#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ስልሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...አንድ ቀን በሚያዝያ ወር ውስጥ ሰዓቱ መሽቶ ለዐይን ሲይዝ ዊልምና ሳቤላ ሳሎን ውስጥ ተቀምጠዋል " ቀኑ ሞቃት ሆኖ ይዋል እንጂ እነዚያ የጸደይ ምሽቶች ግን ይባረዳሉ " የምድጃው እሳት ነዲድ ባይኖረውም ፍሙ ግማሹ ጠፍቶ ግማሹ ይጤሳል ማዳም ቬን እሳቱን ልብ አላለችውም ዊልያም ከሰፋው ተጋድም እሷም ዐይን ዐይኑን ታየዋለች " መነጽሯ በእንባ እየተነከረ አስቸገራት ልጆቹ እንዳያውቁት መሥጋቱንም ትታዋለች " ስለዚህ መጽሯን አወለቀች ልጁም ሊንበራ ደርሶ የተመለሰበት የሠረገላ ጉዞ ስላደከመው ዐይኖቹን ገጥሞ ተጋደመ እሷም የተኛ ሲመስላት ወዲያው መልሶ ገለጣቸው።
“ ከመሞቴ በፊት ስንት ቀን ይኖረኛል ?” አላት "
ያልጠበቀችው ጥያቄ ሆነባትና ናላዋ ዞረባት " “ ምን ማለትህ ነው
ዊልያም ስላንተ መሞት ማን አነሣ? አለችው "
“ ዐውቃለሁ እንጂ ስለኔ የሚወራውን እሰማ የለምእንዴ በቀደም ሐና
ያለችውን ሰምተሽ የለ ?
“ ምን? መቸ ?
“ እኔ ከምንጣፉ ላይ ተኝቼ ሻይ ይዛ የገባች ጊዜ " ለናንተ ቢመስላችሁም እንቅልፍ አልወሰደኝም ነበር " አንቺ እንኳ ልነቃ እንደምችል እንድትጠነቀቅ
ነግረሻት ነበር።
“እንጃ ልጄ እምብዛም አላስታውሰውም ሐና ምን የማትለፈልፈው አርቲ
ቡርቲ አላት ብለህ ነው ?”
“ ወደ መቃብሬ እየተጣደፍኩ መሆኔን ነበር የነገረችሽ " "
"አለች ? ሐና ኮ ማንም አይስማትም የምትናገረውን አታውቅም " ሞኝ ናት " አሁን ብርዳሙ ወቅት ዐልፎ የበጋው ሙቀት ሲገባ በጐ ትሆናለ "
“ ማዳም ቬን ”
“ ምነው የኔ ዓለም ”
“ ያንቺ እኔን ለማታለል መሞከርሽ ምን ይጠቅማል ? እያታለልሽኝ መሆኑን የማይገባኝ ይመስልሻል ? እኔ ሕፃን አይደለሁም አርኪባልድ ቢሆን ኖሮ ልታዋሸው ትችይ ነበር " ግን ምን ሁኘ ነው እንደዚህ የሆንኩት ?
ምንም አልሆንክም " ሰውነትህ ደካማ ከመሆኑ በስተቀር ምንም የለብህ እንደ ገና ስትጠነክር ደግሞ በጐ ትሆናለህ "
ዊልያም ራሱን ነቀነቀ " ልጁ ያስተሳሰቡ ፍጥነትና ጥልቀት ከዕድሜው የላቀ ነው ነገሮችን በማለባበስ ሊታለል የሚችል ልጅ አይደለም " ሲነግር በጀሮው
ያልሰማውን እንኳን ይደረግለት ከነበረው ጥንቃቄ በመነሣት የተሠጋለት መሆኑን በግምት የሚያውቅበት ችሎታ አለው “ እሱ ግን የሐናን አነጋገር የመሰለ ብዙ
ነገር በጆሮው ሰምቶ እንዲጠረጥር የሚያደርጉት ምክንያቶች አጠራቅሟል ስለዚህ ልጁ ሞት እየመጣ ለመሆኑ በደንብ አድርጎ ዐወቆታል "
“ታዲያ ምንም ነገር ከሌለብኝ ዶክተር ማርቲን ለምን ከኔፊት አላነጋገረሽም?
እሱ በሳቡ የነበረውን ሲነግርሽ ለምንድነው እኔን ከሌላ ክፍል አንድቆይ ያደረገኝ?
ማዳም ቬን . . . . እኔም እንዳንቺ ዐዋቂ ነኝ ”
“ አዎን የልጅ ዐዋቂ ነህ ብቻ አንዳንድ ጊዜ ትሳሳታለህ ” አለችው ሁኔታው አንጀት አንጀቷን እየበላት "
“ እግዚአብሔር ከወደደን ኮ ሞት ምንም አይደለም ሎርድ ቬን እንደዚህ
ብሎኛል » እሱም አንድ ትንሽ ወንድም ሙቶበታል
እሱ ገና ከሕፃንነቱ ጀምሮ ተስፋ የተቆረጠበት በሽተኛ ነበር ” አለችው "
"እንዴ አንቺም ታውቂው ነበር ?
“ የሰማሁትን ነው የምነግርህ " አለችው ዝንጉነቷን በስልት አስተካክላ
“ አሁን እኔ እንደምሞት አታውቂም ?
“ አላውቅም "
" ታዲያ ከዶክተር ማርቲን ከተለየን ጀምሮ የምታዝኚው ለምንድነው ? እንዲ
ያውስ ከነጭራሹ ስለኔ ምን አሳዘነሽ ? እኔ ልጅሽ አይደለሁ ?
አነጋገሩና ሁኔታው ከምትችለው በላይ ሆነባት ከሶፋው ተንበረከከች እንባዋ ያለገደብ በአራት ማዕዘን ወረደ።
“ አየህ ዊልያም.....እኔ...እኔ አንድ ልጅ ነበረኝ የራሴ ልጅ አንተን ባየሁህ ቁጥር እሱ ይመጣብኛል " ስለዚህ ነው የማለቅለው "
“ ዐውቃለሁ ስለሱ ከዚህ በፊት ነግረሽኝ ነበር የሱም ስም ዊልያም ነበር
አይደለም?
ከላው ላይ ተደግፋ ትንፋሿን ከትንፋሹ እያቀላቀለች እጁን በእጅዋ ይዛ“ዊልያም ” አለችው " “ ፈጣሪ ከሁሉ አብልጦ የሚወዳቸውን አስቀድሞ እንደሚወስድ ታውቃለህ አንተም ብትሞት ኖሮ የዚህን ዓለም ሐሳብና ጣጣ እዚህ ትተህ መንግሥተ ሰማያት ትግባ ነበር። በሕፃንነታችን ብንሞት ኖሮ ለሁላችንም ደስታችን ነበር
“ ለአንቺም ደስ ይልሽ ነበር ?
“ አዎን ለደርሰብኝ ከሚገባኝ የበለጠ ኀዘንና መከራ ተቀብያለሁ " እንዲያው አንዳንድ ጊዜ ሳስበውስ የምችለውም አይመስለኝም"
“ አሁንም ኀዘንሽ አላለፈም ? አሁንም ብኀዘን ላይ ነሽ ?
“ሀዘኔ ሁልጊዜ ከኔ ጋር ነው " አስክሞትም አብሮኝ ይቆያል » በልጅነቴ
ሙቸ ቢሆን ኖሮ ግን ዊልያም አመልጠው ነበር " ዓለም በኀዘን የተሞላ ነው
“ ምን ዐይነት ኀዘን ?”
“ ሕመም በሽታ ሐሳብ ' ኃጢአት በደል ጸጸት ልፋት ” አለችና በሪጅሙ ተነፈሰች
“ ዓለም ከምታመጣብን መከራ ግማሹን እንኳን ልነግርህ አልችልም " በጣም ሲደክምህ ዊልያም .. ከትንሽ አልጋህ ላይ ጋደም ብለህ እንቅልፍ
እስኪወስድህ ስትጠብቅ ደስ አይልህም ?
“ አዎን እኔም እንደዚያ ድክም ይለኛል ”
“ ስለዚህ እኛም በዓለም ጣጣምች የደከምነው ተጋድመን የምናርፍበት መቃብራችንን እንናፍቃለን ቶሎ እንዲደርስ እንጸልያለን ግን አይገባህም ”
ከመቃብር ኮ አንጋደምም . ማዳም ቬን "
“ የለም የለም ሰውነታችን ከዚያ ያርፋል » በመጨረሻ ቀን በክብር በውበት ይነሣል ምነው!እንዲያው ምነው!አለች እየተኮማተረች ምነው አንተና እኔ
ሁለታችን እዚያ ብንገናኝ ! "
“ ዓለም የኀዘን ቦታ ናት ያለው ነው ... ማዳም ቬን ? እኔስ በተለይ በሙቀት ቀን ፀሐይ ስታበራ ቢራቢሮዎች ሲራወጡ ቆንጆ ትመስለኛለች " አሁን
ኢስትሊን በበጋ ብታይው በአግድመቶችና በቨርተቴዎች ሽቅብና ቁልቁል ስንሮጥ ዛፎች ከራሳችን በላይ ሲወዛወዙ • ሰማዩ ጠርቶ አበባ ሁሉ ፈንድቶ ስታይው የኅዘን ዓለም ነው አትይም ነበር "
“ እነዚያ አበቦች ኮ ከመንግሥተ ሰማያት ነው የምናያቸው »
“መቸ ጠፉኝ » ሥዕላቸውን አይቻለሁ ማርቲን ስለ ምጽአት የሳለቻቸውን ስዕሎች ለማየት ወደ ሊንበራ ሔደን ነበር የዶክተር ማርቲን አይደለም
" ነጭ ነጭ የለበሱ ብዙ ሰዎች አሉ አንድ ወንዝም አለ በወንዙ የሚያማምሩ ጀልባዎች ነፍሶችን ሲያመላልሱ ይታያሉ ከወንዙ ዳር ዳር በቅለው ሲታዩ የነበሩት አበባዎች ድምቀታቸ ደስ ይላል ”
"ሥዕሎቹን ለማየት ማን ወሰዳችሁ ?”
“ አባባ ' እኔ ሉሲ ' ሚስዝ ሔርና ባርባራ ሆነን ሔደን ነበር ባርባራ ያኔ እናታችን አልሆነችም ነበር ” አለና ድምፁን ድንገት ዝቅ በማድረግ '“ ሎሲ አባባን ምን ብላ ጠየቀችው መሰለሽ ?”
"ምን ብላ ጠየቀችው ? "
ከነዚያ ነጭ ነጭ ከለበሱት ብዙ ሰዎች ውስጥ እማማም አብራ ትኖር እንደ
ሆነ ወደ መንግሥተ ሰማያት ሒዳ እንደሆነ ጠየቀችው ያኔ በፊት እናታችን የነበረ
ችውንኮ ነው ወይዘሮ ሳቤላን ደሞ ስትጠይቀው ብዙ ሰው ነበር የሰማት
"አባትህ ምን መልስ ሰጣት ? ”
እንጃ " ምንም የመለሰላት አልመሰለኝም !ከባርባራ ጋር ወሬ ይዞ ነበር " እሷ አይገባትም ስለ ወይዘሮ ሳቤላ አባባ ፊት ምንም እንዳትናገር ዊልሰን ስንት
ጊዜ ነግራት ነበር መሰለሽ « ሚስ ማኒንግም እንደሱ ስትነግራት ነበር ከቤት እንደተመለስን ዊልሰን ሰማችና ትከሻና ትከሻዋን ይዛ አንዘፍዝፋ አንዘፍዝፋ ለቀቀቻት "
ለምንድነው የወይዘሮ ሳቤላ ስም ከፊቱ የማይነሣው ? አለችው »
፡
፡
#ክፍል_ስልሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...አንድ ቀን በሚያዝያ ወር ውስጥ ሰዓቱ መሽቶ ለዐይን ሲይዝ ዊልምና ሳቤላ ሳሎን ውስጥ ተቀምጠዋል " ቀኑ ሞቃት ሆኖ ይዋል እንጂ እነዚያ የጸደይ ምሽቶች ግን ይባረዳሉ " የምድጃው እሳት ነዲድ ባይኖረውም ፍሙ ግማሹ ጠፍቶ ግማሹ ይጤሳል ማዳም ቬን እሳቱን ልብ አላለችውም ዊልያም ከሰፋው ተጋድም እሷም ዐይን ዐይኑን ታየዋለች " መነጽሯ በእንባ እየተነከረ አስቸገራት ልጆቹ እንዳያውቁት መሥጋቱንም ትታዋለች " ስለዚህ መጽሯን አወለቀች ልጁም ሊንበራ ደርሶ የተመለሰበት የሠረገላ ጉዞ ስላደከመው ዐይኖቹን ገጥሞ ተጋደመ እሷም የተኛ ሲመስላት ወዲያው መልሶ ገለጣቸው።
“ ከመሞቴ በፊት ስንት ቀን ይኖረኛል ?” አላት "
ያልጠበቀችው ጥያቄ ሆነባትና ናላዋ ዞረባት " “ ምን ማለትህ ነው
ዊልያም ስላንተ መሞት ማን አነሣ? አለችው "
“ ዐውቃለሁ እንጂ ስለኔ የሚወራውን እሰማ የለምእንዴ በቀደም ሐና
ያለችውን ሰምተሽ የለ ?
“ ምን? መቸ ?
“ እኔ ከምንጣፉ ላይ ተኝቼ ሻይ ይዛ የገባች ጊዜ " ለናንተ ቢመስላችሁም እንቅልፍ አልወሰደኝም ነበር " አንቺ እንኳ ልነቃ እንደምችል እንድትጠነቀቅ
ነግረሻት ነበር።
“እንጃ ልጄ እምብዛም አላስታውሰውም ሐና ምን የማትለፈልፈው አርቲ
ቡርቲ አላት ብለህ ነው ?”
“ ወደ መቃብሬ እየተጣደፍኩ መሆኔን ነበር የነገረችሽ " "
"አለች ? ሐና ኮ ማንም አይስማትም የምትናገረውን አታውቅም " ሞኝ ናት " አሁን ብርዳሙ ወቅት ዐልፎ የበጋው ሙቀት ሲገባ በጐ ትሆናለ "
“ ማዳም ቬን ”
“ ምነው የኔ ዓለም ”
“ ያንቺ እኔን ለማታለል መሞከርሽ ምን ይጠቅማል ? እያታለልሽኝ መሆኑን የማይገባኝ ይመስልሻል ? እኔ ሕፃን አይደለሁም አርኪባልድ ቢሆን ኖሮ ልታዋሸው ትችይ ነበር " ግን ምን ሁኘ ነው እንደዚህ የሆንኩት ?
ምንም አልሆንክም " ሰውነትህ ደካማ ከመሆኑ በስተቀር ምንም የለብህ እንደ ገና ስትጠነክር ደግሞ በጐ ትሆናለህ "
ዊልያም ራሱን ነቀነቀ " ልጁ ያስተሳሰቡ ፍጥነትና ጥልቀት ከዕድሜው የላቀ ነው ነገሮችን በማለባበስ ሊታለል የሚችል ልጅ አይደለም " ሲነግር በጀሮው
ያልሰማውን እንኳን ይደረግለት ከነበረው ጥንቃቄ በመነሣት የተሠጋለት መሆኑን በግምት የሚያውቅበት ችሎታ አለው “ እሱ ግን የሐናን አነጋገር የመሰለ ብዙ
ነገር በጆሮው ሰምቶ እንዲጠረጥር የሚያደርጉት ምክንያቶች አጠራቅሟል ስለዚህ ልጁ ሞት እየመጣ ለመሆኑ በደንብ አድርጎ ዐወቆታል "
“ታዲያ ምንም ነገር ከሌለብኝ ዶክተር ማርቲን ለምን ከኔፊት አላነጋገረሽም?
እሱ በሳቡ የነበረውን ሲነግርሽ ለምንድነው እኔን ከሌላ ክፍል አንድቆይ ያደረገኝ?
ማዳም ቬን . . . . እኔም እንዳንቺ ዐዋቂ ነኝ ”
“ አዎን የልጅ ዐዋቂ ነህ ብቻ አንዳንድ ጊዜ ትሳሳታለህ ” አለችው ሁኔታው አንጀት አንጀቷን እየበላት "
“ እግዚአብሔር ከወደደን ኮ ሞት ምንም አይደለም ሎርድ ቬን እንደዚህ
ብሎኛል » እሱም አንድ ትንሽ ወንድም ሙቶበታል
እሱ ገና ከሕፃንነቱ ጀምሮ ተስፋ የተቆረጠበት በሽተኛ ነበር ” አለችው "
"እንዴ አንቺም ታውቂው ነበር ?
“ የሰማሁትን ነው የምነግርህ " አለችው ዝንጉነቷን በስልት አስተካክላ
“ አሁን እኔ እንደምሞት አታውቂም ?
“ አላውቅም "
" ታዲያ ከዶክተር ማርቲን ከተለየን ጀምሮ የምታዝኚው ለምንድነው ? እንዲ
ያውስ ከነጭራሹ ስለኔ ምን አሳዘነሽ ? እኔ ልጅሽ አይደለሁ ?
አነጋገሩና ሁኔታው ከምትችለው በላይ ሆነባት ከሶፋው ተንበረከከች እንባዋ ያለገደብ በአራት ማዕዘን ወረደ።
“ አየህ ዊልያም.....እኔ...እኔ አንድ ልጅ ነበረኝ የራሴ ልጅ አንተን ባየሁህ ቁጥር እሱ ይመጣብኛል " ስለዚህ ነው የማለቅለው "
“ ዐውቃለሁ ስለሱ ከዚህ በፊት ነግረሽኝ ነበር የሱም ስም ዊልያም ነበር
አይደለም?
ከላው ላይ ተደግፋ ትንፋሿን ከትንፋሹ እያቀላቀለች እጁን በእጅዋ ይዛ“ዊልያም ” አለችው " “ ፈጣሪ ከሁሉ አብልጦ የሚወዳቸውን አስቀድሞ እንደሚወስድ ታውቃለህ አንተም ብትሞት ኖሮ የዚህን ዓለም ሐሳብና ጣጣ እዚህ ትተህ መንግሥተ ሰማያት ትግባ ነበር። በሕፃንነታችን ብንሞት ኖሮ ለሁላችንም ደስታችን ነበር
“ ለአንቺም ደስ ይልሽ ነበር ?
“ አዎን ለደርሰብኝ ከሚገባኝ የበለጠ ኀዘንና መከራ ተቀብያለሁ " እንዲያው አንዳንድ ጊዜ ሳስበውስ የምችለውም አይመስለኝም"
“ አሁንም ኀዘንሽ አላለፈም ? አሁንም ብኀዘን ላይ ነሽ ?
“ሀዘኔ ሁልጊዜ ከኔ ጋር ነው " አስክሞትም አብሮኝ ይቆያል » በልጅነቴ
ሙቸ ቢሆን ኖሮ ግን ዊልያም አመልጠው ነበር " ዓለም በኀዘን የተሞላ ነው
“ ምን ዐይነት ኀዘን ?”
“ ሕመም በሽታ ሐሳብ ' ኃጢአት በደል ጸጸት ልፋት ” አለችና በሪጅሙ ተነፈሰች
“ ዓለም ከምታመጣብን መከራ ግማሹን እንኳን ልነግርህ አልችልም " በጣም ሲደክምህ ዊልያም .. ከትንሽ አልጋህ ላይ ጋደም ብለህ እንቅልፍ
እስኪወስድህ ስትጠብቅ ደስ አይልህም ?
“ አዎን እኔም እንደዚያ ድክም ይለኛል ”
“ ስለዚህ እኛም በዓለም ጣጣምች የደከምነው ተጋድመን የምናርፍበት መቃብራችንን እንናፍቃለን ቶሎ እንዲደርስ እንጸልያለን ግን አይገባህም ”
ከመቃብር ኮ አንጋደምም . ማዳም ቬን "
“ የለም የለም ሰውነታችን ከዚያ ያርፋል » በመጨረሻ ቀን በክብር በውበት ይነሣል ምነው!እንዲያው ምነው!አለች እየተኮማተረች ምነው አንተና እኔ
ሁለታችን እዚያ ብንገናኝ ! "
“ ዓለም የኀዘን ቦታ ናት ያለው ነው ... ማዳም ቬን ? እኔስ በተለይ በሙቀት ቀን ፀሐይ ስታበራ ቢራቢሮዎች ሲራወጡ ቆንጆ ትመስለኛለች " አሁን
ኢስትሊን በበጋ ብታይው በአግድመቶችና በቨርተቴዎች ሽቅብና ቁልቁል ስንሮጥ ዛፎች ከራሳችን በላይ ሲወዛወዙ • ሰማዩ ጠርቶ አበባ ሁሉ ፈንድቶ ስታይው የኅዘን ዓለም ነው አትይም ነበር "
“ እነዚያ አበቦች ኮ ከመንግሥተ ሰማያት ነው የምናያቸው »
“መቸ ጠፉኝ » ሥዕላቸውን አይቻለሁ ማርቲን ስለ ምጽአት የሳለቻቸውን ስዕሎች ለማየት ወደ ሊንበራ ሔደን ነበር የዶክተር ማርቲን አይደለም
" ነጭ ነጭ የለበሱ ብዙ ሰዎች አሉ አንድ ወንዝም አለ በወንዙ የሚያማምሩ ጀልባዎች ነፍሶችን ሲያመላልሱ ይታያሉ ከወንዙ ዳር ዳር በቅለው ሲታዩ የነበሩት አበባዎች ድምቀታቸ ደስ ይላል ”
"ሥዕሎቹን ለማየት ማን ወሰዳችሁ ?”
“ አባባ ' እኔ ሉሲ ' ሚስዝ ሔርና ባርባራ ሆነን ሔደን ነበር ባርባራ ያኔ እናታችን አልሆነችም ነበር ” አለና ድምፁን ድንገት ዝቅ በማድረግ '“ ሎሲ አባባን ምን ብላ ጠየቀችው መሰለሽ ?”
"ምን ብላ ጠየቀችው ? "
ከነዚያ ነጭ ነጭ ከለበሱት ብዙ ሰዎች ውስጥ እማማም አብራ ትኖር እንደ
ሆነ ወደ መንግሥተ ሰማያት ሒዳ እንደሆነ ጠየቀችው ያኔ በፊት እናታችን የነበረ
ችውንኮ ነው ወይዘሮ ሳቤላን ደሞ ስትጠይቀው ብዙ ሰው ነበር የሰማት
"አባትህ ምን መልስ ሰጣት ? ”
እንጃ " ምንም የመለሰላት አልመሰለኝም !ከባርባራ ጋር ወሬ ይዞ ነበር " እሷ አይገባትም ስለ ወይዘሮ ሳቤላ አባባ ፊት ምንም እንዳትናገር ዊልሰን ስንት
ጊዜ ነግራት ነበር መሰለሽ « ሚስ ማኒንግም እንደሱ ስትነግራት ነበር ከቤት እንደተመለስን ዊልሰን ሰማችና ትከሻና ትከሻዋን ይዛ አንዘፍዝፋ አንዘፍዝፋ ለቀቀቻት "
ለምንድነው የወይዘሮ ሳቤላ ስም ከፊቱ የማይነሣው ? አለችው »
👍14