#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አሰር
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የፋንቲን ታሪክ ምን ዓይነት ታሪክ ነው? ያሽከር ታሪክ! አሽከርን
የሚገዛው ሕብረተሰቡ ነው?
ከማን?
ከችግር? ከመከራ? ከስቃይ? ከረሃብ? ከብቸኝነት? የሚቀፍ ግዢ ነፍስ በዳቦ ሲለወጥ! ችግር ግለሰቦች ያልፈቀዱትንና ያልፈለጉትን እንዲሠሩ
ሲያስገድዳቸው! ሕብረተሰቡ ደግሞ በግዳጅ የሚያደርጉትን በደስታ ሲቀበል አይገርምም!
ባርነት ቀርቷል ይባላል፡፡ ውሸት ነው፧ አልቀረም:: አሁንም አለ።
ግን በአሁኑ ጊዜ ጎልቶ የሚታየው በሴቶች ላይ ነው:: ስሙን ቀይረው
ዝሙት አዳሪ ይሉታል፡፡
እስካሁን ባየነው ድራማ ፋንቲን ቀደም ሲል የነበራትን ሁሉ አሟጥጣ ጨርሳ የቀራት ነገር የለም :: ክብርም፧ ስምም፧ እናትነትም፤ ውበትም ምኑ ቅጡ ሁሉም ሄዶአል:: ቢነኳት አካልዋ እንደ በረዶ ቀዝቅዟል። ስሜትዋም ሞቷል፡፡ የፈለገችውን ነው የምታደርገው:: እያወቀች
አታውቅም ፡ እየሰማች አትሰማም፡፡ የተከፋን ፊት አንግታ፤ ሆድ የባሰውን ልብ ተሸክማ እያየ የማያይ ዓይን ሰክታ እየሰማ የማይሰማ ጆሮ አንጠልጥላ እንደፈቀደችው ትኖራለች:: ሕብረተሰቡም ሆነ ሕይወት ከፋንቲን ጋር የነበረውን ግንኙነት አቋረጠ፡፡ እሷም ለምንም ነገር ደንታ አጣች፡፡ሊደርስባት የሚችል መጥፎ ነገር ሁሉ ደርሶባታል፡፡ እርሷም የቻለችውን ያህል ተሸክማዋለች፡፡ ሁሉንም አየችው:: የነበራትን ሁሉ አጣች:: ለሁሉም
አለቀሰች፤ አነባች፡፡ ታዲያ አሁን ምን ይሁን? ሁሉንም እርግፍ አድርጋ ተወችው:: ምቾትና ድሎት ችግርን ስለማያውቁት እንደማይጨነቁለት
ሁሉ እንዲሁም ሕፃን ሞት እንቅልፍ መስሎት ዝም እንደሚል ሁሉ እርስዋም ምንም ነገር እንዳልሆነ ቆጥራ ችግር አልተው ቢላት እርስዋ ተወችው:: የምትፈራው ወይም የምትሸሸው ነገር የለም:: ደመና
ቢያጠልልባት፣ ውቅያኖስ ቢደፋባት ምን ደንታ አላት! የኑሮዋ ስፍንጎና ሞልቶ ፈስሷል፡፡
የፋንቲን እምነት ይህ ነበር፡፡ ግን ተሳስታለች:: ማነው እስቲ
መጨረሻውን የሚያውቅ? ዛሬ እንዴት እንደሚያልፍ፤ ነገ ደግሞ እንዴት ሆኖ እንደሚመጣ ማን ያውቀዋል? ሁሉንም የሚያውቅ ፈጣሪ አምላክ ብቻ ነው::
ትንንሽ ከተማዎች ውስጥ አሉ አይደል ኣንዳንድ ልባቸው ያበጠ
ጎረምሶች! በትንሽ ገቢ እንደ ሀብታም የሚንቀባረሩ! ጉራቸው አያድርስ፤ ሳይኖራቸው ሀብታም፧ ሳይማሩ ተመራማሪ፧ ያልሆኑትን ለመሆን ሞካሪ፤ ቡና ቤት ሲገቡ የሚጀነኑ፤ ሲጃራ ማጨስ፤ ሸሚዝ መጠቅለል፤ የጫማ ተረከዝ ማስረዘም፧ ሳይነኩ መነጫነጭ፤ «እስቲ ቅጂ እባክሽ» ማለት፧ ሻይ
ቤት የሚያዘወትሩ፤ አላፊ አግዳሚውን የሚለክፉ፧ ይህን የመሰሉ ሰዎች የትም አሉ:: በተለይ ትንንሽ ከተማ ውስጥ እድሜያቸው እየገፋ ሲሄድ
እየደደቡ የሚሄዱና በአንጎላቸው ሳይሆን በቂጣቸው የሚያስቡ ሞልተዋል፡፡
በ1823 ዓ.ም. ይህን የመሰለ ጠባይ የነበረው አውደልዳይ፤ ጎፈሬ ብርቁና ዘመናዊ መስሎ በሰው ስቃይ የሚደሰት ጎረምሳ ነበር:: ይህ ጎረምሳ ሰው ከተሰበሰበበት ቡና ቤት ላይ ታች የምትለውን፧ ኑሮ ያንገላታትን፤
የማይሆን ልብስ የለበሰችውና ክበር ገላዋን ለጎረምሳ አሳልፋ የምትሸጠዋን ሴት ደጋግሞ የሚለክፍ ወጣት ነበር፡፡ አንድ ቀን ፋንቲንን እንደልማዱ ለከፋት:: እንዳልሰማ ዝም አለችው:: ሲጃራ ማጨስ ፋሽን ነውና ተመልሳ
በአጠገበ ስታልፍ የሲጃራ ጭስ አቦነነባት:: በአጠገቡ በአለፈች ቁጥር «ፉንጋ፧ ኡኡቴ፣ የምን መኮሳተር ነው? ጥርስ አልጠፋብሽም? እና ሌላም
ሌላም እያለ ሰደባት:: ይህ ሰው ፋንቲንን ሲያናግራት ቀና ብላ እንኳን አላየችውም:: ልክ ቅጣት እንደተወሰነበት ወታደር ከወዲያ ወዲህ ገልመጥ ሳትል ወደፊት ትሄድና ትመለሳለች:: አሁንም እንደገና ወደፊት ትሄድና
ተመልሳ ትመጣለች:: ሰውዬው ብዙ ጊዜ ከለከፋት በኋላ በመጨረሻ ዝም ስትለው በጣም ተናድዶ ኖሮ ቀስ ብሎ ተከትሎአት ይሄድና ልክ ለመመለስ ፊትዋን ስታዞር መንገድ ግራና ቀኝ ተቆልለ ከነበረው በረዶ ያነሳና
በጀርባዋ በኩል ይመታታል፡፡ ይህን ጊዜ ልክ እንደነብር ዘልላ አንገቱ ላይ በመጠምጠም በጥፍርዋ ፊቱን ደም በደም አደረገችው:: ሰምቶት የማያውቅ
የስድብ ናዳ አወረደችበት፡፡
ጩኸትዋ በአካባቢው ከነበረው ሻይ ቤት ተሰምቶ ሰዎች ምንድነው ብለው ወጡ፡፡ ቀስ በቀስ ብዙ ሰው ተሰበሰ ሰውዬው አልሞት ባይ ተጋዳይ ከሚቧጥጠው ጥፍር ይከላከላል፡፡ የተሰበሰበው ሕዝብ «ብራቮ እያለ ይስቃል፤ ያጨበጭባል፡፡ ፋንቲን መቧጠጥ ብቻ ሳይሆን በጥፊ በርግጫ
ትማታለች፡፡
ድንገት አንድ እረጅም ሰው እየሮጠ መጥቶ ሴትዮዋን በጭቃ
የቦካውን ወገብዋን ይዞ «በይ ተከተዪኝ አላት::
እንገትዋን ቀና አደረገች፡፡ የጋለው ሰውነትዋ በረደ ፣ በቁጣ የነደደው
ድምፅዋ ቀዝቀዝ አለ፡፡ በፍርሃት ተንቀጠቀጠች፡፡ የፖሊሱ አዛዥ ዣቬር እንደሆነ አውቀች::
በግርግር አውደልዳዩ ሹልክ ብሎ ከዚያ ጠፋ::
ከዚያ ከብበው የቆሙትን ሁሉ ዣቬር በተናቸው:: ከዚያም ሴትዮዋን እየጐተተ ወደ ቢሮው ወሰዳት፡፡ ቢሮው ከዚያ ሩቅ አልነበረም:: ሴትዮዋ ብዙም ሳታመነታ ተከተለችው:: ቃል አልተነፈሰችም፡፡ ተሰብስቦ የነበረው ሕዝብ ሴትዮዋን ለእብደት በሚዳርግ ፌዝና ሰቆቃ አሽሟጠጣት::
ከፖሊስ ጣቢያ እንደደረሱ ዣቬር በር ከፍቶ ፋንቲንን ይዞ ገባ፡፡ በሩን
መልሶ ዘጋው:: ፋንቲን እንደ ፈራ ውሻ ቃል ሳታሰማ ጥግ ይዛ ከወለሉ ላይ ቁጭ አለች፡፡ ዘበኛው መብራት አበራ፡፡ ዣቬር ከኪሱ ወረቀት አውጥቶ መጻፍ ጀመረ::
የፖሊሱ አዛዥ ኮስተርተር ያለ ሰው በመሆኑ ፊቱ ላይ የመቅበጥበጥ
ምልክት አይታይበትም፡፡ ሕግን የማስከበር ጥማቱ የሚያረካባት ቅጽበት በመሆኑ ሥልጣኑን ለማሳየት ተነሳሳ፡፡ የተቀመጠበት ወንበር ትክክለኛ ፍርድ የሚሰጥበት ሥፍራ እንደሆነ ከልቡ ያምናል፡፡ ከሳሽም፧ ፍርድ
ሰጪም ራሱ ነው፡፡ የሴትዮዋን አድራጎት በይበልጥ በአጤነ ቁጥር ወንጀለኝነቷን ከመጠራጠር ይገታል፡፡ ወንጀል ስትፈጽም በዓይኑ አይቷል፡፡ አንዲት
ሴት አዳሪ አንዱን የከተማ ነዋሪ ከሰው ፊት ደብድባለች፡፡ ለዚህ ጥፋት ዣቬር ራሱ የዓይን ምስክር ነው፡፡ ፀጥ ብሎ ሁኔታውን መዘገበ፡፡
የጊዜውን ራፖር መዝግቦ ሲጨርስ ፊርማውን አኖረበት፡፡ ወረቀቱ አጣጥፎ ለዘበኛው ሰጠው::
«ሦስት ሰዎች ይዘህ ይህችን ሴት እስር ቤት ውሰድዋት፡፡»
ወደ ፋንቲን ዞር ብሎ «የስድስት ወር እስራት ተፈርዶብሻል» አላት፡፡
እድለ ቢስዋ ሴትዮ ሰውነትዋ ተንቀጠቀጠ፡፡
«ስድስት ወር! ወህኒ ቤት ውስጥ ስድስት ወር ሙሉ!» ብላ በኃይል
ተነፈሰች፡፡ «ልጄስ!» ስድስት ወር ሙሉ ምን ልትሆን ወይኔ ልጄ! እስከዛሬ ለእነቴናድዬ ያልከፈልኩት ከመቶ ፍራንክ በላይ እዳ አለብኝ፡፡ ጌታዬ ይህን
ያውቃሉ?» ስትል ዣቬርን ጠየቀችው::
መሬት ላይ ተንከባለለች:: ሦስቱ ሰዎች ከአፈሩ ላይ እንደወደቀች
ጎትተው አስወጥዋት::
«መሴይ ዣቬር ማሩኝ፡ ይቅር በሉኝ» ስትል ጮኸች:: «ምንም
ዓይነት በደል እንዳልፈጸምኩም! እምልልዎታለሁ:: ከመጀመሪያው ጀምሮ ከሥፍራው ቢኖሩ ኖሮ እውነቱን ያዩ ነበር፡፡ በእግዚአብሔር ስም እምላለሁ!
፡
፡
#ክፍል_አሰር
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የፋንቲን ታሪክ ምን ዓይነት ታሪክ ነው? ያሽከር ታሪክ! አሽከርን
የሚገዛው ሕብረተሰቡ ነው?
ከማን?
ከችግር? ከመከራ? ከስቃይ? ከረሃብ? ከብቸኝነት? የሚቀፍ ግዢ ነፍስ በዳቦ ሲለወጥ! ችግር ግለሰቦች ያልፈቀዱትንና ያልፈለጉትን እንዲሠሩ
ሲያስገድዳቸው! ሕብረተሰቡ ደግሞ በግዳጅ የሚያደርጉትን በደስታ ሲቀበል አይገርምም!
ባርነት ቀርቷል ይባላል፡፡ ውሸት ነው፧ አልቀረም:: አሁንም አለ።
ግን በአሁኑ ጊዜ ጎልቶ የሚታየው በሴቶች ላይ ነው:: ስሙን ቀይረው
ዝሙት አዳሪ ይሉታል፡፡
እስካሁን ባየነው ድራማ ፋንቲን ቀደም ሲል የነበራትን ሁሉ አሟጥጣ ጨርሳ የቀራት ነገር የለም :: ክብርም፧ ስምም፧ እናትነትም፤ ውበትም ምኑ ቅጡ ሁሉም ሄዶአል:: ቢነኳት አካልዋ እንደ በረዶ ቀዝቅዟል። ስሜትዋም ሞቷል፡፡ የፈለገችውን ነው የምታደርገው:: እያወቀች
አታውቅም ፡ እየሰማች አትሰማም፡፡ የተከፋን ፊት አንግታ፤ ሆድ የባሰውን ልብ ተሸክማ እያየ የማያይ ዓይን ሰክታ እየሰማ የማይሰማ ጆሮ አንጠልጥላ እንደፈቀደችው ትኖራለች:: ሕብረተሰቡም ሆነ ሕይወት ከፋንቲን ጋር የነበረውን ግንኙነት አቋረጠ፡፡ እሷም ለምንም ነገር ደንታ አጣች፡፡ሊደርስባት የሚችል መጥፎ ነገር ሁሉ ደርሶባታል፡፡ እርሷም የቻለችውን ያህል ተሸክማዋለች፡፡ ሁሉንም አየችው:: የነበራትን ሁሉ አጣች:: ለሁሉም
አለቀሰች፤ አነባች፡፡ ታዲያ አሁን ምን ይሁን? ሁሉንም እርግፍ አድርጋ ተወችው:: ምቾትና ድሎት ችግርን ስለማያውቁት እንደማይጨነቁለት
ሁሉ እንዲሁም ሕፃን ሞት እንቅልፍ መስሎት ዝም እንደሚል ሁሉ እርስዋም ምንም ነገር እንዳልሆነ ቆጥራ ችግር አልተው ቢላት እርስዋ ተወችው:: የምትፈራው ወይም የምትሸሸው ነገር የለም:: ደመና
ቢያጠልልባት፣ ውቅያኖስ ቢደፋባት ምን ደንታ አላት! የኑሮዋ ስፍንጎና ሞልቶ ፈስሷል፡፡
የፋንቲን እምነት ይህ ነበር፡፡ ግን ተሳስታለች:: ማነው እስቲ
መጨረሻውን የሚያውቅ? ዛሬ እንዴት እንደሚያልፍ፤ ነገ ደግሞ እንዴት ሆኖ እንደሚመጣ ማን ያውቀዋል? ሁሉንም የሚያውቅ ፈጣሪ አምላክ ብቻ ነው::
ትንንሽ ከተማዎች ውስጥ አሉ አይደል ኣንዳንድ ልባቸው ያበጠ
ጎረምሶች! በትንሽ ገቢ እንደ ሀብታም የሚንቀባረሩ! ጉራቸው አያድርስ፤ ሳይኖራቸው ሀብታም፧ ሳይማሩ ተመራማሪ፧ ያልሆኑትን ለመሆን ሞካሪ፤ ቡና ቤት ሲገቡ የሚጀነኑ፤ ሲጃራ ማጨስ፤ ሸሚዝ መጠቅለል፤ የጫማ ተረከዝ ማስረዘም፧ ሳይነኩ መነጫነጭ፤ «እስቲ ቅጂ እባክሽ» ማለት፧ ሻይ
ቤት የሚያዘወትሩ፤ አላፊ አግዳሚውን የሚለክፉ፧ ይህን የመሰሉ ሰዎች የትም አሉ:: በተለይ ትንንሽ ከተማ ውስጥ እድሜያቸው እየገፋ ሲሄድ
እየደደቡ የሚሄዱና በአንጎላቸው ሳይሆን በቂጣቸው የሚያስቡ ሞልተዋል፡፡
በ1823 ዓ.ም. ይህን የመሰለ ጠባይ የነበረው አውደልዳይ፤ ጎፈሬ ብርቁና ዘመናዊ መስሎ በሰው ስቃይ የሚደሰት ጎረምሳ ነበር:: ይህ ጎረምሳ ሰው ከተሰበሰበበት ቡና ቤት ላይ ታች የምትለውን፧ ኑሮ ያንገላታትን፤
የማይሆን ልብስ የለበሰችውና ክበር ገላዋን ለጎረምሳ አሳልፋ የምትሸጠዋን ሴት ደጋግሞ የሚለክፍ ወጣት ነበር፡፡ አንድ ቀን ፋንቲንን እንደልማዱ ለከፋት:: እንዳልሰማ ዝም አለችው:: ሲጃራ ማጨስ ፋሽን ነውና ተመልሳ
በአጠገበ ስታልፍ የሲጃራ ጭስ አቦነነባት:: በአጠገቡ በአለፈች ቁጥር «ፉንጋ፧ ኡኡቴ፣ የምን መኮሳተር ነው? ጥርስ አልጠፋብሽም? እና ሌላም
ሌላም እያለ ሰደባት:: ይህ ሰው ፋንቲንን ሲያናግራት ቀና ብላ እንኳን አላየችውም:: ልክ ቅጣት እንደተወሰነበት ወታደር ከወዲያ ወዲህ ገልመጥ ሳትል ወደፊት ትሄድና ትመለሳለች:: አሁንም እንደገና ወደፊት ትሄድና
ተመልሳ ትመጣለች:: ሰውዬው ብዙ ጊዜ ከለከፋት በኋላ በመጨረሻ ዝም ስትለው በጣም ተናድዶ ኖሮ ቀስ ብሎ ተከትሎአት ይሄድና ልክ ለመመለስ ፊትዋን ስታዞር መንገድ ግራና ቀኝ ተቆልለ ከነበረው በረዶ ያነሳና
በጀርባዋ በኩል ይመታታል፡፡ ይህን ጊዜ ልክ እንደነብር ዘልላ አንገቱ ላይ በመጠምጠም በጥፍርዋ ፊቱን ደም በደም አደረገችው:: ሰምቶት የማያውቅ
የስድብ ናዳ አወረደችበት፡፡
ጩኸትዋ በአካባቢው ከነበረው ሻይ ቤት ተሰምቶ ሰዎች ምንድነው ብለው ወጡ፡፡ ቀስ በቀስ ብዙ ሰው ተሰበሰ ሰውዬው አልሞት ባይ ተጋዳይ ከሚቧጥጠው ጥፍር ይከላከላል፡፡ የተሰበሰበው ሕዝብ «ብራቮ እያለ ይስቃል፤ ያጨበጭባል፡፡ ፋንቲን መቧጠጥ ብቻ ሳይሆን በጥፊ በርግጫ
ትማታለች፡፡
ድንገት አንድ እረጅም ሰው እየሮጠ መጥቶ ሴትዮዋን በጭቃ
የቦካውን ወገብዋን ይዞ «በይ ተከተዪኝ አላት::
እንገትዋን ቀና አደረገች፡፡ የጋለው ሰውነትዋ በረደ ፣ በቁጣ የነደደው
ድምፅዋ ቀዝቀዝ አለ፡፡ በፍርሃት ተንቀጠቀጠች፡፡ የፖሊሱ አዛዥ ዣቬር እንደሆነ አውቀች::
በግርግር አውደልዳዩ ሹልክ ብሎ ከዚያ ጠፋ::
ከዚያ ከብበው የቆሙትን ሁሉ ዣቬር በተናቸው:: ከዚያም ሴትዮዋን እየጐተተ ወደ ቢሮው ወሰዳት፡፡ ቢሮው ከዚያ ሩቅ አልነበረም:: ሴትዮዋ ብዙም ሳታመነታ ተከተለችው:: ቃል አልተነፈሰችም፡፡ ተሰብስቦ የነበረው ሕዝብ ሴትዮዋን ለእብደት በሚዳርግ ፌዝና ሰቆቃ አሽሟጠጣት::
ከፖሊስ ጣቢያ እንደደረሱ ዣቬር በር ከፍቶ ፋንቲንን ይዞ ገባ፡፡ በሩን
መልሶ ዘጋው:: ፋንቲን እንደ ፈራ ውሻ ቃል ሳታሰማ ጥግ ይዛ ከወለሉ ላይ ቁጭ አለች፡፡ ዘበኛው መብራት አበራ፡፡ ዣቬር ከኪሱ ወረቀት አውጥቶ መጻፍ ጀመረ::
የፖሊሱ አዛዥ ኮስተርተር ያለ ሰው በመሆኑ ፊቱ ላይ የመቅበጥበጥ
ምልክት አይታይበትም፡፡ ሕግን የማስከበር ጥማቱ የሚያረካባት ቅጽበት በመሆኑ ሥልጣኑን ለማሳየት ተነሳሳ፡፡ የተቀመጠበት ወንበር ትክክለኛ ፍርድ የሚሰጥበት ሥፍራ እንደሆነ ከልቡ ያምናል፡፡ ከሳሽም፧ ፍርድ
ሰጪም ራሱ ነው፡፡ የሴትዮዋን አድራጎት በይበልጥ በአጤነ ቁጥር ወንጀለኝነቷን ከመጠራጠር ይገታል፡፡ ወንጀል ስትፈጽም በዓይኑ አይቷል፡፡ አንዲት
ሴት አዳሪ አንዱን የከተማ ነዋሪ ከሰው ፊት ደብድባለች፡፡ ለዚህ ጥፋት ዣቬር ራሱ የዓይን ምስክር ነው፡፡ ፀጥ ብሎ ሁኔታውን መዘገበ፡፡
የጊዜውን ራፖር መዝግቦ ሲጨርስ ፊርማውን አኖረበት፡፡ ወረቀቱ አጣጥፎ ለዘበኛው ሰጠው::
«ሦስት ሰዎች ይዘህ ይህችን ሴት እስር ቤት ውሰድዋት፡፡»
ወደ ፋንቲን ዞር ብሎ «የስድስት ወር እስራት ተፈርዶብሻል» አላት፡፡
እድለ ቢስዋ ሴትዮ ሰውነትዋ ተንቀጠቀጠ፡፡
«ስድስት ወር! ወህኒ ቤት ውስጥ ስድስት ወር ሙሉ!» ብላ በኃይል
ተነፈሰች፡፡ «ልጄስ!» ስድስት ወር ሙሉ ምን ልትሆን ወይኔ ልጄ! እስከዛሬ ለእነቴናድዬ ያልከፈልኩት ከመቶ ፍራንክ በላይ እዳ አለብኝ፡፡ ጌታዬ ይህን
ያውቃሉ?» ስትል ዣቬርን ጠየቀችው::
መሬት ላይ ተንከባለለች:: ሦስቱ ሰዎች ከአፈሩ ላይ እንደወደቀች
ጎትተው አስወጥዋት::
«መሴይ ዣቬር ማሩኝ፡ ይቅር በሉኝ» ስትል ጮኸች:: «ምንም
ዓይነት በደል እንዳልፈጸምኩም! እምልልዎታለሁ:: ከመጀመሪያው ጀምሮ ከሥፍራው ቢኖሩ ኖሮ እውነቱን ያዩ ነበር፡፡ በእግዚአብሔር ስም እምላለሁ!
👍16❤1🔥1