አትሮኖስ
280K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
460 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#አባሮሽ


#በሕይወት_እምሻው


አብረን ያየን ሰው ሁሉ “አፈስሽ አፈስሽ” እያለ ያወራል፡፡
ቆንጀ ፣ ሎጋ፣ ረጋ ያለና ዝምተኛ ነው፡፡ የወንድ ልጅ አማላይነት
የተሠራው ከእነዚህ ተንኮለኛ ንጥረ ነገሮች አይደል?
በፍቅር መውደቅ ከገደል እንደመውደቅ ያማል? በፍቅር መያዝ
እንደ ተስቦ ያማቅቃል?
አዎ፡፡ ቢሆንም እያመመኝ እወደዋለሁ፡፡ እየማቀቅኩ አፈቅረዋለሁ፡፡
እኔ እወደዋለሁ ፤ እሱ ግን እንደ ሁሉም ሰው በግብረ ሥጋ ሳይሆን
ከመላእክት ተዳቅሎ እንደተፈጠረ ይለጠጥብኛል፡፡ ይንበላጠጥብኛል፡፡
ቢሆንም ስሜቴ ለእርሱ ባሪያ ነው፡፡ ሲያወድሰኝ ብቻ የማብብ -
ሲኮንነኝ የምጠወልግ ፤ ሲመለከተኝ የማምር - ፊቱን ሲያዞርብኝ
የማስቀይም፤ እስከሚመስለኝ ድረስ እወደዋለሁ፡፡
ይሄን ዐውቃለሁ፤ ፍቅሬ አቅብጦታል፡፡ መውደዴ አቀማጥሎታል፡፡
ብዙ ጊዜ ደህና ስንጫወት እንውልና በድንገት ያኮርፈኛል፡፡
ይኮፈሳል፡፡ ዐይኔን ማየት ይጠላል፡፡ ያን ጊዜ ሁሉ ነገር
ይዞርብኛል፡፡ ሣቄ ይከስማል። የልቤ ሱረቃ በሐዘን አታሞ ይተካል፡፡
ይገርመኛል፡፡ በስሜቴ ላይ እንዲህ እንዲሰለጥን ከመፍቀዴ በፊት ፤
እሱን ከማግኘቴ በፊት፤ በምን ነበር የምቀው? በምንስ ነበር የምደሰተው?

“ምን ሆንክብኝ?” እለዋለሁ፡፡ ልክ እንደዚያ ሲሠራው::
“ምንም አልሆንኩም.. ተይኝ ላንብብበት።” ለዚህች ለዚህች ጊዜ
ተዘጋጅታ የምትቀመጥ፣ መዥረጥ አድርጎ የሚያወጣት .
የዘወትር መልሱ ናት፡፡

"ኤሊ..."

“እ...” (ከልቡ ሳይሆን)

“ሻይ በጦስኝ ላፍሳልህ?”

(ሻይ በጦስኝ ስለሚወድ)

“አልፈልግም”

“ፍሬንድስን ልክፈትልህ?” (ፍሬንድስን አይቶ ስለማይጠግብ)
“አላሰኘኝም”

“ቶሎ ሃያ ሁለት ሄጄ የፀሐይን ሽሮ ይዤልህ ልምጣ?” (ከትግሬ ሽሮ ሌላ በዓለም ላይ ደህና ምግብ ያለ ስለማይመስለው)

“አልራበኝም...”

“እሺ ምንድነው ምትፈልገው?»

“ተይኝ ላንብብበት...”

ይሄኔ ነው፣ የአዳም ረታን አንዱን መጽሐፍ አውጥቶ ጥሎኝ
የሚሄደው፡፡ ይሄኔ ነው፣ የራሱን ክብ ዓለም ፈጥሮ አንዱን መጽሐፍ አውጥቶ ጥሎኝ አፈናጥሮ የሚያስወጣኝ።ያን ጊዜ ማውራት መቀጠሌ ለሬሳ መድኀኒት ከመስጠት እንደማይለይ ስለማውቅ ጥዬው ለመሄድ እሰናዳለሁ፡፡
መጽሐፉ ላይ ተተክሎ አንዴ የላዘዘ ፈገግታ ሲያሳይ፣ አንዴ ጮህ ብሎ ሲስቅ
ከዚያ እንደማልቀስ ሲሠራው፤ በእሱ ስሜት ላይ
በሠለጠነው ብቸኛው ሰው አዳም ረታ እቀናለሁ፡፡ አንዳንዴም የምወደውን ልጅ ስለነጠቀኝ እያልጎመጎምኩ በልቤ እረግመዋለሁ፡፡
“ብዕርህ ይንጠፍ... እጅህን ቁርጥማት ይዘዝበት...” ዓይነት ነገር፡፡
“ልሄድ ነው ቻው” እለዋለሁ፣ ጫማዬን አጥልቄ ስጨርስ፡፡
እሺ... ቻው...” ይለኛል ቦግ ቦግ ያሉ ዐይኖቹን ከመጽሐፉ
ሳይለይ፡፡ ስሜቱን ከአዳም ረታ ገጸ ባሕርያት ሳያላቅቅ፡፡
ያን ጊዜ ከእንባዬ እየታገልኩ ወደ ቤቴ!
።።።።።።።።።
ስምንት ወር አብረን ስንወጣ፤ “ስንተኛ ስንነሳ” ፤ ስንገባ፣ ስንወጣ
ብረት አሎሎ ልቡን አልፈታልኝም፡፡ ስለ አለፈ ሕይወቱ አይነግረኝም፡፡ ስለወደፊቱ አያወራኝም፡፡ ከቤተሰብ - ጓደኛ
አያስተዋውቀኝም፡፡
እየቆየ የትርፍ ሰዓት ሥራው መሆኔ ሲገለጽልኝ፣ ጭምቷ ልጅ
ላብድ ደረስኩ፡፡ ተዉኩት ስል እያገረሽ በሚያስቸግረኝ አስቀያሚ
ፍቅሩ ብሸነፍም ቁርጤን ማወቅ እንዳለብኝ አመንኩ፡፡

አንዱን ቅዳሜ ስገሰግስ ቤቱ ደረስኩ። ከሰዐት ዘጠኝ ሰዐት ቢሆንም፣
አብዝቶ የሚለብሰውን፣ እህቱ ከካናዳ የላከችለትን ፒጃማ አድርጎ
ሶፋው ላይ ተጋደም ያነባል፡፡ ማንን? ያንን በየዓመቱ መጽሐፍ የሚያመርተውን አዳም ረታ፡፡
“ስማ ኤልያስ...? እኔ እንደዚህ መቀጠል አልችልም... ማውራት
አለብን...” አልኩ፣ ቦርሳዬን አንዱ ሶፋ ላይ ወርውሬ አጠገቡ
እየተቀመጥኩ፡፡

.
“እ... ?” አለኝ፣ መጸሐፉን ሳይዘጋ ቀና ብሎ እያየኝ፡፡
“ኣመልህ ሊገባኝ አልቻለም... እኔ እወድሃለሁ... ግን የማትወደኝ
ከሆነ... ማለቴ ልብህን የማትሰጠኝ ከሆነ...”

ሳልጨርስ አቋረጠኝ፡፡

“ምንድነው የምትፈልጊው?” ተናዶም በማይለወጠው እርጋታና ግዴለሽነቱ ጠየቀኝ፡፡

.
መጽሐፉን ዘጋ፡፡ ጉዳዩ “ሲሪየስ" ነው!

“እኔ?”

“አዎ አንቺ...! ምንድነው የምትፈልጊው?”

ምንድነው የምፈልገው? እንዴትስ ብዬ ነው የምጠይቀው...?

ከአንጀቱ - እንዲህ በትኩረት እያየኝ ይጠይቀኛል ብዬ አስቤ
ስለማላውቅ፣ እያሰብኩ ያንን ውብ ፊቱን አየሁት፡፡
ጢሙ እንደምወደው አድጓል፡፡ ጠጉሩ ጨብረር ብሏል፡፡ መከረኛ
ቢጃማው እጅጌና አንገቱ ጋር መንችኳል፡፡
ብም ብሎ ያየኛል፡፡ ብዙ ጊዜ ይሄን ያህል ጊዜ ሰጥቶ አያየኝም፡፡

አንሶላ መሀል ገብተን ወንድና ሴት . ድርና ማግ ስንሆን እንኳን፣
እያስበው ዐይኖቹን በዐይኖቼ ስይዘው፣ ዐይኖቹ ላይ ትኩረትና ፍቅር
አላይም፡፡ አንዳንዴ እንደውም ውስጤ መቆየት የሰለቸው... ገላዬ
ውስጥ ዘለዓለም የከረመ ያህል፣ የታከተው የሚመስል ነገር ዐይኖቹ
ላይ አነባለሁ፡፡

እንዲህ ዐይቶኝ አያውቅም፡፡

በማውራት ይሄን ያልተለመደ ክስተት ላቋርጥና ላበላሽ ስላልፈለግኩ፣ ካለሁበት ሶፋ እየተሳብኩ ተጠጋሁት፡ ማየቱን ቀጥሏል፡፡ ደርሼ አንገቴን አንገቱ ውስጥ ቀብሬ በጥልቀት
አሽተትኩት፡፡ ጦስኝ ጦስኝ ይላል፡፡ የምወደው ልጅ በጦስኝ፡፡ልቤ እንደሰም ሲቀልጥ፣ መንፈሴ በስሜት ማዕበል ሲታመስ እንኳን፤ የማወራው የማስበው ነገር ከአንጎሌ ሲተን...

“እህስ ምንድነው የምትፈልጊው?” አለኝ፣ ከአንገቱ ውስጥ በእጁ ጎትቶ እያወጣኝ፡፡

“ምንም...”

“ምንም አትፈልጊም?”

“ኤሊ... እንድትወደኝ... እንድትወደኝ ነው የምፈልገው:: ይከብዳል?” ወደ ኣንገቱ ሥር ተመልሼ ልወሽቅ ስል፣ አሁንም
መልሶ አወጣኝና በእነዚያ አሸባሪ ዐይኖቹ እያየኝ..

“መች ጠላሁሽ...?” አለኝ፡፡

"እንደማትጠላኝ ዐውቃለሁ... ግን አንድ ቀን እወድሻለሁ ብለኸኝ አታውቅም፡፡ እ... _ ከመሬት ተነስተህ ታኮርፈኛለህ:
ታበሻቅጠኛለህ."

“ምንድነው የምትፈልጊው? በሥርዓት ቁጭ ብለን ይሄን ነገር
እንቋጨው...” አለኝ፡፡ ለስብሰባ እንደተቀመጠ ሰው መጽሐፉን
እንደተከፈተ ሶፋው ላይ አስቀምጦ፤ እጆቹን አጣምሮ፡፡ .

ቀና ብዬ ተቀመጥኩ፡፡


“ልብህን... ልብህን ነው የምፈልገው፡፡”

እጆቹን አመሳቀለና ሣቀ፡፡

ተበሳጨሁ፡፡

“ያስቃል?”

“ሃሃ... አዎ... እዚህ መጽሐፍ ላይ ያለው... አንዱ የአዳም ካራክተር' ምን አለ መሰለሽ... ልቤን ለሴት ከምስጥ ለጎረቤት ድመት ብሰጥ ይሻለኛል...”
ዝም ብዬ ዐየሁት፡፡

“ምን ታይኛለሽ... ካ'ንጀቴ እኮ ነው እውነቴን ነው፡፡”

አሁንም ዝም ብዬ ዐየሁት...

ጨረስን? ወደ መጽሐፌ ልመለስ?”

እየቀለድክ አይመስለኝም።

አልኩ፣ | በተቀመጥኩበት እየተቁነጠነጥኩ፡፡

“አይደለም አልኩሽ እኮ...”

“የአንድ ሥራ ፈት ደራሲ ተረት ተረት እና ቅዥት እያነበብክ
የእኛን ሕይወት ማበላሸት አለብህ?”
“አዳም ስለማይገባሽ አልፈርድብሽም...”
“እሱን ተወው... ዝባዝንኬ አይገባኝም... ድመት ምናምን...ሰውየው የሚያወራውን አያውቀው ... ግን አንተ ምነው ለልብህ
እንደዚህ ሣሣህ? ልብህን ስጥተኸው የጎዳህ ሰው ነበር እንዴ?”
እየተቁለጨለጭኩ ተጠየቅኩት፡፡
ዝም ብሎ ሲያየኝ ቆየና...

“ለምን ጦስኝ ሻይ አታፈይልኝም?

ጠዋት የጠጣሁ ነኝ” አለኝ፣

መጽሐፉን እያነሳ..

“ለምን አትመልስልኝም...?

ለምንድነው _ እንደዚህ ፍቅርን የምትፈራው?”

“በናትሽ ሻዩን... እያዛጋኝ ነው...”
የምናብ ደጁ ሊዘጋብኝ ነው። ለዛሬ
👍3
#አባሮሽ

አየሁሽ አየሁህ ስንጫወት አባሮሽ
ስትሸሸገኝ ሳገኝህ ስትሮጥብኝ ስከተልህ
አኩኩሉ ነግቷል ስልህ
የት ነህ የት ነሽ ስንባባል
ስንገናኝ በመሀል
እንቦርቃለን በደስታ
በልጅነት ጨዋታ
ያኔ መልካም ነበረ
ሳቅ ደስታና ፌሽታው
ችግሩ!!
ዛሬም ለአቅመ አዳም ሔዋን ደርሰን
ኑሮ ጎጆ መስርተን
እየኖርን የጋርዮሽ
ትዳር ጨዋታ መስሎህ
ለመደብህ ድብብቆሽህ፡፡

🔘ሰላም ዘውዱ🔘
👍1
#አባሮሽ


#በሕይወት_እምሻው


አብረን ያየን ሰው ሁሉ “አፈስሽ አፈስሽ” እያለ ያወራል፡፡
ቆንጀ ፣ ሎጋ፣ ረጋ ያለና ዝምተኛ ነው፡፡ የወንድ ልጅ አማላይነት
የተሠራው ከእነዚህ ተንኮለኛ ንጥረ ነገሮች አይደል?
በፍቅር መውደቅ ከገደል እንደመውደቅ ያማል? በፍቅር መያዝ
እንደ ተስቦ ያማቅቃል?
አዎ፡፡ ቢሆንም እያመመኝ እወደዋለሁ፡፡ እየማቀቅኩ አፈቅረዋለሁ፡፡
እኔ እወደዋለሁ ፤ እሱ ግን እንደ ሁሉም ሰው በግብረ ሥጋ ሳይሆን
ከመላእክት ተዳቅሎ እንደተፈጠረ ይለጠጥብኛል፡፡ ይንበላጠጥብኛል፡፡
ቢሆንም ስሜቴ ለእርሱ ባሪያ ነው፡፡ ሲያወድሰኝ ብቻ የማብብ -
ሲኮንነኝ የምጠወልግ ፤ ሲመለከተኝ የማምር - ፊቱን ሲያዞርብኝ
የማስቀይም፤ እስከሚመስለኝ ድረስ እወደዋለሁ፡፡
ይሄን ዐውቃለሁ፤ ፍቅሬ አቅብጦታል፡፡ መውደዴ አቀማጥሎታል፡፡
ብዙ ጊዜ ደህና ስንጫወት እንውልና በድንገት ያኮርፈኛል፡፡
ይኮፈሳል፡፡ ዐይኔን ማየት ይጠላል፡፡ ያን ጊዜ ሁሉ ነገር
ይዞርብኛል፡፡ ሣቄ ይከስማል። የልቤ ሱረቃ በሐዘን አታሞ ይተካል፡፡
ይገርመኛል፡፡ በስሜቴ ላይ እንዲህ እንዲሰለጥን ከመፍቀዴ በፊት ፤
እሱን ከማግኘቴ በፊት፤ በምን ነበር የምቀው? በምንስ ነበር የምደሰተው?

“ምን ሆንክብኝ?” እለዋለሁ፡፡ ልክ እንደዚያ ሲሠራው::
“ምንም አልሆንኩም.. ተይኝ ላንብብበት።” ለዚህች ለዚህች ጊዜ
ተዘጋጅታ የምትቀመጥ፣ መዥረጥ አድርጎ የሚያወጣት .
የዘወትር መልሱ ናት፡፡

"ኤሊ..."

“እ...” (ከልቡ ሳይሆን)

“ሻይ በጦስኝ ላፍሳልህ?”

(ሻይ በጦስኝ ስለሚወድ)

“አልፈልግም”

“ፍሬንድስን ልክፈትልህ?” (ፍሬንድስን አይቶ ስለማይጠግብ)
“አላሰኘኝም”

“ቶሎ ሃያ ሁለት ሄጄ የፀሐይን ሽሮ ይዤልህ ልምጣ?” (ከትግሬ ሽሮ ሌላ በዓለም ላይ ደህና ምግብ ያለ ስለማይመስለው)

“አልራበኝም...”

“እሺ ምንድነው ምትፈልገው?»

“ተይኝ ላንብብበት...”

ይሄኔ ነው፣ የአዳም ረታን አንዱን መጽሐፍ አውጥቶ ጥሎኝ
የሚሄደው፡፡ ይሄኔ ነው፣ የራሱን ክብ ዓለም ፈጥሮ  አንዱን መጽሐፍ አውጥቶ ጥሎኝ አፈናጥሮ የሚያስወጣኝ።ያን ጊዜ ማውራት መቀጠሌ ለሬሳ መድኀኒት ከመስጠት እንደማይለይ ስለማውቅ ጥዬው ለመሄድ እሰናዳለሁ፡፡
መጽሐፉ ላይ  ተተክሎ  አንዴ የላዘዘ ፈገግታ ሲያሳይ፣ አንዴ ጮህ ብሎ ሲስቅ
ከዚያ እንደማልቀስ ሲሠራው፤ በእሱ ስሜት ላይ
በሠለጠነው ብቸኛው ሰው አዳም ረታ እቀናለሁ፡፡ አንዳንዴም የምወደውን ልጅ ስለነጠቀኝ እያልጎመጎምኩ በልቤ እረግመዋለሁ፡፡
“ብዕርህ ይንጠፍ... እጅህን ቁርጥማት ይዘዝበት...” ዓይነት ነገር፡፡
“ልሄድ ነው ቻው” እለዋለሁ፣ ጫማዬን አጥልቄ ስጨርስ፡፡
እሺ... ቻው...” ይለኛል ቦግ ቦግ ያሉ ዐይኖቹን ከመጽሐፉ
ሳይለይ፡፡ ስሜቱን ከአዳም ረታ ገጸ ባሕርያት ሳያላቅቅ፡፡
ያን ጊዜ ከእንባዬ እየታገልኩ ወደ ቤቴ!
             ።።።።።።።።።
ስምንት ወር አብረን ስንወጣ፤ “ስንተኛ ስንነሳ” ፤ ስንገባ፣ ስንወጣ
ብረት አሎሎ ልቡን አልፈታልኝም፡፡ ስለ አለፈ ሕይወቱ አይነግረኝም፡፡ ስለወደፊቱ አያወራኝም፡፡ ከቤተሰብ - ጓደኛ
አያስተዋውቀኝም፡፡
እየቆየ የትርፍ ሰዓት ሥራው መሆኔ ሲገለጽልኝ፣ ጭምቷ ልጅ
ላብድ ደረስኩ፡፡ ተዉኩት ስል እያገረሽ በሚያስቸግረኝ አስቀያሚ
ፍቅሩ ብሸነፍም ቁርጤን ማወቅ እንዳለብኝ አመንኩ፡፡

አንዱን ቅዳሜ ስገሰግስ ቤቱ ደረስኩ። ከሰዐት ዘጠኝ ሰዐት ቢሆንም፣
አብዝቶ የሚለብሰውን፣ እህቱ ከካናዳ የላከችለትን ፒጃማ አድርጎ
ሶፋው ላይ ተጋደም ያነባል፡፡ ማንን? ያንን በየዓመቱ መጽሐፍ የሚያመርተውን አዳም ረታ፡፡
“ስማ ኤልያስ...? እኔ እንደዚህ መቀጠል አልችልም... ማውራት
አለብን...” አልኩ፣ ቦርሳዬን አንዱ ሶፋ ላይ ወርውሬ አጠገቡ
እየተቀመጥኩ፡፡

.
“እ... ?” አለኝ፣ መጸሐፉን ሳይዘጋ ቀና ብሎ እያየኝ፡፡
“ኣመልህ ሊገባኝ አልቻለም... እኔ እወድሃለሁ... ግን የማትወደኝ
ከሆነ... ማለቴ ልብህን የማትሰጠኝ ከሆነ...”

ሳልጨርስ አቋረጠኝ፡፡

“ምንድነው የምትፈልጊው?” ተናዶም በማይለወጠው እርጋታና ግዴለሽነቱ ጠየቀኝ፡፡

.
መጽሐፉን ዘጋ፡፡ ጉዳዩ “ሲሪየስ"  ነው!

“እኔ?”

“አዎ አንቺ...! ምንድነው የምትፈልጊው?”

ምንድነው የምፈልገው? እንዴትስ ብዬ ነው የምጠይቀው...?

ከአንጀቱ - እንዲህ በትኩረት እያየኝ ይጠይቀኛል ብዬ አስቤ
ስለማላውቅ፣ እያሰብኩ ያንን ውብ ፊቱን አየሁት፡፡
ጢሙ እንደምወደው አድጓል፡፡ ጠጉሩ ጨብረር ብሏል፡፡ መከረኛ
ቢጃማው እጅጌና አንገቱ ጋር መንችኳል፡፡
ብም ብሎ ያየኛል፡፡ ብዙ ጊዜ ይሄን ያህል ጊዜ ሰጥቶ አያየኝም፡፡

አንሶላ መሀል ገብተን ወንድና ሴት . ድርና ማግ ስንሆን እንኳን፣
እያስበው ዐይኖቹን በዐይኖቼ ስይዘው፣ ዐይኖቹ ላይ ትኩረትና ፍቅር
አላይም፡፡ አንዳንዴ እንደውም ውስጤ መቆየት የሰለቸው... ገላዬ
ውስጥ ዘለዓለም የከረመ ያህል፣ የታከተው የሚመስል ነገር ዐይኖቹ
ላይ አነባለሁ፡፡

እንዲህ ዐይቶኝ አያውቅም፡፡

በማውራት ይሄን ያልተለመደ ክስተት ላቋርጥና ላበላሽ ስላልፈለግኩ፣ ካለሁበት ሶፋ እየተሳብኩ ተጠጋሁት፡ ማየቱን ቀጥሏል፡፡ ደርሼ አንገቴን አንገቱ ውስጥ ቀብሬ በጥልቀት
አሽተትኩት፡፡ ጦስኝ ጦስኝ ይላል፡፡ የምወደው ልጅ በጦስኝ፡፡ልቤ እንደሰም ሲቀልጥ፣ መንፈሴ በስሜት ማዕበል ሲታመስ እንኳን፤ የማወራው የማስበው ነገር ከአንጎሌ ሲተን...

“እህስ ምንድነው የምትፈልጊው?” አለኝ፣ ከአንገቱ ውስጥ በእጁ ጎትቶ እያወጣኝ፡፡

“ምንም...”

“ምንም አትፈልጊም?”

“ኤሊ... እንድትወደኝ... እንድትወደኝ ነው የምፈልገው:: ይከብዳል?” ወደ ኣንገቱ ሥር ተመልሼ ልወሽቅ ስል፣ አሁንም
መልሶ አወጣኝና በእነዚያ አሸባሪ ዐይኖቹ እያየኝ..

“መች ጠላሁሽ...?” አለኝ፡፡

"እንደማትጠላኝ ዐውቃለሁ... ግን አንድ ቀን እወድሻለሁ ብለኸኝ አታውቅም፡፡ እ... ከመሬት ተነስተህ ታኮርፈኛለህ:
ታበሻቅጠኛለህ."

“ምንድነው የምትፈልጊው? በሥርዓት ቁጭ ብለን ይሄን ነገር
እንቋጨው...” አለኝ፡፡ ለስብሰባ እንደተቀመጠ ሰው መጽሐፉን
እንደተከፈተ ሶፋው ላይ አስቀምጦ፤ እጆቹን አጣምሮ፡፡ .

ቀና ብዬ ተቀመጥኩ፡፡


“ልብህን... ልብህን ነው የምፈልገው፡፡”

እጆቹን አመሳቀለና ሣቀ፡፡

ተበሳጨሁ፡፡

“ያስቃል?”

“ሃሃ... አዎ... እዚህ መጽሐፍ ላይ ያለው... አንዱ የአዳም ካራክተር' ምን አለ መሰለሽ... ልቤን ለሴት ከምስጥ ለጎረቤት ድመት ብሰጥ ይሻለኛል...”
ዝም ብዬ ዐየሁት፡፡

“ምን ታይኛለሽ... ካ'ንጀቴ እኮ ነው እውነቴን ነው፡፡”

አሁንም ዝም ብዬ ዐየሁት...

ጨረስን? ወደ መጽሐፌ ልመለስ?”

እየቀለድክ አይመስለኝም።

አልኩ፣ | በተቀመጥኩበት እየተቁነጠነጥኩ፡፡

“አይደለም አልኩሽ እኮ...”

“የአንድ ሥራ ፈት ደራሲ ተረት ተረት እና ቅዥት እያነበብክ
የእኛን ሕይወት ማበላሸት አለብህ?”
“አዳም ስለማይገባሽ አልፈርድብሽም...”
“እሱን ተወው... ዝባዝንኬ አይገባኝም... ድመት ምናምን...ሰውየው የሚያወራውን አያውቀው ... ግን አንተ ምነው ለልብህ
እንደዚህ ሣሣህ? ልብህን ስጥተኸው የጎዳህ ሰው ነበር እንዴ?”
እየተቁለጨለጭኩ ተጠየቅኩት፡፡
ዝም ብሎ ሲያየኝ ቆየና...

“ለምን ጦስኝ ሻይ አታፈይልኝም?

ጠዋት የጠጣሁ ነኝ” አለኝ፣

መጽሐፉን እያነሳ..

“ለምን አትመልስልኝም...?

ለምንድነው
እንደዚህ ፍቅርን የምትፈራው?”

“በናትሽ ሻዩን... እያዛጋኝ ነው...”
የምናብ ደጁ ሊዘጋብኝ ነው። ለዛሬ
👍6011👏2😁1