#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሰባ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ሚስተር ካርይል ምልስ ብሎ ልጁን ከደረቱ እቅፍ ሲያደርገው እንባው ፈሰሰ
አየወረደ የልጁን ፊት አራሰው “ የኔ ልጅ ... አባባ አሁን ይመለሳል " አማማን
እንድታይክ ሊያመጣት ነው
"አናም አብራ ትመጣለች ? ደስ የምትል ልጅ ናትኮ”
"አዎን ከፈለግሃት ሕፃኒቱ አናም ትመጣለች » እነሱን ካመጣኋቸው በኋላ
ካጠግብህ ንቅንቅ አልልም
“ በል እንግዲያሙስ አስተኛኝና ሒድ "
ሚስተር ካርላይል እንባው እየወረደ ልጁን ከሚመታው ልቡ አስጠግቶ
እ.... ቅ ....ፍ ካደረገው በኋላ ትራሱን አመቻችቶ አስተኛው አሁንም
እንድ ማንኪያ የንጆራ ጭማቂ ሰጥቶት እየተጣደፈ ሔዶ "
“ ደኅና ሁን .. አባባ ” አለ ልጁ በደካማው ድምፁ » እሱ ግን አልሰማውም " ሳቤላ ከተንበረከከችበት ብድግ ብላ እጇን ወደ ሰማይ ሰቅላ እንባዋ
ዝርግፍ ዝርግፍ ብሎ እየወረዶ ትንሰቀሰቅ ጀመር
"ዊልያም . . የኔ ዓለም ፡ በዚች የሞት ሰዓት እናት ልሁንልህ " ስትለው
እንደ ገና የደከሙት ዐይኖቹን ገለጠ " ነገሩ እሷ ካለችው ዐይነት አልገባውም
“ አባባ ኮ ሊያመጣት ሔዷል ”
“ እሷን አይደለም የምልህ " እኔ እኔ ” አለችና አቋረጠችው " ከአልጋው ላይ ተደፍታ ዝም ብላ ትንሰቀሰቅ ጀመር " በዚያች በመጨረሻ ስዓት እንኳን እኔ እናትህ ነኝ ' ልትለው አልደፈረችም "
ዊልሰን ተመልሳ መጣችና “ እንቅልፍ የወሰደው ይመስላል ” አለቻት "
“ አዎን ” አለች ሳቤላ “ግድየለም ሒጅ አንድ ነገር ሲያስፈልገው እጠራሻለሁ
ዊልሰን ክፉ ሰው ባትሆንም ከዚያ የጭንቀት ክፍል መቆየቱን ስላልወደደች ወጣች " ሳቤላ ብቻዋን ቀረች " እንደገና ተንበረከከችና..... ወዲያው የዱሮው ትዝታ መጣባት " የሚስተር ካርይል ሙሽራ
ሆና ኢስት ሊን ከጎባችበት ጀምሮ እስከ ዛሬ የነበረውን ታሪኳን አሰበች "
ይህ የዱሮ ታሪኳ በየመልኩ ስታስበው አንዱ እያለ ሌላው እየተተካ እስካሁኑ ሁኔታዋ ድረስ በሐሳብ እንደ ተዋጠች አንድ ስዓት ዐለፈ " ልጁም አላስቸገረም » ሚስተር ካርላይልም ኤልተመለሰም በዚህ ሁኔታ ላይ እንዳለች ጆይስ ደረሰች ሳቤላ ከተንበረከከችበት ብድግ አለች " ጆይስ ቀጥታ መጣችና ዊልያምን
ለማየት ልብሱን ገለጥ አደረገች ዊልያም እንደሚፈልገኝ ጌቶች ነገሩኝ አለችና ስታየው ክው አለች " ማዳም ቬንም አደናገገጧን አይታ ወደ ጀይስ ጠጋብላ
እየች » ጢስ የለበሰው ለጋ ፊት ጸጥ ብሎ ተኝቷል - ያች ሁልጊዜ ዲም -ዲሞ
ስትል የኖረችው ትንሽ ልብም ሥራ አቁማለች "
ራሷን መቆጣጠር አቃታት " እንደሚሞት ተረድታ ሞቱንም በጸጋ በእርጋታ እንደምትቀበለው አምናና ዐውቃ ተቀምጣ ነበር ግን እንደዚያ ቶሎ የሚሞት እልመስላትም " ቢያንስ በጥቂቱ ሰዓት ዕድሜ እንደሚኖረው ገምታ ነበር "
አሁን ሳታስበው እንደ ደራሽ ጎርፍ ቀደማት " ጮሽች ተንሰቀሰቀች : ተጣራች
እላዩ ላይ ወደቀች ጥምጥም አድርጋ ይዛ አቀፈችው " መነጽሯንና ዐይነ ርግቧን ወረወረች » የድሮ መልኳ እንደ ነበረው ቁጭ አለ ፊቷን ከፊቱ አድርጋ አንድ ጊዜ ወደሷ ምልስ እንዲልላት ለመነችው ወደሷ ወደምትወደው ወላጅ እናት
ምልስ ብሎ ስማ እንድታስናብተው ጠራችው።
ጆይስ ከልጁ ሞት ይልቅ የሷ ሁኔታ አስደነገጣት » እንድታስብ ልብ እንድትል ያለችበትን ሁኔታ እንድትግነዘብ ለመነቻት በመጨረሻ ያለ የሌለ ጉልበቷን ተጠቅማ ካቀፈችው የልጁ ሬሳ አለያየቻት "
"ኧረ እመቤቴ ይተዉ ! ይተዉ !
'እመቤቴ ስትላት ነገሩ ልብ ራሷን መታት በዚህ አኳኋን ነበር ዱሮ ጆይስ የምትጠራት ድርቅ ብላ ደነገጠች » ስታብድ የነበረው ኩምሽሽ አለች "
ጆይስን ትክ ብላ አየቻትና የኋሊት አፈፈገች ;
“ እሜቴ . . ይበሎ እንግዲህ ወደ ክፍለዎ ልመሰድዎ " ሚስተር ካርላይል ሚስታቸውን ይዘው እየመጡ ነው " ከፊታቸው እንደዚህ ሆነው አይቆዬዋቸው እባክዎን ቶሎ ይምጡ ”
"አንቺ . . እንዴት ዐወቅሽኝ ?
“እሜቴ . . እሳት ተነሣ ተብሎ ሌሊት ተበራግገን የተነሳን ዕለት ነበር ያወቅኦ " ሕፃኑን አርኪባልድን ከዕቅፍዎ ለመቀበል ስጠጋ ሳይዎ በመንፈስ እንጂ በአካል የተገናኘን አልመሰለኝም " ፊትዎ አልተሸፈነም " በጨረቃው ብርሃን እንደ ፀሐይ ቁልጭ ብሎ ታየኝ ትንሽ ቆይቼ ድንጋጤዬ ለቀቅ ሲያደርገኝ ከእሜቴ ሳቤላ ጋር በአካል መግናኘቴን ተረዳሁ " ይበሉ አሁን እንውጣ ሚስተር ካርላይል ሊገቡ ነው " አለቻት ጆይስ
“ጆይስ . . እዘኝልኝ አታጋልጭኝ ለቅቄ እሄዳለሁ እስካለሁ ድረስ ምሥጢሬን ጠብቂልኝ አደራሽን "
“እሜቴ አይሥጉ " እስከ ዛሬ ድረስ ችዬው ኖሬአለሁ አሁንም እችለዋለዑ"
በርግጥ ወደዚህ በመምጣትዎ ተሳስተዋል " እኔም ካሁን አሁን ምን ይፈጠር ይሆን ? እያልኩ የልብ ሰላም የሌት እንቅልፍ አጥቻለሁ "
"ሰማሽ ጆይስ . . ከነዚህ ካልታደሉት ልጆቼ ተለይቼ መኖሩ አቃተኝ እኔ ግን ወደዚህ በመምጣቴ የተቀጣሁ አይመስልሽም ? እሱን ባሌን የሌላ ባል
ሆኖ ማየቱ ቀላል ነገር ነው ? ይኸ ራሱ አየገደለኝ ነው።
“ ኧረ ይምጡ እባክዎ ! ይኸው ሲመጡ ሰማኋቸው
አንደ ማባበልም እንደ
መጎተትም አድርጋ ከክፍሏ አስገባቻትና እየሮጠች
"ተመለሰች " ልክ ሚስተር ካርሳይል ከልጁ ክፍል ሲገባ አብራ ገባች ከእግር
እስከ ራሷ ተንቀጠቀጠች "
' ጆይስ ! ምን ነካሽ ? አመመሽ ? ” አላት
ጌታዬ ይዘጋጁ ! ዊልያም–– ዊልያም
ጆይስ ! ሞተ እንዳትይኝ ? ”
መቸስ ጌታዬ ምን ይደረጋል? ከዚህ የሚቀር የለም ።
ሚስተር ካርላይል ወደ ወስጥ ገብቶ መዝጊያውን በስተውስጥ ቀርቅሮ ወደ
የመነመነው የሕፃን ፊቱ ልጁ ተጠጋ " ከትራሱ ዝንጥፍ ብሎ ወድቆ አየው
" ልጄ ! ልጄ ወይ ልጄ ! ” እያለ “ጌታ ሆይ ያቺን ያልታደለች እናቱን ተቀ
ብለሃታል ብዬ እንደማምነው ሁሉ የዚህንም ሕፃን ነፍስ ታርፍ ዘንድ ተቀበላት” ብሎ ጸለየ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሎርድ ማውንት ስቨርን ከዊልያም ካርላይል ቀብር ላይ ለመግኘት ከልጁ ጋር
መጣ ዊልሰን እንዳሰበችው ዊልያም ካባቱ አባት ጎን ተቀበረ » መቃብሩ ላይ !
ዊልያም ቬን ካርላይል የኢስት ሊኑ አርኪባልድ ካርላይል የመጀመሪያ ወንድ ልጅ የሚል ዕብነበረድ አቆመበት " ዐይን ካረፈባቸው ኀዘንተኞች አንዱ
ሪቻርድ ሔር ትንሹ ነበር "
ሳቤላ በአእምሮም ሆነ በአካልም ይዞታዋ በጣም የሚያሠጋ ሆነ ነገር ግን
ሐኪም እንዲያያት ስለ አልፈለገች የሕመሟ መጠን አልታወቀላትም ይታይባት
የነበረ የበሽተኝት ምልክት ዊልያምን ያለ ዕረፍት ስታስታምም ከድካም ብዛት
የመጣ ስለመሰለ በቤተሰብ ዘንድ አሳሳቢ ሆኖ አልታየም " ከክፍሏ መውጣት
ስትተው ጆይስ ታስታምማት ጀመር " እሷ ግን የሰው ልጆች ኃይልና ጥበብ
ሊመልሰው የማይችል ሞት በመምጣት ላይ እንደ ነበር ዐውቃው ነበር ነገር
ግን ኢስት ሊን ሆና ለመሞት አልፈለገችም ሐሳቧን በሙሉ አሰባስባ ከኢስት
ሊን የምትወጣበትን መንገድ ማውጣት ማውረድ ተግባሯ አደረገችው " እንዳትታወቅ የነበራት ሥጋት እንደ ወትሮው ማስጨነቁን እየቀነሰላት ሔደ መታወቋ ሊያስከትለው ለነበረው ውጤት ማሰቡንም ተወችው " ወደ መቃብር ሲቃረቡ ማንኛቸውም ዐይነት የዚህ ዓለም ፍራቶችና ተስፋዎች ሁሉ ኃይላቸውን ያጣል
፡
፡
#ክፍል_ሰባ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ሚስተር ካርይል ምልስ ብሎ ልጁን ከደረቱ እቅፍ ሲያደርገው እንባው ፈሰሰ
አየወረደ የልጁን ፊት አራሰው “ የኔ ልጅ ... አባባ አሁን ይመለሳል " አማማን
እንድታይክ ሊያመጣት ነው
"አናም አብራ ትመጣለች ? ደስ የምትል ልጅ ናትኮ”
"አዎን ከፈለግሃት ሕፃኒቱ አናም ትመጣለች » እነሱን ካመጣኋቸው በኋላ
ካጠግብህ ንቅንቅ አልልም
“ በል እንግዲያሙስ አስተኛኝና ሒድ "
ሚስተር ካርላይል እንባው እየወረደ ልጁን ከሚመታው ልቡ አስጠግቶ
እ.... ቅ ....ፍ ካደረገው በኋላ ትራሱን አመቻችቶ አስተኛው አሁንም
እንድ ማንኪያ የንጆራ ጭማቂ ሰጥቶት እየተጣደፈ ሔዶ "
“ ደኅና ሁን .. አባባ ” አለ ልጁ በደካማው ድምፁ » እሱ ግን አልሰማውም " ሳቤላ ከተንበረከከችበት ብድግ ብላ እጇን ወደ ሰማይ ሰቅላ እንባዋ
ዝርግፍ ዝርግፍ ብሎ እየወረዶ ትንሰቀሰቅ ጀመር
"ዊልያም . . የኔ ዓለም ፡ በዚች የሞት ሰዓት እናት ልሁንልህ " ስትለው
እንደ ገና የደከሙት ዐይኖቹን ገለጠ " ነገሩ እሷ ካለችው ዐይነት አልገባውም
“ አባባ ኮ ሊያመጣት ሔዷል ”
“ እሷን አይደለም የምልህ " እኔ እኔ ” አለችና አቋረጠችው " ከአልጋው ላይ ተደፍታ ዝም ብላ ትንሰቀሰቅ ጀመር " በዚያች በመጨረሻ ስዓት እንኳን እኔ እናትህ ነኝ ' ልትለው አልደፈረችም "
ዊልሰን ተመልሳ መጣችና “ እንቅልፍ የወሰደው ይመስላል ” አለቻት "
“ አዎን ” አለች ሳቤላ “ግድየለም ሒጅ አንድ ነገር ሲያስፈልገው እጠራሻለሁ
ዊልሰን ክፉ ሰው ባትሆንም ከዚያ የጭንቀት ክፍል መቆየቱን ስላልወደደች ወጣች " ሳቤላ ብቻዋን ቀረች " እንደገና ተንበረከከችና..... ወዲያው የዱሮው ትዝታ መጣባት " የሚስተር ካርይል ሙሽራ
ሆና ኢስት ሊን ከጎባችበት ጀምሮ እስከ ዛሬ የነበረውን ታሪኳን አሰበች "
ይህ የዱሮ ታሪኳ በየመልኩ ስታስበው አንዱ እያለ ሌላው እየተተካ እስካሁኑ ሁኔታዋ ድረስ በሐሳብ እንደ ተዋጠች አንድ ስዓት ዐለፈ " ልጁም አላስቸገረም » ሚስተር ካርላይልም ኤልተመለሰም በዚህ ሁኔታ ላይ እንዳለች ጆይስ ደረሰች ሳቤላ ከተንበረከከችበት ብድግ አለች " ጆይስ ቀጥታ መጣችና ዊልያምን
ለማየት ልብሱን ገለጥ አደረገች ዊልያም እንደሚፈልገኝ ጌቶች ነገሩኝ አለችና ስታየው ክው አለች " ማዳም ቬንም አደናገገጧን አይታ ወደ ጀይስ ጠጋብላ
እየች » ጢስ የለበሰው ለጋ ፊት ጸጥ ብሎ ተኝቷል - ያች ሁልጊዜ ዲም -ዲሞ
ስትል የኖረችው ትንሽ ልብም ሥራ አቁማለች "
ራሷን መቆጣጠር አቃታት " እንደሚሞት ተረድታ ሞቱንም በጸጋ በእርጋታ እንደምትቀበለው አምናና ዐውቃ ተቀምጣ ነበር ግን እንደዚያ ቶሎ የሚሞት እልመስላትም " ቢያንስ በጥቂቱ ሰዓት ዕድሜ እንደሚኖረው ገምታ ነበር "
አሁን ሳታስበው እንደ ደራሽ ጎርፍ ቀደማት " ጮሽች ተንሰቀሰቀች : ተጣራች
እላዩ ላይ ወደቀች ጥምጥም አድርጋ ይዛ አቀፈችው " መነጽሯንና ዐይነ ርግቧን ወረወረች » የድሮ መልኳ እንደ ነበረው ቁጭ አለ ፊቷን ከፊቱ አድርጋ አንድ ጊዜ ወደሷ ምልስ እንዲልላት ለመነችው ወደሷ ወደምትወደው ወላጅ እናት
ምልስ ብሎ ስማ እንድታስናብተው ጠራችው።
ጆይስ ከልጁ ሞት ይልቅ የሷ ሁኔታ አስደነገጣት » እንድታስብ ልብ እንድትል ያለችበትን ሁኔታ እንድትግነዘብ ለመነቻት በመጨረሻ ያለ የሌለ ጉልበቷን ተጠቅማ ካቀፈችው የልጁ ሬሳ አለያየቻት "
"ኧረ እመቤቴ ይተዉ ! ይተዉ !
'እመቤቴ ስትላት ነገሩ ልብ ራሷን መታት በዚህ አኳኋን ነበር ዱሮ ጆይስ የምትጠራት ድርቅ ብላ ደነገጠች » ስታብድ የነበረው ኩምሽሽ አለች "
ጆይስን ትክ ብላ አየቻትና የኋሊት አፈፈገች ;
“ እሜቴ . . ይበሎ እንግዲህ ወደ ክፍለዎ ልመሰድዎ " ሚስተር ካርላይል ሚስታቸውን ይዘው እየመጡ ነው " ከፊታቸው እንደዚህ ሆነው አይቆዬዋቸው እባክዎን ቶሎ ይምጡ ”
"አንቺ . . እንዴት ዐወቅሽኝ ?
“እሜቴ . . እሳት ተነሣ ተብሎ ሌሊት ተበራግገን የተነሳን ዕለት ነበር ያወቅኦ " ሕፃኑን አርኪባልድን ከዕቅፍዎ ለመቀበል ስጠጋ ሳይዎ በመንፈስ እንጂ በአካል የተገናኘን አልመሰለኝም " ፊትዎ አልተሸፈነም " በጨረቃው ብርሃን እንደ ፀሐይ ቁልጭ ብሎ ታየኝ ትንሽ ቆይቼ ድንጋጤዬ ለቀቅ ሲያደርገኝ ከእሜቴ ሳቤላ ጋር በአካል መግናኘቴን ተረዳሁ " ይበሉ አሁን እንውጣ ሚስተር ካርላይል ሊገቡ ነው " አለቻት ጆይስ
“ጆይስ . . እዘኝልኝ አታጋልጭኝ ለቅቄ እሄዳለሁ እስካለሁ ድረስ ምሥጢሬን ጠብቂልኝ አደራሽን "
“እሜቴ አይሥጉ " እስከ ዛሬ ድረስ ችዬው ኖሬአለሁ አሁንም እችለዋለዑ"
በርግጥ ወደዚህ በመምጣትዎ ተሳስተዋል " እኔም ካሁን አሁን ምን ይፈጠር ይሆን ? እያልኩ የልብ ሰላም የሌት እንቅልፍ አጥቻለሁ "
"ሰማሽ ጆይስ . . ከነዚህ ካልታደሉት ልጆቼ ተለይቼ መኖሩ አቃተኝ እኔ ግን ወደዚህ በመምጣቴ የተቀጣሁ አይመስልሽም ? እሱን ባሌን የሌላ ባል
ሆኖ ማየቱ ቀላል ነገር ነው ? ይኸ ራሱ አየገደለኝ ነው።
“ ኧረ ይምጡ እባክዎ ! ይኸው ሲመጡ ሰማኋቸው
አንደ ማባበልም እንደ
መጎተትም አድርጋ ከክፍሏ አስገባቻትና እየሮጠች
"ተመለሰች " ልክ ሚስተር ካርሳይል ከልጁ ክፍል ሲገባ አብራ ገባች ከእግር
እስከ ራሷ ተንቀጠቀጠች "
' ጆይስ ! ምን ነካሽ ? አመመሽ ? ” አላት
ጌታዬ ይዘጋጁ ! ዊልያም–– ዊልያም
ጆይስ ! ሞተ እንዳትይኝ ? ”
መቸስ ጌታዬ ምን ይደረጋል? ከዚህ የሚቀር የለም ።
ሚስተር ካርላይል ወደ ወስጥ ገብቶ መዝጊያውን በስተውስጥ ቀርቅሮ ወደ
የመነመነው የሕፃን ፊቱ ልጁ ተጠጋ " ከትራሱ ዝንጥፍ ብሎ ወድቆ አየው
" ልጄ ! ልጄ ወይ ልጄ ! ” እያለ “ጌታ ሆይ ያቺን ያልታደለች እናቱን ተቀ
ብለሃታል ብዬ እንደማምነው ሁሉ የዚህንም ሕፃን ነፍስ ታርፍ ዘንድ ተቀበላት” ብሎ ጸለየ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሎርድ ማውንት ስቨርን ከዊልያም ካርላይል ቀብር ላይ ለመግኘት ከልጁ ጋር
መጣ ዊልሰን እንዳሰበችው ዊልያም ካባቱ አባት ጎን ተቀበረ » መቃብሩ ላይ !
ዊልያም ቬን ካርላይል የኢስት ሊኑ አርኪባልድ ካርላይል የመጀመሪያ ወንድ ልጅ የሚል ዕብነበረድ አቆመበት " ዐይን ካረፈባቸው ኀዘንተኞች አንዱ
ሪቻርድ ሔር ትንሹ ነበር "
ሳቤላ በአእምሮም ሆነ በአካልም ይዞታዋ በጣም የሚያሠጋ ሆነ ነገር ግን
ሐኪም እንዲያያት ስለ አልፈለገች የሕመሟ መጠን አልታወቀላትም ይታይባት
የነበረ የበሽተኝት ምልክት ዊልያምን ያለ ዕረፍት ስታስታምም ከድካም ብዛት
የመጣ ስለመሰለ በቤተሰብ ዘንድ አሳሳቢ ሆኖ አልታየም " ከክፍሏ መውጣት
ስትተው ጆይስ ታስታምማት ጀመር " እሷ ግን የሰው ልጆች ኃይልና ጥበብ
ሊመልሰው የማይችል ሞት በመምጣት ላይ እንደ ነበር ዐውቃው ነበር ነገር
ግን ኢስት ሊን ሆና ለመሞት አልፈለገችም ሐሳቧን በሙሉ አሰባስባ ከኢስት
ሊን የምትወጣበትን መንገድ ማውጣት ማውረድ ተግባሯ አደረገችው " እንዳትታወቅ የነበራት ሥጋት እንደ ወትሮው ማስጨነቁን እየቀነሰላት ሔደ መታወቋ ሊያስከትለው ለነበረው ውጤት ማሰቡንም ተወችው " ወደ መቃብር ሲቃረቡ ማንኛቸውም ዐይነት የዚህ ዓለም ፍራቶችና ተስፋዎች ሁሉ ኃይላቸውን ያጣል
👍15