#ነበረ!
እንደነገርኩህ ነው የለም የምነግርህ
ብቻ ግን ይኸውልህ ፥
ፊቱ እህል ቀርቦ መብላት ያላወቀ
በርሀብ የራደ በችግር ያለቀ ፥
ለእንቆቅልሽ መፍቻ የመሰረት ያለ
ሰንደቃ'ላማ ፊት ሀገሩን 'ሚረሳት አንድ ወጣት ነበረ!
ውሉ የጠፋበት ዳቦ መግዣ ያጣ
ለእርዳታ ስንዴ ገንዘብ የሚያዋጣ፤
ፅድቅ ይሉት ኩነኔ አጣምሮ ሚሰፋ
ቀኑ እንዳይገፋው፥ ቀኑን የሚገፋ!
ካልሲ ለጠየቀው ጫማ እየጨመረ
አፀድ ስር ቁጭ ብሎ እርቃኑን የቀረ
አንድ ወጣት ነበረ!
እንጀራ አቅርቦ መብላት የሚያስጠፋው
እየቀለድክለት ቀልድክ የሚያስከፋው ፣
መርዶ እየነገርከው ጮቤ ሚያሰረግጠው
ተስፋ'ለህ ስትለው ተስፋ ሚያሰቆርጠው፣
መድሃኒት ፍለጋ እንዳቀረቀረ፥ አጎንብሶ የቀረ
አንድ ወጣት ነበረ!
ብርቱ! ሆነ ስንል፤ ደ'ሞ እየደከመ
መዳኑ ነው ሲባል፤ ብሶ እየታመመ፥
መውደቁ ነው ስንል፤ ድሆ እየተነሳ
ሊታወስ ነው ሲባል፤ ሰርክ እየተረሳ፥
ብቻውን የቀረ፣
አንድ ወጣት ነበረ!
ከእንቅልፉ ሲነቃ፤ እንቅልፍ የሚጥለው
ድነሀል ስትለው፣ ድህነት! የገደለው፤
ከመሔዱ ብዛት መንገድ ያከሰረው
ከመንገዱ ይልቅ መድማት ያስተማረው፣
በመንገድ በመድማት በመሔድ የቀረ፣
የማርያም ንግስ እለት ደጃፏ ቁጭ ብሎ ማርያምን ሚረሳት አንድ ወጣት ነበረ!
"በምድር ዘላለም" አቀርቅሮ የቀረ፣
ነበረ የሚለኝ አንድ ወጣት ነበረ!
በጠራራ ፀሀይ ይነጋል እያለ ጨረቃን በመስደብ ብዙ አመት የኖረ፣
አንድ ወጣት ነበረ!
በየ እግረ መንገዱ "በተስፋ" የኖረ፣
እስታውሰኝ የሚለኝ አንድ ወጣት ነበረ!
በአዳም ፊርማ ላይ አሻራ ፍለጋ አቀርቅሮ የቀረ፣
ቀና በል የሚለኝ አንድ ወጣት ነበረ!
እንጀራ ለመብላት፤ እንጀራ የሸጠ
ከሚዲያ ጀርባ ሊቀበል የሰጠ፣
ዝንት አለም ሲጠላ ሲገፋ የኖረ
ሰርአተ ቀብሩ ላይ ምስኪን ነበር እኮ አፈር በልቶት ቀረ፤
ብለው ማያወሩለት አንድ ወጣት ነበረ!
በአንድ ወጣት ታሪክ ተመስጦ የቀረ፣
አንድ ወጣት ነበረ እያለ የሚፅፍም አንድ ወጣት ነበረ!
ነበረ!
ነበረ!!
ነበረ!!!
🔘ዩሐንስ ስለሺ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እንደነገርኩህ ነው የለም የምነግርህ
ብቻ ግን ይኸውልህ ፥
ፊቱ እህል ቀርቦ መብላት ያላወቀ
በርሀብ የራደ በችግር ያለቀ ፥
ለእንቆቅልሽ መፍቻ የመሰረት ያለ
ሰንደቃ'ላማ ፊት ሀገሩን 'ሚረሳት አንድ ወጣት ነበረ!
ውሉ የጠፋበት ዳቦ መግዣ ያጣ
ለእርዳታ ስንዴ ገንዘብ የሚያዋጣ፤
ፅድቅ ይሉት ኩነኔ አጣምሮ ሚሰፋ
ቀኑ እንዳይገፋው፥ ቀኑን የሚገፋ!
ካልሲ ለጠየቀው ጫማ እየጨመረ
አፀድ ስር ቁጭ ብሎ እርቃኑን የቀረ
አንድ ወጣት ነበረ!
እንጀራ አቅርቦ መብላት የሚያስጠፋው
እየቀለድክለት ቀልድክ የሚያስከፋው ፣
መርዶ እየነገርከው ጮቤ ሚያሰረግጠው
ተስፋ'ለህ ስትለው ተስፋ ሚያሰቆርጠው፣
መድሃኒት ፍለጋ እንዳቀረቀረ፥ አጎንብሶ የቀረ
አንድ ወጣት ነበረ!
ብርቱ! ሆነ ስንል፤ ደ'ሞ እየደከመ
መዳኑ ነው ሲባል፤ ብሶ እየታመመ፥
መውደቁ ነው ስንል፤ ድሆ እየተነሳ
ሊታወስ ነው ሲባል፤ ሰርክ እየተረሳ፥
ብቻውን የቀረ፣
አንድ ወጣት ነበረ!
ከእንቅልፉ ሲነቃ፤ እንቅልፍ የሚጥለው
ድነሀል ስትለው፣ ድህነት! የገደለው፤
ከመሔዱ ብዛት መንገድ ያከሰረው
ከመንገዱ ይልቅ መድማት ያስተማረው፣
በመንገድ በመድማት በመሔድ የቀረ፣
የማርያም ንግስ እለት ደጃፏ ቁጭ ብሎ ማርያምን ሚረሳት አንድ ወጣት ነበረ!
"በምድር ዘላለም" አቀርቅሮ የቀረ፣
ነበረ የሚለኝ አንድ ወጣት ነበረ!
በጠራራ ፀሀይ ይነጋል እያለ ጨረቃን በመስደብ ብዙ አመት የኖረ፣
አንድ ወጣት ነበረ!
በየ እግረ መንገዱ "በተስፋ" የኖረ፣
እስታውሰኝ የሚለኝ አንድ ወጣት ነበረ!
በአዳም ፊርማ ላይ አሻራ ፍለጋ አቀርቅሮ የቀረ፣
ቀና በል የሚለኝ አንድ ወጣት ነበረ!
እንጀራ ለመብላት፤ እንጀራ የሸጠ
ከሚዲያ ጀርባ ሊቀበል የሰጠ፣
ዝንት አለም ሲጠላ ሲገፋ የኖረ
ሰርአተ ቀብሩ ላይ ምስኪን ነበር እኮ አፈር በልቶት ቀረ፤
ብለው ማያወሩለት አንድ ወጣት ነበረ!
በአንድ ወጣት ታሪክ ተመስጦ የቀረ፣
አንድ ወጣት ነበረ እያለ የሚፅፍም አንድ ወጣት ነበረ!
ነበረ!
ነበረ!!
ነበረ!!!
🔘ዩሐንስ ስለሺ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
❤8👍2👏1