አትሮኖስ
280K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
472 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቀስ_ብሎ_ይቆማል


#ሰባት


#በአሌክስ_አብርሃም


....“አብርሽ እንቅልፌ መጣ” አለች ትልልቅ ውብ ዓይኖቿን እያንከባለለች (አሄሄ እንቅልፍ ሲመጣ እንደዚህ ነው እንዴ ?
ይህቺ አይነቷ መስለምለም የሌላ ጉዳይ ናት)

“ትንሽ እናውራ ናፍቀሽኛል”

“ከመቼ ጀምሮ ነው ወሬ የወደድከው ግን ?" አለችኝ። ትዝ ሲለኝ ለካ ለሙና ዝምተኛ ልጅ ነበርኩ
(ስምንተኛው ሺ አሉ እኚያ ሰውዬ)። እጄን ይዛ እየጎተተች ወሰደችኝ። መኝታ ቤት እንደገባን መሀል ሜዳው ላይ ቆማ ልብሷን በቁሟ ብትጥለው ማታ እኔ መኝታ ቤት ፀሐይ ፏ ብሎ ወጣ። ፀሐይ
ከምስራቅም ከምዕራብም ሳይሆን፣ በቃ ከልብስ ውስጥ ፍንትው ብሎ ወጣ። እስቲ አሁን እዚህ ፀሐይ ላይ ቆሞ የማይፍታታ ወንድ የት አባቱ ሄዶ ሊፍታታ ነው ? ሲጀመርስ ምናባቱ ሊሰራ ወደዚች ምድር መጣ ? ቀስ ብዬ ልብሴን ማወላለቅ ጀመርኩ። አወላለቄ ከመንቀርፈፉና ከፍርሃቴ ብዛት፣
“ልብስህን አውልቅና አርባ ጅራፍ ትሞሸለቃለህ” የተባልኩ እንጂ ውብ ፍቅረኛዬ ጋር ልተኛ የምዘጋጅ አልመስልም ነበር። የአልጋ ልብሱን ወደታች ገፈፍኩት፣ ብርድ ልብሱን፣ አንሶላውን፣ መቃብሬን የምቆፍር ነበር የመሰለኝ።
ቀስ ብዬ አንሶላዬ ውስጥ ገባሁና (ሙና ገና ከመግባቴ እንደ መዥገር ተለጠፈችብኝ ምን አስቸኮላት ለመርዶ) አንሶላና ብርድልብሱን ወደላይ ስቤ ስደርብ የመቃብር አፈር በላዬ ላይ የመለስኩ መሰለኝ።

“ውይ አፈንከኝ የተሸፋፈንበትን ብርድ ልብስ ገለጠችው፡፡ ገብቶኛል በነዛ ዓይኖቿ እየተስለመለመች የፈራሁትን አጀንዳ ልትከፍት ነው። ተንጠራርቼ መብራቱን አጠፋሁት፤ ትልቅ ስህተት ! ሙና መብራት ሲጠፋ በብርሃን የፈራሁትን በጨለማ ልዘምትበት መስሏት የበለጠ ተጠጋችኝ፡፡ ሰውነቴ ላይ
ከመጠበቋ ብዛት ሁለት ሰውም እንድ ሰውም ሳይሆን ግማሽ ሰው መሰልን። አንድ እግሯን ታፋዬ
ላይ ደርባ ተጠመጠመችብኝ። አሁን እንግዲህ .. አርማጌዶን !!

እና ለምን እንደምወድህ ሳልነግርህ አረሳሳኸኝ ሙና በጨለማው ውስጥ አንሾካሾከች።
“ለምንድን ነው ?"
እርጋታህ ! ማንም ወንድ እዚህ ድረስ ይታገሳል ብዬ አስቤ አላውቅም። ሰምቼም አላውቅ። ልዩ እኮ ነህ አብርሽ … እሟ” (ምኔን እንደሳመችኝ እኔጃ) እኔኮ ግራ የሚገባኝ ካለሥማችን ስም እየሰጡ ለምን ጨዋ ያደርጉናል ?! ኧረ የቸጎረቸግሮን ነው ቀዝቀዝ ያልነው(እስካሁን አገር ሰላም ቢሆን በሩጫ ሞያሌ
ደርሰን ነበር አሉ ጋሽ ምትኩ)። ስለጋሽ ምትኩማሰብ ጀመርኩ። ጋሽ ምትኩ በሕፃንነታችን ሰፈራችን ውስጥ ይኖሩ የነበሩ የድሮ ወታደር ናቸው። ቆይ ግን ጋሽ ምትኩ የፂማቸው አበቃቀል አይገርምም? ልክ እንደ ፍየል ፂም ሹገጥ ያለች ሆና ደረታቸውን ትነካለች። ጋሽ ምትኩ እኮ በሕፃንነቴ ከእማማ ሊባኖስ ፅድ ላይ ወድቄ የግራ ክንዴን ተሰብሬ አሽተው አድነውኛል፡፡ የግራ ከንዴ ስል ትዝ አለኝና ላነሳው ስሞክር ሙና ተኝታበታለች። ሙና ትዝ አለችኝ። አሁንም እንገቴን እየሳመችኝ ነው። ሙቀቱ
ውቀት አይደለም፡፡ እሳት ተነስቷል እዚህ ብርድ ልብስ ውስጥ፡፡ (ደመዟን የሚከፍሏት እሳት ነው
እንዴ፤ አጠራቅማ ይዛው መጥታ ይሆን…)

ቆይ ግን የዓለም ሙቀት መጨመር ... ብዬ ሌላ ሐሳብ ውስጥ ልገባ ስል ድክ…ም ባለ ድምፅ የሆነ መካከለኛው አፍሪካ አካባቢ ቆማ ስሜን የጠራችው እስኪመስለኝ በራቀ ድምፅ…

“አ..ብርሽ” አለችኝ።

“አብርሽ የለም ! አሁን ወጣ” ማለት አምሮኝ ነበር።

“እወድሃለሁ" ውይ !ይሄ ሁሉ ጥሪ ለዚች ነው ? ብዬ መውደዷን ለመንኳስስ ብሞከር አልተሳካልኝም።
እኔም እንደ ራሴ ነው የምወድሽ ሙና” ብዬ ዓየር እስኪያጥራት ከንፈሯን ሳምኳት። እግሯ ተንቀሳቀሰ (ወዴት ነው…ባለህበት ቁም ብያለሁ የሙና ግራ እግር !) እንግዲህ ፊት ሲሰጧቸው…
በእንግሊዝኛ እንዲህ አለችኝ፣
'አር ዩ ሬዲ ?” እንደው አማርኛችን ወሲብ ላይ ሐሞቷ የሚፈስሰው ለምንድን ነው ? ወሲብ ነክ
ላይ እንግሊዝኛ ይቀለናል። “ሴክስ” “ኪሲንግ" ቋንቋችን መከበር አለበት !በራሳችን ቋንቋ የራሳችንን ጉድ ማውራት አለብን ! የራሱ ጉዳይ ... ! አሁን በዚህ ሰዓት አማርኛ ፤ ምንኛ ላይ
ምርምር ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው ?ቁም ነገሩ በአማርኛ ይሁን በእንግሊዝኛ ይሁን በጀርመንኛ ወላ በእብራይስጥ ትናገረው እኔ እንደሆንኩ እንትን ላይ የለሁበትም !!
እንግዲህ ሙና ከመጠጋቷ ብዛት እልፉኝ ሙሄድ ቀራት፣ እኔ ዝም!
ሳመችኝ
ዝም
ነካካችኝ
ዝም
አፍ አውጥታ “በቃ እናድርግ" አለች
ዝም!
በመጨረሻ ሰውነቷን ከሰውነቴ ቀስ እድርጋ አላቀቀች። ሰውነታችን ሲላቅቅ ፕላስተር ከሆነ ነገር ላይ
ሲላጥ የሚያሰማውን ዓይነት ድምፅ አሰማ። በላባችን አጣብቆን ነበር፡፡ ምንም ላልተፈጠረ ቅጡ ይሄ
ሁሉ ላብ በከንቱ። ሙና ተንጠራርታ መብራቱን አበራችውና ቀጥ ብላ ፊቴን ተመለከተችኝ አቤት ስታስፈራ፡ አቤት ስታምር..

ምንድን ነው የሆንከው ስለኔ የሰማኸው መጥፎ ነገር አለ ?አለችኝ በሚንቀለቀል ቁጣ። ዝም ብዬ አየኋት። ዝም ብላ አየችኝ። ፊቷ ላይ ግራ መጋባት ያሁን ፍርሃት ያልገባኝ ስሜት ያንዣብባል።

ሌላ ሴት ጋር ጀምረኸል አይደል ግልፁን ንገረኝ ?” ቁጣዋ ተንቀለቀለ። እኔ ደግሞ እፌ ተያያዘ ዝም፡
ብርድ ልብሱን በንዴት ገፍፋ ወደዛ ጣለችውና ቤቱን በሚያደበላልቅ ጩኸት፣

“ምንድን ነው ችግርህ፣ ለምን ትዘጋኛለህ … ላንተ እንዲህ መሆኔ ለሁሉም ወንድ እንደዚህ የምሆን
ልክስክስ እንድመስልህ አድርጎህ ነው ወይስ … ለምን ትገፋኛለህ፣ ለምን ዝቅ አድርገህ ታየኛለህ
አንድ ቀን እንደ ሰው፣ እንደ ፍቅረኛ አይተኸኝ አታውቅም። ሁልጊዜም ሴትነቴን፣ ከብሬን ዝቅ አድርጌ ላንተ ነው የኖርኩት። ስንት እና ስንት ርቀት ተሰቃይቼ የምመጣው አንተን ብዬ ምንድነው ችግርህ ንገረኝ፣ አስጠላሁህ ? ያስቀየምኩህ ነገር አለ ? ለምንድነው እንደዚህ ቅዝቅዝ
የምትለው ? ችግር ካለ ንገረኝ። ልርቅህ አልፈልግም፡ አፈቅርሃለሁ … አፈቅርሃለሁ ... አፈቅርሃለዉ
እንባዋ ተዘረገፈ። ከወገቤ በላይ ራቁቴን እንደሆንኩ አልጋው ላይ ተቀመጥኩ። ሙና ሁሉም ሰውነታ
ተራቁቶ ነበር። የአልጋ ልብሱን ላለብሳት ስምከር ከነእጄ ወደዛ ወረወረችው፤ ፈራኋት። ተፋጠጥን!

አሁን ነው ጊዜው!እውነት እርቃኗን አልጋ ላይ ይቻት ይህ በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ወሳኝ ጊዜ ነው። አለ አይደል ላይመለሱ በስደት ከአገር ሊወጡ ዞር ብለው ተራራ ሸንተረሩን፣ ያደጉበትን ሰፈር የሚመለከቱባት ቅፅበት። ሙና ለእኔ ሰፈሬ ናት፤ ፍቅር እየተራጨሁ ፍቅር ያደግኩባት። አለ አይደል የደከመች እናት በመጨረሻ እስትንፋሷ ከአልጋ ላይ ሽቅብ ልጇን ተመልክታ በተስፋ መቁረጥ ዓይኖቿን የምትጨፍንበት፣ አለ አይደል አብሮን የተፈጠረ አብሮን ያደገና የኖረ እግር፣ እጅ በሆነ በሽታ ምክንያት ሊቆረጥ የመጨረሻው ማደንዘዣ ሲሰጥ … ይሄ ጊዜ ያ ሁሉ ነው። በዚህች ቅፅበት ሴት
ብትሄድ ሴት ትተካለች አይባልም። ሙና ሴት ብቻ አይደለችም። ማንም ሴት ላፈቀራት ወንድ መልዓክ ምትሆንባት ነጥብ አላት። “ማንም ሴት በአካል የማይደገም ግልባጯን ልብ ላይ የምታትምበት ቅፅበት አለ፡ ጣጣ የለኝም የሚለውና የምትለው ሰዎች ሁሉ ጣጣ የሚኖርባቸው፡ ውጋት የሚለቅ ቅፅበት አለ ይሄው ያ ቅፅበት።.

ሙናን ወደኔ ስቤ ከንፈሯን ሳምኳት። የሆነ በቀል የሚመስል አሳሳም። ልቧ ሳይፈራ አልቀረም።
በፍርሃት አየችኝ። ፊቴ ላይ ምን እንዳየች እንጃ።

"ሙና"

"ወዬ አብርሽ” ፈርታለች። ለምን እንደፈራች አላወቅም። ብቻ እንድ ነገር መኖሩን የጠረጠረች
ይመስለኛል።
👍42
#ዶክተር_አሸብር


#በአሌክስ_አብርሃም


#ሰባት


ቁጥር ስፍር የሌለው ሕዝብ ለቅሶ ለመድረስ የወይዘሮ እጥፍወርቅን ግቢ አጥለቀለቀው:: ቀስ
በቀስ አስተዛዛኙ እየተመናመነ መጥቶ በመጨረሻ ግቢው ወደ ነበረው ገዝምታ ተመለሰ፡፡ ከሀዘኑ
በኋላ ነገሮች ህልም በሚመስል ሁኔታ ተቀያየሩ። ሀዘኑ ባበቃ በጥቂት ወራት ውስጥ ፋናዬን
ወንድሞቿ ሲዊዲን ወደሚባል ሀገር ወሰዷት፡፡

ፋኒ የእኔ እህት አቲዬን ስማ በተሰበረ ልብ ግቢውን ለቀቀች፡፡ አቲዬ በምድር ላይ ያሏትን ሁለት
ዘመዶች አጣች፡፡ ዛሬም ይሄን ስታወራኝ ዓይኗ ውስጥ ህመም ይንቀለቀላል። ነፍሷ ይቃትታል፣
ዝም ብላ ትቆይና፤

"አሹዋ” ትለኛለች፡፡

“አቤት አቲዩ!"

"ሱዲን የሚሎት ሀገር ወዴት ነው? ፡፡ ስዊዲን ሀገር ቤትና ሕዝብ ተቆጥሮ የሕንዘቡ ቁጥር
ምንትስ ሚሊዮን ደረሰ ሲባል አቲዬ አታምንም፡፡ የስዊዲን ህዝብ ቁጥር አንድ ብቻ ነው ፋናዬ ብቻ !! አቲዬ የዛችን ደግ ሴት ልጅ ፋናዬን እንደ እየሩሳሌም አንድ ቀን ልታያት ፅኑ መሻት ፊቷ ላይ ይንቀለቀላል፡፡

አንዲት እድሜዋ አርባ የሚሆን ሽቅርቅር፡ ሲበዛ ቆንጆ የሆነች ሴትዬ (የወይዘሮ እጥፍወርቅ እህት ናት ይላሉ) ከሁለት ጨምላቃ ሴት ልጆቿ ጋር፣
ወር ሳይሆን ጠብቂ ተብላ
እግዜር ይወቅ ብቻ ግቢውን ትኖርበት ጀመረ፡፡ ሆቴሉ ተሸጠ፡፡ እች ሴት አስቴር ትባላለች፡፡ ምኗም የማይጨበጥ ተልካሻ ሴት ! ከዕድሜዋ ጋር ጦርነት የገጠመች ማቶ !

አንዳንዴ በተረት የሚታወቀው አስማተኛ መስተዋት መኝታ ቤቷ ውስጥ የተቀመጠ ይመስል
ገብታ በወጣች ቁጥር ልብስ የምትቀይር፣ “የሆነ ቦታ በመልክ የምትበልጥሽ ውብ ሴት አለች
እያላት መስተዋቱ፡ ፊቷ ላይ የትራስ ሰንበር ከሚወጣ ኢትዮጲያ ላይ ከሰሜን እስከ ደቡብ
ጫፍ አዲስ ስምጥ ሸለቆ ሲፈጠር የምትመርጥ የውበት ስስታም " የዕለት እንጀራዋ የሰው
ዓይን የሆነ ከንቱ፣ የእጥፍወርቅን ግቢ በባለቤትነት ታስተዳድር ጀመር፡፡

አቲዬን እንደ ሰራተኛ ስለምታስባት ማመናጨቅ የጀመረቻት ገና የሀዘንተኛው እግር ጨርሶ ሳይወጣ ነበር፡፡ እኔንማ ግልገል ሰይጣን አድርጋ ነው የምታየኝ፡፡ በወይዘሮ እጥፍወርቅ የለመድኩትን መዘባነን ታጥቄ ወደ ሳሎን ዘው ስል በቲሸርቴ አንጠልጥላ መሬት ለመሬት እየጎተተች በረንዳው
ላይ የመወርወር ያህል ትጎትተኝና፣ “ማነሽ አንች ልጅ ነይ ወደዛ ውሰጅ ይሄን ልጅሽን !
እንዴ የምን መጨማለቅ ነው እሱ…ሁለተኛ እዚህ ምንጣፍ ሳይ ሲወጣ እንዳላይ!" ብላ እጇን
ታራግፋለች::

አቲዬ ነፍስና ስጋዋ እየተሟገተ መወልወያ ይዛ ትገባና ያበላሸሁት ነገር ካለ ትፈልጋለች። ብዙ
ጊዜ ግን የዚህች ከንቱ ጩኻት ምከንያት አልነበረውም፡፡ ምክንያቷ ሰው አለመፈለግ ነው።
ሰውን በማራቅ ሰላም ይገኝ ይመስል ! ሁካታ ነፍሷን ሀቅ አጉርሳ ዝም እንደማስባል የቀረባትን ሁሉ ታፍናለች፡፡

በዚያ ከወራት በፊት ምግብ ይልከሰከስበት በነበረ ግቢ ውስጥ ጣረሞት ራህብ ያንዣብብ
ጀመረ፤ በፊት ወተት የምትገዛልኝ እጥፍወርቅ ነበረች፡፡ መሶቧ መሶባችን፣ ድስቷም ድስታችን
ነበረ፡፡ እንዲህ ባጭር ጊዜ ከጓዳችን ቁራሽ ዳቦ፣ ንጣይ እንጀራ ይነጥፋል ብሎ ማን አስቦ !

አንዳንዴ ምቾት ያዘናጋል፡፡ ምቾት ስትኖርበት ዘላለማዊ ይመስላል፡፡ ሜዳ ላይ ጥሎህ እንደ
ጉም ሲተን ነው ፊቱ ላይ ቀዝቃዛ ውሀ እንደቸለሱሰት ሰው የምትበረግገው:: ስንቱ ቤተሰብ
ድንገት ከምቾቱ ችግር ተኮርኩሞ ነቅቷል፡፡ ስንቱ ባለስራ ስራውን ተደግፎ፣ ድጋፉ ሲከዳው
ወድቆ ቀርቷል፡፡ ሰንቷ ባለትዳር፣ የባሏ እጅ ሲነጥፍ አብሮ ቅስሟ ተሰብሯል፡፡ አግኝቶ ማጣት
ብሎ ህዝቡ የሚጠራው ይሄንን አይደል ተገኝቶ መጥፋት ቢሉት ይሻል ነበር !

አስቴር አቲየን ታዝዛታለች፣ ታመናጭቃታለች፣ ትልካታለች፣ ግን ብርም ሆነ ምግብ አትሰጣትም፤ የሚገርመው ደግሞ ቤቱ ውስጥ እንጀራ አይጋገርም ወጥም አይሰራም፡፡ እናትና ቦዘኔ ልጆቿ የታሸገ ነገር ይገዙና መኪናውም ውስጥ መንገድም ላይ ይበላሉ ማሸጊያውን ወዳገኙበት ይወረውሩታል፡፡ እነዛን ደማቅ ጽሑፍ ያላቸው የቸኮሌት ላስቲኮች በርሃብ እየተንሰፈሰፍኩ
ቀድጄ የላስኩባቸው ጊዚያት ብዙ ነበሩ ዛሬ ቸኮሌት እንደ መርዝ እጠላለሁ !! እነዛ ባዶ
የፍራፍሬ ጭማቂ ዕቃዎች ስይት ነበሩ ለኔ፡፡ ዘመናዊነት ያደነዘዛቸው እናትና ልጆች ምቾት
ውስጥ የመነኑ የስንፍናና የክፋት ቆብ የጫኑ ርኩሶች ነበሩ፡፡ እንኳን ግቢያቸው ውስጥ ለተጠጉ
ሚስኪኖች፣ እርስ በርሳቸውም የተለያዩ የሰው ከብቶች፡፡

መኝታ ቤታቸውን በየፊናቸው ዘግተው፣ ማንም አራት እግሩን ቢበላ አልሰማንም አላየንም
ብሎ የሚጮህ ጋግርታም የግለኝነት ባሕር ውስጥ የተጠመቁ፡፡ የምዕራባዊያኑን ቆሻሻ ግለኝነት የስልጣኔ አልፋ፣ የዕውቀት ኦሜጋ ያደረጉ ፉዙዎች፡፡ በእንግሊዝኛ እየተለፋደዱ፣ በአማርኛ
የአዕምሮ መቃወስ ውስጥ የተዘፈቁ የቤት ዕቃዎች፡፡ የሞራልም ይሁን የሀይማኖት፣ አልያም ከነፍስ ስልጣኔ የሚመነጭ ጠንካራ ስብዕና የሌለው ኢትዮጲያዊ፣ ውጭ ሀገር ደርሶ ሲመለስ ምን አይነት አስቃቂ ማቶንት ውስጥ እንደሚነከር የታዘብኩት በእነዚህ ከንቱዎት ነበር፡፡እናታቸው ሀያ ዓመት፣ ልጆቹ እየሄዱ እየመጡ ከአስር ዓመት በላይ አሜሪካ ኖረዋል፡፡ አስቴር
ታዲያ ለዓመታት ከኖረችበት አሜሪካ ምን ይዛ መጣች? ሰምቻታለሁ ለመጣ ለሄደው፣

“አበሻ ስራ አይወድም፣ ነጮቹ እኮ ለሰዓት ያላቸው ክብር ለስራ ያላቸው… "

“አበሻ የተመጣጠነ ምግብ አያውቅም ማድፋፋት፣ ጥሬ ከብስል ማጋበስ…"

“አበሻ መች ንፅህና ይወዳል ነጮቹ እኮ."

"ኤዲያ የሀበሻ ወንድ መች ሴት ያከብራል ነጮቹኮ”

“የአበሻ ልጅ አስተዳደግ.…

የአበሻ ሕክምና ደግሞ ራሱ በሽታ ነው፡፡ ነጮቹ እኮ”

አበሻ ገንዘብ ከመሬት የሚታፈስ ነው የሚመስለው፡፡ ዓይኑን በጨው አጥቦ፣ ዶላር ላኩ ነው
ነጮቹ እኮ አስራ ስምንት ዓመት ከሞላቸው… "

ነጭ የባርነት ቀንበር ጫንቃዋ ላይ ተሸክማ የምትደሰኩር ቱልቱላ፡ ከየትም የፈለፈለቻቸው ልጆቿ
በአስተዳደግ ይሁን የግል ባህሪ ምን ዓይነት እናት አንደሆነች ጮኸው እያወጁ፣ “ዓይናችሁን
ጨፍኑ ላሞኛችሁ” ትለናለች፡፡

የነጮቹ ፅንፍ የለሽ ውክቢያ ዕድሜዋን ሙሉ ያጨቀባት የታላቅነት አባዜ አበሻን በበጎ እንዳታይ እንደ ጋሪ ፈረስ ቀይዷት፣ ለእግዜር ሰላምታ የቀረባት ሁሉ የፈጋችበትን ዶላር የሚነጥቃት
እየመሰላት ስጋዋ ያልቃል፡፡ ልጆቿም በየአጥሩ ጥግ ከሚያናንቁት የአበሻ ወንድ ጋር ሲሳሳሙ እና በየመሸታ ቤቱ ሲዳሩ ከማምሸት ውጭ የፈየዱት ተዓምር የለም፡፡ በነፃይቱ ሀገር ኖረው ለመጡ የስልጣኔ ጥጎች፣ የከንፈር ዋጋው የዶላሩን ያህል ውድ አይደለም፡፡ እነዛ ወንበር ስበው በክብር ሴትን ልጅ የሚያስቀምጡ ነጫጭ ወንዶች የሴትነትን ክብር እየሰበኩ ሰብዓዊነታቸውን ከእግራቸው ስር እንደጨፈላለቁት ለመረዳት የጋረዳቸው ነጭ ደመና አይፈቅድላቸውም

ለእነዚህ የስልጣኔ ርዝራዦች የሰው ልጅ ስለክብሩ መኖር፣ ስለማተቡ ዓለማዊነትን በልክ ይሁን ማለቱ ተራ መኮፈስ ነው:: ቦርሳቸውን ከመከፈት፣ ለማንም አላፊ አግዳሚ እግራቸውን መከፈት ይቀላቸዋል፡፡ ምክንያቱም “ዶላር የተከበሩት የነጮች ውድ ቅርስ” ሲሆን ሰውነታቸው ግን
የርካሾቹ፣ የሰነፎቹ፣ ያልተማሩት፣ ሥራ የማይወዱት፣ ብር ከመሬት የሚታፈስ የሚመስላቸው
አበሾች ርካሽ ንብረት ነው፡፡

በዚህ ፍልስፍና አገሩን አጥምቀውት አገሬው ፈረንጅ ባል ፍለጋ ሲራኮት ሲታይ ምን ይገርማል !

አቲዬ አንድ ቀን እየፈራች ሴትየዋን አናገረቻት፤ “እትዬ ወጥቼ አንዳንድ ስራ ልሰራ ነበረ ምናልባት ከፈለጉኝ ብዩ ነው…"
👍312