አትሮኖስ
282K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
489 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


  ተገለበጣና   ፊቱን ወደእሷ አዞረ…‹ከደፈረኝ በኃላ እዚሁ ሲጥ አድርጎ በጨረሰኝ››ስትል ተመኘች…

እሱ ግን ማውራት ጀመረ‹‹ስሜ አይያዝልሽም አይደል…እረስተሸው ከሆነ ዛሬም መልሼ ላስታውሽ፣፣ ቀናው ይመር እባላለሁ፡፡ይገርምሻል ብዙውን ጊዜ ስምህን እረሳሁት ብለሽ ደጋግመሽ ስትጠይቂኝ በደስታ ነው የምነግርሽ..እና ሁሌ ባገኘሁሽ ቁጥር ስሜ ጠፍቶባት ብትጠይቀኝ እያልኩ አመኛለሁ…ያው ምን አልባት ካንቺ ጋ ማውራት የተለየ ስሜት ይፈጥርብኛል መሰለኝ…..ሰባ አሁን ያለሽበትን ሁኔታ በጣም እረዳዋለሁ፡፡ እንዴት አድርጌ እንደማግዝሽ ግን ስለማላውቅ ነው ዝም ብዬ ማይሽ...ምክንያቱም እኔም እንደአንቺ ቁስለኛ..እኔም እንደአንቺ በሽተኛ ነኝ፡፡እኔ የወሎ ልጅ ነኝ…ቤተሰቦቼ  ገጠር  ኑዋሪ  ገበሬዎች  ናቸው፡፡ሀይስኩል  ደሴ  ወ.ሮ ሰህን ነበር የተማርኩት፡፡ ከ9 ዓመት በፊት ነው ማትርክ  የወሰድኩት  ፡፡በወቅቱ እንደ ኢትዬጵያ ትልቁ ውጤት  የእኔ  ነበር….ወዲያው  እስኮላር  አገኘሁና ወደአሜሪካ ወጣሁ፡፡በቃ በዛን ጊዜ የነበረኝ ደስታ…በውስጤ  የተፈጠረው ፈንጠዝያ አለምን በእጄ የጨበጥኩ  ነበር  የመሰኝ..ከአንዲት  መንደር  ተነስቼ የልዕለ    ሀያሎ    አሜሪካ     ሜትሮፖሊቲያን     ዩኒቨርሲቲ     ኦፍ     ዴንቨር ተማሪ ስሆን…ይህቺን ደሀ  ሀገር  ተመልሼ  እንደምመራና  ልዕለኃያል  ኃያል ላደርጋት ባልችል እንኳን ኃያል  እንደማደርጋት  እየፎከርኩ  ወጣሁ…እዚህ  ላይ አንድ አዛውንት የተናገሩትን ልጥቀስልሽ.. ወጣት ሳለሁ እኔ አስብና

እግዚያብሄርን በፀሎት ጠይቅ የነበረው ..እግዚያብሄር ሆይ አለምን ጠቅላላ የምቀይርበትና    ምስቅልቅሏን    የማስተካክልበት    ኃይል     ስጠኝ     "ብዬ ነበር።ትንሽ በሰል ስል ደግሞ "ጌታ ሆይ አለምን መቀየር በጣም ከባድና ለእኔ አቅም የሚሰፋ ዕቅድ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።እስከአሁን አንድ ነጠላ ሰው እንኳን ሳልቀይር   ዕድሜዬ   እየነጎደ   ነው።ቤተሰቤ  ለእኔ በቂ ነው።ቤተሰቤን የምቀይርበት ኃይልና ጥበብ ስጠኝ"ብዬ ወደመፀለይ ተሸጋገርኩ አሁን ሳረጅ ደግሞ እቤተሰቦቼ ራሱ በጣም እንደሚበዙ ተረዳው"..እራሴን መቀየርና ማስተካከል ከቻልኩ በቂ ነው...አሁን ወደትክክለኛው መስመር ተመልሼያለሁ ..ስለዚህ ይሄንን እንዳደርግ የሚያግዘኝ ኃይልና ጥበብ ስጠኝ "ብዬ የመጨረሻ ፀሎቴን ፀለይኩ።አምላክም መለሰልኝ"አሁን የቀረህ ምንም አይነት እንጥፍጣፊ ጊዜ የለህም።ይሄንን መጠየቅ የነበረብህ ከአመታት በፊት በጉልምስና ወራትህ ላይ ነበር..አሁን  ግን  ረፍዶብሀል"አለኝ።እና  ልጄ  የእኔ  እጣ እንዳያጋጥምህ ዛሬውኑ ንቃ...ፀሎትህን አስተካክል...ምኞትህን አርቅ...ብለው የመጨረሻ ምክራቸውን ለገሱ…
ሽማግሌው እንዳሉት አለም ምስቅልቅል ያለች የሚመስለን ምስቅልቅሎን የሚያስተካክል ሰው ስለጠፋ ሳይሆን እራሱን ለማስተካከል የሚጥር ሰው ጥቂት ስለሆነ እንደሆነ ለመረዳት እኔም ረጅም ጊዜ ወስዶብኛል፡፡ለማንኛውም ወደ ታሪኩ ልመለስልሽ፡፡
እዛ እንደደረስኩ ሁሉ  ነገር  አሪፍ  ነበር…ልጅ  ስለነበርኩ  ሁሉን  ነገር  በፍጥነት ነበር  አዳብት  የደረኩት…ትምህርቴን  እንደጨረስኩ.  ወደ  ሚኒሶታ  ሙቭ አደረኩና ፍላይንግ ክላውድ አየር ማረፊያ አካባቢ ዋና ቢሮውን ያደረገ ኬ.ቢ ኢንተርናሽናል ኮስሞቲክ ካምፓኒ ውስጥ ስራ ያዝኩ፡፡ ወዲያው ከአንዲት አሜሪካዊት    የካምፓኒ    ሰራተኛ  ጋር ወዲያው ፍቅር ያዘኝ…ትዝ ይለኛል…የተያየነው ሰኞ ቀን ነው…ማክሰኞ ፍቅር እንደያዘኝ ገባኝና ከስራ

መውጫችን ላይ ከስሯ ኩስ ኩስ እያልኩ  ተከትዬ  አዋራኋት…በሁለተኛው  ቀን እራት አብረን በላን…ይሄንን ያዩ አብረውኝ ሚሰሩ ወንዶች  በአድነቆት  ፈዘው ሲያዩኝ ግራ ገባኝ…‹‹ምንድነው ቆንጆ ስለሆነች እሺ አትለውም  ብለው  እስበው ነበር ማለት ነው?››ስል ማሰላሰል ጀመርኩና በጥረቴ ገፋሁበት..ከሁለት ሳምንት በኃላ እፍ ያለ ፍቅር ውስጥ ያሉ ፍቅረኛሞች ሆን…ከአንድ ወር በኃላ የሚገርም ዜና ሰማሁ..ለካ በድፍረት የጠበስኩት የስራ ባለደረባዬን ብቻ ሳይሆን የተቀጠርኩበት ካምፓኒ ብቸኛ ልጅ እና የወደፊት ወራሽ የሆነችውን ልጅ ነው…ወንዶቹ ሁሉ በድፍረቴ ለምን እንደተደመሙ ቆይቶ  ነው  የገባኝ..እኔም ቀድሜ ባውቅ ያንን አይነት ድፍረት አይኖረኝም ነበር፡፡
ሳባ ከትንፋሹ ጋ ተደባልቆ የሚወጣው ሙቅ አየር ጉንጮቾ ላይ ሲያርፍ እየተሰማት በፀጥታና በተመስጦ እያዳመጠችው ነው፡፡
ካትሪና  በጣም  ቆንጆ፤ንፅህ  ደፋር  ቀጥተኛን  ፤ልታይ  ልታይ  ማትል፤የተለየ  ስብዕና ያላት ልጅ ነበረች..እኔ ግን ይሄንን ሁሉ አይቼና መዝኜ ሳይሆን ዝም ብዬ ድንገት ሳያት ድንገጥ ስላልኩባት ነው ያፈቀርኳት፡፡ የመጀመሪያ   እይታ   ስንተያይ ከአይኖቾ የተረጩ ብርሀን ልቤን ሰንጥቆት ስለነበረነው፡፡ከስድስት ወር በኃላ ተጋባን፡፡በሁለት አመት ውስጥ የተደራጀ ቤትና ኑሮ ኖረን..ሁሉነገር እስደሳችና የገነት ኑሮ መሰለ…ከትሪን ሌላ ካትሪንን አረገዘች፣፣በቃ በደስታ አቅሌን ልስት ደረስኩ፡፡ ወደኢትዬጵያ ተመልሶ ለዚህ ህዝብ መሲ የመሆን   እቅዴ   እየደበዘዘ ሙሉ በሙሉ በአሜሪካ ኑሮ እየተሰባኩ በአሜሪካኖች   ስነልቦና   እየተዋጥኩ ሄድኩ፡፡
ከኢትዬጵያ ጋር የሚያገናኙን ወላጆቼ ነበሩ፡፡ ለእነሱ በሶስት ወርም ሆነ በስድስት ወር ለእኔ ትንሽ  የሚባል  ለእነሱ  ግን  ህይወታቸውን  ሊቀይር  የሚችል  አይነት ብር እልክላቸዋለሁ…በቃ

ከዛ ሱዛና ተወለደች…የእኔ ሱዛና ትንሽዬ መልአክ ነበር የምትመስለው፤እጆቾ ድንብሽብሽ ያሉ አይኖቾ የተቁለጨለጩ…አቤት ሁሉ ነገር እንዴት ፐርፌክት እንደነበረ….ሱዛና ተወልዳ ስድስት ወር ሳይሞላት የካትሪና እናት ሞተችና ወደ 5 መቶ ሚሊዬን ዶላር ሀብት ያለውን ያን ካማፓኒ  ወረሰች  በዛን  ጊዜ  ካትሪን ስራዋን ሙሉ በሙሉ ለቃ የቤት እመቤት ሆና ነበር ፡፡እዛው እቤት ሆና የእድሜ ልክ ታለንቶ የሆነው ሙዚቃ ላይ ትሰራ ስለነበረ ወደስራ ተመልሶ ካምፓኒውን የማስተዳደሩ ፍላጎት ምንም አልነበራም..በዛ ምክንያት እኔ የካማፓኒው ዋና ሰው ሆንኩ…ከዛ  ካትሬን  ሌላ  ልጅ  አረገዘችልኝ…ታዲያ  የዛ  ሁሉ  የተትረፈረፈ የቤተሰብ ደስታ፤ የዛ ሁሉ  የተትረፈረፈ ሀብት ባለቤት የሆንኩት ያ ሸራ ጫማ መግዣ ይቸግረው የነበረው?ያ በሶ እየበጠበጠ በመጠጣት ረሀቡን በማስታገስ የተማረው ቀናው ነኝ...ብዬ በመደመም ሰው ከለፋና ከጣረ.. የት ድረስ መድርስ እንደሚችል እና እድልም ለእሱ አጎብድዳ እንደምታገለግለው ላገኘሁት  ሰው ሁሉ ልክ እንደሞቲቬሽናል  እስፒከር  በመጎረር  ስተርክ  የምውል  በራስ  መተማመኔ ጣራ የነካ ሰው ሆንኩ…..፡፡

ታዲያ ምን ሆነ ዳቢሎስ ቁጣውን በምድር ላይ አዘነበ….እግዚያብሄርም ተባባሪው ነበር…ወይንም መጀመሪያውኑ ዋናው እቅድ  የራሱ  የእግዚያብሄር  ይሆናል፡፡ ጃንዋሪ 2020 አካባቢ ከካምፓኒው ጋር ለተያያዘ ስራ ቻይና ለአንድ ወር ቆይቼ ነበር…በወቅቱ ቻይና አዲስ ቨይረስ መከሰቱን እየተወራ ነበር.ወደአሜሪካ በተመለስኩ በቀናት ውስጥ ቨይረሱ  በቻይና  ምድር  እየተስፋፋ  መሆኑን መንግስት ግን የደበቀ መሆኑን ሀኪሞች መረጃውን እያሾለኩ ማውጣት ጀመሩ የቻይና መንግስትም አመነ፣ብዙ ሰዎች እየሞቱበት እነደሆነ ተናገረ..ከዛ ሌሎች ሀገሮችም ተዛመተ አሜሪካ ገባ ተብሎ ሶስት ቀን ሳይሞላው ካትሪን ያተኩሳት ጀመር፤ወዲያው ትንፋሽ አጠራት …ጉሮሮዋ ቆሰለ..… ዶክተራችን መጥቶ አያትና
👍945🥰2👏2