አትሮኖስ
279K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
456 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ታአምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_ሀያ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

‹‹ሁሉም ወደኋላ ግልምጥ እያሉ ከፊት ለፊታቸው ሊመጣ ያለውም እንዳያመልጣቸው እየፈሩ..ይመልሱለት ጀመር‹‹አይ የሆነ የተለየ ፍጡር አይተን ነው››
‹‹ኑ ባካችሁ ነገ ይደርሳል…አንተ ደግሞ አዲሷ ጓደኛህ እኮ ዱንኳንህ አጠገብ ተቀምጣ እየጠበቀችህ ነው››አለው ወደአንድሪው እየተመለከተ፡፡

‹‹የማ የእኔ…ኬድሮን ነች?››

‹‹ስሟን መች ለኔ  ነገረችኝ...ባለንስሯ አፍሪካዊት ልጅ››ሲለው እስከአሁን ከተገረመባት በላይ ይበልጥ እየተገረመና እንደጅል ካሜራውን ደቅኖ በዚህ ሲጠብቃት ቤት ዞር ከጀርባው እንደተገኝች በመደነቅ ካሜራውን እንዳንጠለጠለ ሁሉንም ባሉበት ጥሎ እየሮጠ ወደካንፑ ተመለሰ …ጓደኞቹም በሁኔታው ግራ ተጋብተው እየተሳሳቁና እየተገረሙ በዝግታ እርምጃ ተከተሉት፡፡
߷߷
እንደደረሰ ከጎኗ ዝርፍጥ ብሎ ተቀመጠና ካሜራውን እግሩ ስር አስቀምጦ ዝም ብሎ አቀርቅሮ ማለክለክ ጀመረ
‹‹ከሜራ ደቅነህ የምትጠብቀኝ ቀረጸህ ለአለም ልታሰራጭ ነበር አይደል?››

‹‹እና ገብቶሽ ነው የሸወድሺኝ?››

‹‹አይመስልህም?››

‹‹አዎ ትክክል ነሽ..ግን እንድታውቂው የምፈለገው ፈርቼሻለሁም ወድጄሻለሁም››

‹‹አውቃለሁ›› አለችው፡፡

ሁሉም ተሰበሰበ፣ አካባቢው እየጨለመ መጣ.. ያላቸውን ፋኖስ ለኮሱና የተሰራውን እራት እየበሉ ሁሉም የጋራ የሆነ ጫወታ ሲጫወቱ ቆዩና አራት ሰዓት አካባቢ ሁሉም በእንቅልፍ እየተሸነፈ ተራ በተራ ወደ ድንኳኑ ገባ… 
አንድሪውና ኬድሮን እና ንስሯ ብቻ ቀሩ፡፡ሰማይ ላይ በቅርብ ባለ ኮርኒስ ላይ የተንጠለጠለች የምትመስለው ጨረቃ ብቻ ሳትሆን በዙሪያዋ በተን በተን የተደረጉ የሚመስሉ ልብ ሰንጣቂ ውበት ያላቸው ከዋክብትን  አንጋጠው እየተመለከቱ በራሳቸው ሀሳብ ቁዘማ ውስጥ ገቡ…፡፡

‹‹አሁን ድንኳን ውስጥ ገብተሸ ተኚ.››

‹‹አንተስ…?›

‹‹ችግር የለውም ካንድ ጓደኛዬ ጋር እዳበላለሁ››

‹‹አይ ችግር የለም…እኔ ካልፈለኩ ማንም ወንድ ሊደፍረኝ አይችልም…አብረን ገብተን እንተኛ፡፡››

‹‹እርግጠኛ ነሽ?››

‹‹በንስሬ  ሙሉ እምነት አለኝ….ጀግናዬ አብረኸን ወደ  ድንኳን ትገባለህ ወይስ የተሻለ ማደሪያ ትፈልጋለህ?››ስትል ወደንስሯ ዞራ ጠየቀችው፡፡

በተተተት ብሎ ካለበት ተነሳና በጨለማ ውስጥ ሰንጥቆ በረረ..

‹‹ሄደብሽ እኮ››› አላት አንድሪው 
‹‹ይሂድ.. ሊያጣብበን ስላልፈለገ ነው…ና ተነስ እንግባ›› ብላ አንድ እጁን ይዛ እየጎተተች ልክ እንደራሷ ድንኳን ይዛው ገባች…..እጁን  በያዘችበት እጇ ከእሱ የሚነሳ የኤሌክትሪክ ሞገድ ወደውስጧ ሲፈስ በደንብ እየታወቃት ነው…የተነጠፈችው ፍራሽ ከአንድ ሜትር የማትበልጥ በመሆኗ ተጣብቆ ከመተኛት ውጭ ሌላ ምርጫ አልነበራቸውም…..እሷ ደግሞ  ሲፈርድባት ከእናቷ እና ከንስሯ ውጭ ከሌላ ሰው ጋር የመተኛት ምንም አይነት አጋጣሚ ኖሯት አያውቅም፡፡በተለይ ከወንድ ጋር ይሄ የመጀመሪያ ቀን ገጠመኞ ነው፡፡

ስለዚህ ወዲያው ነበር መፍራት ብቻ ሳይሆን መንቀጥቀጥ የጀመረችው፡፡

‹‹ታውቃለህ አይደለህ እሺ ብዬህ ድንኳን ውስጥ መግባት አልነበረብኝም›› አለችው በሚርበተበት ድምፅ..፡፡

‹‹ለምን ?ምን አጠፋሁ?›አላት ግራ በመጋት፡፡

‹‹አይ አንተ ምንም አላጠፋህ እኔ ግን…?››

‹‹አንቺ ምን?››

‹‹ድንግል ነኝ…እርግጥ በእናንተ ባህል ለድንግልና የምትሰጡት ግምትና በእኛ የተለየ ነው፡፡››

‹‹አውቃለሁ…ኢትዬጵያን በአካል ሄጄ ጎብኝቻታለሁ ስልሽ እኮ ልክ እንደአንድ ጎብኚ መልከ ምድሯንና የመስህብ ቦታዎቾን ብቻ ጎብኝቼ ነው የተመለስኩት እያልኩሽ አይደለም…እዛ ለሶስት ወር ነው የቆየሁት ፤በሞያዬ አንትሮፖሎጂስት ነኝ …ለሶስተኛ ዲግሪዬን ማሞያ ጥናቴን ለመስራት ነበር የሄድኩት …በዛም ምክንያት የሀገራችሁን ባህሏንና ታሪኮን በተቻለኝ መጠን ለማጥናትና ለማወቅ እድሉን አግኝቼለሁ.. በዛም የተነሳ የባህል ልዩነቱንም በደንብ እረዳለሁ፡፡››

የድንኳኑ ጣሪያ ላይ ሰክታ የነበረውን አይኖቾን አነሳችና  ከአንገቷ ወደእሱ ዞረች… በተመሰሳይ ሰዓት እሱም ወደእሷ ሲያዞር አፍንጫቸው ቀድሞ ተሳሳመ፡፡ ከእሱ አንደበት የሚወጣው ትንፋሽ ወደእሷ ሲስርግና ከእሷም ወደእሱ ሲመለስ ትንፋሽ ብቻ ሳይሆን ሉጋሙን የሳተ የወሲብ እሳት ነበር ከአንደኛው ወደሌላው እየተላለፈ የነበረው.. ፡፡በጠቅላላ አካለቸው በመሰራጨት ያነዳቸው ጀመረ….አንድሪው በዚህ ጉዳይ ለአመታት የበሰለና የጠነከረ ልምድ አለው….የብዙ ሀገር ዜግነት ያላቸውን ጥቁርም ፈረንጅ፤አረብም ከየአይነቱ በተለያየ ጊዜ በተለያ ሁኔታና መጠን ፍቅርን ተጋርቷል…በፍቅር ወድቋል በፍቅርም ጥሎ ያውቃል…በዚህ የተነሳ እራሱን ልክ እንደኤክስፐርት ነበር የሚቆጥረው…ማረጋገጫ ዲፕሎማ እጁ ላይ ባይኖረውም እንደሁለተኛ ሞያው ነው የሚቆጥረው…….ዛሬ ግን ከጎኑ ያለችው እንግዳና ተአምራዊ ልጅ ‹‹እኔ ልምድ የለኝም ድንግል ነኝ;›› ብላ እየነገረችው..ውስጡ የሚያምነው ግን ተቃራኒውን ነው፡፡
እሱ ራሱ ልምድ አልባ እንደሆነ እና ለመጀመሪያ ጊዜ ጥልቀት ያለው የፍርሀት  ስሜት እየተሰማው እንደሆነ.... አሁን በሚሰማው ልክ የሚያቃትት የወሲብ ረሀብ ፍፅም ተሰምቶት እንደማያውቅ እርግጠኛ ነው ፡፡እስከመቼ ታግሶ መቆየት እንደሚችል እርግጠኛ አይደለም…ፍቃደኛ ካልሆነችለት ደግሞ በግድ ጉልበት ተጠቅሞ ሊሞክር አይችልም….እንደህ አይነት ድርጊት በህይወቱ በጣም የሚጠየፈው ከመሆኑም በተጨማሪ  ልጅቷም ለዛ አይነት ጥቃት ሽብርክ  የምትል እንዳልሆነች አፍ አውጥታ ነግራዋለች እና አምኗትል….ግን ደግሞ ረሀቡ ልክ የመተንፈስ ችግር እንዳለበት ሰው  አሁን እሱ ባለበት ከፍታ ላይ ሲገኝ ኦክስጅን አንሶት መሬት ወድቆ እንደሚንፈራፈርና ምን አልባትም እስከ ወዲያኛው ሊዘጋና ሊሞት እንደሚችል እሱም እንደዛ አይነት አደጋ በራሱ ላይ  እንደሚደርስበት አይነት ስሜት ነው እየተሰማው ያለው…ስለአፍሪካ ጠንቋዬች የተወሰነ ታሪክ አንብቧል….‹‹ዋናዋን ጠንቋይ ይሆን እንዴ በአካል ያገኘኋት …?.ቀልቧን አሳርፋብኝ እያደነዘቺኝ  ይሆን እንዴ?››ይሄን ሁሉ ጥያቄ በውስጡ የሚያጉላላው አይኖቹን አይኖቾ ላይ አፍጥጦ..አፍንጫውን ከአፍንጫዋ አጣብቆ ..ከንፈሮቹ እየተንቀጠቀጡ ነው፡፡
እጆቹን በጀርባዋ አሻግሮ ሊያቅፋትና ከንፈሩን ከንፈሮቾ ላይ ሊያጣብቅ በጣም ፈልጓል፤ ቀሚሷን ወደላይ ገልቦ ወይም ከስር ወደላይ ተርትሮ ቀዶ በመጣል መላ ሰውነቷን በግልፅ ማየት ፈልጎል  ፡፡እሱም የለበሰውን ልብስ ብቻ ሳይሆን ከተቻለ ቆዳውንም አውልቆ በመጣል ነፍሱን ከነፍሷ ማዋሀድና ማዋሰብ ነው የፈለገው….. ‹‹ነፍስ ከነፍስ ይዋሰባል እንዴ ?…በራሱ ምኞት ተገረመ ፡፡
የሚገርመው በእሷም በኩል ያለው ስሜት ተመሳሳይ ነበር….የሚለየው ግን እሷ እታች ብልቷ አካባቢ ባለው ጭኖቾ መካከል የሆነ የሚርመሰመስ ነገር እንደገባባት እየተሰማት ነው፡፡የሚረብሽ የጉንዳን አይነት..ቆንጠጥ ..አከክ .ቦጨቅ የሚያደርግ….እግሮቾን በዘዴ እርስ በርስ ለማፋተግና ከሚበላት ነገር ለመገላገል ሙከራ ብታደርግም ከመባሳጨት ውጭ ምንም የተቀየረ ነገር የለም…..በዚህ ሰዓት ማድረግ የምትፈልገው ብቸኛ ነገር ቢኖር ቀጥታ እጇን ወደታች ሰዳ ቀሚሷን ገልባ  ፓንቷን ወደታች መንቅራ ጥላ አካባቢው እስኪቆስል ማከክ..አዎ ከዛም አልፎ እጣቷን ብልቷ ስንጥቅ ውስጥ ከታ የሚበላት ነገር አደብ እስኪገዛና እዛ ስፍራ የሚነተከተከው ነገር እስኪበርድላት ድረስ ማማሰል አዋ ያን ማድረግ ነው
👍97😁65🥰4
#ታአምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
""
‹‹ነገርኩሽ እኮ… ዛሬ እሮብ ነው አይደል እስከቅዳሜ አልጋሽን ለቀሽ ያልደረሻቸውን ለቅሶዋችና የታመሙ ወዳጆችሽን እየዞርሽ ትጠይቂያለሽ…››

‹‹እንደአፍሽ ያድርገው››

‹‹እማ እኔ እንዲህ በቁም ነገር ተናግሬ ያልሆነ ነገር አለ…ደግሞ ጀግናዬ ነው መልዕክቱን የነገረኝ…ምን አልባት መድሀኒቱን አባቴ ማለቴ  የድሮ ፍቅረኛሽ ይሆናል በሚስጥራዊ መንገድ  በእሱ በኩል የላከልሽ››

እናትዬዋ በንግግሯ ባለመደሰት ኮስተር ብላ‹‹አባትሽ የድሮ ፍቅረኛዬ ሳይሆን ….የዘላለም ፍቅረኛዬ ነው።››አለቻት፡፡

"እሺ ይሁንልሽ…አሁን ቻው ያዶት ልንሄድ  ነው…ደስ ስላለኝ በዚህ በጥዋት ሂጄ መዋኘት እፈልጋለሁ።››

‹‹እንዴ ቁርስ አፍሽ ላይ ጣል ሳታደርጊ?››

‹‹አይ ስመለስ››ብላ ንስሯን እንዳቀፈች ከቤት ወጣችና ግቢውንም ለቃ ወደ ያዶት ወንዝ ጉዞዋን ቀጠለች፡፡

‹‹ጀግናዬ ስላደረጋችሁት ነገር በጣም አመስግናለሁ...ማለት አንተና አባቴ….ቃል በገባሁት መሰረት የዘላለም ውለታችሁ አለብኝ...ግን እናቴ ከአመት በኃላ ቀጣይ ዕድሜ እንዲኖራትስ ምንድነው ማድረግ ያለብኝ…? መቼስ ከባድ ነገር ነው የሚጠበቅብኝ?››

‹‹አይ ቀላል ነው››

‹‹ቀላል ነው ስትል? 

‹ከእናትሽ ጋር መኖር ማቆምሽ ለእሷ ተጨማሪ ዕድሜ ይሰጣታል፡፡

አንቺ ከተፈጥሮሽ የተነሳ ፍቅርሽ እሷን ለመኖር ያላትን ኃይል ይመጣል….አንቺ ስትወጂም ሆነ ስትጠይ እኩል ነው ሰውን ምትጎጂው….በፍቅርም ሆነ በጥላቻ የተለየ ትኩረት ያሳረፍሽበት ማንኛውንም የሰው ልጅ ኃይሉን ነው ምትመጪበት… ያ ኃይል ደግሞ ከዕድሜው ላይ ይጎመዳል..ምን አልባት እናትሽ አንድ ቀን ከአንቺ ጋር ለማሳለፍ ከእድሜዋ ላይ ሀያ ሰላሳ ቀን መገበር ይጠበቅባት ይሆናል…"
የምትሰማውን ዜና ተቋቁማ ወደፊት መቀጠል አልቻለችም …ከመንገድ ጎራ ብላ ቁጥቋጦ ውስጥ ገባችና የተደላደለ ቦታ ፈልጋ ተቀመጠች… ንስሯን ከፊት ለፊቷ አስቀመጠችው…. ከንፈር የማይንቀሳቀስበት ፤አፍ ማይከፈትበት ድምፅ አልባ ንግግሩን ቀጠለ…‹‹.እና አሁን ከእናቴ አልለይም የሆነው ይሁን የምትይ ከሆነ አንድ አመቱን ከእሷ ጋር አሪፍ የምትይውን የደስታ ጊዜ አሳልፊ…አይ እናቴ አርባ ሀምሳ አመት መኖር አለባት የምትይ ከሆነ ግን ዛሬ ነገ ሳትይ ይሄን ሀገር ለቀን መሄድ አለብን፡፡››

‹‹ግን እናቴን ምን እላታለሁ?››
‹‹እውነቱን ንገሪያት..እርግጥ አትስማማም…ግን ቢሆንም ንገሪያትና አንቺ ውሳኔውን ወስኚ።››

‹‹ቆይ ብዋሻትስ?››

‹‹ምን ብለሽ?››

‹‹ለምሳሌ እኔ አብሬአት መኖር ምቀጥል ከሆነ በሽታው ወደእኔ ተላልፎ በጥቂት ቀናት ውስጥ እንደምሞት እንዳወቅኩ ብነግራት የእኔን መሞት ማሰብም ስለማትፈልግ በፍጥነት የምትስማማ ይመስለኛል›"
ላቀረበችው ሀሳብ ከአእምሮው የድጋፍ ወይም የተቃውሞ መልስ ለማንበብ ስትጠብቅ….እሱ በተለየ ብርሀን የደመቁ አይነት ቀለማትን ረጨ.እንዲህ የሚያደረገው በነገሮች ሲደነቅ ወይም ሲደሰት እንደሆነ ታውቃለች፡፡

‹‹ምነው የማይረባ ሀሳብ ነው እንዴ?››

‹‹አረ አባትሽም እንዲህ  አይነት ሸር በዚህ ፍጥነት ማሰብ መቻሉን ስለተጠራጠርኩ አድንቄሽ ነው..››

‹ዲቃላ መሆን ጥቅሙ እኮ ይሄ ነው…ግን አሁን የት ነው የምንሄደው ..ማለቴ የት ሀገር ብንኖር ይሻላል?፡፡››

‹‹ደስ ያለሽ ቦታ..ደስ ያለሽ ሀገር››

‹‹ምን ሰርተን ነው የምንኖረው…ትምህርቴን ገና የ10 ክፍል ማትሪክ እንኳን አልተፈተንኩ..ከብት ከማርባት እና እትክልቶችን ከመንከባከብ ውጭ ምንም ሌላ ማውቀው ሞያ የለኝም››

‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ አንቺ እኮ ማንኛውንም ሞያ ለመልመድ ከሌላው የሰው ልጅ በመቶ እጥፍ በላይ አቅም ነው ያለሽ....በዛ ላይ ታንዛኒያ የሄድን ጊዜ ኬኒያ ድንበር ያገኘነውን ዳይመንድ አለን....በጣም ሀብታም ነሽ እኮ››

‹‹ማለት አባቴ የሌላ አለም ፍጡር ስለሆነ?››

‹‹አዎ ለሰው ልጆች ጥበብ እና እውቀትን ያስተማሩት እኮ አባትሽ እና ከእሱ ጋር ከገነት የወደቁት ጭምር ናቸው››

‹‹ይሄ ነገር እውነት ነው ማለት ነው?››

"አዎ..በከፊል እውነት ነው››
‹‹በከፊል ስትል.ከፊሉስ እውነት?››

‹እሱን ሌላ ጊዜ..እንድነግርሽ ሲፈቀድልኝ?››

‹‹እንዳልክ …ግን የአባቴ ዘመዶች ለሰው ልጆች ያሰተማሯቸው ዕውቀትንና ጥበብን ብቻ ነው …?››

‹‹አይ እሱማ ክፋትና ተንኮልን…ግድያንና ዘረፋንም ጭምር አስተምረዋል፡፤››

‹‹እና የሰው ልጅ ባለውለታ ናቸው ነው የሚባለው ወይስ ጠላት?››

‹‹አይ እኔ ምለው ማንም ቢሆን ማንኛውንም ጥሩ ነገር ለማግኘት መክፈል ሚገባው ክፍያ አለ…አባትሽና ወገኖቹ ለሰው ልጆች ያበረከቱት ጥሩ ጥሩ ነገሮች እንዳሉ ሁሉ ከሰው ልጆችም የነጠቁት መልካምነቶች አሉ››

‹‹ሳስበው ሳስበው የሰው ልጅ ግን ውለታ ቢስ እኮ ነው፡፡

በየቤተክርስቲያኑም ሆነ መስጊዱ ምሰማው የክፋት ሁሉ ምንጭ ሰይጣን እንደሆነ ጥበብና እውቀትን ደግሞ እግዚያብሄር እንዳስተማራቸው  ነው የሚያወሩት››
መልስ ብትጠብቅም ምንም አልመለሰላትም. እዕምሮዋን ዘጋባት

‹‹ምነው? አንተም እግዚያብሄርን ትፈራዋለህ እንዴ?›

አሁንም የተቀየረ ነገር የለም..ለንግግሯ ምንም አይነት አስተያየት ለመስጠት እምሮውን እንደቆለፈ በዛው ገፋበት…ተደነቀች፡፡

‹‹የኃያላን  ኃያል ፤ የጌቶች ሁሉ ጌታ እሱ እግዚያብሄር ነው..የሚል ስብከት መስማቷን አስታወሰችና መልሳ በልቧ አኖረችው…
ሄዶ ሄዶ የሁሉ  ነገር ማሰሪያና የኃይሎች ሁሉ ጥቅል ኃይል እግዚያብሄር ከሆነ ታዲያ የእነ አባቴ ቀድሞ መንፈራገጥ ለምን ይሆን ?ብላ እራሷን ጠየቀችና  ..መልሳ ሌላውን ጥያቄ ተወችና 
‹‹ በል ተነስ እንሂድ.. ወደየት ሀገር እንደምንሄድ አስብበት.››ብላ መንገዷን ስትቀጥል እሱ ክንፍን አማቶና በአየር ላይ ተርገፍግፎ እሷን በመተው በተቃራኒው ወደ ደኑ ውስጥ ገባ..‹‹እርቧሀል ማለት ነው ?››ብላ እሷ ለመዋኘት ወደ ያዶት ወንዝ ጉዞዋን ቀጠለች፡፡

ይቀጥላል
👍12712👎4🥰3👏3