም?
ፊቴን በቅጡ ሳልታጠብ፣ ከመታጠቢያ ቤቱ ወጥቼ በጥድፊያ ጫማዬን አድርጌ፣ ቦርሳዬን አነገብኩና... “ስሚኝ...” ምናምን...የሚለኝን ሳሙኤል ሙሉ በሙሉ ዘግቼ እግሬ በፈቀደልኝ ፍጥነት
ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ፡፡
የኮንዶሚኒየሙን ደረጃ እየወረድኩ ስልኬን አወጣሁ፡፡
.
ዐሥራ ዘጠኝ ያመለጡኝ ጥሪዎች፡፡ ሰባት የጽሑፍ መልዕክቶች፡፡ከፈትኩት፡፡
ዐሥራ ስድስቱ የእጮኛዬ ጥሪ ነው፡፡ ስማግጥ ያልመለስኳቸው 16
ጥሪዎች፡፡ እርምጃዬን አቁሜ እጄ እየተንቀጠቀጠ መልዕእክቶቹን
ከፈትኳቸው፡፡ ሁሉም ከእሱ ናቸው፡፡
“ማሬ ስልክ አታነሺም” ... “በሰላም ነው...?”... “ኧረ ተጨነቅኩ”...
.
“በደህናሽ ነው?”... “እባክሽ ደውይልኝ... “ትዕግስትም አላነሳ አለችኝ ... “በናትሽ ደውይልኝ” ....
ኮንዶሚኒየሙ ጣራ ላይ ወጥቼ መፈጥፈጥ አማረኝ፡፡
ልደውልለት ግን ጉልበት አጣሁ፡፡ እሱን ትቼ ትዕግስት ጋር ደወልኩ፡፡ በሁለተኛው ዙር ከአራት ጥሪ በኋላ አነሳች፡፡
ሰላምም ሳልላት፣ “አንቺ ማታ ምንድነው የተፈጠረው?” ብዬ ጮኽኩባት፡፡
“እንዴ እኔ ምናባሽ አውቅልሻለሁ... የት ሆነሽ ነው...?” አለችኝ።ድምፅዋ፣ ቤተክርስትያን ሲያስቀድስ አድሮ የመጣ ሰላማዊ ሰው እንጂ፤ አሸሼ ገዳሜ ሲል ያደረ አይመስልም፡፡
“ምን የት ነሽ?” ትይኛለሽ... ሳሚ ጋር ነበርኩ... እንዴት እንዲህ
ዓይነት ነገር ሲደረግ... እዚህ ሲያመጣኝ ዝም ትያለሽ?” አልኩ፣ ቱግ ብዬ እርምጃዬን እያፈጠንኩ፡፡
“እንዴ... ኧረ ቀስ...! አንቺ አይደለሽ ስንት ሆነን ስንለምንሽ፣ ከእሱ በስተቀር ከማንም ጋር አልሄድም እያልሽ፤ እንደ
እባብ ስትጠመጠሚበት ያመሸሽው?” አለችኝ ቆጣ ብላ፡፡
ወሬውን በስልክ መቀጠል ስላልፈለግኩ፣ ቤት መሆኗን አረጋግጬ ራይድ ጠራሁና ስበር ቤቷ ደረስኩ፡፡
በስልክ የጀመረችልኝን አጠናክራ፣ ለያዥ ለገናዥ ማስቸገሬን፤ ያየኝ ሰው ሁሉ ሲሥቅ እንደነበር፤ መጨረሻ ላይ እንደፈለጋት ትሁን ብለው እንደተዉኝ በሚያም ዝርዝር ነገረችኝ፡፡
ያቀረበችልኝን ቁርስ ሳልነካ ሻዩን ብቻ እየማግኩ፣
“ቲጂ...” አልኳት፡፡
“ወይ...” አለች፣ ዐይን ዐይኔን እያየች፡፡
“ደሬ የሚሰማ ይመስልሻል...? ማለቴ ሰው ቢነግረውስ?” አልኳት፡፡
“እ...ህ አይመስለኝም... ደግነቱ እንደዛ ስታብጂ የነበረው አብዛኛው ሰው ከሄደ በኋላ ነው...ማሐቴ ሳሙኤል ካልተናገረ" አለችኝ።
ሳሙኤል ካልተናገረ!
በተቀመጥኩበት መርዶ እንደተረዳ ሰው
❤1👍1
#የአልጋ_ላይ_ዱካ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
ትላንት ማታ ክፉ ነገር ተፈጠረ፡፡
መልከ መልካሙና ገራገሩ እጮኛዬ ላይ ማገጥኩበት፡፡
ያች በልጣጣ ጓደኛዬ ትዕግስት ናት፣ እዚህ ሁሉ ጣጣ ውስጥ የከተተችኝ።
ሁሌም ለሰኔ ሚካኤል ቤቷ ድል ያለ ድግስ ታዘጋጃለች፡፡ የምታውቀውን ሰው ሁሉ ትጋብዛለች፡፡ ከልክ በላይ
ታበላለች፡፡ ከመጠን በላይ ታጠጣለች፡፡ አንድ ውስኪ ለሦስት ሰው እየቀረበ፣ በረዶ አንሷል እየተባለ ውስኪ እንደተፈጠረ በጉሮሮ ሲንቆረቆር፣ ሰዉ ሁሉ ከማያውቀው ሰው እንደ አብሮ አደግ ይሣሣቃል፣ ያሽካካል፡፡ ምስጢር ይጋራል፡፡ ይሟዘዛል፡፡ የትዕግስት
ፓርቲ እንዲህ ነው፡፡ ነጠላ
ሆኖ የመጣን፣ ጥንድ አድርጎ
ይሸኛል፡፡ አይተው ከማያውቁት ሰው አደጋግፎ፤ አስተቃቅፎ፣አልጋ ድረስ ያጓትታል፡፡
ውስኪዋ ውስጥ ትንሽ ቅንዝር ጠብ፣ ብዙ የፍትወት ፍላጎትና የመማገጥ ዓላማ ሙጅር ታደርግበት ይመስል፤ በየዓመቱ የሚወራ የወሲብ ገድል መነሻ ይሆናል፡፡
ለስድስት ዓመታት ይሄንን የተቀበረ የመጠጥ ፈንጂ አልፌ፤ ዘንድሮው ግን ረገጥኩት፡፡
እርግጥ አድርጌ ብ......ው......
አደረግኩት፡፡ አጀማመሩ እንዲህ ነበር፡፡
ጥሬና ጥብሱን ሥጋ፣ ከዚህ በኋላ ለሳምንት አትበሉም የተባልን ያህል ተስገብግበን ጎስረን፣ ጎስረን፣ “እሰቲ አወራርዱት... እስቲ ጥረጉት” እያለች የምታስተናብረውን ትዕግስት እየሰማን፣ ሁለት ጠርሙስ ውስኪያችንን በጉሮሯችን እያንቆረቆርን ስድስት ሆነን
አንድ ጠረጴዛ ላይ ተሰይመናል፡፡
ከለብታ አልፎ ሞቅታ፣ ከሞቅታ አልፎ ስካር ሲጀማምረኝ ትዕግስት
ወደ ጠረጴዛችን መጥታ፣ “አወራርዱት” ባለች ቁጥር፤ የሞት ሞቴን የብርጭቆዬን አፍ በእጆቼ ለመክደን ብሞክርም፣ ልክ ትንኝ እንደምታባርር ሁሌ እጄን ጧ እያደረገች ታስከፍተኝና በውስኪ
ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ቺርስ ባሉ ቁጥር እጠጣለሁ፡፡
“አትጨምሪልኝ... በቃኝ” እያልኩ በእጄ ብርጭቆውን ለመዝጋት እሞክራለሁ፡፡
እጄን ጧ አድርጋ፣ ብርጭቆዬን አስከፍታኝ ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ቺርስ ባሉ ቁጥር እጠጣለሁ፡፡
እንደገና “አትጨምሪልኝ... በቃኝ” እያልኩ በእጄ ብርጭቆውን ለመዝጋት እሞክራለሁ፡፡
እጄን ጧ አድርጋ፣ ብርጭቆዬን አስከፍታኝ ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ይሄ አዙሪት ለዐሥራ ምናምን ጊዜ እንደቆየ ሳሙኤል ከፊቴ ተከሰተ፡፡ ያንን ሰንደቅ የሚያስቅል ቁመቱን፤ የቀይ ዳማ የደስ ደሳም ፊቱን፣ ቦርጭ አልባ ሰውነቱን ይዞ፣ ሳሙኤል ከፊቱ ተከሰተ፡፡ ያውም አንዴ ሁለት፣ አንዴ አራት፣ አንዴ ስድስት
ሆኖ... ሞቅታዬ አብዝቶት፣ ስካሬ አባዝቶት የቀድሞ ፍቅረኛዬ ሳሙኤል ከፊቴ ተከሰተ።
ሲቀመጥ ትዝ አይለኝም፡፡ እጆቼን ሲያሻሸኝ ግን ትዝ ይለኛል፡፡
መጀመሪያ ሲስመኝ ትዝ አይለኝም፡፡ አፌን አፉ ውስጥ ሳገኘው ግን ትዝ ይለኛል።
መኪናው ላይ ስሳፈር አላስታውስም፡፡ አልጋው ውስጥ መግባቴ ግን ውል ይለኛል፡፡ ልብሳችንን ስናወልቅ ትዝ
አይለኝም፡፡ ዕራቁት ሰውነቱን በስሜት ስቧጭር ግን በደንብ ትዝ ይለኛል።
ከንፈር እየተሻማን ስንቃበጥ፣ አንገቴን ሲልስም፣ ሲስምም፤ ኋላም ሴትነቴን በወፍራም ወንድነቱ ሲከድን፣ መሀሉ መሀሉ ጭለማ በገባበት ሁኔታ ትዝ ይለኛል፡፡
ይሄው ነው፡፡
ጠዋት ላይ፣ አልጋው ውስጥ አናት ከሚፈልጥ ራስ ምታት ጋር
ስነቃ፣ ትላልቅ ድፍርስ ዐይኖቹ ተቀበሉኝ፡፡
ራሴን በሁለት እጆቼ ካልደገፍኩ ቷ ብሎ የሚፈነዳ ስለመሰለኝ፣በቀኝም በግራም እጆቼ ጭንቅላቴን ይዤ፣ ከወገቤ በላይ ብድግ አልኩና፣
“ምንድነው ...! ምንድነው ያደረግነው?” ብዬ ጮኽኩ፡፡ ሳሙኤል
ትላልቅ ዐይኖቹን ፊቱ ላይ እያንጎማለለ ሲያየኝ፣ የራሴ ጩኸት ራስ ምታቴን እያባሰው ከወገቤ በታች ዐየሁ፡፡ እንደፈጠረኝ ነኝ፡፡
“ሳሙኤል... እዚሀ እንዴት መጣሁ...? ምንድነው ያደረገገው...?”አልኩ በአንሶላው ተጠቅልዬ ከአልጋው የመሸሽ ያህል እየወጣሁ:ከአልጋው ፈንጠር ብሎ ወጣ፡፡ ቁምጣ ከሚያህል ቡራቡሬ የውስጥ ሱሪ ሌላ ምንም አላደረገም፡፡
“ሆሆሆ! ምንድነው ያደረግነው? ካርታ ስንጫወት ነዋ ያደርነው”አለኝ፣ እየሣቀ፡፡ ጥርስህ ይርገፍ፡፡
ዝም ብዬው ልብሶቼን ፍለጋ ጀመርኩ፡፡
ሮዝ ጡት ማስያዣዬን አልጋው ግርጌ፣ ጥብቅ ያለው ቀይ የድግስ ቀሚሴን ከአልጋው በስተቀኝ መሬት ላይ አግኝቼ፣ በሰማያዊው ለስላሳ አንሶላ እንደተጠመጠምኩ ወደ ማውቀው መታጠቢያ ቤት ገብቼ ፊቴን ሳልታጠብ መስታወቱ ፊት ቆምኩ፡፡
ምንድነው የሠራሁት?
ምን ነካኝ?
እሺ ለብ ይበለኝ፡፡ እሺ ሞቅ ይበለኝ፡፡ እሺ ልስከር፡፡ እሺ እጄን እንዲይዝ ልፍቀድለት፡፡ እሺ ሲስመኝ ልሳመው፡፡ እሺ ትንሽ ልቃበጥ፡፡ ግን ምንስ ያህል ብጠጣ ከትዕግስት ቤት ወጥቼ፣
መኪናው ውስጥ ገብቼ፣ ከብስራተ ገብርኤል ሰሚት ድረስ ንፋስ እየመታኝ መጥቼ፣ እቤቱ ሄጄ፣ መኝታ ቤቱ ገብቼ፣ አልጋው ጋር ሄጄ፣ አልጋው ውስጥ ገብቼ፣ ልብሴን አውልቄ፣ ራቁቴን ሆኜ፣
እጮኛ (ያውም የሰው ጥግ) እያለኝ፤ ከቀድሞ ፍቀረኛዬ ጋር ስዳራ
ማደሬ ልክ ነው?
ለመልአክ ሩብ ጉዳይ በሆነ እጮኛዬ ላይ
መልከስከሴ ግፍ አይደለም?
ቢሰማ አያብድም?
ቢያውቅ ራሱን አያጠፋም?
ፊቴን በቅጡ ሳልታጠብ፣ ከመታጠቢያ ቤቱ ወጥቼ በጥድፊያ ጫማዬን አድርጌ፣ ቦርሳዬን አነገብኩና... “ስሚኝ...” ምናምን...የሚለኝን ሳሙኤል ሙሉ በሙሉ ዘግቼ እግሬ በፈቀደልኝ ፍጥነት
ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ፡፡
የኮንዶሚኒየሙን ደረጃ እየወረድኩ ስልኬን አወጣሁ፡፡
.
ዐሥራ ዘጠኝ ያመለጡኝ ጥሪዎች፡፡ ሰባት የጽሑፍ መልዕክቶች፡፡ከፈትኩት፡፡
ዐሥራ ስድስቱ የእጮኛዬ ጥሪ ነው፡፡ ስማግጥ ያልመለስኳቸው 16
ጥሪዎች፡፡ እርምጃዬን አቁሜ እጄ እየተንቀጠቀጠ መልዕእክቶቹን
ከፈትኳቸው፡፡ ሁሉም ከእሱ ናቸው፡፡
“ማሬ ስልክ አታነሺም” ... “በሰላም ነው...?”... “ኧረ ተጨነቅኩ”...
.
“በደህናሽ ነው?”... “እባክሽ ደውይልኝ... “ትዕግስትም አላነሳ አለችኝ ... “በናትሽ ደውይልኝ” ....
ኮንዶሚኒየሙ ጣራ ላይ ወጥቼ መፈጥፈጥ አማረኝ፡፡
ልደውልለት ግን ጉልበት አጣሁ፡፡ እሱን ትቼ ትዕግስት ጋር ደወልኩ፡፡ በሁለተኛው ዙር ከአራት ጥሪ በኋላ አነሳች፡፡
ሰላምም ሳልላት፣ “አንቺ ማታ ምንድነው የተፈጠረው?” ብዬ ጮኽኩባት፡፡
“እንዴ እኔ ምናባሽ አውቅልሻለሁ... የት ሆነሽ ነው...?” አለችኝ።ድምፅዋ፣ ቤተክርስትያን ሲያስቀድስ አድሮ የመጣ ሰላማዊ ሰው እንጂ፤ አሸሼ ገዳሜ ሲል ያደረ አይመስልም፡፡
“ምን የት ነሽ?” ትይኛለሽ... ሳሚ ጋር ነበርኩ... እንዴት እንዲህ
ዓይነት ነገር ሲደረግ... እዚህ ሲያመጣኝ ዝም ትያለሽ?” አልኩ፣ ቱግ ብዬ እርምጃዬን እያፈጠንኩ፡፡
“እንዴ... ኧረ ቀስ...! አንቺ አይደለሽ ስንት ሆነን ስንለምንሽ፣ ከእሱ በስተቀር ከማንም ጋር አልሄድም እያልሽ፤ እንደ
እባብ ስትጠመጠሚበት ያመሸሽው?” አለችኝ ቆጣ ብላ፡፡
ወሬውን በስልክ መቀጠል ስላልፈለግኩ፣ ቤት መሆኗን አረጋግጬ ራይድ ጠራሁና ስበር ቤቷ ደረስኩ፡፡
በስልክ የጀመረችልኝን አጠናክራ፣ ለያዥ ለገናዥ ማስቸገሬን፤ ያየኝ ሰው ሁሉ ሲሥቅ እንደነበር፤ መጨረሻ ላይ እንደፈለጋት ትሁን ብለው እንደተዉኝ በሚያም ዝርዝር ነገረችኝ፡፡
ያቀረበችልኝን ቁርስ ሳልነካ ሻዩን ብቻ እየማግኩ፣
“ቲጂ...” አልኳት፡፡
“ወይ...” አለች፣ ዐይን ዐይኔን እያየች፡፡
“ደሬ የሚሰማ ይመስልሻል...? ማለቴ ሰው ቢነግረውስ?” አልኳት፡፡
“እ...ህ አይመስለኝም... ደግነቱ እንደዛ ስታብጂ የነበረው አብዛኛው ሰው ከሄደ በኋላ ነው...ማሐቴ ሳሙኤል ካልተናገረ" አለችኝ።
ሳሙኤል ካልተናገረ!
በተቀመጥኩበት መርዶ እንደተረዳ ሰው
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
ትላንት ማታ ክፉ ነገር ተፈጠረ፡፡
መልከ መልካሙና ገራገሩ እጮኛዬ ላይ ማገጥኩበት፡፡
ያች በልጣጣ ጓደኛዬ ትዕግስት ናት፣ እዚህ ሁሉ ጣጣ ውስጥ የከተተችኝ።
ሁሌም ለሰኔ ሚካኤል ቤቷ ድል ያለ ድግስ ታዘጋጃለች፡፡ የምታውቀውን ሰው ሁሉ ትጋብዛለች፡፡ ከልክ በላይ
ታበላለች፡፡ ከመጠን በላይ ታጠጣለች፡፡ አንድ ውስኪ ለሦስት ሰው እየቀረበ፣ በረዶ አንሷል እየተባለ ውስኪ እንደተፈጠረ በጉሮሮ ሲንቆረቆር፣ ሰዉ ሁሉ ከማያውቀው ሰው እንደ አብሮ አደግ ይሣሣቃል፣ ያሽካካል፡፡ ምስጢር ይጋራል፡፡ ይሟዘዛል፡፡ የትዕግስት
ፓርቲ እንዲህ ነው፡፡ ነጠላ
ሆኖ የመጣን፣ ጥንድ አድርጎ
ይሸኛል፡፡ አይተው ከማያውቁት ሰው አደጋግፎ፤ አስተቃቅፎ፣አልጋ ድረስ ያጓትታል፡፡
ውስኪዋ ውስጥ ትንሽ ቅንዝር ጠብ፣ ብዙ የፍትወት ፍላጎትና የመማገጥ ዓላማ ሙጅር ታደርግበት ይመስል፤ በየዓመቱ የሚወራ የወሲብ ገድል መነሻ ይሆናል፡፡
ለስድስት ዓመታት ይሄንን የተቀበረ የመጠጥ ፈንጂ አልፌ፤ ዘንድሮው ግን ረገጥኩት፡፡
እርግጥ አድርጌ ብ......ው......
አደረግኩት፡፡ አጀማመሩ እንዲህ ነበር፡፡
ጥሬና ጥብሱን ሥጋ፣ ከዚህ በኋላ ለሳምንት አትበሉም የተባልን ያህል ተስገብግበን ጎስረን፣ ጎስረን፣ “እሰቲ አወራርዱት... እስቲ ጥረጉት” እያለች የምታስተናብረውን ትዕግስት እየሰማን፣ ሁለት ጠርሙስ ውስኪያችንን በጉሮሯችን እያንቆረቆርን ስድስት ሆነን
አንድ ጠረጴዛ ላይ ተሰይመናል፡፡
ከለብታ አልፎ ሞቅታ፣ ከሞቅታ አልፎ ስካር ሲጀማምረኝ ትዕግስት
ወደ ጠረጴዛችን መጥታ፣ “አወራርዱት” ባለች ቁጥር፤ የሞት ሞቴን የብርጭቆዬን አፍ በእጆቼ ለመክደን ብሞክርም፣ ልክ ትንኝ እንደምታባርር ሁሌ እጄን ጧ እያደረገች ታስከፍተኝና በውስኪ
ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ቺርስ ባሉ ቁጥር እጠጣለሁ፡፡
“አትጨምሪልኝ... በቃኝ” እያልኩ በእጄ ብርጭቆውን ለመዝጋት እሞክራለሁ፡፡
እጄን ጧ አድርጋ፣ ብርጭቆዬን አስከፍታኝ ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ቺርስ ባሉ ቁጥር እጠጣለሁ፡፡
እንደገና “አትጨምሪልኝ... በቃኝ” እያልኩ በእጄ ብርጭቆውን ለመዝጋት እሞክራለሁ፡፡
እጄን ጧ አድርጋ፣ ብርጭቆዬን አስከፍታኝ ሞልታው ትሄዳለች፡፡
ይሄ አዙሪት ለዐሥራ ምናምን ጊዜ እንደቆየ ሳሙኤል ከፊቴ ተከሰተ፡፡ ያንን ሰንደቅ የሚያስቅል ቁመቱን፤ የቀይ ዳማ የደስ ደሳም ፊቱን፣ ቦርጭ አልባ ሰውነቱን ይዞ፣ ሳሙኤል ከፊቱ ተከሰተ፡፡ ያውም አንዴ ሁለት፣ አንዴ አራት፣ አንዴ ስድስት
ሆኖ... ሞቅታዬ አብዝቶት፣ ስካሬ አባዝቶት የቀድሞ ፍቅረኛዬ ሳሙኤል ከፊቴ ተከሰተ።
ሲቀመጥ ትዝ አይለኝም፡፡ እጆቼን ሲያሻሸኝ ግን ትዝ ይለኛል፡፡
መጀመሪያ ሲስመኝ ትዝ አይለኝም፡፡ አፌን አፉ ውስጥ ሳገኘው ግን ትዝ ይለኛል።
መኪናው ላይ ስሳፈር አላስታውስም፡፡ አልጋው ውስጥ መግባቴ ግን ውል ይለኛል፡፡ ልብሳችንን ስናወልቅ ትዝ
አይለኝም፡፡ ዕራቁት ሰውነቱን በስሜት ስቧጭር ግን በደንብ ትዝ ይለኛል።
ከንፈር እየተሻማን ስንቃበጥ፣ አንገቴን ሲልስም፣ ሲስምም፤ ኋላም ሴትነቴን በወፍራም ወንድነቱ ሲከድን፣ መሀሉ መሀሉ ጭለማ በገባበት ሁኔታ ትዝ ይለኛል፡፡
ይሄው ነው፡፡
ጠዋት ላይ፣ አልጋው ውስጥ አናት ከሚፈልጥ ራስ ምታት ጋር
ስነቃ፣ ትላልቅ ድፍርስ ዐይኖቹ ተቀበሉኝ፡፡
ራሴን በሁለት እጆቼ ካልደገፍኩ ቷ ብሎ የሚፈነዳ ስለመሰለኝ፣በቀኝም በግራም እጆቼ ጭንቅላቴን ይዤ፣ ከወገቤ በላይ ብድግ አልኩና፣
“ምንድነው ...! ምንድነው ያደረግነው?” ብዬ ጮኽኩ፡፡ ሳሙኤል
ትላልቅ ዐይኖቹን ፊቱ ላይ እያንጎማለለ ሲያየኝ፣ የራሴ ጩኸት ራስ ምታቴን እያባሰው ከወገቤ በታች ዐየሁ፡፡ እንደፈጠረኝ ነኝ፡፡
“ሳሙኤል... እዚሀ እንዴት መጣሁ...? ምንድነው ያደረገገው...?”አልኩ በአንሶላው ተጠቅልዬ ከአልጋው የመሸሽ ያህል እየወጣሁ:ከአልጋው ፈንጠር ብሎ ወጣ፡፡ ቁምጣ ከሚያህል ቡራቡሬ የውስጥ ሱሪ ሌላ ምንም አላደረገም፡፡
“ሆሆሆ! ምንድነው ያደረግነው? ካርታ ስንጫወት ነዋ ያደርነው”አለኝ፣ እየሣቀ፡፡ ጥርስህ ይርገፍ፡፡
ዝም ብዬው ልብሶቼን ፍለጋ ጀመርኩ፡፡
ሮዝ ጡት ማስያዣዬን አልጋው ግርጌ፣ ጥብቅ ያለው ቀይ የድግስ ቀሚሴን ከአልጋው በስተቀኝ መሬት ላይ አግኝቼ፣ በሰማያዊው ለስላሳ አንሶላ እንደተጠመጠምኩ ወደ ማውቀው መታጠቢያ ቤት ገብቼ ፊቴን ሳልታጠብ መስታወቱ ፊት ቆምኩ፡፡
ምንድነው የሠራሁት?
ምን ነካኝ?
እሺ ለብ ይበለኝ፡፡ እሺ ሞቅ ይበለኝ፡፡ እሺ ልስከር፡፡ እሺ እጄን እንዲይዝ ልፍቀድለት፡፡ እሺ ሲስመኝ ልሳመው፡፡ እሺ ትንሽ ልቃበጥ፡፡ ግን ምንስ ያህል ብጠጣ ከትዕግስት ቤት ወጥቼ፣
መኪናው ውስጥ ገብቼ፣ ከብስራተ ገብርኤል ሰሚት ድረስ ንፋስ እየመታኝ መጥቼ፣ እቤቱ ሄጄ፣ መኝታ ቤቱ ገብቼ፣ አልጋው ጋር ሄጄ፣ አልጋው ውስጥ ገብቼ፣ ልብሴን አውልቄ፣ ራቁቴን ሆኜ፣
እጮኛ (ያውም የሰው ጥግ) እያለኝ፤ ከቀድሞ ፍቀረኛዬ ጋር ስዳራ
ማደሬ ልክ ነው?
ለመልአክ ሩብ ጉዳይ በሆነ እጮኛዬ ላይ
መልከስከሴ ግፍ አይደለም?
ቢሰማ አያብድም?
ቢያውቅ ራሱን አያጠፋም?
ፊቴን በቅጡ ሳልታጠብ፣ ከመታጠቢያ ቤቱ ወጥቼ በጥድፊያ ጫማዬን አድርጌ፣ ቦርሳዬን አነገብኩና... “ስሚኝ...” ምናምን...የሚለኝን ሳሙኤል ሙሉ በሙሉ ዘግቼ እግሬ በፈቀደልኝ ፍጥነት
ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ፡፡
የኮንዶሚኒየሙን ደረጃ እየወረድኩ ስልኬን አወጣሁ፡፡
.
ዐሥራ ዘጠኝ ያመለጡኝ ጥሪዎች፡፡ ሰባት የጽሑፍ መልዕክቶች፡፡ከፈትኩት፡፡
ዐሥራ ስድስቱ የእጮኛዬ ጥሪ ነው፡፡ ስማግጥ ያልመለስኳቸው 16
ጥሪዎች፡፡ እርምጃዬን አቁሜ እጄ እየተንቀጠቀጠ መልዕእክቶቹን
ከፈትኳቸው፡፡ ሁሉም ከእሱ ናቸው፡፡
“ማሬ ስልክ አታነሺም” ... “በሰላም ነው...?”... “ኧረ ተጨነቅኩ”...
.
“በደህናሽ ነው?”... “እባክሽ ደውይልኝ... “ትዕግስትም አላነሳ አለችኝ ... “በናትሽ ደውይልኝ” ....
ኮንዶሚኒየሙ ጣራ ላይ ወጥቼ መፈጥፈጥ አማረኝ፡፡
ልደውልለት ግን ጉልበት አጣሁ፡፡ እሱን ትቼ ትዕግስት ጋር ደወልኩ፡፡ በሁለተኛው ዙር ከአራት ጥሪ በኋላ አነሳች፡፡
ሰላምም ሳልላት፣ “አንቺ ማታ ምንድነው የተፈጠረው?” ብዬ ጮኽኩባት፡፡
“እንዴ እኔ ምናባሽ አውቅልሻለሁ... የት ሆነሽ ነው...?” አለችኝ።ድምፅዋ፣ ቤተክርስትያን ሲያስቀድስ አድሮ የመጣ ሰላማዊ ሰው እንጂ፤ አሸሼ ገዳሜ ሲል ያደረ አይመስልም፡፡
“ምን የት ነሽ?” ትይኛለሽ... ሳሚ ጋር ነበርኩ... እንዴት እንዲህ
ዓይነት ነገር ሲደረግ... እዚህ ሲያመጣኝ ዝም ትያለሽ?” አልኩ፣ ቱግ ብዬ እርምጃዬን እያፈጠንኩ፡፡
“እንዴ... ኧረ ቀስ...! አንቺ አይደለሽ ስንት ሆነን ስንለምንሽ፣ ከእሱ በስተቀር ከማንም ጋር አልሄድም እያልሽ፤ እንደ
እባብ ስትጠመጠሚበት ያመሸሽው?” አለችኝ ቆጣ ብላ፡፡
ወሬውን በስልክ መቀጠል ስላልፈለግኩ፣ ቤት መሆኗን አረጋግጬ ራይድ ጠራሁና ስበር ቤቷ ደረስኩ፡፡
በስልክ የጀመረችልኝን አጠናክራ፣ ለያዥ ለገናዥ ማስቸገሬን፤ ያየኝ ሰው ሁሉ ሲሥቅ እንደነበር፤ መጨረሻ ላይ እንደፈለጋት ትሁን ብለው እንደተዉኝ በሚያም ዝርዝር ነገረችኝ፡፡
ያቀረበችልኝን ቁርስ ሳልነካ ሻዩን ብቻ እየማግኩ፣
“ቲጂ...” አልኳት፡፡
“ወይ...” አለች፣ ዐይን ዐይኔን እያየች፡፡
“ደሬ የሚሰማ ይመስልሻል...? ማለቴ ሰው ቢነግረውስ?” አልኳት፡፡
“እ...ህ አይመስለኝም... ደግነቱ እንደዛ ስታብጂ የነበረው አብዛኛው ሰው ከሄደ በኋላ ነው...ማሐቴ ሳሙኤል ካልተናገረ" አለችኝ።
ሳሙኤል ካልተናገረ!
በተቀመጥኩበት መርዶ እንደተረዳ ሰው
👍70❤6😱3🔥2👏1