#ቀስ_ብሎ_ይቆማል
፡
፡
#ስድስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ወደ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ቤተክርስቲያን ሄድኩ። እንደ እብድ ብቻዬን ማውራት ጀምሬ ነበር። ቀጥ ብዬ ዋናውን በር አልፌ ገባሁ። ትዝ ሲለኝ አልተሳለምኩም፤ ተመልሼ ግራ ቀኝ በሩን ተሳለምኩ። ዘው
አይባልም ዘሎ፤ ፈጣሪ የተጎዳ ልቤን ቢመለከትም ቅሉ እዚህ ድረስ ልብ ውልቅ መሆኔ ለኔም ደግ አይደል ወደ ውስጥ ስገባ የቤተክርስቲያኑ ድባብ፣ የቤተመቅደሱ ወፋፍራም የጣውላ ከፈፎች ላይ የሰፈሩት ዋነሶች፣ እድሜ ጠገቦቹ ዛፎች፣ ከምንም በላይ ደግሞ ዝምታው ከውስጥ ብሶቴ ተዳምሮ አጃዬን አመጣው። ከምርም የሰው ልጅ ምናምኒት አቅም እንደሌለው የሚያውቅበት የሆነ ጭብጦ ነገር መሆኑን የሚረዳበት ቦታ ሲኖር ቤተክርስቲያን ይመስለኛል።
ፈጣሪን ምን ማለት እንዳለብኝ ግራ ገባኝ። ታቆምልኛለህ ወይስ አታቆምልኝም…” ከይባል ነገር። ቆይ ግን ከዘፍጥረት ጀምሮ በዚህ ጕዳይ እግዜር ፊት ቆሞ የፀለየ ሰው ይኖር ይሆን ? በሐሳቤ ስቀላምድ ቆየሁና ዞር ዞር ብዬ አካባቢዩን ቃኘሁ። ከእኔ ወደ ግራ ሲል ቢጫ ልብስ የለበሱ መነኩሴ ተቀምጠዋል።ምን እንደገፋኝ እንጃ ወደሳቸው ገሰገስኩ፤ ምናልባት እዛው እንደ ደንቡ እግዜርን በሚያዝንበት ቋንቋ
ቢያናግሩልኝ ብዬም እንደሆን እንጃ ! አጠገባቸው ስደርስ፣
“አባ " አልኳቸው።
"አቤት የኔ ልጅ፣ እንደምን ዋልክ” አሃ !ለካ ሰላምታም ነበር።
"ጓደኛዬ ልትመጣ ሦስት ቀን ቀራት፤ ከመቀሌ ከሦስት ቀን በኋላ ትመጣለች፤ ሙና ነው ስሟ
ሦስት ቀን ብቻ ቀና ብለው በእርጋታ አዩኝና ከጎናቸው ያለውን ግንድ መቁጠሪያ በያዘ እጃቸው
እያመሰከቱኝ፣
"ና እስቲ እዚህ አረፍ በል የኔ ልጅ” አሉኝ።
“አይ እሄዳለሁ" ብያቸው ያመለከቱብኝ ቦታ ላይ ተቀመጥኩ። (ሁለት ሰው የሆንኩ መሰለኝ፤)
የምናገረው ሌላ የማደርገው ሌላ
“ምን ሆነህ ነው የምታለቅስ ልጄ” ቢሉኝ እጄ ወደ ዓይኔ ሄደ አይገርምም ? እየተነፋረቅኩ ነበረ
ለካ፡ እንባዩን በእጄ ሞዥቄ አባን የሆነውን ሁሉ ነገርኳቸው። አቤት መስማት ሲችሉበት
በጥሞና ሲሰሙኝ ቆይተው፣ "የኔ ልጅ እግዲህ ዋናው ነገር … እግዜር የጊዜ አምላክ ነው፤ የሰውና የአግዜር አሰራር ልዩነቱ ይሄ ነው። ሰው የቻላትን ባሰኘው ጊዜ ያደርጋል፥ እግዜር ግን ሁሉን ይችላል የሚያደርገው ግን ለልጆቹ በሚጠቅመው ጊዜ በሚጠቅመው ልክ ነው። ካለጊዜው እንዲህ ያለው ነገር
ውስጥ እንዳትገባ ሊያስተምረህ ወድዶ ይሆናል አንድም ደሞ የምድር ጠቢባን ያቃታቸውን ሁሉ
የሚችል መሆኑን ሊገልጥልህ ሲወድ እንደሆነ ምኑ ይታወቃል ልጄ.."
"እና ምን ላርግ አባ፤ ሶስት ቀን ብቻ ቀራት እኮ"
“መምጣቷ መልካም ነው ! ታዲያ መውደድ ሲሞላ ብቻ አይደለም፣ ሲጎድልም እንጂ፤ መሳቅህን
ብቻ እያሳየህ በወዳጅህ ፊት ትልቅ አትምሰል ልጄ፡ ሰው ነህ ድከመት አለብህ፣ ድክመትህን ለራሷ ንገራት፤ እውነቱን ተናገር። የውሸትና ማስመሰል ዙፋን ከእንቧይ ገንብተህ ንገሽ ብትላት እሷንም ተንዶ ጉድ ይሰራታል፣ ላንተም ፀፀት ነው። የውሸት እና ማስመሰል ካባ ከነፍስ ከረምት፣ ከመንፈስም ቁር አያስጥልም፤ አትድከም! ግራ ቀኝም አትበል፤ እሷን ሸፋፍነህ ብታሳምናት ከራስህ ልብ የገባህው
አተካራ አያባራም። እውነቱን ንገራት፣ ከእውነት የበለጠ ፈውስ የለም የኔ ልጀ።”
"ከዛስ እባ ፤"
ከዛማ እውነት ከተናገርከ ሰውም ምክርም አያሻህ፤ እውነት ራሱ መንገዱን ይምራሄል።"ብለው ወደ
መቁጠሪያቸው አቀረቀሩ። ደህና ዋሉ ልበላቸው አልሰላቸው እንጃ ወደ ቤቴ ተመልሼ ጥቅልል ብዬ
ተኛሁ። እውነት መንገዱን ይመራሃል፤ እውነት ዋጋ ያስከፍላል ያውም ከነወለዱ። ከሆንስ ሆነና እውነት ዋጋው ስንት ነው?
እውነት ዋጋው ስንት ነው?
እውነት ዋጋው ስንት ነው?
እውነት ዋጋው ስንት ነው?
የቱንም ያህል ዋጋው ቢወደድ፣ በቃ ለሙና እውነቱን እነግራታለሁ። ወሰንኩ !
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የቁርጥ ቀን!
እነሆ የተንኳኳ በሬን ከፈትኩ፤ ልብ የሚያቀልጥ የሙና ውበት ከወትሮው ሰባት እጅ ደምቆ በሬ ላይ ቆሟል። ሙናን አፈቅራታለሁ፤ ልለያት አልፈልግም። ሳያት ልክ ብርሃን ጨለማ ክፍልን ድንገት ቦግ ብሎ እንደሚሞላው ውስጤን የሚሞላው አንዳች ነገር አላት፤ እንደ ባዶ ፊኛ የሟሸሽ መንፈሴ ሙናን ሳያት በዓየር እንደተሞላ ባሉን በፍቅርና በደስታ ሕዋ ላይ ይንሳፈፋል። ይሄው የእውነት ዋጋው በሬ ላይ። እውነት ዋጋው ይሄን ያህል ውድ ነው። እቅጩን ተናግሬ የነፍሴን ግማድ ሙናን መክፈል፤አልያም ሰቆቃዬ ላይ ስሳቀቅ በየዕለቱ በማስመሰልና በሽሽት ሚስማር የፍርሃት ጉልላቴ ላይ መቸንከር።
በሐሴት የሚንሳፈፍ የነፍሴን ባሉን፣ ክፉ እሾህ ጠቅ አድርጎ ሊያተነፍሰው ወደኔ ሲወነጨፍም
እከላከልበት ዘንድ በእጄ ያለው መሳሪያ አባ ያስታጠቁኝ ጋሻ ብቻ ነው እውነት !! እውነቱን ተናግሬ
የመሸበት አድራለሁ። እስከመቼ የነገር አንጆ ሳመነዥክ ልኑር ? በቃኝ !!
ምን እንዳረጋጋኝ እንጃ በውስጤ "ሙና ብትሄድ ሺ ሙናዎች ይተካሉ” ስል ረጋ ብዬ ፎከርኩ። ላንዲት ሙና ያልሆንኩ እኔ ለሺ ሙና ስፎክር የሰማ ራሴ ቢታዘበኝም ግድ አልሰጠኝም። ፉከራ ከጀግንነት ብቻ ሳይሆን ጥልቅ ከሆነ ፍርሃትም እንደሚመነጭ የገባኝ ያኔ ነው።
ሙና በእቅፏ ሙሉ አፍሳኝ በሞቃት ከንፈሯ በናፍቆት ግጥም አድርጋ ስትስመኝ ነፍሴ ከተወዘፈችበት ኩርፊያ ተመንጥቃ ልትወጣ ተጣጣረች፤ ቢሆንም እንቅ አድርጌ ነፍሴን ያዝኳት። መቆጣት አለብኝ መኮሳተር አለብኝ። ሙና የሆነ ነገር ሆኗል ዛሬ ልለፈው" እንድትል የሆነ ነገር የሆንኩ መምሰል አለብኝ። ተሸከማ የመጣችውን እሳት በቁጣ ውኃ በር ላይ ማጥፋት፡ መደርገም አለብኝ። ቦርሳዋን
ጠረጴዛ ላይ ወርወር አደረገችና በናፍቆት አንዴ ቤቱን ከእግር እስከ ራሱ ዙሪያውን ቃኝታ በረዥሙ
ተነፈሰችና ለሞላ ቦታ መጥታ ጉልበቴ ላይ ተቀመጠች። ደረቷ ላይ አስጠግታ አቀፈችኝ ለሞላ
የሰውነት ክፍል ፀጉሬን ሳመችኝ።
“ፀጉርህ አድጓል” ብላ በጣቷ መንጨር መንጨርጨ አደረገችኝ። ወይ ነዶ ልጅቱማ የፍቅር ሰው
ነበረች፤ ካለቦታው ተከሰተች እንጂ። ተነስታ ወደ ውስጥ ገባችና የእኔን ቁምጣ ለበሰች፤ ቁምጣ የተሰራው የሙና ዓይነት እግር ላላቸው ሰዎች ይመስለኛል። የእኔን ቲሸርት ለበሰች፤ ቲሸርት
የተፈጠረው የሙና ዓይነት ጡት ላላቸው ሴቶች ብቻ ይመስለኛል። ከዛም ወደ ኪችን። ዝም ብዬ
አያታለሁ፤ ፊቷ ላይ ምንም ነገር የለም፤ ረጋ ያለ ለስላሳ ፊት፤ ትረጋጋ እንጂ እሷ ምን አለባት
የመጣው ቢመጣ ሁሉ በጇ፣ በአንድ እይታ ብቻ ወደ እሳት ነበልባልነት የሚለወጥ አረር ሰውነት ምን አስጨነቃት።
እያጠናኋት ነበር፤ መለያየታችን እንደማይቀር አንድ ነገር ሹክ ስሳለኝ እድሜ ልኬን እንዳልረሳ
እያጠናኋት ነበር። ሙናን መቼም ቢሆን መርሳት አልፈልግም፣ ፍቅረኛዬ ስለሆነች አይደለም
በሕይወት ውስጥ የመሰላል እርካን ሆነው አንድ ደረጃ ከፍ የሚያደርጉን ሰዎች አሉ፣ ሙና እንደዚ ናት ለእኔ። ምን ያህል ልትናፍቀኝ እንደምትችል አሁን ላይ ሆኜ አውቀዋለሁ። ዝም ብዪ አያታለሁ ድንገት ዞር ስትል ዓይናችን ተገጣጠመ ሳቀች። ፍፁም ገራገር እና ንፁህ ፊት። እኔ ግን ደነገጥኩ፡ ወይ ጉድ፡ ሰው በሰላም አገር እንደ ሌባ ደንጋጭ ሆኖ ይቀራል ?!
፡
፡
#ስድስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ወደ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ቤተክርስቲያን ሄድኩ። እንደ እብድ ብቻዬን ማውራት ጀምሬ ነበር። ቀጥ ብዬ ዋናውን በር አልፌ ገባሁ። ትዝ ሲለኝ አልተሳለምኩም፤ ተመልሼ ግራ ቀኝ በሩን ተሳለምኩ። ዘው
አይባልም ዘሎ፤ ፈጣሪ የተጎዳ ልቤን ቢመለከትም ቅሉ እዚህ ድረስ ልብ ውልቅ መሆኔ ለኔም ደግ አይደል ወደ ውስጥ ስገባ የቤተክርስቲያኑ ድባብ፣ የቤተመቅደሱ ወፋፍራም የጣውላ ከፈፎች ላይ የሰፈሩት ዋነሶች፣ እድሜ ጠገቦቹ ዛፎች፣ ከምንም በላይ ደግሞ ዝምታው ከውስጥ ብሶቴ ተዳምሮ አጃዬን አመጣው። ከምርም የሰው ልጅ ምናምኒት አቅም እንደሌለው የሚያውቅበት የሆነ ጭብጦ ነገር መሆኑን የሚረዳበት ቦታ ሲኖር ቤተክርስቲያን ይመስለኛል።
ፈጣሪን ምን ማለት እንዳለብኝ ግራ ገባኝ። ታቆምልኛለህ ወይስ አታቆምልኝም…” ከይባል ነገር። ቆይ ግን ከዘፍጥረት ጀምሮ በዚህ ጕዳይ እግዜር ፊት ቆሞ የፀለየ ሰው ይኖር ይሆን ? በሐሳቤ ስቀላምድ ቆየሁና ዞር ዞር ብዬ አካባቢዩን ቃኘሁ። ከእኔ ወደ ግራ ሲል ቢጫ ልብስ የለበሱ መነኩሴ ተቀምጠዋል።ምን እንደገፋኝ እንጃ ወደሳቸው ገሰገስኩ፤ ምናልባት እዛው እንደ ደንቡ እግዜርን በሚያዝንበት ቋንቋ
ቢያናግሩልኝ ብዬም እንደሆን እንጃ ! አጠገባቸው ስደርስ፣
“አባ " አልኳቸው።
"አቤት የኔ ልጅ፣ እንደምን ዋልክ” አሃ !ለካ ሰላምታም ነበር።
"ጓደኛዬ ልትመጣ ሦስት ቀን ቀራት፤ ከመቀሌ ከሦስት ቀን በኋላ ትመጣለች፤ ሙና ነው ስሟ
ሦስት ቀን ብቻ ቀና ብለው በእርጋታ አዩኝና ከጎናቸው ያለውን ግንድ መቁጠሪያ በያዘ እጃቸው
እያመሰከቱኝ፣
"ና እስቲ እዚህ አረፍ በል የኔ ልጅ” አሉኝ።
“አይ እሄዳለሁ" ብያቸው ያመለከቱብኝ ቦታ ላይ ተቀመጥኩ። (ሁለት ሰው የሆንኩ መሰለኝ፤)
የምናገረው ሌላ የማደርገው ሌላ
“ምን ሆነህ ነው የምታለቅስ ልጄ” ቢሉኝ እጄ ወደ ዓይኔ ሄደ አይገርምም ? እየተነፋረቅኩ ነበረ
ለካ፡ እንባዩን በእጄ ሞዥቄ አባን የሆነውን ሁሉ ነገርኳቸው። አቤት መስማት ሲችሉበት
በጥሞና ሲሰሙኝ ቆይተው፣ "የኔ ልጅ እግዲህ ዋናው ነገር … እግዜር የጊዜ አምላክ ነው፤ የሰውና የአግዜር አሰራር ልዩነቱ ይሄ ነው። ሰው የቻላትን ባሰኘው ጊዜ ያደርጋል፥ እግዜር ግን ሁሉን ይችላል የሚያደርገው ግን ለልጆቹ በሚጠቅመው ጊዜ በሚጠቅመው ልክ ነው። ካለጊዜው እንዲህ ያለው ነገር
ውስጥ እንዳትገባ ሊያስተምረህ ወድዶ ይሆናል አንድም ደሞ የምድር ጠቢባን ያቃታቸውን ሁሉ
የሚችል መሆኑን ሊገልጥልህ ሲወድ እንደሆነ ምኑ ይታወቃል ልጄ.."
"እና ምን ላርግ አባ፤ ሶስት ቀን ብቻ ቀራት እኮ"
“መምጣቷ መልካም ነው ! ታዲያ መውደድ ሲሞላ ብቻ አይደለም፣ ሲጎድልም እንጂ፤ መሳቅህን
ብቻ እያሳየህ በወዳጅህ ፊት ትልቅ አትምሰል ልጄ፡ ሰው ነህ ድከመት አለብህ፣ ድክመትህን ለራሷ ንገራት፤ እውነቱን ተናገር። የውሸትና ማስመሰል ዙፋን ከእንቧይ ገንብተህ ንገሽ ብትላት እሷንም ተንዶ ጉድ ይሰራታል፣ ላንተም ፀፀት ነው። የውሸት እና ማስመሰል ካባ ከነፍስ ከረምት፣ ከመንፈስም ቁር አያስጥልም፤ አትድከም! ግራ ቀኝም አትበል፤ እሷን ሸፋፍነህ ብታሳምናት ከራስህ ልብ የገባህው
አተካራ አያባራም። እውነቱን ንገራት፣ ከእውነት የበለጠ ፈውስ የለም የኔ ልጀ።”
"ከዛስ እባ ፤"
ከዛማ እውነት ከተናገርከ ሰውም ምክርም አያሻህ፤ እውነት ራሱ መንገዱን ይምራሄል።"ብለው ወደ
መቁጠሪያቸው አቀረቀሩ። ደህና ዋሉ ልበላቸው አልሰላቸው እንጃ ወደ ቤቴ ተመልሼ ጥቅልል ብዬ
ተኛሁ። እውነት መንገዱን ይመራሃል፤ እውነት ዋጋ ያስከፍላል ያውም ከነወለዱ። ከሆንስ ሆነና እውነት ዋጋው ስንት ነው?
እውነት ዋጋው ስንት ነው?
እውነት ዋጋው ስንት ነው?
እውነት ዋጋው ስንት ነው?
የቱንም ያህል ዋጋው ቢወደድ፣ በቃ ለሙና እውነቱን እነግራታለሁ። ወሰንኩ !
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የቁርጥ ቀን!
እነሆ የተንኳኳ በሬን ከፈትኩ፤ ልብ የሚያቀልጥ የሙና ውበት ከወትሮው ሰባት እጅ ደምቆ በሬ ላይ ቆሟል። ሙናን አፈቅራታለሁ፤ ልለያት አልፈልግም። ሳያት ልክ ብርሃን ጨለማ ክፍልን ድንገት ቦግ ብሎ እንደሚሞላው ውስጤን የሚሞላው አንዳች ነገር አላት፤ እንደ ባዶ ፊኛ የሟሸሽ መንፈሴ ሙናን ሳያት በዓየር እንደተሞላ ባሉን በፍቅርና በደስታ ሕዋ ላይ ይንሳፈፋል። ይሄው የእውነት ዋጋው በሬ ላይ። እውነት ዋጋው ይሄን ያህል ውድ ነው። እቅጩን ተናግሬ የነፍሴን ግማድ ሙናን መክፈል፤አልያም ሰቆቃዬ ላይ ስሳቀቅ በየዕለቱ በማስመሰልና በሽሽት ሚስማር የፍርሃት ጉልላቴ ላይ መቸንከር።
በሐሴት የሚንሳፈፍ የነፍሴን ባሉን፣ ክፉ እሾህ ጠቅ አድርጎ ሊያተነፍሰው ወደኔ ሲወነጨፍም
እከላከልበት ዘንድ በእጄ ያለው መሳሪያ አባ ያስታጠቁኝ ጋሻ ብቻ ነው እውነት !! እውነቱን ተናግሬ
የመሸበት አድራለሁ። እስከመቼ የነገር አንጆ ሳመነዥክ ልኑር ? በቃኝ !!
ምን እንዳረጋጋኝ እንጃ በውስጤ "ሙና ብትሄድ ሺ ሙናዎች ይተካሉ” ስል ረጋ ብዬ ፎከርኩ። ላንዲት ሙና ያልሆንኩ እኔ ለሺ ሙና ስፎክር የሰማ ራሴ ቢታዘበኝም ግድ አልሰጠኝም። ፉከራ ከጀግንነት ብቻ ሳይሆን ጥልቅ ከሆነ ፍርሃትም እንደሚመነጭ የገባኝ ያኔ ነው።
ሙና በእቅፏ ሙሉ አፍሳኝ በሞቃት ከንፈሯ በናፍቆት ግጥም አድርጋ ስትስመኝ ነፍሴ ከተወዘፈችበት ኩርፊያ ተመንጥቃ ልትወጣ ተጣጣረች፤ ቢሆንም እንቅ አድርጌ ነፍሴን ያዝኳት። መቆጣት አለብኝ መኮሳተር አለብኝ። ሙና የሆነ ነገር ሆኗል ዛሬ ልለፈው" እንድትል የሆነ ነገር የሆንኩ መምሰል አለብኝ። ተሸከማ የመጣችውን እሳት በቁጣ ውኃ በር ላይ ማጥፋት፡ መደርገም አለብኝ። ቦርሳዋን
ጠረጴዛ ላይ ወርወር አደረገችና በናፍቆት አንዴ ቤቱን ከእግር እስከ ራሱ ዙሪያውን ቃኝታ በረዥሙ
ተነፈሰችና ለሞላ ቦታ መጥታ ጉልበቴ ላይ ተቀመጠች። ደረቷ ላይ አስጠግታ አቀፈችኝ ለሞላ
የሰውነት ክፍል ፀጉሬን ሳመችኝ።
“ፀጉርህ አድጓል” ብላ በጣቷ መንጨር መንጨርጨ አደረገችኝ። ወይ ነዶ ልጅቱማ የፍቅር ሰው
ነበረች፤ ካለቦታው ተከሰተች እንጂ። ተነስታ ወደ ውስጥ ገባችና የእኔን ቁምጣ ለበሰች፤ ቁምጣ የተሰራው የሙና ዓይነት እግር ላላቸው ሰዎች ይመስለኛል። የእኔን ቲሸርት ለበሰች፤ ቲሸርት
የተፈጠረው የሙና ዓይነት ጡት ላላቸው ሴቶች ብቻ ይመስለኛል። ከዛም ወደ ኪችን። ዝም ብዬ
አያታለሁ፤ ፊቷ ላይ ምንም ነገር የለም፤ ረጋ ያለ ለስላሳ ፊት፤ ትረጋጋ እንጂ እሷ ምን አለባት
የመጣው ቢመጣ ሁሉ በጇ፣ በአንድ እይታ ብቻ ወደ እሳት ነበልባልነት የሚለወጥ አረር ሰውነት ምን አስጨነቃት።
እያጠናኋት ነበር፤ መለያየታችን እንደማይቀር አንድ ነገር ሹክ ስሳለኝ እድሜ ልኬን እንዳልረሳ
እያጠናኋት ነበር። ሙናን መቼም ቢሆን መርሳት አልፈልግም፣ ፍቅረኛዬ ስለሆነች አይደለም
በሕይወት ውስጥ የመሰላል እርካን ሆነው አንድ ደረጃ ከፍ የሚያደርጉን ሰዎች አሉ፣ ሙና እንደዚ ናት ለእኔ። ምን ያህል ልትናፍቀኝ እንደምትችል አሁን ላይ ሆኜ አውቀዋለሁ። ዝም ብዪ አያታለሁ ድንገት ዞር ስትል ዓይናችን ተገጣጠመ ሳቀች። ፍፁም ገራገር እና ንፁህ ፊት። እኔ ግን ደነገጥኩ፡ ወይ ጉድ፡ ሰው በሰላም አገር እንደ ሌባ ደንጋጭ ሆኖ ይቀራል ?!
👍36🥰2❤1
#ዶክተር_አሸብር
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
፡
፡
#ስድስት
፡
፡
አቲዬ ለመርገጥ የሚያስፈራው የወይዘሮ እጥፍወርቅ ግቢ ውስጥ አንዲት ቆንጆ ሠርቪስ ቤት
ተሰጠቻት፡፡ ያውም ከነሙሉ ዕቃው፡፡
“ማነው ስምሽ እናቱ?” አለቻት አቲዩን ወይዘሮ እጥፍወርቅ፡፡
“አፀደ"
"ውይ የኔ ድንቡሽቡሽ! ስንት ወሩ ነው” አለች እኔን እያያች፡፡
“አሁን የፊታችን ገብሬል መንፈቅ ይሞላዋል" እጇን ወደኔ ዘረጋች። ፈገግ ብዬ እጇን ለቀም፡፡ ሕፃናትን
መለይካው ይመራቸዋል የሚባለው እውነት ሳይሆን አይቀርም። ወይም ሴትዬዋ እጅ ላይ የተገጠገጠው የወርቅ ቀለበትና ጌጣጌጥ መጫወቻ መስሎኝ:: ወይዘሮ እጥፍወርቅ አቲዬን እንዲህ አለቻት፤
“ላንችና ለልጅሽ ሆድ አታስቢ.! እዚህ ተርፎ ለሚደፉ እህል የበላነውን ትበያለሽ፡፡ ብትወጅ እኛ ጋር እየሰራሽ፣ ከፈለግሽም የፈለክሽውን እየሰራሽ እዚሁ ኑሪ ቤትሽ ነው::
ኑሪ ኑረ ኑሪ ኑሪ…ኑሪ…በሕይወት ኑሪ፡፡ ሌሊት ኮሽ ባለ ቁጥር ሳትሰጊ ኑሪ፡፡ ልጅሸን
እንደፈለግሽ የምታጥቢበት፣ የሽንት ጨርቅ የምታጥቢበት ውሀ ሳያሳስብሽ ኑሪ፡፡ ልጅሽ የሚበላው
ነገር ሳይቸግረው ኑሬኑሪ.: እግዚርም ሲናገር ልክ እንዲህ ነበር፡ ያውላችሁ ምድር ኑሩበት፤
ውሀው ያው ምግቡ ያው፣ መኖሪያው ያው ይሄው ወይዘሮ እጥፍወርቅ ግቢ ዘፍጥረት
ራሱን ሲደግም፡፡
“በመጀመሪያ ምድር ባዶ ነበረ፡፡ ባዶው ላይ አንዲት የጨለመባት ሚስኪን ሴት ልጅ አዝላ ቆማ ነበረ፡፡ እግዜር ብርሃን ይሁን አለ፡፡ ቦግ !” ከእግዜር ብርሃን ጋር ሲወዳደር ቀለመወርቅ አብሪ ትል ማለት ነው፡፡ ዘርፌ ሀይሏን የጨረሰች የእጅ ባትሪ፡፡ ወይዘሮ እጥፍወርቅ ጨረቃ የእግዜርን ብርሃን የምታንፀባርቅ፡፡ እግዜር ግን ፀሐይ ከአድማስ እስከ አድማስ በብርሃን የሚያጥለቀልቅ እናም የሚምቅ !
አቲዩ በተሰጣት ምርጫ መሠረት እዛው ቤት ልትሰራ ወሰነች፡፡ በዕርግጥም የተሻለ ምርጫ
ነበረ፡፡ የማንንም ፊት ከማየት በእጅጉ የተሻለ፡፡ ለእኔ በተለይ ግቢው መቦረቂያዬ፣ የወይዘሮ
እጥፍወርቅ ፈገግታ ምቾቴ ሆነልኝ፡፡ በዛ ሰፊ ግቢ ውስጥ ወይዘሮ እጥፍወርቅ፣ ወጣት ተማሪ ልጃቸውና እኛ ብቻ ነበርን የምንኖረው፡፡ የወይዘሮ እጥፍወርቅ አምስት ልጆች ኑሯቸው ቀውጭ ሀገር ነበር፡፡
ወይዘሮ እጥፍወረቅ አስገራሚ ሴት ነበረች፡፡ እንኳን አቲዬ የድሮ እመቤቷ ዘርፌ ራሷ
የማታልመውን ከውጭ ሀገር የመጣ አንድ ሻንጣ ልብስ ለአቲዬ ሰጠቻት፡፡ ለእኔም ቆንጆ
ቆንጆ ልብስ ገዛችልኝ ዘነጥን !! እኔና እቲዬ ቂቅ ብለን ዘነጥን ደግሞ ስናምር!!
አቲዩ ከወይዘሮ እጥፍወርቅ የተሰጣትን ልብስ ለበሳ አበባ መስላ ብቅ ስትል ዘርፌ ዓይኗ ደም ለበሰ፣ ቀለመወርቅ ደም ግፊቱ ከፍ አለ፡፡ ክፉ አሳቢዎች ምን ሀብት ቢተርፋቸው የያዙት ነገር አያስደስታቸውም፡፡ ይልቅ የሚያጠሉት ሰው ጥቃቅን ለውጥ ያንገበግባቸዋል፡፡ ዘርፌና ቀለመወርቅ የምቀኛ ግንባር ፈጥረው ተንገበገቡ፡፡ የግንባሩ ጸሐፊ ሰይጣን!! እናም ሰይጣን ከቀለመወርቅ እና ዘርፌ ኋላ እግዜርም ከአቲዬ ፊት ቆመው ጦርነቱ ተጀመረ !! አሁን በኑሮ ማስፈራራት በክብር መንጠባረር የለም፡፡ ማንም ሆዱ ከሞላ ጀግና ነው፡፡ ማንም ቢመታ የሚወድቅበት፣ ሲቆስል የሚታከምበት ካለው ጀግና ነው፡፡ ማንም የሚያከብረው ሰው ከጎኑ ካለ ለሌሎች ንቀት ሞራሉ እንደደረቅ እንጨት አይሰበርም፡፡ ዋናው ስንቅና ትጥቅ ግን ማንም እግዚያብሄር ከኋላው እንዳለ ካመነ ልበ ሙሉ ነው !!
እቲዬ ይሄን ሁሉ ሆና ነው ወደ ጦርነቱ የገባችው !! እናም ጦርነቱ በታሪክ ወርቃማው ጦርነት በመባል ይታወቃል በእኔ በነፍሴ ዘገባ !! ወደፊት ልጆቼ “ለምን ወርቃማው ጦርነት ተባለ ?” ብለው ሲጠይቁኝ መልሴ አንድ እና አንድ ነው፤ “በቀለመወርቅ እና በእጥፍወርቅ መካከል በተደረገ ሰብዓዊ ጦርነት በእሳት የተፈተኑ ወርቆች ወደ ምቾት አገር ስለተሰደዱ” እላቸዋለሁ፡፡
የባርነት አስከፊ ገፅታ ያለው በባርነት መግዛቱ ላይ ሳይሆን በባርነት የተገዙበት መንገድ ላይ
ነው፡፡ በፍላጎት ለሌሎች ባሪያ መሆን ለራስ ህሊና የጌትነት ማዕረግ ሰለሚያጎናፅፍ፣ ለነፃነት
ትግል ሳይሆን ምስጋና ራስህን እንድታዘጋጅ ነው የሚያደርግህ:: እሰይ! እንኳንም ባሪያ ሆንኩ የሚባልለት ባርነት አለኮ፡፡ ሰዎች በፍቅር ለሀገራቸው ባሪያ ይሆናሉ፡፡ ለፈጣሪያቸው ይገዛሉ፡፡ ለሚወዷቸው ያገለግላሉ፡፡ ግን ደስተኞች ናቸው፡፡ ለምን ? መንገዱ ፍቅር ነዋ !
አቲዬ ዙሪያውን በረዥም የግንብ አጥር ወደተከበበው ግቢ ገብታ ብትከትምም ዕጣፋንታዋን ግን አላመለጠችውም፡፡ ዕጣፋንታ እኮ ጥላ ነው:: በዙሪያህ ያለውን ችግርና መከራ ፍንትው
አድርጎ የሚያሳይ ብርሃን ሲጠፋ፣ አብሮ የጠፋ ይመስለሃል እንጂ፣ ቀን የሚሉት ፀሐይ ወጋገኑን
ሲቀድ ከትላንቱ በላይ ደምቆ ካንተ በላይ ገዝፎ ከፊትህ ይመራሀል ከኋላህም ይከተልሀል፡፡
አትዬም ዕጣ ፋንታዋን ስንዝር አላመለጠችውም፡፡ ከባርነት ወደ ፍቅር ባርነት ተቀይሮ በትልቁ
ነፍስ ዘራችበት፡፡ ሰፊውን ግቢ ከጧት እስከ ማታ አፅድታ ትልቁን ቤት ውብት ትደፋበታለች፤
ግቢ ውስጥ ጠበቃት እንጂ፡፡ሰው አጥቶ፣ ውርማ ውጦት የነበረውን የወይዘሮ እጥፍወርቅ ግቢ
የወይዘሮ እጥፍወርቅን ሆቴልም ቀጥ አድርጋ የያዘችው አቲዬ ራሷ ነበረች፡፡
የሆቴሉን እንጀራ ሙሉ በሙሉ ትጋግራለች፡፡ የአልቤረጎዎቹን አንሶላዎች ታጥባለች፡፡ እንደዛም
ሆኖ በጣም ደስተኛ ነበረች፡፡ ወይዘሮ እጥፍወርቅ ደግ ሴት ነበረችና ምንም በደረግላት ይገባታል፤የአቲዬ ባርነት ጣፋጭ ነበር፡፡ መሀተመ ጋንዲ ወደ ወይዘሮ እጥፍወርቅ ግቢ ጎራ ቢሉ ኖሮ፣ "ነመስቴ…እኛም የታገልነው ለዚህች አይነቷ ባርነት ነበር በርቱ!” ብለው የሚሄዱ ይመስለኛል!
በእርግጥ ወይዘሮ እጥፍወርቅ አቲዬን እንጀራ ጋግሪ አላለቻትም፡፡ ራሷ አቲዬ ለሆቴሉ እንጀራ
ግዥ እየተባለ በቅን የሚወጣውን ብር ስትመለከት፣ “ምጣድ ግዙልኝ ሪሴ እጋግራለሁ" አለች እንጂ፡፡ የሆቴሉን አንሶላ፣ “እጠቢ ያላት ማንም አልነበረም፡፡ አጣቢዋ ስትጨማለቅ ስታያት አቲዬ የኔ የልብ ሰው፣ “ምነው እቴ ሰው የሚታኛበት እይደለም እንዴ” አለችና አጇን ሰቅስቃ
ገባችበት፡፡“አቦ የእጥፍወርቅ ቤርጎ እንሶላው ብትል ፎጣው እንዴት ይጸዳል” እስኪባል፡፡ የወይዘሮ እጥፍወርቅ ልብ አቲን በልጅነት መንበር ላይ ወስዶ አስቀመጣት፤ እኔንም የልጅ ልጅነት !!
ግቢው የእኔ ነበር፡፡ እንዳሻኝ የምሆንበት ግዛቴ፡፡ የሳሎኑ ዕቃ የእኔ ነበር፡፡ ጆሮ ጭው የሚያደርግ ዋጋ የተከሰከሰበት ሶፋ ላይ ሸንቼበታለሁ፣ ወተት ደፍቼበታለሁ፡ አቀርሽቼበታለሁ፡፡ ለዓይን የሚያሳሳውን የቡፌ ዕቃ እንኮታኩቼዋለሁ፡፡ የወደዘሮ አጥፍወርቅን ባለ አልማዝ ፈርጥ የአንገት ሀብል ከእንገቷ ላይ በጣጥሼዋለሁ፡፡ (የዚህ ሀገር ወርቅ አንጥረኛ አይሰራውም ተብሎ ተቀምጦ ቀረ…) የፋናዬን (እህቴ ማለት ናት - የወይዘሮ እጥፍወርቅ ልጅ) ቀይና ውብ ፊት ቦጫጭረዋለሁ፣ ፋኒዬን እንደ ህፃን ልጅ ነበር የማስለቅሳት፡፡
አትዬ ስትነግረኝ ፋናዬ ከትምህርት ቤት ስትመጣ ቦርሳዋን እንዳዘለች እኔ ላይ ትጠመጠምና ድበድብ ነው፡፡ ሱቅ የተሰቀለ አሻንጉሊት ካየች፣ የሕግን ልብስና መጫወቻ ዓይኗ ውስጥ ከገባ፡ ለእኔ ለመግዛት ከእናቷ ጋር ብር ስጭኝ አልሰጥም” ጦርነት ነው::
የእናቴ ንፁህ ልብ እንደስፖንጅ ፍራሽ በሕይወቴ መንገድ ላይ ተነጥፎ የዛች ቅፅበት የነበረ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
፡
፡
#ስድስት
፡
፡
አቲዬ ለመርገጥ የሚያስፈራው የወይዘሮ እጥፍወርቅ ግቢ ውስጥ አንዲት ቆንጆ ሠርቪስ ቤት
ተሰጠቻት፡፡ ያውም ከነሙሉ ዕቃው፡፡
“ማነው ስምሽ እናቱ?” አለቻት አቲዩን ወይዘሮ እጥፍወርቅ፡፡
“አፀደ"
"ውይ የኔ ድንቡሽቡሽ! ስንት ወሩ ነው” አለች እኔን እያያች፡፡
“አሁን የፊታችን ገብሬል መንፈቅ ይሞላዋል" እጇን ወደኔ ዘረጋች። ፈገግ ብዬ እጇን ለቀም፡፡ ሕፃናትን
መለይካው ይመራቸዋል የሚባለው እውነት ሳይሆን አይቀርም። ወይም ሴትዬዋ እጅ ላይ የተገጠገጠው የወርቅ ቀለበትና ጌጣጌጥ መጫወቻ መስሎኝ:: ወይዘሮ እጥፍወርቅ አቲዬን እንዲህ አለቻት፤
“ላንችና ለልጅሽ ሆድ አታስቢ.! እዚህ ተርፎ ለሚደፉ እህል የበላነውን ትበያለሽ፡፡ ብትወጅ እኛ ጋር እየሰራሽ፣ ከፈለግሽም የፈለክሽውን እየሰራሽ እዚሁ ኑሪ ቤትሽ ነው::
ኑሪ ኑረ ኑሪ ኑሪ…ኑሪ…በሕይወት ኑሪ፡፡ ሌሊት ኮሽ ባለ ቁጥር ሳትሰጊ ኑሪ፡፡ ልጅሸን
እንደፈለግሽ የምታጥቢበት፣ የሽንት ጨርቅ የምታጥቢበት ውሀ ሳያሳስብሽ ኑሪ፡፡ ልጅሽ የሚበላው
ነገር ሳይቸግረው ኑሬኑሪ.: እግዚርም ሲናገር ልክ እንዲህ ነበር፡ ያውላችሁ ምድር ኑሩበት፤
ውሀው ያው ምግቡ ያው፣ መኖሪያው ያው ይሄው ወይዘሮ እጥፍወርቅ ግቢ ዘፍጥረት
ራሱን ሲደግም፡፡
“በመጀመሪያ ምድር ባዶ ነበረ፡፡ ባዶው ላይ አንዲት የጨለመባት ሚስኪን ሴት ልጅ አዝላ ቆማ ነበረ፡፡ እግዜር ብርሃን ይሁን አለ፡፡ ቦግ !” ከእግዜር ብርሃን ጋር ሲወዳደር ቀለመወርቅ አብሪ ትል ማለት ነው፡፡ ዘርፌ ሀይሏን የጨረሰች የእጅ ባትሪ፡፡ ወይዘሮ እጥፍወርቅ ጨረቃ የእግዜርን ብርሃን የምታንፀባርቅ፡፡ እግዜር ግን ፀሐይ ከአድማስ እስከ አድማስ በብርሃን የሚያጥለቀልቅ እናም የሚምቅ !
አቲዩ በተሰጣት ምርጫ መሠረት እዛው ቤት ልትሰራ ወሰነች፡፡ በዕርግጥም የተሻለ ምርጫ
ነበረ፡፡ የማንንም ፊት ከማየት በእጅጉ የተሻለ፡፡ ለእኔ በተለይ ግቢው መቦረቂያዬ፣ የወይዘሮ
እጥፍወርቅ ፈገግታ ምቾቴ ሆነልኝ፡፡ በዛ ሰፊ ግቢ ውስጥ ወይዘሮ እጥፍወርቅ፣ ወጣት ተማሪ ልጃቸውና እኛ ብቻ ነበርን የምንኖረው፡፡ የወይዘሮ እጥፍወርቅ አምስት ልጆች ኑሯቸው ቀውጭ ሀገር ነበር፡፡
ወይዘሮ እጥፍወረቅ አስገራሚ ሴት ነበረች፡፡ እንኳን አቲዬ የድሮ እመቤቷ ዘርፌ ራሷ
የማታልመውን ከውጭ ሀገር የመጣ አንድ ሻንጣ ልብስ ለአቲዬ ሰጠቻት፡፡ ለእኔም ቆንጆ
ቆንጆ ልብስ ገዛችልኝ ዘነጥን !! እኔና እቲዬ ቂቅ ብለን ዘነጥን ደግሞ ስናምር!!
አቲዩ ከወይዘሮ እጥፍወርቅ የተሰጣትን ልብስ ለበሳ አበባ መስላ ብቅ ስትል ዘርፌ ዓይኗ ደም ለበሰ፣ ቀለመወርቅ ደም ግፊቱ ከፍ አለ፡፡ ክፉ አሳቢዎች ምን ሀብት ቢተርፋቸው የያዙት ነገር አያስደስታቸውም፡፡ ይልቅ የሚያጠሉት ሰው ጥቃቅን ለውጥ ያንገበግባቸዋል፡፡ ዘርፌና ቀለመወርቅ የምቀኛ ግንባር ፈጥረው ተንገበገቡ፡፡ የግንባሩ ጸሐፊ ሰይጣን!! እናም ሰይጣን ከቀለመወርቅ እና ዘርፌ ኋላ እግዜርም ከአቲዬ ፊት ቆመው ጦርነቱ ተጀመረ !! አሁን በኑሮ ማስፈራራት በክብር መንጠባረር የለም፡፡ ማንም ሆዱ ከሞላ ጀግና ነው፡፡ ማንም ቢመታ የሚወድቅበት፣ ሲቆስል የሚታከምበት ካለው ጀግና ነው፡፡ ማንም የሚያከብረው ሰው ከጎኑ ካለ ለሌሎች ንቀት ሞራሉ እንደደረቅ እንጨት አይሰበርም፡፡ ዋናው ስንቅና ትጥቅ ግን ማንም እግዚያብሄር ከኋላው እንዳለ ካመነ ልበ ሙሉ ነው !!
እቲዬ ይሄን ሁሉ ሆና ነው ወደ ጦርነቱ የገባችው !! እናም ጦርነቱ በታሪክ ወርቃማው ጦርነት በመባል ይታወቃል በእኔ በነፍሴ ዘገባ !! ወደፊት ልጆቼ “ለምን ወርቃማው ጦርነት ተባለ ?” ብለው ሲጠይቁኝ መልሴ አንድ እና አንድ ነው፤ “በቀለመወርቅ እና በእጥፍወርቅ መካከል በተደረገ ሰብዓዊ ጦርነት በእሳት የተፈተኑ ወርቆች ወደ ምቾት አገር ስለተሰደዱ” እላቸዋለሁ፡፡
የባርነት አስከፊ ገፅታ ያለው በባርነት መግዛቱ ላይ ሳይሆን በባርነት የተገዙበት መንገድ ላይ
ነው፡፡ በፍላጎት ለሌሎች ባሪያ መሆን ለራስ ህሊና የጌትነት ማዕረግ ሰለሚያጎናፅፍ፣ ለነፃነት
ትግል ሳይሆን ምስጋና ራስህን እንድታዘጋጅ ነው የሚያደርግህ:: እሰይ! እንኳንም ባሪያ ሆንኩ የሚባልለት ባርነት አለኮ፡፡ ሰዎች በፍቅር ለሀገራቸው ባሪያ ይሆናሉ፡፡ ለፈጣሪያቸው ይገዛሉ፡፡ ለሚወዷቸው ያገለግላሉ፡፡ ግን ደስተኞች ናቸው፡፡ ለምን ? መንገዱ ፍቅር ነዋ !
አቲዬ ዙሪያውን በረዥም የግንብ አጥር ወደተከበበው ግቢ ገብታ ብትከትምም ዕጣፋንታዋን ግን አላመለጠችውም፡፡ ዕጣፋንታ እኮ ጥላ ነው:: በዙሪያህ ያለውን ችግርና መከራ ፍንትው
አድርጎ የሚያሳይ ብርሃን ሲጠፋ፣ አብሮ የጠፋ ይመስለሃል እንጂ፣ ቀን የሚሉት ፀሐይ ወጋገኑን
ሲቀድ ከትላንቱ በላይ ደምቆ ካንተ በላይ ገዝፎ ከፊትህ ይመራሀል ከኋላህም ይከተልሀል፡፡
አትዬም ዕጣ ፋንታዋን ስንዝር አላመለጠችውም፡፡ ከባርነት ወደ ፍቅር ባርነት ተቀይሮ በትልቁ
ነፍስ ዘራችበት፡፡ ሰፊውን ግቢ ከጧት እስከ ማታ አፅድታ ትልቁን ቤት ውብት ትደፋበታለች፤
ግቢ ውስጥ ጠበቃት እንጂ፡፡ሰው አጥቶ፣ ውርማ ውጦት የነበረውን የወይዘሮ እጥፍወርቅ ግቢ
የወይዘሮ እጥፍወርቅን ሆቴልም ቀጥ አድርጋ የያዘችው አቲዬ ራሷ ነበረች፡፡
የሆቴሉን እንጀራ ሙሉ በሙሉ ትጋግራለች፡፡ የአልቤረጎዎቹን አንሶላዎች ታጥባለች፡፡ እንደዛም
ሆኖ በጣም ደስተኛ ነበረች፡፡ ወይዘሮ እጥፍወርቅ ደግ ሴት ነበረችና ምንም በደረግላት ይገባታል፤የአቲዬ ባርነት ጣፋጭ ነበር፡፡ መሀተመ ጋንዲ ወደ ወይዘሮ እጥፍወርቅ ግቢ ጎራ ቢሉ ኖሮ፣ "ነመስቴ…እኛም የታገልነው ለዚህች አይነቷ ባርነት ነበር በርቱ!” ብለው የሚሄዱ ይመስለኛል!
በእርግጥ ወይዘሮ እጥፍወርቅ አቲዬን እንጀራ ጋግሪ አላለቻትም፡፡ ራሷ አቲዬ ለሆቴሉ እንጀራ
ግዥ እየተባለ በቅን የሚወጣውን ብር ስትመለከት፣ “ምጣድ ግዙልኝ ሪሴ እጋግራለሁ" አለች እንጂ፡፡ የሆቴሉን አንሶላ፣ “እጠቢ ያላት ማንም አልነበረም፡፡ አጣቢዋ ስትጨማለቅ ስታያት አቲዬ የኔ የልብ ሰው፣ “ምነው እቴ ሰው የሚታኛበት እይደለም እንዴ” አለችና አጇን ሰቅስቃ
ገባችበት፡፡“አቦ የእጥፍወርቅ ቤርጎ እንሶላው ብትል ፎጣው እንዴት ይጸዳል” እስኪባል፡፡ የወይዘሮ እጥፍወርቅ ልብ አቲን በልጅነት መንበር ላይ ወስዶ አስቀመጣት፤ እኔንም የልጅ ልጅነት !!
ግቢው የእኔ ነበር፡፡ እንዳሻኝ የምሆንበት ግዛቴ፡፡ የሳሎኑ ዕቃ የእኔ ነበር፡፡ ጆሮ ጭው የሚያደርግ ዋጋ የተከሰከሰበት ሶፋ ላይ ሸንቼበታለሁ፣ ወተት ደፍቼበታለሁ፡ አቀርሽቼበታለሁ፡፡ ለዓይን የሚያሳሳውን የቡፌ ዕቃ እንኮታኩቼዋለሁ፡፡ የወደዘሮ አጥፍወርቅን ባለ አልማዝ ፈርጥ የአንገት ሀብል ከእንገቷ ላይ በጣጥሼዋለሁ፡፡ (የዚህ ሀገር ወርቅ አንጥረኛ አይሰራውም ተብሎ ተቀምጦ ቀረ…) የፋናዬን (እህቴ ማለት ናት - የወይዘሮ እጥፍወርቅ ልጅ) ቀይና ውብ ፊት ቦጫጭረዋለሁ፣ ፋኒዬን እንደ ህፃን ልጅ ነበር የማስለቅሳት፡፡
አትዬ ስትነግረኝ ፋናዬ ከትምህርት ቤት ስትመጣ ቦርሳዋን እንዳዘለች እኔ ላይ ትጠመጠምና ድበድብ ነው፡፡ ሱቅ የተሰቀለ አሻንጉሊት ካየች፣ የሕግን ልብስና መጫወቻ ዓይኗ ውስጥ ከገባ፡ ለእኔ ለመግዛት ከእናቷ ጋር ብር ስጭኝ አልሰጥም” ጦርነት ነው::
የእናቴ ንፁህ ልብ እንደስፖንጅ ፍራሽ በሕይወቴ መንገድ ላይ ተነጥፎ የዛች ቅፅበት የነበረ
👍24❤5