#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ስልሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
“ስለ ሰውዬው ወንጀል እኔ አላውቅም " ልጅዎ ግን ነጻ እንዲሚወጣ አይጠራጠሩ አይዞዎ ፤አይጨነቁ " የደስታ ዘመን እየመጣልዎ ነው” ብሎ አበራታቷትና አሳምኗት ወጣ
ሚስ ካርላይል የወንድሟን የምርጫ ቀን ምክንያት በማድረግ በሕይወቷ
አድርጋው የማታውቀውን እስከ መጨረሻው አጊጣ ለብሳ ስትንጎራደድ በነበረችበት ወቅት ዐይን አውጣዋ አፊ ሆሊጆንም በበኩሏ ከሚስ ካርላይል አሽከሮች ጋር ተመሳጥራ ሾልካ በመግባት ሚስ ካርላይል ከነበረችበት በላይ ከነበረው ፎቅ ወጣች " በተጐነጐነው ጸጉሯ ላይ ቆብ ደፍታ እስከ ሽንጧ ድረስ ደረጃ እየመጣለት የተሰፋው የነጭና የአረንጓዴ ዝንጉርጉር ቀሚስ ለብሳለች » ዐይነ ርግብና ለስላሳ ነጫጭ የጅ ጓንቲዎች አጥልቃ በዳንቴል የተከፈፈና ሽቶ የተርከፈከፈ መሐረብ ይዛ ባጠቃላይ ውድና ቀለመ ደማቅ በሆነ ሙሉ ልብስ አጊጣ እንደ ሱፍ አበባ ጐልታና ደምቃ በአደባባይ ለመላው ሕዝብ እየተጐማለለች ስትታይ ቆየች ደግነቱ ግን ሚስ ካርሳይል አላየቻትም ።
“ መልከ መልካም ነውኮ !” አለች ለሚስ ካርላይል ገረዶች ሰር ፍራንሲዝ ሌቪሰን ከፊት ለፊታቸው ሲደርስ አየችውና "
ግን መጥፎ ሰው ነው የሚል ነበር ያገኘችው መልስ ። ሚስተር አርኪባልድ ጋር ተወዳድሬ “አሸንፋለሁ ብሎ ማሰቡና እዚህ መምጣቱም ያስገርማል” አሏት"
“ምን እያደረጉ ነው?” አለችና'“እንዴ ኧረ ፖሊሶችም አሉ !” ብላ ጮኸችና'' እጁን በካቴና እያሰሩት ነው ምን አደረጋቸው ? እያለች ለፈለፈች።
ለጩኸቷ መልስ አላገኘችም ። ፊቷ ዐሥር ጊዜ እየተለዋወጠ በጭንቀት ስትመለከት ቆየችና “ አንዴ ” አለች ሰዎች ሲናገሩ ነገሩን ከአፊ ቀድማ የሰማችው
አንዷ ሠራተኛ ሰር ፍራንሲዝ ሌቪስንና ኦትዌይ ቤቴል አባትሽን ሆን ብለው
ስለ ገደሉ ተይዘዋል ነው የሚባል ”አለቻት "
ምን ! ” ብላ ጮኸች አፊ "
“ ገዳዬ ሴቪሰን ነው " ሪቻርድ ሔር ከደሙ ንጹሕ ነው ይላሉ " አለቻት።
አፊ ነገሩን አዳመጠች " ምን ማለት እንደሆነ አሰበች " ከዚያ እየተንገዳገደችና እየተንቀጠቀጠች ሙሉ ለሙሉ መሬት ላይ ተዘረረች አፊ ሆሊጆን ሕሊና
ዋን ሳተች።
አፊ ሆሊጆን አቅሏን ስታ የነበረችው ለቋት ወደ ሚስ ካርይል ቤት ተሸሽጋ
እንደ ገባች ሁሉ ተሸሽጋ ወጣች " ከሚስ ካርላይል ቤት ትንሽ ራቅ ብሎ ዐይብ ያሣማ ሥጋና ልዩ ልዩ የምግብ ቅባቶች የሚሸጡበት ሱቅ አለ » ሱቁ ጥሩ ታዋቂነት እንዳለው ካጠና በኋላ ገዝቶ
የሚሠራበት አንድ ከለንደን የመጣ መልከኛ ልጅ እግር ነጋዴ ነው ሱቁ ምርጥ
ዕቃ በማቅረቡ የታወቀ ለመሆኑ የሚስ ካርላይል ደንበኛ ለመሆን መብቃቱ ብቻ መረጃ ነበር " የፊተኛው ባለቤቱ በቂ ገንዘብ ስለ አጠራቀመ ለሚስተር ጂፍን
ሲሸጠው ሰዎች እሱም ሠርቶ የሚበቃውን ያህል ገንዘብ ሲይዝ እንደ ፊተኛው
ሰውዬ ይሸጠዋል " እያሉ ተንብየውበታል "
አፊ ከሚስ ካርላይል ቤት ወጥታ ከሱቁ ፊት ለፊት ስትደርስ ሚስተር ጀፊንን ከሱቁ በር ቁሞ ታየዋለች ከውስጥ ረዳቱ ከዕንጨት በርሜል እያወጣ ቅቤ
ይሸጣል " አፊ ቆም አለች " ሚስተር ጂፊን መቸም የሷ ነገር ጭንቁ ነው " ልቡ
እስኪጠፋ ይወዳታል እሷም እሱ ሲያወዳድሳት ደስ ደስ ይላታል "
“ እንደ ምን ዋልሽ ... አፊ” አላት ነጭ ሽርጡ እንዳይታይበት ተጠንቅቆ
አጣጥፎ ከደበቀ በኋላ እጁን ወደሷ ዘረጋ ። ምክንያቱም ስለ ሽርጡ አሳፋሪነት አንድ ጊዜ ጠቆም አድርጋው ነበር "
“ ደኅና ነህ ጄፈን" አለችውና ነጫጭ ጓንቲዎቿን እንዳደረገች ራሷን ዝቅ በማድረግ ለሰላምታ የቀረበላትን እጅ በጣቷ ጫፍ ነካ አደረገችው “እኔ
ደሞ ” አለችው የጅ መሐረቧን ዐይነ ርግቧንና ( ቀለበትኛ የተሠራውን ጸጉሯን በማሳየት እየተውረገረገች “ዛሬ ሱቅህን ዘግተህ ዕረፍት ያደረግህ መስሎኝ ነበር
ሚስተር ጂፊን ” አለችው።
“ ሥራ መከበር አለበት” አላት ጂፍን ሐሳቡ በሷ ፍቅር ተይዞ ነጻ ሆነሽ በሽርሽር ላይ መሆን መቻልሽን ባውቅ ኖሮ ምናልባት ባጋጣሚ እንደማገኝሽ ተስፋ በማድረግ እኔም ዕረፍት እወስድ ነበር"
አባባሉ ከእውነተኛ ፍቅር የመነጨ መሆኑን ተገንዝባ ' “ ምንም እኮ አያውቅም ሥራው ሁሉ እንደ ከብት ነው ' አለች ' በሐሳቧ "
“ እኔ በሕይወቴ ያለኝ ታላቅ ደስታ .. ሚስ አፊ አንቺ ስታልፊ በሱቁ መስኮት አሻግሬ ማየት ነው ”
“ ኧረ ጉዴ !” አለች አፊ ገፍቶ የመጣባትን ሣቅ ለማገድ እየሞከረች : “ለምን እንደሚጠቅምህ አላውቅም "ዐይን ካለህ ከአንድ ሁለት ሰዓት በፊት ወደ ሚስ ካርላይል ዘንድ ስሔድ አይተኸኝ ይሆናል”
“ አዬ ! ዐይኖቼ የት ሔደው ኖሮ ይሆን?” አለ እየተጸጸተ “ አሃ ! ገባኝ እነዚያ የቅቤ በርሜሎችን ስመረምር ነው ይገርምሻል . . . ሚስ ሆሊጆን የተበላሹትን ስለ ላኩልኝ መልሼ ልልክላቸው ነው ”
“ አ ... ይ ! እኔ የቅቤ በርሜሎች ብሎ ነገር አላውቅም " እንዲህ እንዲህ ያለው ነገር ከክብሬ በታች ነው
“ እንዴታ እሱስ እውነትሽን ነው ... ሚስ ሆሊጆን “ ምንም እንኳን የገበያውን ጥቅም ለሚገባው ከፍተኛ ትርፍ ቢኖረሙም ካንቺ ክብር ጋር አይስማማም »
“ የምን ጩኽት ነው የምሰማው ? አለች አፊ "
"መራጮች ለሚስተር ካርላይል ሲያጨበጭቡ ነው መመረጡን ስምተሻል
ይመስለኛል
" የለም አልሰማሁም ”
ያኛውማ የገዛ ወዳጆቹ አስወጡትና ተገላገሉት » እንግዲህ እንደራሴአችን
ሚስተር ካርይል መሆኑ ነ&ዘው " ይባዋል ... መቸም እንደሱ ያለ ሰው የለም ‥
“እነዚህ ሁሉ ደንበኞችህ ናቸው እንዴ ? ሁሉንም ማስተናድ ከባድ ሥራ
ነው ሰውዬህ ብቻውን አይዘልቀውም " ስለዚህ እያወራሁ ጊዜ ልወስድብህ አልፈልግም ሔድኩልህ "
አለችውና እየተንሳፈፈች ሔደች " ጂፊን ፍዝዝ ብሎ
ሲያያት ከቆየ በኋላ ከይኑ ስትጠፋ የግዱን ደንበኞቹን ወደ ማስተናገድ ዞረ »
ጂፊን በፍቅሯ ወጥመድ መግባቱን ዐውቃና እንደሚያገባትም ተማምና አፊ በዚያ በቅባት በተባላሸው ሱቅ በኩል ሳይሆን በጓዳ በር እየገባች ጠቅላላ የቤቱንና የእቃውን አያያዝና አቀማመጥ ' ባሏንም እንዴት እንደምትንከባከበውና እንዴት አድርጋ በፍቅሯ ዐሥሬ የመሽቀርቀርያ መሣሪያ እንደምታደርገው እያሰላሰለች በምኞት አየር ላይ ሰገነት ሠርታ በሐሳቧ እየተሽሞነሞነች ስትራመድ ኧበንዘር ጀምዝ ደርሶ ለቀም አደረጋት ።
“ እንደምነሽ . . አፊ ? ዛሬ ጧት ሚስ ኮርኒ መስኮቶች ላይ አየሁሽ "
“ ያንተ ነገር እንግዲህ በቃኝ . . . ኧበንዘር ጀምዝ በቀደም ለሚስተር ጀፊን የዱሮ ወዳጄ ነበረች ማለትህን እኮ ሰምቸሃለሁ ”
“ አዎን ነበርሽና ” አላት እየሣቀ "
“ አልነበርኩም " እኔ በዚያን ጊዜ ከበላዮችህ ጋር እንጂ ካንተ ጋር ምንም ግኙነት አልነበረኝም አሁንም እኔን ለመጉዳት ብለህ በሐሰት ስሜን ለማጥፋት ብታስብ ተሳስተሃል ... ኧበንዘር ጀምዝ " እኔ በዚህ ቦታ የተከበርኩ ሰው ነኝ " ስለዚሀ ዐርፈህ ተቀመጥ ”
“ ምነው አፊ ? ለምን እንደዚህ ትሆኛለሽ ? እኔ አንቺን ለመጉዳት አልፈልግም አንቺ እንደምትይው ብሞክርም አይሆንልኝም " አላት እየሣቀ "
ይኸው ነው ይበቃሃል አሁን ከኔ ራቅ የአንተ ህዝብ መሀል መታየትህ ለስሜ ደግ አይደለም " አለችው።
ደኅና መልእክቴን ከተቀበልሺኝ እሔድልሻለሁ " በይ አሁን ለዛሬ በዘጠኝ ሰዓት ፍርድ ቤት ከችሎቱ አዳራሽ ስለምትፈለጊ እንዳትቀሪ "
ከችሎት አዳራሽ ? እኔን ? ለምን ?
፡
፡
#ክፍል_ስልሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
“ስለ ሰውዬው ወንጀል እኔ አላውቅም " ልጅዎ ግን ነጻ እንዲሚወጣ አይጠራጠሩ አይዞዎ ፤አይጨነቁ " የደስታ ዘመን እየመጣልዎ ነው” ብሎ አበራታቷትና አሳምኗት ወጣ
ሚስ ካርላይል የወንድሟን የምርጫ ቀን ምክንያት በማድረግ በሕይወቷ
አድርጋው የማታውቀውን እስከ መጨረሻው አጊጣ ለብሳ ስትንጎራደድ በነበረችበት ወቅት ዐይን አውጣዋ አፊ ሆሊጆንም በበኩሏ ከሚስ ካርላይል አሽከሮች ጋር ተመሳጥራ ሾልካ በመግባት ሚስ ካርላይል ከነበረችበት በላይ ከነበረው ፎቅ ወጣች " በተጐነጐነው ጸጉሯ ላይ ቆብ ደፍታ እስከ ሽንጧ ድረስ ደረጃ እየመጣለት የተሰፋው የነጭና የአረንጓዴ ዝንጉርጉር ቀሚስ ለብሳለች » ዐይነ ርግብና ለስላሳ ነጫጭ የጅ ጓንቲዎች አጥልቃ በዳንቴል የተከፈፈና ሽቶ የተርከፈከፈ መሐረብ ይዛ ባጠቃላይ ውድና ቀለመ ደማቅ በሆነ ሙሉ ልብስ አጊጣ እንደ ሱፍ አበባ ጐልታና ደምቃ በአደባባይ ለመላው ሕዝብ እየተጐማለለች ስትታይ ቆየች ደግነቱ ግን ሚስ ካርሳይል አላየቻትም ።
“ መልከ መልካም ነውኮ !” አለች ለሚስ ካርላይል ገረዶች ሰር ፍራንሲዝ ሌቪሰን ከፊት ለፊታቸው ሲደርስ አየችውና "
ግን መጥፎ ሰው ነው የሚል ነበር ያገኘችው መልስ ። ሚስተር አርኪባልድ ጋር ተወዳድሬ “አሸንፋለሁ ብሎ ማሰቡና እዚህ መምጣቱም ያስገርማል” አሏት"
“ምን እያደረጉ ነው?” አለችና'“እንዴ ኧረ ፖሊሶችም አሉ !” ብላ ጮኸችና'' እጁን በካቴና እያሰሩት ነው ምን አደረጋቸው ? እያለች ለፈለፈች።
ለጩኸቷ መልስ አላገኘችም ። ፊቷ ዐሥር ጊዜ እየተለዋወጠ በጭንቀት ስትመለከት ቆየችና “ አንዴ ” አለች ሰዎች ሲናገሩ ነገሩን ከአፊ ቀድማ የሰማችው
አንዷ ሠራተኛ ሰር ፍራንሲዝ ሌቪስንና ኦትዌይ ቤቴል አባትሽን ሆን ብለው
ስለ ገደሉ ተይዘዋል ነው የሚባል ”አለቻት "
ምን ! ” ብላ ጮኸች አፊ "
“ ገዳዬ ሴቪሰን ነው " ሪቻርድ ሔር ከደሙ ንጹሕ ነው ይላሉ " አለቻት።
አፊ ነገሩን አዳመጠች " ምን ማለት እንደሆነ አሰበች " ከዚያ እየተንገዳገደችና እየተንቀጠቀጠች ሙሉ ለሙሉ መሬት ላይ ተዘረረች አፊ ሆሊጆን ሕሊና
ዋን ሳተች።
አፊ ሆሊጆን አቅሏን ስታ የነበረችው ለቋት ወደ ሚስ ካርይል ቤት ተሸሽጋ
እንደ ገባች ሁሉ ተሸሽጋ ወጣች " ከሚስ ካርላይል ቤት ትንሽ ራቅ ብሎ ዐይብ ያሣማ ሥጋና ልዩ ልዩ የምግብ ቅባቶች የሚሸጡበት ሱቅ አለ » ሱቁ ጥሩ ታዋቂነት እንዳለው ካጠና በኋላ ገዝቶ
የሚሠራበት አንድ ከለንደን የመጣ መልከኛ ልጅ እግር ነጋዴ ነው ሱቁ ምርጥ
ዕቃ በማቅረቡ የታወቀ ለመሆኑ የሚስ ካርላይል ደንበኛ ለመሆን መብቃቱ ብቻ መረጃ ነበር " የፊተኛው ባለቤቱ በቂ ገንዘብ ስለ አጠራቀመ ለሚስተር ጂፍን
ሲሸጠው ሰዎች እሱም ሠርቶ የሚበቃውን ያህል ገንዘብ ሲይዝ እንደ ፊተኛው
ሰውዬ ይሸጠዋል " እያሉ ተንብየውበታል "
አፊ ከሚስ ካርላይል ቤት ወጥታ ከሱቁ ፊት ለፊት ስትደርስ ሚስተር ጀፊንን ከሱቁ በር ቁሞ ታየዋለች ከውስጥ ረዳቱ ከዕንጨት በርሜል እያወጣ ቅቤ
ይሸጣል " አፊ ቆም አለች " ሚስተር ጂፊን መቸም የሷ ነገር ጭንቁ ነው " ልቡ
እስኪጠፋ ይወዳታል እሷም እሱ ሲያወዳድሳት ደስ ደስ ይላታል "
“ እንደ ምን ዋልሽ ... አፊ” አላት ነጭ ሽርጡ እንዳይታይበት ተጠንቅቆ
አጣጥፎ ከደበቀ በኋላ እጁን ወደሷ ዘረጋ ። ምክንያቱም ስለ ሽርጡ አሳፋሪነት አንድ ጊዜ ጠቆም አድርጋው ነበር "
“ ደኅና ነህ ጄፈን" አለችውና ነጫጭ ጓንቲዎቿን እንዳደረገች ራሷን ዝቅ በማድረግ ለሰላምታ የቀረበላትን እጅ በጣቷ ጫፍ ነካ አደረገችው “እኔ
ደሞ ” አለችው የጅ መሐረቧን ዐይነ ርግቧንና ( ቀለበትኛ የተሠራውን ጸጉሯን በማሳየት እየተውረገረገች “ዛሬ ሱቅህን ዘግተህ ዕረፍት ያደረግህ መስሎኝ ነበር
ሚስተር ጂፊን ” አለችው።
“ ሥራ መከበር አለበት” አላት ጂፍን ሐሳቡ በሷ ፍቅር ተይዞ ነጻ ሆነሽ በሽርሽር ላይ መሆን መቻልሽን ባውቅ ኖሮ ምናልባት ባጋጣሚ እንደማገኝሽ ተስፋ በማድረግ እኔም ዕረፍት እወስድ ነበር"
አባባሉ ከእውነተኛ ፍቅር የመነጨ መሆኑን ተገንዝባ ' “ ምንም እኮ አያውቅም ሥራው ሁሉ እንደ ከብት ነው ' አለች ' በሐሳቧ "
“ እኔ በሕይወቴ ያለኝ ታላቅ ደስታ .. ሚስ አፊ አንቺ ስታልፊ በሱቁ መስኮት አሻግሬ ማየት ነው ”
“ ኧረ ጉዴ !” አለች አፊ ገፍቶ የመጣባትን ሣቅ ለማገድ እየሞከረች : “ለምን እንደሚጠቅምህ አላውቅም "ዐይን ካለህ ከአንድ ሁለት ሰዓት በፊት ወደ ሚስ ካርላይል ዘንድ ስሔድ አይተኸኝ ይሆናል”
“ አዬ ! ዐይኖቼ የት ሔደው ኖሮ ይሆን?” አለ እየተጸጸተ “ አሃ ! ገባኝ እነዚያ የቅቤ በርሜሎችን ስመረምር ነው ይገርምሻል . . . ሚስ ሆሊጆን የተበላሹትን ስለ ላኩልኝ መልሼ ልልክላቸው ነው ”
“ አ ... ይ ! እኔ የቅቤ በርሜሎች ብሎ ነገር አላውቅም " እንዲህ እንዲህ ያለው ነገር ከክብሬ በታች ነው
“ እንዴታ እሱስ እውነትሽን ነው ... ሚስ ሆሊጆን “ ምንም እንኳን የገበያውን ጥቅም ለሚገባው ከፍተኛ ትርፍ ቢኖረሙም ካንቺ ክብር ጋር አይስማማም »
“ የምን ጩኽት ነው የምሰማው ? አለች አፊ "
"መራጮች ለሚስተር ካርላይል ሲያጨበጭቡ ነው መመረጡን ስምተሻል
ይመስለኛል
" የለም አልሰማሁም ”
ያኛውማ የገዛ ወዳጆቹ አስወጡትና ተገላገሉት » እንግዲህ እንደራሴአችን
ሚስተር ካርይል መሆኑ ነ&ዘው " ይባዋል ... መቸም እንደሱ ያለ ሰው የለም ‥
“እነዚህ ሁሉ ደንበኞችህ ናቸው እንዴ ? ሁሉንም ማስተናድ ከባድ ሥራ
ነው ሰውዬህ ብቻውን አይዘልቀውም " ስለዚህ እያወራሁ ጊዜ ልወስድብህ አልፈልግም ሔድኩልህ "
አለችውና እየተንሳፈፈች ሔደች " ጂፊን ፍዝዝ ብሎ
ሲያያት ከቆየ በኋላ ከይኑ ስትጠፋ የግዱን ደንበኞቹን ወደ ማስተናገድ ዞረ »
ጂፊን በፍቅሯ ወጥመድ መግባቱን ዐውቃና እንደሚያገባትም ተማምና አፊ በዚያ በቅባት በተባላሸው ሱቅ በኩል ሳይሆን በጓዳ በር እየገባች ጠቅላላ የቤቱንና የእቃውን አያያዝና አቀማመጥ ' ባሏንም እንዴት እንደምትንከባከበውና እንዴት አድርጋ በፍቅሯ ዐሥሬ የመሽቀርቀርያ መሣሪያ እንደምታደርገው እያሰላሰለች በምኞት አየር ላይ ሰገነት ሠርታ በሐሳቧ እየተሽሞነሞነች ስትራመድ ኧበንዘር ጀምዝ ደርሶ ለቀም አደረጋት ።
“ እንደምነሽ . . አፊ ? ዛሬ ጧት ሚስ ኮርኒ መስኮቶች ላይ አየሁሽ "
“ ያንተ ነገር እንግዲህ በቃኝ . . . ኧበንዘር ጀምዝ በቀደም ለሚስተር ጀፊን የዱሮ ወዳጄ ነበረች ማለትህን እኮ ሰምቸሃለሁ ”
“ አዎን ነበርሽና ” አላት እየሣቀ "
“ አልነበርኩም " እኔ በዚያን ጊዜ ከበላዮችህ ጋር እንጂ ካንተ ጋር ምንም ግኙነት አልነበረኝም አሁንም እኔን ለመጉዳት ብለህ በሐሰት ስሜን ለማጥፋት ብታስብ ተሳስተሃል ... ኧበንዘር ጀምዝ " እኔ በዚህ ቦታ የተከበርኩ ሰው ነኝ " ስለዚሀ ዐርፈህ ተቀመጥ ”
“ ምነው አፊ ? ለምን እንደዚህ ትሆኛለሽ ? እኔ አንቺን ለመጉዳት አልፈልግም አንቺ እንደምትይው ብሞክርም አይሆንልኝም " አላት እየሣቀ "
ይኸው ነው ይበቃሃል አሁን ከኔ ራቅ የአንተ ህዝብ መሀል መታየትህ ለስሜ ደግ አይደለም " አለችው።
ደኅና መልእክቴን ከተቀበልሺኝ እሔድልሻለሁ " በይ አሁን ለዛሬ በዘጠኝ ሰዓት ፍርድ ቤት ከችሎቱ አዳራሽ ስለምትፈለጊ እንዳትቀሪ "
ከችሎት አዳራሽ ? እኔን ? ለምን ?
👍19