#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ስልሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...“ አዬ ሚስተር ካርላይል እኛ ሥጋ ለባሾች ምስኪን ሐኪሞች ታላቁ ሐኪም ብቻ ሊፈጽመው የሚችለውን ተአምር መሥራት ብንችል ፈሊያጊያችን ምን ያህል
በበዛ ነበር ? በጥቁሩ ዳመና ውስጥም ስውር ትኩረት መኖሩን አስታውስ አትርሳ በል ደህና ሁን ወንድሜ
ሚስተር ካርላይል ተመልሶ ገባ ወደ ሳቤላ ቀረበና
እንደ ተቀመጠች ቁል
ቁል ተመለከታት » ፊቷን ደህና አድርጋ በመነጽሯ ሸፍናው ስለ ነበር በጣም
ሊታየው አልቻለም የሱም ሐሳብ እሷን ለማነጋገር
እንጂ ፊቷን ለማጥናት አልነበረም “ይኸ በጣም ከባድ መርዶ ነው " አንቺ ግን ከኔ ይበልጥ የተገነዘብሺውና
ያሰብሽበት ይመስለኛል ”
ከተቀመጠችበት ድንገት ብድግ አለችና ወደ መስኮቱ ሔደች " አንድ የምትፈልገው ሰው በመንገዱ ሲያልፍ ያየች ይመስል ወደ ውጭ ትመለከት ጀመር "
ስሜቷ በሙሉ በሠራ አካላቷ ተማሰለ " ቅንጦቿ ይነዝራሉ ጉሮሮዋ ለብቻው
ይመታል ትንፋቯ ቁርጥ ቁርጥ ይላል " ምን ትሁን ? በልጃቸው ጤንነት ከሱ
ካባቱ ጋር በምስጢር መነጋገሩን እንዴት ትቻለው የእጅ ሹራቦቹን እንደ አሳት
ከሚፈጃት እጆቹ አወለቀቻቸው " ላቧን ከግንባሯ ጠረገች ለመረጋጋት ሞክረች
ለሚስተር ካርላይል ምን ምክንያት ትስጠው ?
“ልጁን በጣም ነው የምወደው ...ጌታዬ ” አለችው በከፊል ፊቷን ወደሱ መለስ አድርጋ“ ስለዚህ የሐኪሙ ግልጽና ቁርጥ አነጋገር አንጀቴን አላወሰው !የምሆነውን አሳጣኝ ለሕመም ሰጠኝ "
አሁንም ሚስተር ካርይል ወደ ቆመችበት ተጠጋና “በውነቱ ለኔ ልጅ ይህን
ያህል መጪነቅሽ ሲበዛ ደግ ሰው ነሽ ” አላት "
እሷ ግን ምንም አልመለሰችለትም "
“ በይ እንግዲህ ይህን ነገር ለሚስዝ ካርላይል እንዳትነግሪያት " አላትና
ነገሩን በመቀጠል፡“እኔው ራሴ ብነግራት ይሻላል " በአሁኑ ሰዓት በድንገት ማዘንም መደንገጥም አይኖርባትም።”
“ምን የሚያሳዝናቸው ወይም የሚያስደነግጣቸው ነግር አለ እናቱ አይደሉ?”
አለችው " አነጋገሯ በቁጭት በንዴትና በግለት ስለነበር ባርባራን የምታጥላላ መሰለባት " ልትጨምርበት ስትል የሷንና የባርባራን ያሁኑ ማንነት ትውስ አላት "
በገጽታዋ ሳታሳይ ድንግጥ አለችና መደምደሚያውን በጣም አለዘበች " ሚስተር ካርላይል ዐይኖቹን አፈጠጠ " ድምፁ ተለዋወጠ "
“ ሳታስተውይ በችኮላ ትናገሪያለሽ ... ማዳም " አላት "
በተናገረችው መልስ ደነገጠች " ማን መሆኗን አሰበች " ኃፍረትም ውርደትም ተሰማት ። እሷ ስለ ሚስቱ እንደዚህ ብላ ሳትናገር ሚስተር ካርላይል ከዕብድ የባሰች አድርጎ ሊገምታት እንደሚችል ተሰማት ትቷት ሲሔድ የልመና ከንፈሮቿን
እያንቀጠቀጠች ወደሱ ምልስ አለች "
“በትክክል ገብቶኝ ከሆነ የሚወስደው ስለሌለ ወደ ሙቀት አገር ሊሔድ አይችልም ስትባባሉ የሰማሁ መሰለኝ " ይህ ከሆነ ለምን እኔ ይዤው አልሔድም ?አደራውን ለኔ ይስጡኝ "
“ አይሔድም ዶክተር ማርቲን የረባ ዕድሜ ስለማይጨምርለት ባይሔድ
ይሻላል ማለቱን ሰምተሻል "
“እሱማ ለጥቂት ሳምንት ብቻ ነው ብሏል " ታዲያ እነሱስ ቢሆኑ ዋጋ የላቸውም አለችው።
“ሊኖራቸው ይችላል # ግን ጥቅማቸው ከምኑ ላይ ነው ? ለሱ ኮ ከቤተሰቡ
ተነጥሎ በብቸነት የሚሠቃይባቸው ሳምንቶች ይሆኑበታል" ስለዚህ ልጄ ከኔ መለየቱ የማይቀርለት ከሆነ እስከ መጨረሻው የመለያያ ቅጽበት አብሮኝ መቆየት አለበት።
ዊልያም በሩን ከፈት አደረገና ጭንቅላቱን ብቅ አድርጎ ተመለከተ "ሔደ
አይደለም እኔ ኮ የዓሳ ዘይት እንዳይሰጠኝ ካልወጣ ኤልመጣም ብዬ ነው የቆየሁት” አለ።
ሚስተር ካርላይል ተቀመጠና ዊልያምን ከጉልበቱ ላይ ቁጭ አድርጎ ግንባሩን ከልጁ ሐርማ ጸጉር አሳርፎ ሰማህ ልጄ!ዘይቱ በጎ እንዲያደርግህና እንዲያበረታህ መሆኑን ታውቃለህ?። አለው
"እኔ ግን የሚያጠነክረኝ አይመስለኝም " ዶክተር “ማርቲን እኔን ይሞታል
አለኝ ?
"ስለ መሞት ደግሞ ማን ነገረህ ?”
“ አንዳንዶቹ ያወሩታል "
“ ዝም ብለህ እንድትሞት አናደርግም " አንተን ለማዳን ምን ማድረግ እንዳለብን ለማወቅ እንሞክራለን ይኸን ታውቃለህ ዊልያም ?
“ አዎን ዐውቃለሁ ”
ሚስተር ካርላይል ተነሣና ልጁን ለማዳም ቬን ስጥቶ'“ በይ ደህና አድርገሽ
ተጠንቅቀሽ ያዥው ብሏት ወደ ኮሪደሩ ዐለፈ
“ አባባ ! ... አባባ!እፈልግሃለሁ ” አለና ማዳም ቬንን ትቶ ወደሱ እየሮጠ
በእግርህ ነው ወደ ቤት የምትመለሰው ? አብሬህ በእግሬ ልምጣ ?”
በዚያ ሰዓት በዚያ ስሜት የልጁን ጥያቄ ለመቀበል እምቢ የሚልበት አንጀት አልነበረውም “ እሺ እስክመለስ ድረስ እዚህ ጠብቀኝ ” ብሎት ወጣና
ደርሶ ተመለሰ " እሱ የዊልያምን እጅ ይዞ ማዳም ቬን ከዊልያም ቀጥላ ፈንጠር ብላ ጉዞ ቀጠሉ "
በዚህ ዐይነት እየሔዱ ሳለ ትንሹ ሰውዬ ከፖስታ ቤት እየሮጠ ወጣና ከነሱ
ጋር ፊት ለፊት ግጥም አሉ ሰውየው የተደናገጠ ይመስል ነበር መንገደኞችንም
ድንገት ድቅን በማለት ካደናገራቸው በኋላ ወደ ጐርፍ መሔጃው ዘወር አለ " ሰውየው ፍራንሲዝ ሌቪሰን ነበር !
ዊልያም በልጅነት ቅንነቱ ዞር ብሎ አይቶት እኔ እንደዚህ ሰውዬ አስቀ
ያሚና መጥፎ ሰው አልሆንም " አንተሳ . . . አባባ ?
ሚስተ ካርላይል አልመለሰለትም " ማዳም ቬንም ሳታስበው ድንገት አይታዋለች » ከዚያም መንግዳቸውን ቀጠሎና ሚስተር ጀስቲስ ሔር በር ሲደርሱ ባለቤቱንም ከዚያው ቁሞ አገኙት ዊልያም' ሚስዝ ሔርን ከአትክልቱ ቦታ ወንበር
ላይ ተቀምጣ አያትና ሊስማት ሔደ ሚስዝ ሔርን ልጆቹ ሁሉ ይወዷት ነበር "
“ እኔ የምለው ሚስተር ካርላይል ዛሬ ወደ ፍርድ ቤት አልሔድኩም ነበር "
አንድ ማመልከቻ በምስጢር እንደ ቀረበላቸው ፒነር ነገረኝ ዝም ብለው የማይታመን የማይሆን ነገርኮ ነው " አንተስ ምን የምታውቀው ነገር አለ ?
" እኔ ያወቅሁት ነገር የለም ”
ነገሩ ዲክ ሆሊጆንን ያለመግደሉን ለማሳወቅ የታሰበ ይመስላል” አለ በዛፎቹ ሥር በስውር የሚያዳምጡ እንዳይኖሩ የሠጋ ይመስል ድምፁን ዝቅ አድርጎ "
የገደለው ሌቪሰን እንጂ ... ትሰማኛለህ ? ሌቪሰን እንጂ እሱ አይደለም " የሚል
ነገር አቅርበዋል አሉ " ግን በጭራሽ የማይሆን የማይመስል ወሬ ነው”
“ ስለ ሪቻርድ ከደሙ ንጹሕነት ” አለ ሚስተር ካርላይል !“ እኔም ካመንኩበት ብዙ ዘመኔ ነው
“ስለ ሌቪስን ወንጀለኝነትሳ ? አለ ጀስቲስ ሔር ዐይኖቹን በመገረም አፍጦ።
“ ስለሱ የምሰጠው አስተያየት አይኖረኝም ” አለው ሚስተር ካርላይል ቀዝቀዝ ብሎ።
“ ሊሆን አይችልም ። ዲክ ነጻ ሊሆን አይችልም ዲክ ነጻ ሆነ ማለት ዓለም
ተገለበጠች ማለት ነው !! ”
“ አንዳንዴም አይሆንም ያሉት ይሆናል " ሪቻርድ ንጹሕ የመሆኑ ነገር በፀሐይ ባደባባይ ሊረጋገጥ ነው” አለ ሚስተር ካርላይል
“ በዚያኛው ከተመሰከረበት ደግሞ የመያዣውን ከፖሊስ ወስደህ አንተው ራስህ ትይዘዋለህ ”
“ እኔስ በእንጨትም አልነካው ሰውየው ከተቀጣ ይቀጣል እኔ ግን የቅጣቱን መንገድ ጠራጊ በመሆን አልረዳም ”
“ እና ዲክ ነጻ ሊሆን ይችላል ?” ታዲያ ለምን ጠፋ ? ለምን ቀርቦ እንደዚህ ብሎ አላመለከተም ?”
"እርስዎ አንቀው ለፍርድ እንዲያቀርቡት ነው? ለማቅረብ መማለልዎን ያውቃሉ ? አለው ሚስተር ካርላይል "
ጀስቲስ ሔር በጣም እየበረዶ ሔዶ ።
“ እንዴ ግን ካርላይል
ያቺ ከንቱ በሕይወት ቆይታ ብታይ ኖሮ አንጀትህ
እንዴት በሻረ ! ያ የተሳሳተ አድራጎቷ ምን ያህል ይቆጫት ምን ያህል ያሳርራት ነበር !”
፡
፡
#ክፍል_ስልሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...“ አዬ ሚስተር ካርላይል እኛ ሥጋ ለባሾች ምስኪን ሐኪሞች ታላቁ ሐኪም ብቻ ሊፈጽመው የሚችለውን ተአምር መሥራት ብንችል ፈሊያጊያችን ምን ያህል
በበዛ ነበር ? በጥቁሩ ዳመና ውስጥም ስውር ትኩረት መኖሩን አስታውስ አትርሳ በል ደህና ሁን ወንድሜ
ሚስተር ካርላይል ተመልሶ ገባ ወደ ሳቤላ ቀረበና
እንደ ተቀመጠች ቁል
ቁል ተመለከታት » ፊቷን ደህና አድርጋ በመነጽሯ ሸፍናው ስለ ነበር በጣም
ሊታየው አልቻለም የሱም ሐሳብ እሷን ለማነጋገር
እንጂ ፊቷን ለማጥናት አልነበረም “ይኸ በጣም ከባድ መርዶ ነው " አንቺ ግን ከኔ ይበልጥ የተገነዘብሺውና
ያሰብሽበት ይመስለኛል ”
ከተቀመጠችበት ድንገት ብድግ አለችና ወደ መስኮቱ ሔደች " አንድ የምትፈልገው ሰው በመንገዱ ሲያልፍ ያየች ይመስል ወደ ውጭ ትመለከት ጀመር "
ስሜቷ በሙሉ በሠራ አካላቷ ተማሰለ " ቅንጦቿ ይነዝራሉ ጉሮሮዋ ለብቻው
ይመታል ትንፋቯ ቁርጥ ቁርጥ ይላል " ምን ትሁን ? በልጃቸው ጤንነት ከሱ
ካባቱ ጋር በምስጢር መነጋገሩን እንዴት ትቻለው የእጅ ሹራቦቹን እንደ አሳት
ከሚፈጃት እጆቹ አወለቀቻቸው " ላቧን ከግንባሯ ጠረገች ለመረጋጋት ሞክረች
ለሚስተር ካርላይል ምን ምክንያት ትስጠው ?
“ልጁን በጣም ነው የምወደው ...ጌታዬ ” አለችው በከፊል ፊቷን ወደሱ መለስ አድርጋ“ ስለዚህ የሐኪሙ ግልጽና ቁርጥ አነጋገር አንጀቴን አላወሰው !የምሆነውን አሳጣኝ ለሕመም ሰጠኝ "
አሁንም ሚስተር ካርይል ወደ ቆመችበት ተጠጋና “በውነቱ ለኔ ልጅ ይህን
ያህል መጪነቅሽ ሲበዛ ደግ ሰው ነሽ ” አላት "
እሷ ግን ምንም አልመለሰችለትም "
“ በይ እንግዲህ ይህን ነገር ለሚስዝ ካርላይል እንዳትነግሪያት " አላትና
ነገሩን በመቀጠል፡“እኔው ራሴ ብነግራት ይሻላል " በአሁኑ ሰዓት በድንገት ማዘንም መደንገጥም አይኖርባትም።”
“ምን የሚያሳዝናቸው ወይም የሚያስደነግጣቸው ነግር አለ እናቱ አይደሉ?”
አለችው " አነጋገሯ በቁጭት በንዴትና በግለት ስለነበር ባርባራን የምታጥላላ መሰለባት " ልትጨምርበት ስትል የሷንና የባርባራን ያሁኑ ማንነት ትውስ አላት "
በገጽታዋ ሳታሳይ ድንግጥ አለችና መደምደሚያውን በጣም አለዘበች " ሚስተር ካርላይል ዐይኖቹን አፈጠጠ " ድምፁ ተለዋወጠ "
“ ሳታስተውይ በችኮላ ትናገሪያለሽ ... ማዳም " አላት "
በተናገረችው መልስ ደነገጠች " ማን መሆኗን አሰበች " ኃፍረትም ውርደትም ተሰማት ። እሷ ስለ ሚስቱ እንደዚህ ብላ ሳትናገር ሚስተር ካርላይል ከዕብድ የባሰች አድርጎ ሊገምታት እንደሚችል ተሰማት ትቷት ሲሔድ የልመና ከንፈሮቿን
እያንቀጠቀጠች ወደሱ ምልስ አለች "
“በትክክል ገብቶኝ ከሆነ የሚወስደው ስለሌለ ወደ ሙቀት አገር ሊሔድ አይችልም ስትባባሉ የሰማሁ መሰለኝ " ይህ ከሆነ ለምን እኔ ይዤው አልሔድም ?አደራውን ለኔ ይስጡኝ "
“ አይሔድም ዶክተር ማርቲን የረባ ዕድሜ ስለማይጨምርለት ባይሔድ
ይሻላል ማለቱን ሰምተሻል "
“እሱማ ለጥቂት ሳምንት ብቻ ነው ብሏል " ታዲያ እነሱስ ቢሆኑ ዋጋ የላቸውም አለችው።
“ሊኖራቸው ይችላል # ግን ጥቅማቸው ከምኑ ላይ ነው ? ለሱ ኮ ከቤተሰቡ
ተነጥሎ በብቸነት የሚሠቃይባቸው ሳምንቶች ይሆኑበታል" ስለዚህ ልጄ ከኔ መለየቱ የማይቀርለት ከሆነ እስከ መጨረሻው የመለያያ ቅጽበት አብሮኝ መቆየት አለበት።
ዊልያም በሩን ከፈት አደረገና ጭንቅላቱን ብቅ አድርጎ ተመለከተ "ሔደ
አይደለም እኔ ኮ የዓሳ ዘይት እንዳይሰጠኝ ካልወጣ ኤልመጣም ብዬ ነው የቆየሁት” አለ።
ሚስተር ካርላይል ተቀመጠና ዊልያምን ከጉልበቱ ላይ ቁጭ አድርጎ ግንባሩን ከልጁ ሐርማ ጸጉር አሳርፎ ሰማህ ልጄ!ዘይቱ በጎ እንዲያደርግህና እንዲያበረታህ መሆኑን ታውቃለህ?። አለው
"እኔ ግን የሚያጠነክረኝ አይመስለኝም " ዶክተር “ማርቲን እኔን ይሞታል
አለኝ ?
"ስለ መሞት ደግሞ ማን ነገረህ ?”
“ አንዳንዶቹ ያወሩታል "
“ ዝም ብለህ እንድትሞት አናደርግም " አንተን ለማዳን ምን ማድረግ እንዳለብን ለማወቅ እንሞክራለን ይኸን ታውቃለህ ዊልያም ?
“ አዎን ዐውቃለሁ ”
ሚስተር ካርላይል ተነሣና ልጁን ለማዳም ቬን ስጥቶ'“ በይ ደህና አድርገሽ
ተጠንቅቀሽ ያዥው ብሏት ወደ ኮሪደሩ ዐለፈ
“ አባባ ! ... አባባ!እፈልግሃለሁ ” አለና ማዳም ቬንን ትቶ ወደሱ እየሮጠ
በእግርህ ነው ወደ ቤት የምትመለሰው ? አብሬህ በእግሬ ልምጣ ?”
በዚያ ሰዓት በዚያ ስሜት የልጁን ጥያቄ ለመቀበል እምቢ የሚልበት አንጀት አልነበረውም “ እሺ እስክመለስ ድረስ እዚህ ጠብቀኝ ” ብሎት ወጣና
ደርሶ ተመለሰ " እሱ የዊልያምን እጅ ይዞ ማዳም ቬን ከዊልያም ቀጥላ ፈንጠር ብላ ጉዞ ቀጠሉ "
በዚህ ዐይነት እየሔዱ ሳለ ትንሹ ሰውዬ ከፖስታ ቤት እየሮጠ ወጣና ከነሱ
ጋር ፊት ለፊት ግጥም አሉ ሰውየው የተደናገጠ ይመስል ነበር መንገደኞችንም
ድንገት ድቅን በማለት ካደናገራቸው በኋላ ወደ ጐርፍ መሔጃው ዘወር አለ " ሰውየው ፍራንሲዝ ሌቪሰን ነበር !
ዊልያም በልጅነት ቅንነቱ ዞር ብሎ አይቶት እኔ እንደዚህ ሰውዬ አስቀ
ያሚና መጥፎ ሰው አልሆንም " አንተሳ . . . አባባ ?
ሚስተ ካርላይል አልመለሰለትም " ማዳም ቬንም ሳታስበው ድንገት አይታዋለች » ከዚያም መንግዳቸውን ቀጠሎና ሚስተር ጀስቲስ ሔር በር ሲደርሱ ባለቤቱንም ከዚያው ቁሞ አገኙት ዊልያም' ሚስዝ ሔርን ከአትክልቱ ቦታ ወንበር
ላይ ተቀምጣ አያትና ሊስማት ሔደ ሚስዝ ሔርን ልጆቹ ሁሉ ይወዷት ነበር "
“ እኔ የምለው ሚስተር ካርላይል ዛሬ ወደ ፍርድ ቤት አልሔድኩም ነበር "
አንድ ማመልከቻ በምስጢር እንደ ቀረበላቸው ፒነር ነገረኝ ዝም ብለው የማይታመን የማይሆን ነገርኮ ነው " አንተስ ምን የምታውቀው ነገር አለ ?
" እኔ ያወቅሁት ነገር የለም ”
ነገሩ ዲክ ሆሊጆንን ያለመግደሉን ለማሳወቅ የታሰበ ይመስላል” አለ በዛፎቹ ሥር በስውር የሚያዳምጡ እንዳይኖሩ የሠጋ ይመስል ድምፁን ዝቅ አድርጎ "
የገደለው ሌቪሰን እንጂ ... ትሰማኛለህ ? ሌቪሰን እንጂ እሱ አይደለም " የሚል
ነገር አቅርበዋል አሉ " ግን በጭራሽ የማይሆን የማይመስል ወሬ ነው”
“ ስለ ሪቻርድ ከደሙ ንጹሕነት ” አለ ሚስተር ካርላይል !“ እኔም ካመንኩበት ብዙ ዘመኔ ነው
“ስለ ሌቪስን ወንጀለኝነትሳ ? አለ ጀስቲስ ሔር ዐይኖቹን በመገረም አፍጦ።
“ ስለሱ የምሰጠው አስተያየት አይኖረኝም ” አለው ሚስተር ካርላይል ቀዝቀዝ ብሎ።
“ ሊሆን አይችልም ። ዲክ ነጻ ሊሆን አይችልም ዲክ ነጻ ሆነ ማለት ዓለም
ተገለበጠች ማለት ነው !! ”
“ አንዳንዴም አይሆንም ያሉት ይሆናል " ሪቻርድ ንጹሕ የመሆኑ ነገር በፀሐይ ባደባባይ ሊረጋገጥ ነው” አለ ሚስተር ካርላይል
“ በዚያኛው ከተመሰከረበት ደግሞ የመያዣውን ከፖሊስ ወስደህ አንተው ራስህ ትይዘዋለህ ”
“ እኔስ በእንጨትም አልነካው ሰውየው ከተቀጣ ይቀጣል እኔ ግን የቅጣቱን መንገድ ጠራጊ በመሆን አልረዳም ”
“ እና ዲክ ነጻ ሊሆን ይችላል ?” ታዲያ ለምን ጠፋ ? ለምን ቀርቦ እንደዚህ ብሎ አላመለከተም ?”
"እርስዎ አንቀው ለፍርድ እንዲያቀርቡት ነው? ለማቅረብ መማለልዎን ያውቃሉ ? አለው ሚስተር ካርላይል "
ጀስቲስ ሔር በጣም እየበረዶ ሔዶ ።
“ እንዴ ግን ካርላይል
ያቺ ከንቱ በሕይወት ቆይታ ብታይ ኖሮ አንጀትህ
እንዴት በሻረ ! ያ የተሳሳተ አድራጎቷ ምን ያህል ይቆጫት ምን ያህል ያሳርራት ነበር !”
👍14