#ባይተዋር
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
ስናይና ላምሮት በስንት ጊዜያቸው፣ ስንት ጊዜ ለምኗት፣ ስንት ጊዜ ተለማምጧት፣ ስንት "በናትሽ"አባክኖባት፣ ስንት የኔ ቆንጆ ስወድሽ" ፣ “እስቲ አንዳንዴ እንኳን ያለልጆቹ እንደ ድሮው ወጣ ብለን እንዝናና” አዝንቦባት፧ እየጠጡ ሊያመሹ ቦሌ አካባቢ፣ አንዱ በሚደነቁር ሙዚቃ እና በሲጋራ ጢስ የታፈነ ባር ቁጭ ብለዋል፡፡እሱ ቮድካውን ይለጋል፣ እሷ ጣፋጭ ወይኗን ለኮፍ ለኮፍ ታደርጋለች።
እራት በልተው እሱ አራተኛ ደብል ቮድካው ላይ ሲደርስ፣ እሷ ግን
ያቺኑ አንዲት ብርጭቆ ወይን ታባብላለች፡፡ከተጋቡ 12 ዓመታቸው
ነው ፤ ልጆች ስላሏቸው ብዙ አያመሹም፤ እስከ እኩለ ሌሊት፣ እስከ ከሌሊቱ ዐሥር ሰዐት ሲጠጡና ሲደንሱ የማደር፣ የ”ኦቨር ናይት” ጭፈራ ዘመን ለእነሱ ካበቃ ቆይቷል፡፡ ድሮ ቀረ፡፡ ቢያንስ ላምሮት
በምልጃም ቢሆን ከሦስት ሰዐት በላይ አታመሽም፡፡ሁሌም ከሥራ ወደቤት መሄድ፣ ጓደኞቿን እንኳን ቤቷ መቅጠር፣ በጊዜ በጋቢ ተጠቅልላ ቴሌቪዥን ፊት መጎለት የምትወድ ዓይነት ሴት ናት።
“ኡፋፋ.....! ይሄ ሙዚቃ እስከዚህ ከጣራ በላይ መጮህ አለበት? ሰው እንዴት ብሎ ያወራል? ደግሞ የሲጋራው ጭስ... ምኑ ደስ፣እንደሚልህ አላውቅም እንዲህ አይነት ቦታ ማምሸት....? በናትህ ወደቤት እንሂድ...እ?” ብላ ማማረር ከመጀመሯ፣ ፊት ለፊቷ፣ከአንገቱ ብዙ ካልጎደለው የወይን ጠርሙሷ አጠገብ፣ ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠችው ስልኳ ጮኸ፡፡
ሰናይ ሰዐቱን ዐየ፡፡ ሦስት ሰዐት ከሠላሳ አምስት፡፡
(ማነው በዚህ ሰዐት የሚደውልላት..? ከቤት ነው? ሰራተኛቸው ናት? ልጆቹ ደህና አይደሉም?)
ስልኩን አንስታ፣ “ሄሎ” አለችና ሌላ ቃል ሳታወጣ ዝም ብላ አዳመጣ ዘጋችው።
ሁኔታዋ ግራ ቢያጋባውም ፤ ሰናይ፣
“ማነው በዚህ ሰዐት የሚደውልልሽ?” ብሎ ሚስቱን የሚነዘንዝ፣ አምባጓሮ የሚያስነሳ፣በራሱ የማይተማመን ባል፤ ሚስቱም በዚህ ሰዐት በሚደወል፣
ተገቢ ያልሆነ ግንኙነትና የስልክ
ጥሪ” የምትጠረጠር ሴት ስላልሆነች ምንም አላላትም፡፡
በመሃል ከስልክ ጥሪው ጋር የማይገናኝ አንድ ሁለት አረፍተ ነገር ወሬ ካወሩ በኋላ፣ አምስት ከማይሞላ ደቂቃ በኋላ ስልኳን አንስታ የሆነ ነገር ፃፈች፡፡ ቴክስት መሰለው፡፡
ከዐሥር ደቂቃ በኋላ የሙዚቃውን ጩኸት፣ የወጣቶቹን ጫጫታና
የሲጋራውን ሽታ መቋቋም ስላልቻለች፥ ሰናይ ሂሳቡን ከፍሎ፣ ለአስተናጋጇ ጉርሻ ሰጥቶ፣ ጃኬቱን ደርቦ ወደቤታቸው ሄዱ፡፡
ይሄ የሆነው አርብ ዕለት ነበር፡፡የዚያኑ ዕለተ ማታ ቤት ደርሰው፣ ልብስ ቀይረው አልጋቸው ውስጥ ሲገቡ፣ ሚስቱ በዚያ ሰዐት የተደወለላትን ስልክ አንስታ
ከሄሎ በስተቀር አንዲት ቃል ሳትናገር መዝጋቷ ሆድ ሆዱን እየበላው ነበር።
በነጋታው ቅዳሜ ጠዋት፣ ሁሌም እንደሚያደርገው ሳሎን ላፕቶፕ
ከሳምንት የተረፈ ሥራ ሲሠራ፤ ፒጃማዋን
እንደለበሰች፣ ጠዋት የጠበሰችውን እንቁላል እንቁላል እየሸተተች አጠገቡ መጣችና፣
“ሰናይዬ፣ ይሄ ስልክ ዜንደሩ አልሠራም ብሎ አስቸገረኝ... እስቲ ዕይና አስተካክልልኝ”ብላ፣ ስልኳን አቀበለችው፡፡ ላምሮት የቴክኖሎጂ ነገር የማይሆንላት፣ ለትንሹም ለትልቁም የእሱን እርዳታ የምትጠይቅ ዓይነት ሚስት ናት፡፡ሪሞት ኮንትሮል በትክክል አነጣጥራ ቲቪ መክፈት ሲያቅታት ቢሮ ደውላ፣ “እምቢ
አለኝ…ምን ላድርግ” የምትል ዓይነት
ሚስት።“ባትሪው ላልቶ ይሆናል እስቲ ክፈቺውና ነካ ነካ አድርገሽ እንደገና ሞክሪው”ሲላት በቃ ስትመጣ ዐያለው” ብላ የምትዘጋ ሚስት።
ስልኳን ሰጠችውና ወደ በረንዳ ወጥታ ቀድማ ካዘጋጀችው ባልዲ እየቀዳች አትክልቶቿን ውሃ ማጠጣት ጀመረች፡፡
በራሱም በሚስቱም የማይተማመን ባል፣ ይሄን አጋጣሚ ተጠቅሞ አርብ ማታ፣ ለአራት ሃያ አምስት ጉዳይ ላይ ለሚስቱ የደወለው ማን እንደሆን ለማጣራት ስልኩን ይበረብር ነበር፡፡ ሰናይ ግን
እንዲህ ያለ ባል ለመሆን ዝግጁ አልነበረም፡፡ እሱ፣ ሚስቱን የሚያፈቅርና የሚያምን፣ በሦስት ልጆች የጸና ጠንካራና ደስተኛ ትዳር ያለው ሰው ነው፡፡ አእምሮው የተረጋጋ፣ መንፈሱ ያረፈ
አባወራ ነው፡፡
አይደለም እንዴ?
ሁለት ደቂቃ ሳይሞላ የስልክ ጥሪዎች ታሪክ የሚጠራቀምበት ቦታ ገብቶ አርብ ማታ የደወለውን ሰው ቁጥር መፈለግ ያዘ፡፡
አርብ፣ ከምሽቱ 3:35 ደቂቃ “ኤ” በሚል
ስም የተመዘገበ የማያውቀው ቁጥር፣
ጥሪው የቆየበት ጊዜ፡ አምስት ሰከንዶች፡፡
እምምምም....!
ጣቶቹን አፍጥኖ ወደ መልእክት ሳጥኗ ገባ፡፡ በዚያው ምሽት፣ ከእሱ ጋር ተቀምጣ፣ ለ “ኤ” የፃፈችውን መልእክት አየ፡፡ ሃይ፣ ፓርቲ ነኝ... ጫጫታ ስለሆነ አይሰማም፡፡ እደውልልሃለሁ” ይላል፡፡
ፓርቲ ነኝ?
ወደ ላይ ሄደና ከዚያ በፊት የጸፈችለትን ማየት ጀመረ፡፡ ሐሙስ ዕለት ማታ የጻፈችውን፣ “ሃሃሃ ... ይገርማል... ትዝታው ሊገልህ ነዋ! “ የሚል አገኘ፡፡
ትዝታው? የምን ትዝታ?
ከዚያ በፊት ኤ የጻፈውን ዐየ፡፡
“ስሚ ቆንጅዬ... ባለፈው ሳምንት ቀኑን ሙሉ ተአምር የሠራንበትን ራሱን ክፍል መልሰው አይሰጡኝም? አይገርምም?” ይላል፡፡
ይሄን ጊዜ ሰናይ ሁለመናው ከዕንጨት እንደተሠራ ሁሉ ይደርቃል፡፡
ከአፉ ምራቅ ይጠፋል፡፡
ዐይኑ ይደፈርሳል፡፡
ሚዛኑ ይዛባል፡፡
ልቡ ልክ ባልሆነ ዘዬ ይመታል፡፡
ጣቶቹ መንቀጥቀጥ ይጀምራሉ፡፡
ሁሉም ጸጉሮቹ መቆም ይጀምራሉ፡፡
ወደ ላይ ይለዋል፡፡ ሽንቱ ይወጥረዋል፡፡
መሬት ላይ ተዘርሮ ቁና ቁና መተንፈስን ይመኛል፡፡
ግን በሚንቀጠቀጡ ጣቶቹ የስልኳን ገጽ ወደ ላይ ይገልጣል። የኤ እና የታማኝ ሚስቱን የቃላት ድሪያዎች ለደቂቃዎች ያነባል።
አንዱ መልእክት ወደሌላው እየመራው፣ አንዱ አንዱን አንብብ እያለው የሚያንፈራፍር የሆድ ሕመም እስኪይዘው ድረስ ብዙ ጉድ አየ፣ ብዙ ጉድ አነበበ፡፡ ማለቂያ የሌለው የብልግና መልእክት ክምር ውስጥ ራሱን አገኘ፡፡
ማንበብ ማቆም ይፈልጋል፡፡ ግን ያቅተዋል፡፡
በእያንዳንዱ መልእክት የሚስቱ ስብእና ይሸራረፍበታል፡፡
በእያንዳንዱ ፣ “ሃይ ፍቅሬ” ቤቱ ይፈራርስበታል፡፡
በእያንዳንዱ፣ “እኔም ናፍቀኸኛል” ዓለሙ ይጠብበታል፡፡
ግን ማንበብ ማቆም ያቅተዋል፡፡
ባገኙት መድረክ ሁሉ ይባልጋሉ፣ ይሞላፈጣሉ፣ ይጨማለቃሉ፡፡ዋትስአፕ፣ ቫይበር፣ ቴሌግራም፡፡ ....ሃያ ባልሞላ ደቂቃ ውስጥ የ12 ዓመት ትዳሩ አፈር ከድሜ ጋጠ፡፡ የሚያፈቅራት ሚስቱ፣
የሦስት ልጆቹ እናት ፤ በሃያ ደቂቃ ዕድሜ፣ የቡና ቤት ሴት፣ ጎዳና ላይ ቆማ ገበያ የምትጠብቅ ሴት አዳሪ ሆነች፡፡ በሃያ ደቂቃ ዕድሜ ሕይወቱ አይሆኑ ሆነ፡፡
የደስታ ኑሮው አፈር ለበሰ፡፡ብዙ መጠጥ ጠጥቶ ጢምበራው እንደዞረ ሰው ጭ....ው...እንዳለበት፣ እንደተወዛገበ፣ አለሙ እንደጠበበ፣ሁለንተናው
እንደተበጠበጠ፣ ሦስት ልጆቹ ጠባቡ ግቢ ውስጥ ሲጫወቱ ይሰማዋል፡፡ ላምሮት... ይህች የማያውቃት፣ ባይተዋር ሴት፤ አትክልቶቿ አጠገብ በርጩማ ላይ ተቀምጣ ስታያቸው ይታየዋል፡፡
የረፋድ ፀሐይ በረጅሙ መስኮት በኩል ወደቤት ገብታለች፡፡
ምንድነው የሚያደርገው?
ቀጥታ ወደ ኩሽና ሄዶ፣ ከቢላዎች መሃል ትልቁን ቢላ መርጦ እየተምዘገዘገ አጠገቧ ደርሶ አትክልቶቿ ፊት እንደ አትክልት ይከትፋታል?
የኔ አንጀት እንዲህ ነው የተበጠሰው ብሎ፣ በቢላው አንጀቷን በጥሶ
ያሳያታል?
ልጆቿ /ልጆቻቸው ፊት ይገድላታል?
አያደርገውም፡፡
ፊትለፊቱ የተቀመጠውን ትልቅ መስኮት የሚያህል ቴሌቪዥን (ያ ሁሌ እንደ ጨዋ ሴት በጊዜ ቤቷ ተሰብስባ፣ ተጎልታ የምታየውን) ይከሰክሰዋል።
ልብሷን ሁሉ እያወጣ፣ ፀያፍ ስድብ እየተሳደበ... “አንቺ ሸርሙጣ”
ምናምን እያለ በረንዳ ላይ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
ስናይና ላምሮት በስንት ጊዜያቸው፣ ስንት ጊዜ ለምኗት፣ ስንት ጊዜ ተለማምጧት፣ ስንት "በናትሽ"አባክኖባት፣ ስንት የኔ ቆንጆ ስወድሽ" ፣ “እስቲ አንዳንዴ እንኳን ያለልጆቹ እንደ ድሮው ወጣ ብለን እንዝናና” አዝንቦባት፧ እየጠጡ ሊያመሹ ቦሌ አካባቢ፣ አንዱ በሚደነቁር ሙዚቃ እና በሲጋራ ጢስ የታፈነ ባር ቁጭ ብለዋል፡፡እሱ ቮድካውን ይለጋል፣ እሷ ጣፋጭ ወይኗን ለኮፍ ለኮፍ ታደርጋለች።
እራት በልተው እሱ አራተኛ ደብል ቮድካው ላይ ሲደርስ፣ እሷ ግን
ያቺኑ አንዲት ብርጭቆ ወይን ታባብላለች፡፡ከተጋቡ 12 ዓመታቸው
ነው ፤ ልጆች ስላሏቸው ብዙ አያመሹም፤ እስከ እኩለ ሌሊት፣ እስከ ከሌሊቱ ዐሥር ሰዐት ሲጠጡና ሲደንሱ የማደር፣ የ”ኦቨር ናይት” ጭፈራ ዘመን ለእነሱ ካበቃ ቆይቷል፡፡ ድሮ ቀረ፡፡ ቢያንስ ላምሮት
በምልጃም ቢሆን ከሦስት ሰዐት በላይ አታመሽም፡፡ሁሌም ከሥራ ወደቤት መሄድ፣ ጓደኞቿን እንኳን ቤቷ መቅጠር፣ በጊዜ በጋቢ ተጠቅልላ ቴሌቪዥን ፊት መጎለት የምትወድ ዓይነት ሴት ናት።
“ኡፋፋ.....! ይሄ ሙዚቃ እስከዚህ ከጣራ በላይ መጮህ አለበት? ሰው እንዴት ብሎ ያወራል? ደግሞ የሲጋራው ጭስ... ምኑ ደስ፣እንደሚልህ አላውቅም እንዲህ አይነት ቦታ ማምሸት....? በናትህ ወደቤት እንሂድ...እ?” ብላ ማማረር ከመጀመሯ፣ ፊት ለፊቷ፣ከአንገቱ ብዙ ካልጎደለው የወይን ጠርሙሷ አጠገብ፣ ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠችው ስልኳ ጮኸ፡፡
ሰናይ ሰዐቱን ዐየ፡፡ ሦስት ሰዐት ከሠላሳ አምስት፡፡
(ማነው በዚህ ሰዐት የሚደውልላት..? ከቤት ነው? ሰራተኛቸው ናት? ልጆቹ ደህና አይደሉም?)
ስልኩን አንስታ፣ “ሄሎ” አለችና ሌላ ቃል ሳታወጣ ዝም ብላ አዳመጣ ዘጋችው።
ሁኔታዋ ግራ ቢያጋባውም ፤ ሰናይ፣
“ማነው በዚህ ሰዐት የሚደውልልሽ?” ብሎ ሚስቱን የሚነዘንዝ፣ አምባጓሮ የሚያስነሳ፣በራሱ የማይተማመን ባል፤ ሚስቱም በዚህ ሰዐት በሚደወል፣
ተገቢ ያልሆነ ግንኙነትና የስልክ
ጥሪ” የምትጠረጠር ሴት ስላልሆነች ምንም አላላትም፡፡
በመሃል ከስልክ ጥሪው ጋር የማይገናኝ አንድ ሁለት አረፍተ ነገር ወሬ ካወሩ በኋላ፣ አምስት ከማይሞላ ደቂቃ በኋላ ስልኳን አንስታ የሆነ ነገር ፃፈች፡፡ ቴክስት መሰለው፡፡
ከዐሥር ደቂቃ በኋላ የሙዚቃውን ጩኸት፣ የወጣቶቹን ጫጫታና
የሲጋራውን ሽታ መቋቋም ስላልቻለች፥ ሰናይ ሂሳቡን ከፍሎ፣ ለአስተናጋጇ ጉርሻ ሰጥቶ፣ ጃኬቱን ደርቦ ወደቤታቸው ሄዱ፡፡
ይሄ የሆነው አርብ ዕለት ነበር፡፡የዚያኑ ዕለተ ማታ ቤት ደርሰው፣ ልብስ ቀይረው አልጋቸው ውስጥ ሲገቡ፣ ሚስቱ በዚያ ሰዐት የተደወለላትን ስልክ አንስታ
ከሄሎ በስተቀር አንዲት ቃል ሳትናገር መዝጋቷ ሆድ ሆዱን እየበላው ነበር።
በነጋታው ቅዳሜ ጠዋት፣ ሁሌም እንደሚያደርገው ሳሎን ላፕቶፕ
ከሳምንት የተረፈ ሥራ ሲሠራ፤ ፒጃማዋን
እንደለበሰች፣ ጠዋት የጠበሰችውን እንቁላል እንቁላል እየሸተተች አጠገቡ መጣችና፣
“ሰናይዬ፣ ይሄ ስልክ ዜንደሩ አልሠራም ብሎ አስቸገረኝ... እስቲ ዕይና አስተካክልልኝ”ብላ፣ ስልኳን አቀበለችው፡፡ ላምሮት የቴክኖሎጂ ነገር የማይሆንላት፣ ለትንሹም ለትልቁም የእሱን እርዳታ የምትጠይቅ ዓይነት ሚስት ናት፡፡ሪሞት ኮንትሮል በትክክል አነጣጥራ ቲቪ መክፈት ሲያቅታት ቢሮ ደውላ፣ “እምቢ
አለኝ…ምን ላድርግ” የምትል ዓይነት
ሚስት።“ባትሪው ላልቶ ይሆናል እስቲ ክፈቺውና ነካ ነካ አድርገሽ እንደገና ሞክሪው”ሲላት በቃ ስትመጣ ዐያለው” ብላ የምትዘጋ ሚስት።
ስልኳን ሰጠችውና ወደ በረንዳ ወጥታ ቀድማ ካዘጋጀችው ባልዲ እየቀዳች አትክልቶቿን ውሃ ማጠጣት ጀመረች፡፡
በራሱም በሚስቱም የማይተማመን ባል፣ ይሄን አጋጣሚ ተጠቅሞ አርብ ማታ፣ ለአራት ሃያ አምስት ጉዳይ ላይ ለሚስቱ የደወለው ማን እንደሆን ለማጣራት ስልኩን ይበረብር ነበር፡፡ ሰናይ ግን
እንዲህ ያለ ባል ለመሆን ዝግጁ አልነበረም፡፡ እሱ፣ ሚስቱን የሚያፈቅርና የሚያምን፣ በሦስት ልጆች የጸና ጠንካራና ደስተኛ ትዳር ያለው ሰው ነው፡፡ አእምሮው የተረጋጋ፣ መንፈሱ ያረፈ
አባወራ ነው፡፡
አይደለም እንዴ?
ሁለት ደቂቃ ሳይሞላ የስልክ ጥሪዎች ታሪክ የሚጠራቀምበት ቦታ ገብቶ አርብ ማታ የደወለውን ሰው ቁጥር መፈለግ ያዘ፡፡
አርብ፣ ከምሽቱ 3:35 ደቂቃ “ኤ” በሚል
ስም የተመዘገበ የማያውቀው ቁጥር፣
ጥሪው የቆየበት ጊዜ፡ አምስት ሰከንዶች፡፡
እምምምም....!
ጣቶቹን አፍጥኖ ወደ መልእክት ሳጥኗ ገባ፡፡ በዚያው ምሽት፣ ከእሱ ጋር ተቀምጣ፣ ለ “ኤ” የፃፈችውን መልእክት አየ፡፡ ሃይ፣ ፓርቲ ነኝ... ጫጫታ ስለሆነ አይሰማም፡፡ እደውልልሃለሁ” ይላል፡፡
ፓርቲ ነኝ?
ወደ ላይ ሄደና ከዚያ በፊት የጸፈችለትን ማየት ጀመረ፡፡ ሐሙስ ዕለት ማታ የጻፈችውን፣ “ሃሃሃ ... ይገርማል... ትዝታው ሊገልህ ነዋ! “ የሚል አገኘ፡፡
ትዝታው? የምን ትዝታ?
ከዚያ በፊት ኤ የጻፈውን ዐየ፡፡
“ስሚ ቆንጅዬ... ባለፈው ሳምንት ቀኑን ሙሉ ተአምር የሠራንበትን ራሱን ክፍል መልሰው አይሰጡኝም? አይገርምም?” ይላል፡፡
ይሄን ጊዜ ሰናይ ሁለመናው ከዕንጨት እንደተሠራ ሁሉ ይደርቃል፡፡
ከአፉ ምራቅ ይጠፋል፡፡
ዐይኑ ይደፈርሳል፡፡
ሚዛኑ ይዛባል፡፡
ልቡ ልክ ባልሆነ ዘዬ ይመታል፡፡
ጣቶቹ መንቀጥቀጥ ይጀምራሉ፡፡
ሁሉም ጸጉሮቹ መቆም ይጀምራሉ፡፡
ወደ ላይ ይለዋል፡፡ ሽንቱ ይወጥረዋል፡፡
መሬት ላይ ተዘርሮ ቁና ቁና መተንፈስን ይመኛል፡፡
ግን በሚንቀጠቀጡ ጣቶቹ የስልኳን ገጽ ወደ ላይ ይገልጣል። የኤ እና የታማኝ ሚስቱን የቃላት ድሪያዎች ለደቂቃዎች ያነባል።
አንዱ መልእክት ወደሌላው እየመራው፣ አንዱ አንዱን አንብብ እያለው የሚያንፈራፍር የሆድ ሕመም እስኪይዘው ድረስ ብዙ ጉድ አየ፣ ብዙ ጉድ አነበበ፡፡ ማለቂያ የሌለው የብልግና መልእክት ክምር ውስጥ ራሱን አገኘ፡፡
ማንበብ ማቆም ይፈልጋል፡፡ ግን ያቅተዋል፡፡
በእያንዳንዱ መልእክት የሚስቱ ስብእና ይሸራረፍበታል፡፡
በእያንዳንዱ ፣ “ሃይ ፍቅሬ” ቤቱ ይፈራርስበታል፡፡
በእያንዳንዱ፣ “እኔም ናፍቀኸኛል” ዓለሙ ይጠብበታል፡፡
ግን ማንበብ ማቆም ያቅተዋል፡፡
ባገኙት መድረክ ሁሉ ይባልጋሉ፣ ይሞላፈጣሉ፣ ይጨማለቃሉ፡፡ዋትስአፕ፣ ቫይበር፣ ቴሌግራም፡፡ ....ሃያ ባልሞላ ደቂቃ ውስጥ የ12 ዓመት ትዳሩ አፈር ከድሜ ጋጠ፡፡ የሚያፈቅራት ሚስቱ፣
የሦስት ልጆቹ እናት ፤ በሃያ ደቂቃ ዕድሜ፣ የቡና ቤት ሴት፣ ጎዳና ላይ ቆማ ገበያ የምትጠብቅ ሴት አዳሪ ሆነች፡፡ በሃያ ደቂቃ ዕድሜ ሕይወቱ አይሆኑ ሆነ፡፡
የደስታ ኑሮው አፈር ለበሰ፡፡ብዙ መጠጥ ጠጥቶ ጢምበራው እንደዞረ ሰው ጭ....ው...እንዳለበት፣ እንደተወዛገበ፣ አለሙ እንደጠበበ፣ሁለንተናው
እንደተበጠበጠ፣ ሦስት ልጆቹ ጠባቡ ግቢ ውስጥ ሲጫወቱ ይሰማዋል፡፡ ላምሮት... ይህች የማያውቃት፣ ባይተዋር ሴት፤ አትክልቶቿ አጠገብ በርጩማ ላይ ተቀምጣ ስታያቸው ይታየዋል፡፡
የረፋድ ፀሐይ በረጅሙ መስኮት በኩል ወደቤት ገብታለች፡፡
ምንድነው የሚያደርገው?
ቀጥታ ወደ ኩሽና ሄዶ፣ ከቢላዎች መሃል ትልቁን ቢላ መርጦ እየተምዘገዘገ አጠገቧ ደርሶ አትክልቶቿ ፊት እንደ አትክልት ይከትፋታል?
የኔ አንጀት እንዲህ ነው የተበጠሰው ብሎ፣ በቢላው አንጀቷን በጥሶ
ያሳያታል?
ልጆቿ /ልጆቻቸው ፊት ይገድላታል?
አያደርገውም፡፡
ፊትለፊቱ የተቀመጠውን ትልቅ መስኮት የሚያህል ቴሌቪዥን (ያ ሁሌ እንደ ጨዋ ሴት በጊዜ ቤቷ ተሰብስባ፣ ተጎልታ የምታየውን) ይከሰክሰዋል።
ልብሷን ሁሉ እያወጣ፣ ፀያፍ ስድብ እየተሳደበ... “አንቺ ሸርሙጣ”
ምናምን እያለ በረንዳ ላይ
👍3