#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሰባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
የሊንበረ የችሎት አዳራሽ በጣም ሰፊ ባይሆን ኖሮ ሰር ፍራንሲዝ ሌቪሰን
በጆርጅ ሆሊጆን ማድያ የተከሰሰበትን ፍርድ ለመስማት ከመጣው ብዙ ሕዝብ አብዛኛው ቦታ ባለ ማግኘት ሳይሰማ ይቀር ነበር "
ጕዳዩ ከተከሳሹ ማዕረግ ጋር በማነጻጸር ተከሳሹ ቀደም ሲል ከነበረው ታሪክና በተለይም እመቤት ሳቤላ ካርላይልን ከሚመለከተው ሥራው ጋር በማገናዘብ
በሪቻርድ ሔር የተላለፈው ፍርድ ወንጀሉ የተፈጸመበት ዘመን መርዘም አፊ የተጫወተችው ሚና የኦትዌይ ቤቴልን ትክክለኛ ድርጊት ለማወቅ ከፍተኛ ጕጕት ነበረ የድርጊቱን ዝርዝር ትክከለኛ ገጽታ የመረዳት ፍላጐት ሁሉ
የሕዝቡን ጉጕት አራገበው » ከጠቅላላው ሕዝብ ውስጥ የሚስተር ካርላይል :
የሔር ቤተሰቦችና ወዳጆች : የሻሎነር የእስረኛው ቤተሰቦችና ወዳጆች ጭምር ነበሩ ኮሎኔል ቤቴልና ጀስቲስ ሔር ግልጽ ከሆነ ቦታ ላይ ተቀምጠው ነበር ።
ዳኞቹ ከሦስት ስዓት ጥቂት ቆይተው ተሠየሙ ኦትዌይ ቤቴል የዐቃቤ ሕግ
ምስክር እንዲሆን ተደረገ የሚል ዳኞቹ ገና ሳይሠየሙ ወሬው ካፍ ወደ አፍ ሲሸጋግር ቆይቶ ነበር " የዚህንም ወሬ ትክክለኛነት ለመስማት የጓጉ ሁሉ አንገታቸውን እያስገጉ ለማዳመጥ ይጠብቁ ጀመር
ቀደም ሲል የሰጡትን ምስክርነት መድገም አላስፈለገም ነበር " የጎደለ
ቢኖር አንዳንዶቹ እየተጠየቁ ካስተካከሉ በኋላ'ያልተሰሙ ምስክሮች እንዲስሙ
ተደረገ።
“ሪቻርድ ሔርን ጥራ ” አለ ዳኛው
ሚስተር ሔርን የሚያውቁ ሁሉ ስሙ እየተጠራ ለምን እንደማይነሣ ራሳቸውን እየጠየቁ ሲደነቁ ሪቻርድ ሔር ትንሹ” ብቅ አለ "
በፍርድ ቤቱ አዳራሽ የነበረው ሕዝብ ሲንሾካሾክ ተሰማ " የተሰደዶው ሞተ የተባለው አሁንም ሕይወቱ በአጠራጣሪ ሁኔታ ያለው ሪቻርድ ሔር ሲዘልቅ አጫጭሮች ደኅና አድርገው ለማየት እየተንጠራሩ በግሮቻቸው ጫፍ ቆሙ።ሰብሳቢው ሁሉም ጸጥ እንዲል ጠየቀ ሁለት መኮንኖች ቀስ ብለው መጥተው ከኋላ ቆሙ እሱ ሊያቀው ባይችልም በጥበቃ ሥር ዋለ በደንቡ መሠረት ምሎ ማንነቱን ሁሉ ተናግሮ ምስክርነቱን ቀጠለ
“እስረኛውን ዞር በልና ደህና አድርገህ ተመልከተው
“ታውቀዋለህ ?
“ አሁን ስር ፍራንሲዝ ሌቪሰን መሆኑን ዐወቅሁት እስካለፈው ሚያዝያ
ድረስ ግን ስሙ ቶርን መሆኑን ነበር የማውቀው
እስኪ የግድያው ዕለት ማታ እስከምታውቀው ድረስ የሆነውን ንገረን ።”
“ ያን ዕለት ማታ ከአፊ ጋር ቀጠሮ ስለ ነበረኝ ወደ ቤታቸው ሔድኩ "
ቀጠሮህ በምስጢር ነበር ?”
"በከፊል ከዎን » ከአፊ ጋር የመቃረቤን ነገር ወላጆቼ ስለማይወዱልኝ
እኔም መሔዴን እንዲያውቁ አልፌልግም ነበር " ስለዚህ ከራት በኋላ ጠበንጃ ይዤ
ስወጣ አባቴ የምሔድበትን
ቢጠይቁኝ ቦሻ ዘንድ ብዬ ዋሽቼ ሔድኰ እኔ ግን ለሆሊጆን ላውሰው ቃል ገብቸለት የነበረውን ጠበንጃ ይዠ ከቤቱ ስደርስ
አፊ ሥራ አለብኝ ብላ እንዳልገባ ከለከለችኝ " እኔም ቶርን ከቤት መኖሩ
ገባኝ " ከዚያ በፊትም እሷ በሰጠችኝ ቀጠሮ እየሔድኩ ከአንድ ጊዜ በላይ ከውጭ
መልሳኝ ነበር እኔም እንቅፋት እየሆነ ከደጅ እንድመለስ ያደረገኝ የቶርን
ከቤት መኖር መሆኑን ደጋግሜ ደርሸበት ነበር " "
“ከቶርን ጋር ትቀናኑ ነበር ማለት ነው ?
“የሱን አውቅም እኔ ግን በርግጥ እቀና ነበር ” አለ ሪቻርድ
“ እሺ ቀጥል የምሽቱን ሁኔታ "
“ከሷ ጋር ብጨቃጨቅም እንዳላስገባችኝ ቁርጡን ሳውቅ ጠበንጃው መጕረሱን ነግሬያት ለአባቷ እንድትሰጥ አስረክቤያት ተመለስኩ "ቶርን ከቤት
መኖሩን ስለ ካዶች እውነቷን መሆኑን በዐይኔ አይቸ ለማረጋገጥ ወደ ዱር ገባ ብዬ ተሸሽጌ እመለከት ጀመር " ሎክስሌይ አየኝና ለምን እንደ ተሸሽግሁ ቢጠይቀኝ ምንም ሳልመልስለት ዝም አልኩ ግማሽ ሰዓት ሳልቆይ ከሆሊጆን ቤት በኩል
ተኩስ ሰማሁ " እንግዲህ ሆሊጆንን የገደለው ያ ተኩስ ነበር "
“ ተኩስ በኦትዌይ ቤቴል ሊተኮስ የሚችል ይመስልሃል ?
አይችልም " እሱ ከነበረበት ራቅ ብሎ ነበር የተተኮሰው ቤቴል ከነበረበት ጠፋ " ወዲያው አንድ ሰውዬ ፊቱ ጭው ብሎ ገርጥቶ • ዐይኖቹን አፍጦ ቁና ቁና እየተነፈሰ ልቡ እስኪወልቅ እየበረረ መጣና ሽው ብሎ ዐልፎኝ ሲሔድ ቶርን መሆኑን አየሁት " ከኔ ዐልፎ እንደ ሔዶ ወዲያው የፈረስ ኮቴ ሰማሁ "ከዱሩ አስሮት ነበር "
“ተከተልከሙ ?
“ የለም " ምን እንደዚያ እንዳደረገው እየገረመኝ አፊ ለሁለታችንም አለው
እያለች ስለ አታለለችኝ ልሰድባት እየሮጥኩ እንደ ገባሁ አነቀፈኝና ከተዘረረው
የሆሊጆን ሬሳ ላይ ወደቅሁ " ነፍሱ ወጥቶ ከመዝጊያው ሥር ወድቆ ነበር" ጠበንጃዬ ጥይቱ ተተኰሶ ቀፎው ብቻ ከወሉሉ ተጥሉ አገኘሁት "
በአዳራሹ ውስጭ ጸጥታ ስፈነ "
“ከቤቱ ውስጥ ማንም አልነበረም አፊንም ብጠራት አልመልስልኝ አለች”
ጠበንጃዬን አነሣሁና ከቤቱ ወጥቼ ስሮጥ ሎክስሌይ ከዱሩ ወጥቶ አየኝ ግራ
ገባኝ ፈራሁ " ጠበንጃውን መልሼ ከነረበት ጣልኩና ሮጥኰ "
“ ስሸሽ ቤቴልን አገኘሁት ተኩሱ እንደ ተሰማ ወዶ ሆሊጆን ቤት ከሔደ በኋላ ተመልሶ ወደ ዱሩ ስለ ገባ ማንንም አለማየቱን " ሲነግረኝ አመንኩትና
ጥየው ሄድኩ።
“ታዲያ ዌስት ሊንን ለቀህ ሔድክ ?”
በዚያው ሌሊት ለአንድ ሁለት ቀን ዘወር ብዬ ቆይቸ ሁኔታውን ለማየት ነበር አሳቤ "
ምርመራው ቀጠለ " በመጨረሻ ጥፋቱ በኔ ላይ ተጣለ " ስለዚህ ካገር ጠፋሁ።
ቀጥላ አፊ ሃሊዮን እንደገና ተጠራች « የሰጠችው ምስክርነት ከሬቻርድ
አነጋግር ጋር አንድ ሆነ "
ከዚያ ኦትዌይ ቤቴል ተጠራና የምስክርነት ቃሉን ሰጠ።
"ሆሊጆን የተገለ ማታ አይ ጫካ ውስጥ ነበርኩ " ሪቻርድ ሔር ከወደ
ቤቱ ጠበንጃ ይዞ ሲወርድ እየሁት "
" ሪቻርድሳ አይቶህ ነበር?”
የለም " ከጫካው ገባ ብዬ ስለ ነበር ሊያየኝ አይችልም ነበር " ከቤቱ በር እንደ ተጠጋ አፊ ቶሎ ወጣችና መዝጊያውን በስተኋላዋ ይዛ ካነጋረችው በኋላ ጠበንጃውን ተቀብላው ገባች ራቅ ብዬ ስለ ነበር የተነጋገሩትን አልሰማሁም እሱም ከዚያ ቤት ተመልሶ እኔ ከነበርኩበት ርቆ ሔደ ሲደበቅ አየሁት ምን እንዳስደበቀው ሳስብ ከሆሊጆን ቤት በኩል ተኩስ ሰማሁ "
“ የተተኮሰው በሪቻርድ ሊሆን ይችላል ?
አይችልም » ተኩሱ የተሳማበት አካባቢ ከሪቻርድ ሔር ይልቅ ለእኔ
ይቀርብ ነበር "
"ቀጥል ”
“የተኮሰው ማን እንደሆነ ለመገመት እንኳን አልቻልኰም » ነገሩን ይበልጥ ለማወቅ ተኩሱን ወደ ሰማሁበት ቦታ ሳመራ ካፒቴን ቶርን እያለከለከ ሲሮጥ መጣ በጣም መደንገጡና መረበሹ ከገጽታው በግልጽ ይታይ ነበር " ዐልፎኝ ሊሔድ ሲል ክንዱን ያዝኩና፡“ምን ሆነሃል ? የተኮስከው አንተ ነበርክ? ” አልኩት
“ቆይ ለምን ጠረጠርከው ?
“ደንግጦ ነበር መጨነቁንና መርበትበቱን በቀላሉ ዐወቅሁበት እንዲያም ስይዘሙ ጊዜ በጣም ተጨነቀ " ነጥቆኝ ሊሔድ ሞከረ አልሆነለትም ።
ስለዚህ ነግሩን ማለስለስ ፈለገ“ ዝም እንድል ነገረኝ “የዝምታሀን ዋጋ እሰጥሃለሁ » ሳይታሰብ በንዴት ያደረግሁት ነው ሰውየው ሁልጊዜ ይሰድበኛል ልጂቱን " ምንም አላደረግኋትም” አለኝና የሃምሳ ፓውንድ ኖት በእጄ ሸጎጠልኝ » የሆነ ነግር ያልሆነ ማድረግ አይቻልም " ስለዚህ እኔን ማየትህን መናገር ለምንም አይጠቅምህም ሲለኝ ፡ እኔም ያንን ገንዘብ ወሰድኩና እንደማልናገር
ነገርኩት " ነገር ግን ሰው መግደሉን አላወቅሁም !አልጠረጠርኩም ነበር »
“ ታዲያ ምን ተደርጓል ብለህ አሰብh ?”
፡
፡
#ክፍል_ሰባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
የሊንበረ የችሎት አዳራሽ በጣም ሰፊ ባይሆን ኖሮ ሰር ፍራንሲዝ ሌቪሰን
በጆርጅ ሆሊጆን ማድያ የተከሰሰበትን ፍርድ ለመስማት ከመጣው ብዙ ሕዝብ አብዛኛው ቦታ ባለ ማግኘት ሳይሰማ ይቀር ነበር "
ጕዳዩ ከተከሳሹ ማዕረግ ጋር በማነጻጸር ተከሳሹ ቀደም ሲል ከነበረው ታሪክና በተለይም እመቤት ሳቤላ ካርላይልን ከሚመለከተው ሥራው ጋር በማገናዘብ
በሪቻርድ ሔር የተላለፈው ፍርድ ወንጀሉ የተፈጸመበት ዘመን መርዘም አፊ የተጫወተችው ሚና የኦትዌይ ቤቴልን ትክክለኛ ድርጊት ለማወቅ ከፍተኛ ጕጕት ነበረ የድርጊቱን ዝርዝር ትክከለኛ ገጽታ የመረዳት ፍላጐት ሁሉ
የሕዝቡን ጉጕት አራገበው » ከጠቅላላው ሕዝብ ውስጥ የሚስተር ካርላይል :
የሔር ቤተሰቦችና ወዳጆች : የሻሎነር የእስረኛው ቤተሰቦችና ወዳጆች ጭምር ነበሩ ኮሎኔል ቤቴልና ጀስቲስ ሔር ግልጽ ከሆነ ቦታ ላይ ተቀምጠው ነበር ።
ዳኞቹ ከሦስት ስዓት ጥቂት ቆይተው ተሠየሙ ኦትዌይ ቤቴል የዐቃቤ ሕግ
ምስክር እንዲሆን ተደረገ የሚል ዳኞቹ ገና ሳይሠየሙ ወሬው ካፍ ወደ አፍ ሲሸጋግር ቆይቶ ነበር " የዚህንም ወሬ ትክክለኛነት ለመስማት የጓጉ ሁሉ አንገታቸውን እያስገጉ ለማዳመጥ ይጠብቁ ጀመር
ቀደም ሲል የሰጡትን ምስክርነት መድገም አላስፈለገም ነበር " የጎደለ
ቢኖር አንዳንዶቹ እየተጠየቁ ካስተካከሉ በኋላ'ያልተሰሙ ምስክሮች እንዲስሙ
ተደረገ።
“ሪቻርድ ሔርን ጥራ ” አለ ዳኛው
ሚስተር ሔርን የሚያውቁ ሁሉ ስሙ እየተጠራ ለምን እንደማይነሣ ራሳቸውን እየጠየቁ ሲደነቁ ሪቻርድ ሔር ትንሹ” ብቅ አለ "
በፍርድ ቤቱ አዳራሽ የነበረው ሕዝብ ሲንሾካሾክ ተሰማ " የተሰደዶው ሞተ የተባለው አሁንም ሕይወቱ በአጠራጣሪ ሁኔታ ያለው ሪቻርድ ሔር ሲዘልቅ አጫጭሮች ደኅና አድርገው ለማየት እየተንጠራሩ በግሮቻቸው ጫፍ ቆሙ።ሰብሳቢው ሁሉም ጸጥ እንዲል ጠየቀ ሁለት መኮንኖች ቀስ ብለው መጥተው ከኋላ ቆሙ እሱ ሊያቀው ባይችልም በጥበቃ ሥር ዋለ በደንቡ መሠረት ምሎ ማንነቱን ሁሉ ተናግሮ ምስክርነቱን ቀጠለ
“እስረኛውን ዞር በልና ደህና አድርገህ ተመልከተው
“ታውቀዋለህ ?
“ አሁን ስር ፍራንሲዝ ሌቪሰን መሆኑን ዐወቅሁት እስካለፈው ሚያዝያ
ድረስ ግን ስሙ ቶርን መሆኑን ነበር የማውቀው
እስኪ የግድያው ዕለት ማታ እስከምታውቀው ድረስ የሆነውን ንገረን ።”
“ ያን ዕለት ማታ ከአፊ ጋር ቀጠሮ ስለ ነበረኝ ወደ ቤታቸው ሔድኩ "
ቀጠሮህ በምስጢር ነበር ?”
"በከፊል ከዎን » ከአፊ ጋር የመቃረቤን ነገር ወላጆቼ ስለማይወዱልኝ
እኔም መሔዴን እንዲያውቁ አልፌልግም ነበር " ስለዚህ ከራት በኋላ ጠበንጃ ይዤ
ስወጣ አባቴ የምሔድበትን
ቢጠይቁኝ ቦሻ ዘንድ ብዬ ዋሽቼ ሔድኰ እኔ ግን ለሆሊጆን ላውሰው ቃል ገብቸለት የነበረውን ጠበንጃ ይዠ ከቤቱ ስደርስ
አፊ ሥራ አለብኝ ብላ እንዳልገባ ከለከለችኝ " እኔም ቶርን ከቤት መኖሩ
ገባኝ " ከዚያ በፊትም እሷ በሰጠችኝ ቀጠሮ እየሔድኩ ከአንድ ጊዜ በላይ ከውጭ
መልሳኝ ነበር እኔም እንቅፋት እየሆነ ከደጅ እንድመለስ ያደረገኝ የቶርን
ከቤት መኖር መሆኑን ደጋግሜ ደርሸበት ነበር " "
“ከቶርን ጋር ትቀናኑ ነበር ማለት ነው ?
“የሱን አውቅም እኔ ግን በርግጥ እቀና ነበር ” አለ ሪቻርድ
“ እሺ ቀጥል የምሽቱን ሁኔታ "
“ከሷ ጋር ብጨቃጨቅም እንዳላስገባችኝ ቁርጡን ሳውቅ ጠበንጃው መጕረሱን ነግሬያት ለአባቷ እንድትሰጥ አስረክቤያት ተመለስኩ "ቶርን ከቤት
መኖሩን ስለ ካዶች እውነቷን መሆኑን በዐይኔ አይቸ ለማረጋገጥ ወደ ዱር ገባ ብዬ ተሸሽጌ እመለከት ጀመር " ሎክስሌይ አየኝና ለምን እንደ ተሸሽግሁ ቢጠይቀኝ ምንም ሳልመልስለት ዝም አልኩ ግማሽ ሰዓት ሳልቆይ ከሆሊጆን ቤት በኩል
ተኩስ ሰማሁ " እንግዲህ ሆሊጆንን የገደለው ያ ተኩስ ነበር "
“ ተኩስ በኦትዌይ ቤቴል ሊተኮስ የሚችል ይመስልሃል ?
አይችልም " እሱ ከነበረበት ራቅ ብሎ ነበር የተተኮሰው ቤቴል ከነበረበት ጠፋ " ወዲያው አንድ ሰውዬ ፊቱ ጭው ብሎ ገርጥቶ • ዐይኖቹን አፍጦ ቁና ቁና እየተነፈሰ ልቡ እስኪወልቅ እየበረረ መጣና ሽው ብሎ ዐልፎኝ ሲሔድ ቶርን መሆኑን አየሁት " ከኔ ዐልፎ እንደ ሔዶ ወዲያው የፈረስ ኮቴ ሰማሁ "ከዱሩ አስሮት ነበር "
“ተከተልከሙ ?
“ የለም " ምን እንደዚያ እንዳደረገው እየገረመኝ አፊ ለሁለታችንም አለው
እያለች ስለ አታለለችኝ ልሰድባት እየሮጥኩ እንደ ገባሁ አነቀፈኝና ከተዘረረው
የሆሊጆን ሬሳ ላይ ወደቅሁ " ነፍሱ ወጥቶ ከመዝጊያው ሥር ወድቆ ነበር" ጠበንጃዬ ጥይቱ ተተኰሶ ቀፎው ብቻ ከወሉሉ ተጥሉ አገኘሁት "
በአዳራሹ ውስጭ ጸጥታ ስፈነ "
“ከቤቱ ውስጥ ማንም አልነበረም አፊንም ብጠራት አልመልስልኝ አለች”
ጠበንጃዬን አነሣሁና ከቤቱ ወጥቼ ስሮጥ ሎክስሌይ ከዱሩ ወጥቶ አየኝ ግራ
ገባኝ ፈራሁ " ጠበንጃውን መልሼ ከነረበት ጣልኩና ሮጥኰ "
“ ስሸሽ ቤቴልን አገኘሁት ተኩሱ እንደ ተሰማ ወዶ ሆሊጆን ቤት ከሔደ በኋላ ተመልሶ ወደ ዱሩ ስለ ገባ ማንንም አለማየቱን " ሲነግረኝ አመንኩትና
ጥየው ሄድኩ።
“ታዲያ ዌስት ሊንን ለቀህ ሔድክ ?”
በዚያው ሌሊት ለአንድ ሁለት ቀን ዘወር ብዬ ቆይቸ ሁኔታውን ለማየት ነበር አሳቤ "
ምርመራው ቀጠለ " በመጨረሻ ጥፋቱ በኔ ላይ ተጣለ " ስለዚህ ካገር ጠፋሁ።
ቀጥላ አፊ ሃሊዮን እንደገና ተጠራች « የሰጠችው ምስክርነት ከሬቻርድ
አነጋግር ጋር አንድ ሆነ "
ከዚያ ኦትዌይ ቤቴል ተጠራና የምስክርነት ቃሉን ሰጠ።
"ሆሊጆን የተገለ ማታ አይ ጫካ ውስጥ ነበርኩ " ሪቻርድ ሔር ከወደ
ቤቱ ጠበንጃ ይዞ ሲወርድ እየሁት "
" ሪቻርድሳ አይቶህ ነበር?”
የለም " ከጫካው ገባ ብዬ ስለ ነበር ሊያየኝ አይችልም ነበር " ከቤቱ በር እንደ ተጠጋ አፊ ቶሎ ወጣችና መዝጊያውን በስተኋላዋ ይዛ ካነጋረችው በኋላ ጠበንጃውን ተቀብላው ገባች ራቅ ብዬ ስለ ነበር የተነጋገሩትን አልሰማሁም እሱም ከዚያ ቤት ተመልሶ እኔ ከነበርኩበት ርቆ ሔደ ሲደበቅ አየሁት ምን እንዳስደበቀው ሳስብ ከሆሊጆን ቤት በኩል ተኩስ ሰማሁ "
“ የተተኮሰው በሪቻርድ ሊሆን ይችላል ?
አይችልም » ተኩሱ የተሳማበት አካባቢ ከሪቻርድ ሔር ይልቅ ለእኔ
ይቀርብ ነበር "
"ቀጥል ”
“የተኮሰው ማን እንደሆነ ለመገመት እንኳን አልቻልኰም » ነገሩን ይበልጥ ለማወቅ ተኩሱን ወደ ሰማሁበት ቦታ ሳመራ ካፒቴን ቶርን እያለከለከ ሲሮጥ መጣ በጣም መደንገጡና መረበሹ ከገጽታው በግልጽ ይታይ ነበር " ዐልፎኝ ሊሔድ ሲል ክንዱን ያዝኩና፡“ምን ሆነሃል ? የተኮስከው አንተ ነበርክ? ” አልኩት
“ቆይ ለምን ጠረጠርከው ?
“ደንግጦ ነበር መጨነቁንና መርበትበቱን በቀላሉ ዐወቅሁበት እንዲያም ስይዘሙ ጊዜ በጣም ተጨነቀ " ነጥቆኝ ሊሔድ ሞከረ አልሆነለትም ።
ስለዚህ ነግሩን ማለስለስ ፈለገ“ ዝም እንድል ነገረኝ “የዝምታሀን ዋጋ እሰጥሃለሁ » ሳይታሰብ በንዴት ያደረግሁት ነው ሰውየው ሁልጊዜ ይሰድበኛል ልጂቱን " ምንም አላደረግኋትም” አለኝና የሃምሳ ፓውንድ ኖት በእጄ ሸጎጠልኝ » የሆነ ነግር ያልሆነ ማድረግ አይቻልም " ስለዚህ እኔን ማየትህን መናገር ለምንም አይጠቅምህም ሲለኝ ፡ እኔም ያንን ገንዘብ ወሰድኩና እንደማልናገር
ነገርኩት " ነገር ግን ሰው መግደሉን አላወቅሁም !አልጠረጠርኩም ነበር »
“ ታዲያ ምን ተደርጓል ብለህ አሰብh ?”
👍17👎1