#አሜሪካን_ጉዞ
#በሕይወት_እምሻው
እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ታዳጊ ፣ አሜሪካ ለመሄድ ሰ...ፍ ማለት
የጀመርኩት በልጅነቴ ለሚከተሉት ነገሮች በተከታታይ ተጋልጬ ስለነበር ነው።
1. 0ሥር ዓመት ሲሆነኝ የዕድሜ እኩያዬ ካሌብ ፣ “ባቡር መንገድ” ተሻግሮ ትልቅ ሕንጻ ከሚሠራበት ቦታ ፣ ትንሽ ስቶኮ ሰርቆና ደብቆ አመጣና ሁላችንንም ሰብስቦ ፣ “እዩ! የአሜሪካን ጭቃ!” አለን ከስንት ወረፋና ልመና በኋላ የአሜሪካ ጭቃውን፤ አስነካኝ ፡ :
ጣቶቹ በፍራሽ ላይ የሚዘሉ መሰለኝ ይደላል ይመቻል።
“የአሜሪካ ጭቃ ይሄ ነው?” አልኩት ፡ :
“አዎ... ዝናብ ሲዘንብ ጭቃቸው ይሄ ነው ... ደስ አይልም?” አh፤ : :
ሲቆይ የኔ እንዳይመስለኝ፤ ፈርቶ ነው መሰለኝ፤ ስቱኮው፣ እየነጠቀኝ ፡ :
''ጭቃው እንኳን እዲህ ያማር ሀገሩ ፣ ምንኛ ግሩም ነው?” ብዬ እያሰብኩና የሃገሬን ከአፈርና ውሃ የተሰራ ''ተራ" ጭቃ በእግሮቼ እያቦካሁ ወደ ቤቴ ዔድኩ ፡ :
2. በዐሥራ ሁለት ዓመቴ አብሮን የሚማረው የአጎኔ ልጅ ጋዲሳ ፣
አሜሪካ ለመሄድ “ፕሮሰስ”መጀመሩ እንደ ከባድ የሃገር ሚስጥር በእናቴ ፣ በእሱ እናት ፣ በአባቴና በእሱ አባት መካከል በሹክሹክታ ሲወራ ጓዳ ሆኜ ባጋጣሚ ሰማሁ : :
“ፕሮሰስ” ቃሏ ባትገባኝም ወሳኝ ነገር መሆኗ ገብቶኛ:
"ደሞ ለማንም እንዳታወሪ... ፕሮሰስ ለሰው ከተወራ ይበላሻል: : ” እናቴ
ናት ቀስ ብላ ያለችው : :
“አር እኔ ፤ ለማ፣ ምን፣ ብዬ አወራለሁ ...? በሚስጥር ያስጀመረችው
ድንግል በምስጢር ታሳካከት እንጂ...” የጋዲሳ እናት እትዬ ወላንሳ : :
“እናንተ፤ ናችሁ መቼም ወሬ አይጎዳም እያችሁ የምታዛመቱት! ዛሬ ሰው
ተንኮለኛ ነው ... አንድ ሰው አፍ ውስጥ ከገባ 'ለምን' ሆነለት ብሎ ለማፋርስ ሌተ ቀን የሚሰራ ብዙ ነው : : ዋ! ነገርኩ እንግዲህ! ይሄ ነገር ከዚች ቤት እንዳይወጣ!” አባቴ ነው : :
ሴቶቹን በቁጣ ሲያይ ኮሎኔል መንግስቱ መድረክ ላይ ቆመው ለሕዝብ ንግግር ሲያደርጉ እንደሚሆኑት ይሠራዋል : :
“ፕሮሰስ” ከባድ ነገር እንደሆነ የገባኝ ያኔ ነው : :
ከጥቂት ሳምንታት በኋካ ፤ እማዬ ፣ የእትዬ ወላንሳ የሴቶች ማኅበር
ድግስ ይዛኝ ሄደች : : ተጨማሪ ሰሃን አምጪ ተብዬ ኩሽና ገብቼ ስመለስና ያለ አቃሟ ትልልቅ ሶፈፋዎችና ሴቶች ይዛ የተጣበበችው ሳሎን በእልልታ በአንድ እግሯ ስትቆም አንድ ሆነ
“አቤት ድንግል ምን ይሳናታል? ድንግል ምን ይሳናታል!
“ ቸሩ መድኀኔአለም እኮ ይሰማል... እሱ ሰመሽ! ወላንሳዬ ፈጣሪ ሰማሽ!
በሚሉ ከዚህም ከዚያም በሚመጡ ዓረፍተ ነገሮች ታጅቦ ዕልልታው
ቀለጠ : :
“የጋዲሳ ፕሮሰስ ተሳካ!” ከሚለው የእትዬ ወላንሳና የእማዬ መረጃ የተሰጠ
ምላሽ ነበር : :
የልጅ የአሜሪካ “ፕሮሰስ” መጀመርና መሳካት ከእናት ፣ ከአክስት ፣ብሎም ለቀበሌው ሴቶች ሁኩ እንዲህ ያለ ደስታ እንዳመጣ ባየሁ ጊዜ ፤
“ወይኔ ይህቺ አሜሪካ ምን ዓይነት ግሩም ሀገር ናት? ያላያት ሁሉ ለሚያያት
ዕልል ለሚልባት ሀገር!” እያልኩና በትልቁ ተቆርሶ የተሰጠንን ድፎ ዳቦ እየገመጥኩ ወደ ቤት ተመለስን።
በሳምቱ ቡዔ ነበር : : የደራው ጭፈራ ግን እኛ ቤት ብቻ ነበር ተደጋግሞ የተሰማው ግጥም ደግሞ ይሄ
“እዛ ማዶ አንድ ጀሪካን ፣
እዚህ ማዶ አንድ ጀሪካን ፣
የኔማ ጋዲሳ ሊሄድ ነው አሜሪካን፣ : :
(በነገራኝ፣ ላይ ሀበሻ አሜሪካን ለምን፣ “አመሪካ” ብቻ ማለት እንደማይችል አይገባኝም : : “አሜሪካን ሀገር ለማለት ፣ “አሜሪካን ሀገር” እንላለ3 ፡ : ነው ወይስ እንዲህ ቡሄ ቡሄ ሲመጣ ስሟ ከጀሪካን ፣
ጋር ገጥሞ ሂያጅ ሀገር እየሰማ እንዲወደስባት ነው?
3. ጋዲሳ ወደ አሜሪካ የሚሔድበት ቀን ደረሰ : :
ቀኑ በብዙ ነገሮች የታጨቁ ቢሆንም በተለይ ትዝ የሚለኝ ግን የሚከተለው
ነው : :
ለወትሮው የት ገባህ? የት ወጣህ? የማይባለው ጋዲሳ ፤ለወትሮው ምን
በላህ? ምን፣ ጠጣህ? ተብሎ የማይጠየቀው ጋዲሳ ፤ ለወትሮው አስር
ጊዜ መታቀፍ ቀርቶ ፣ ዞር ተብሎ ታይቶ የማይታወቀው ጋዲሳ ፤ ልክ በድንገት እንደፀነሰች መሀን ሴት ፤ ልክ በምልጃና ምህላ እንደተገኙ የስለት ልጅ ፤ እንክብካቤ በዛበት ፡ :
“ጋዲሳ ሻወር አድርግ አሁን ፤ ... ሰዐት ደረሰ እኮ!” (ጉዞው ከምሽቱ አራት ተኩል ነው : : ይሄን የተባለውን ግን ከጠዋቱ አምስት ሰዐት ከሩብ ላይ : : )
“ጋዴ...! ለምን የዳግምን፣ ሰማያዊ ጃኬት አትወስደውም? ለብርዱ ይሆንሃል በዛ ላይ አዲስ ነው :የዛሬ ሁለት ዓመት ነው ፣ የቀኝ አዝማች ልጅ ትዕግስት ከእንግሊዝ የላከችለት... አንተ ዳግም! ዳግም!
ከጋዲ ያንን ጃኬት ስጠው!”
ዳግም እባ ቀረሽ ኩርፊያ አኩርፎ ፣ “እምቢ! ለምን እሱ አሜሪካ ሊሄድ ነው
... እኔ ምን አለኝ?” ሲል እናቴ ተቆጥታ ፣
“ያን የመሰለ ጃኬት አንተ የት ትለብሰዋለህ? እሱ ለብሶት ቢሄድ ምን አለበት? ብላው ፣ፍቃዱን ሳትጠይቅ ከቁምሳጥን አውጥታ ሰጠችበት ፡ :
“ጋዲሳ... የአውሮፕላን ምግብ ጥሩ አይደለም ሲሉ እሰማለሁ... እራትህን፣
በደንብ ብላ... ሰዐቱ እኮ ደረሰ!” ይህን የተባለው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዐት ተኩል
ላይ ነው : :
የጋዲሳ ዋጋ በአንድ ጊዜ እንዲህ ከፍ ሲል ቁጭ ብዬ አየሁ።
ጋዲሳ ተከበር : : ጋዲሳ ተወደደ: : አሜሪካ ስለሚሄድ ወርቅ እንቁላል
እንደምትጥል ዶሮ እንክብካቤ በዛበት : :
ወደ ዐሥር ሰዐት ገደማ ፣ ጋዲሳ እንደ ታቦት እየረገዱ ከከበቡት ሰዎች መሀል
ብድግ አለና ፣"በቃ እላይ ሰፈር ሄጄ እነቱቱን ቻው ልበላቸው"ሲል
“በቃ እላይ ሰፈር ሄጄ ራሴን ልግደል " ያለ ይመስል ሁሉም ሰው በአንድነት ክው አለ።
እትዬ ወላንሳ እየሮጠች አጠገቡ ሄደችና “አንተ ልጅ ምን ሆነሃል? መናገደኛ ሆነህ በዛሬ ቀን ከቤት ልትወጣ? ሊያውም ትንሽ ሰዐት ሲቀርህ? ” ስትከው ሁሉም ሰው ፤ “አዎ ... በዛሬ ቀን ባትቀዥቀዥ ጥሩ ነው! ”
“አርፈህ ተቀመጥ!”
“ሆ .…. አንድ ነገር ብትሆንስ? ” በማለት አገዟት ፡ :
ከፖሮሰሱ በፊት ጋዲሳ ከሰፈር ጅብ ጋር እየተጋፋ ሌሊት ስምንት ሰዐት ሲገባ አስታውሳለሁ : :
በቡድን የሰፈር ጠብ ውስጥ ፊታውራሪ ሆኖ በየቦታው እየተፈነካከተ ሲመጣ
ዕይቻhሁ : :
ጠጥቶ በየቱቦው ሲወድቅም ተመልክቻhሁ : :
ያኔ ፣ “አንድ ነገር እንዳትሆን.. ቶሎ ግባ... ተጠንቀቅ!” ያለው ሰው አልነበረም።
ነገሩ ገባኝ : :
ጋዲሳ በዛሬ ቀን እንዳይወጣ የተፈለገው ወጥቶ አንድ ነገር እንዳይሆን ወይ እንዳይሞት ሳይሆን ፤ አንድ ነገር ሆኖ ፣ ወይ ሞቶ ከአሜሪካ እንዳይቀር ነበር : :
ልድገመው : :
ጋዲሳ በዛሬ ቀን እንዳይወጣ የተፈለገው ወጥቶ አንድ ነገር እንዳይሆን ወይ እንዳይሞት ሳይሆን ፤ አንድ ነገር ሆኖ ፣ ወይ ሞቶ ከአሜሪካ እንዳይቀር ነበር : :
ስለዚህ የስንት ዘመን ባልንጀሮቹን እነ ቱቱን ሳይሰናበት ቀረ።
እንደ ዓመት በዓል ሲጠበቅ የነበረው የመሄጃ ሰአት ሲደርስና እቃው ሲመዘን ከሚፈቀደው በላይ ሆነ በሚል ትንሽ ግርግር ከተፈጠረ በኋካ ፣ ጎረቤታች፣ ጋሽ አስራት በሚነዳት ላዳ ታክሲ ወደ ቦሌ ለመሄድ ገባ ፡ ከመኪናዋ ውጪ በጠባቧ ግቢ ውስጥ የሚራኮተው ሰው ሁሉ ዐይን አርፎበታል : : ጋዲሳ ፣ በከፊል በተከፈተው የታክሲዎ የመስኮት መስታወት ሁሉንም እንባ ባቀረረ ዐይኖቹ ያያል : :
ይህን ጊዜ ነው የዲሳ ጓዝ ከመጠን በላይ እንደ ከበደ የገባኝ ፡፡ : ትከሻው ላይ የእናቱን ተስፋ ፣ የአክስቱን አደራ ፤ የእኛን 'ወጥተህ አውጣን” ምኞት
#በሕይወት_እምሻው
እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ታዳጊ ፣ አሜሪካ ለመሄድ ሰ...ፍ ማለት
የጀመርኩት በልጅነቴ ለሚከተሉት ነገሮች በተከታታይ ተጋልጬ ስለነበር ነው።
1. 0ሥር ዓመት ሲሆነኝ የዕድሜ እኩያዬ ካሌብ ፣ “ባቡር መንገድ” ተሻግሮ ትልቅ ሕንጻ ከሚሠራበት ቦታ ፣ ትንሽ ስቶኮ ሰርቆና ደብቆ አመጣና ሁላችንንም ሰብስቦ ፣ “እዩ! የአሜሪካን ጭቃ!” አለን ከስንት ወረፋና ልመና በኋላ የአሜሪካ ጭቃውን፤ አስነካኝ ፡ :
ጣቶቹ በፍራሽ ላይ የሚዘሉ መሰለኝ ይደላል ይመቻል።
“የአሜሪካ ጭቃ ይሄ ነው?” አልኩት ፡ :
“አዎ... ዝናብ ሲዘንብ ጭቃቸው ይሄ ነው ... ደስ አይልም?” አh፤ : :
ሲቆይ የኔ እንዳይመስለኝ፤ ፈርቶ ነው መሰለኝ፤ ስቱኮው፣ እየነጠቀኝ ፡ :
''ጭቃው እንኳን እዲህ ያማር ሀገሩ ፣ ምንኛ ግሩም ነው?” ብዬ እያሰብኩና የሃገሬን ከአፈርና ውሃ የተሰራ ''ተራ" ጭቃ በእግሮቼ እያቦካሁ ወደ ቤቴ ዔድኩ ፡ :
2. በዐሥራ ሁለት ዓመቴ አብሮን የሚማረው የአጎኔ ልጅ ጋዲሳ ፣
አሜሪካ ለመሄድ “ፕሮሰስ”መጀመሩ እንደ ከባድ የሃገር ሚስጥር በእናቴ ፣ በእሱ እናት ፣ በአባቴና በእሱ አባት መካከል በሹክሹክታ ሲወራ ጓዳ ሆኜ ባጋጣሚ ሰማሁ : :
“ፕሮሰስ” ቃሏ ባትገባኝም ወሳኝ ነገር መሆኗ ገብቶኛ:
"ደሞ ለማንም እንዳታወሪ... ፕሮሰስ ለሰው ከተወራ ይበላሻል: : ” እናቴ
ናት ቀስ ብላ ያለችው : :
“አር እኔ ፤ ለማ፣ ምን፣ ብዬ አወራለሁ ...? በሚስጥር ያስጀመረችው
ድንግል በምስጢር ታሳካከት እንጂ...” የጋዲሳ እናት እትዬ ወላንሳ : :
“እናንተ፤ ናችሁ መቼም ወሬ አይጎዳም እያችሁ የምታዛመቱት! ዛሬ ሰው
ተንኮለኛ ነው ... አንድ ሰው አፍ ውስጥ ከገባ 'ለምን' ሆነለት ብሎ ለማፋርስ ሌተ ቀን የሚሰራ ብዙ ነው : : ዋ! ነገርኩ እንግዲህ! ይሄ ነገር ከዚች ቤት እንዳይወጣ!” አባቴ ነው : :
ሴቶቹን በቁጣ ሲያይ ኮሎኔል መንግስቱ መድረክ ላይ ቆመው ለሕዝብ ንግግር ሲያደርጉ እንደሚሆኑት ይሠራዋል : :
“ፕሮሰስ” ከባድ ነገር እንደሆነ የገባኝ ያኔ ነው : :
ከጥቂት ሳምንታት በኋካ ፤ እማዬ ፣ የእትዬ ወላንሳ የሴቶች ማኅበር
ድግስ ይዛኝ ሄደች : : ተጨማሪ ሰሃን አምጪ ተብዬ ኩሽና ገብቼ ስመለስና ያለ አቃሟ ትልልቅ ሶፈፋዎችና ሴቶች ይዛ የተጣበበችው ሳሎን በእልልታ በአንድ እግሯ ስትቆም አንድ ሆነ
“አቤት ድንግል ምን ይሳናታል? ድንግል ምን ይሳናታል!
“ ቸሩ መድኀኔአለም እኮ ይሰማል... እሱ ሰመሽ! ወላንሳዬ ፈጣሪ ሰማሽ!
በሚሉ ከዚህም ከዚያም በሚመጡ ዓረፍተ ነገሮች ታጅቦ ዕልልታው
ቀለጠ : :
“የጋዲሳ ፕሮሰስ ተሳካ!” ከሚለው የእትዬ ወላንሳና የእማዬ መረጃ የተሰጠ
ምላሽ ነበር : :
የልጅ የአሜሪካ “ፕሮሰስ” መጀመርና መሳካት ከእናት ፣ ከአክስት ፣ብሎም ለቀበሌው ሴቶች ሁኩ እንዲህ ያለ ደስታ እንዳመጣ ባየሁ ጊዜ ፤
“ወይኔ ይህቺ አሜሪካ ምን ዓይነት ግሩም ሀገር ናት? ያላያት ሁሉ ለሚያያት
ዕልል ለሚልባት ሀገር!” እያልኩና በትልቁ ተቆርሶ የተሰጠንን ድፎ ዳቦ እየገመጥኩ ወደ ቤት ተመለስን።
በሳምቱ ቡዔ ነበር : : የደራው ጭፈራ ግን እኛ ቤት ብቻ ነበር ተደጋግሞ የተሰማው ግጥም ደግሞ ይሄ
“እዛ ማዶ አንድ ጀሪካን ፣
እዚህ ማዶ አንድ ጀሪካን ፣
የኔማ ጋዲሳ ሊሄድ ነው አሜሪካን፣ : :
(በነገራኝ፣ ላይ ሀበሻ አሜሪካን ለምን፣ “አመሪካ” ብቻ ማለት እንደማይችል አይገባኝም : : “አሜሪካን ሀገር ለማለት ፣ “አሜሪካን ሀገር” እንላለ3 ፡ : ነው ወይስ እንዲህ ቡሄ ቡሄ ሲመጣ ስሟ ከጀሪካን ፣
ጋር ገጥሞ ሂያጅ ሀገር እየሰማ እንዲወደስባት ነው?
3. ጋዲሳ ወደ አሜሪካ የሚሔድበት ቀን ደረሰ : :
ቀኑ በብዙ ነገሮች የታጨቁ ቢሆንም በተለይ ትዝ የሚለኝ ግን የሚከተለው
ነው : :
ለወትሮው የት ገባህ? የት ወጣህ? የማይባለው ጋዲሳ ፤ለወትሮው ምን
በላህ? ምን፣ ጠጣህ? ተብሎ የማይጠየቀው ጋዲሳ ፤ ለወትሮው አስር
ጊዜ መታቀፍ ቀርቶ ፣ ዞር ተብሎ ታይቶ የማይታወቀው ጋዲሳ ፤ ልክ በድንገት እንደፀነሰች መሀን ሴት ፤ ልክ በምልጃና ምህላ እንደተገኙ የስለት ልጅ ፤ እንክብካቤ በዛበት ፡ :
“ጋዲሳ ሻወር አድርግ አሁን ፤ ... ሰዐት ደረሰ እኮ!” (ጉዞው ከምሽቱ አራት ተኩል ነው : : ይሄን የተባለውን ግን ከጠዋቱ አምስት ሰዐት ከሩብ ላይ : : )
“ጋዴ...! ለምን የዳግምን፣ ሰማያዊ ጃኬት አትወስደውም? ለብርዱ ይሆንሃል በዛ ላይ አዲስ ነው :የዛሬ ሁለት ዓመት ነው ፣ የቀኝ አዝማች ልጅ ትዕግስት ከእንግሊዝ የላከችለት... አንተ ዳግም! ዳግም!
ከጋዲ ያንን ጃኬት ስጠው!”
ዳግም እባ ቀረሽ ኩርፊያ አኩርፎ ፣ “እምቢ! ለምን እሱ አሜሪካ ሊሄድ ነው
... እኔ ምን አለኝ?” ሲል እናቴ ተቆጥታ ፣
“ያን የመሰለ ጃኬት አንተ የት ትለብሰዋለህ? እሱ ለብሶት ቢሄድ ምን አለበት? ብላው ፣ፍቃዱን ሳትጠይቅ ከቁምሳጥን አውጥታ ሰጠችበት ፡ :
“ጋዲሳ... የአውሮፕላን ምግብ ጥሩ አይደለም ሲሉ እሰማለሁ... እራትህን፣
በደንብ ብላ... ሰዐቱ እኮ ደረሰ!” ይህን የተባለው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዐት ተኩል
ላይ ነው : :
የጋዲሳ ዋጋ በአንድ ጊዜ እንዲህ ከፍ ሲል ቁጭ ብዬ አየሁ።
ጋዲሳ ተከበር : : ጋዲሳ ተወደደ: : አሜሪካ ስለሚሄድ ወርቅ እንቁላል
እንደምትጥል ዶሮ እንክብካቤ በዛበት : :
ወደ ዐሥር ሰዐት ገደማ ፣ ጋዲሳ እንደ ታቦት እየረገዱ ከከበቡት ሰዎች መሀል
ብድግ አለና ፣"በቃ እላይ ሰፈር ሄጄ እነቱቱን ቻው ልበላቸው"ሲል
“በቃ እላይ ሰፈር ሄጄ ራሴን ልግደል " ያለ ይመስል ሁሉም ሰው በአንድነት ክው አለ።
እትዬ ወላንሳ እየሮጠች አጠገቡ ሄደችና “አንተ ልጅ ምን ሆነሃል? መናገደኛ ሆነህ በዛሬ ቀን ከቤት ልትወጣ? ሊያውም ትንሽ ሰዐት ሲቀርህ? ” ስትከው ሁሉም ሰው ፤ “አዎ ... በዛሬ ቀን ባትቀዥቀዥ ጥሩ ነው! ”
“አርፈህ ተቀመጥ!”
“ሆ .…. አንድ ነገር ብትሆንስ? ” በማለት አገዟት ፡ :
ከፖሮሰሱ በፊት ጋዲሳ ከሰፈር ጅብ ጋር እየተጋፋ ሌሊት ስምንት ሰዐት ሲገባ አስታውሳለሁ : :
በቡድን የሰፈር ጠብ ውስጥ ፊታውራሪ ሆኖ በየቦታው እየተፈነካከተ ሲመጣ
ዕይቻhሁ : :
ጠጥቶ በየቱቦው ሲወድቅም ተመልክቻhሁ : :
ያኔ ፣ “አንድ ነገር እንዳትሆን.. ቶሎ ግባ... ተጠንቀቅ!” ያለው ሰው አልነበረም።
ነገሩ ገባኝ : :
ጋዲሳ በዛሬ ቀን እንዳይወጣ የተፈለገው ወጥቶ አንድ ነገር እንዳይሆን ወይ እንዳይሞት ሳይሆን ፤ አንድ ነገር ሆኖ ፣ ወይ ሞቶ ከአሜሪካ እንዳይቀር ነበር : :
ልድገመው : :
ጋዲሳ በዛሬ ቀን እንዳይወጣ የተፈለገው ወጥቶ አንድ ነገር እንዳይሆን ወይ እንዳይሞት ሳይሆን ፤ አንድ ነገር ሆኖ ፣ ወይ ሞቶ ከአሜሪካ እንዳይቀር ነበር : :
ስለዚህ የስንት ዘመን ባልንጀሮቹን እነ ቱቱን ሳይሰናበት ቀረ።
እንደ ዓመት በዓል ሲጠበቅ የነበረው የመሄጃ ሰአት ሲደርስና እቃው ሲመዘን ከሚፈቀደው በላይ ሆነ በሚል ትንሽ ግርግር ከተፈጠረ በኋካ ፣ ጎረቤታች፣ ጋሽ አስራት በሚነዳት ላዳ ታክሲ ወደ ቦሌ ለመሄድ ገባ ፡ ከመኪናዋ ውጪ በጠባቧ ግቢ ውስጥ የሚራኮተው ሰው ሁሉ ዐይን አርፎበታል : : ጋዲሳ ፣ በከፊል በተከፈተው የታክሲዎ የመስኮት መስታወት ሁሉንም እንባ ባቀረረ ዐይኖቹ ያያል : :
ይህን ጊዜ ነው የዲሳ ጓዝ ከመጠን በላይ እንደ ከበደ የገባኝ ፡፡ : ትከሻው ላይ የእናቱን ተስፋ ፣ የአክስቱን አደራ ፤ የእኛን 'ወጥተህ አውጣን” ምኞት
👍1