#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ቀና ሰው
በ1815 መሴ ቻርለስ ብየንቬኑ መሪል የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ነበሩ፡፡ እድሜያቸው 75 ሲሆን የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ሁነው የተሾሙት በ1806 ዓ.ም ነበር፡፡ ጳጳሱ ወደ ሀገረ
ስብከታቸው ሲመጡ እህታቸው ወ/ት ባፕቲስታን አብረዋቸው ነበር
የመጡት:: እህትዬዋ ምንም እንኳን ትዳር ባይዙም እድሜ የጠገቡ ሲሆኑ ወንድማቸውን በአሥር ዓመት ይበልጧቸዋል፡፡
ከጳጳሱ ቤት ውስጥ ሌላም ሴት ነበሩ፡፡ እኝህ ሴት የወ/ት ባፕቲስታን እኩያ ናቸው:: ሴትዬዋ ወ/ሮ ማግልዋር ይባላሉ:: ሴትዮዋ ቀደም ሲል የሌላ ሰው አገልጋይ ሆነው ሠርተዋል፡፡ አሁን ደግሞ የወ/ት ባፕቲስታንና
የጳጳሱ ቤት ጠባቂ ሁነው ተቀጥረው ይሠራሉ፡፡
ጳጳሱ ከሀገረ ስብከታቸው እንደደረሱ በሀገሩ ደምብ መሠረት ከፊልድ ማርሻል ቀጥሎ ያለውን ሹመት ይሰጣቸዋል፡፡ የክፍለ ሀገሩ መሪና የማዘጋጃ ቤቱ ሹም ከቤታቸው ሄደው «እንኳን ደህና መጡ» በማለት እጅ ይነስዋቸዋል፡፡ አቡኑም በተራቸው ከዚያ ለተገኙ ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ቡራኬ ይሰጣሉ፡፡ የከተማው ሕዝብ በአጠቃላይ አዲስ የተሾሙለትን ጳጳስ
ለማየት በጉጉት ሲጠባበቅ ነበር፡፡
የጳጳሱ ቤት ከአንድ ሆስፒታል አጠገብ ሲሆን ቤቱ እጅግ በጣም
ሰፊና ያማረ ነው:: ሆስፒታሉ ይገኝ የነበረው ከረባዳ ሥፍራ ላይ ሲሆን ግቢው እንደ ጳጳሱ ቤት አይሰፋም:: ጳጳሱ ወደዚያ ሲሄዱ በሦስተኛው ቀን ሆስፒታሉን ይጎበኛሉ:: ከጉብኝቱ በኋላ የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ ከቤታቸው
ድረስ መጥቶ እንዲያነጋግራቸው ይጋብዙታል:: አስተዳዳሪው ከጳጳሱ ቤት ይሄዳል::
በሆስፒታሉ ውስጥ «ስንት በሽተኞች አሉ? » ሲሉ አስተዳዳሪው ጠየቁ::
«ሃያ ስድስት» ሲል መለሰላቸው::
«ልክ እኔ እንደቆጠርኳቸው ናቸው አልተሳሳትክም» አሉ ጳጳሱ::
ጳጳሱ የቤታቸውን አዳራሽ በዓያናቸው ቃኙ:: አመለካከታቸው
አዳራሹን በዓይነ ሕሊናቸው የሚለኩና የሚያከፋፍሉ ይመስሉ ነበር ።
«ይህ ክፍል ብቻ ሀያ አልጋ ይይዛል» አሉ እርስ በራሳቸው? ሲነጋገሩ።
ከዚያም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚቀጥለውን ተናገሩ::
«ወዳጄ የምለውን አጢነህ ስማኝ፡፡ እዚህ ቦታ አንድ ስህተት የተፈጸመ ይመስላል፡፡ እናንተ አምስት ወይም ስድስት ጠባብ ክፍሎች ናቸው ያሏችሁ::
ከዚያ ውስጥ ሃያ ስድስት ሰዎች ይተኛሉ፡፡ እኛ እዚህ ሦስት ሰዎች ብቻ ነን፡፡ ያለው ቦታ ግን ለስልሣ ሰው የሚበቃ ነው:: ታዲያ ይህ የአደላደል ስህተት አይመስልህም? የእኔን ቤት አንተ ብትወስድ ፤ የአንተን ደግሞ እኔ
ብወስድ ይሻላል፡፡›
በሚቀጥለው ቀን ሃያ ስድስቱ በሽተኞች ወደ ጳጳሱ ቤት ተዛወሩ፡፡
ጳጳሱም ሆስፒታሉን ተረከቡ:: ወሬው በከተማው ተነዛ፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጳጳሱን በጎ ምግባር በመከተል ለበጎ ተግባር የሚውል እርዳታ ይጎርፍ ጀመር፡፡ በየቀኑ ከጳጳሱ ቤት በር የሚያንኳኳ ሰው ቁጥር እየበዛ
ሄደ፡፡ ሆኖም የሚመጣው ሰው ሁሉ እርዳታ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን ምፅዋት ለመቀበልም ነበር፡፡ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጳጳሱ የብዙ ችግረኞች ቀላቢ፣ ምፅዋት ሰጪና ገንዘብ ሰብሳቢ ሆነ፡፡ ብዙ ገንዘብም ከጳጳሱ እጅ እየገባ ለድሃ ይሰጥ ጀመር:: የሚገኘው ገቢ ግን ልክ ከደረቀ
አፈር ላይ እንደሚፈስ ውሃ ገና ከመገኘቱ ወጪ ሆኖ በቶሎ ያልቃል፡፡ጳጳሱ ገንዘብ ቢያገኙም ከተገኘው ገቢ ጥቂቱን እንኳን ለራሳቸው ወደኋላ አላሉም፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው የራሳቸውንም ይዞ ይሄድ ጀመር፡፡
ጳጳሳትን ከስማቸው አስቀድሞ ንጽህናቸውን ለማረጋገጥ ብፁዕ ወቅዱስ እያሉ መጥራት የተለመደ ቢሆንም በዚያ አካባቢ ይገኙ የነበሩት ነዳያን ፍቅራቸውንና ቅርበታቸውን ለመግለጽና የጳጳሱን ደግነት ለማውሳት ብፁዕ ወቅዱስ በማለት ፈንታ «አባ ደጉ» እያሉ ይጠርዋቸዋል፡፡
እኚህ ደግ ሰው በ1815 ዓ.ም ምንም እንኳን 75 ዓመት ቢሞላቸወም ከስልሣ ዓመት በላይ የሆናቸው አይመስሉም ነበር:: ቁመታቸው እጅግም ረጅም ሳይሆን መጠነኛ ሆኖ ሰውነታቸው ደልዳላ ነው:: ክብደታቸውን
ለመቆጣጠር በእግር መሄድ ያዘወትራሉ:: ሲራመዱ መሬት በኃይል እየረገጠ ከወገባቸው ትንሽ ጎበጥ ይላሉ::
የልጅ ፈገግታ በተጎናጸፈ አንደበት ሲናገሩ ከግርማ ሞገሳቸው ብዛት
የሰማቸው ሁሉ የመንፈስ እርካታን ያገኛል:: ከመላ ሰውነታቸው ደስታ
የሚንፀባረቅ ይመስላል፡፡ ደግነት የተቆራኘው አካላቸውና ወተት የመሰለው ጥርሳቸው ፈገግ ሲል እኚያ «ጨዋ ሰው ፤ እድሜ የተቸረ ሽማግሌ፤ ደግ ሰው» በማለት ለደጋግ ሰዎች የምንሰጠው ቅጻል ሁሉ በእኚህ ሰው ላይ ጎልቶ ይታያል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ላያቸው እንኳን ስለብቃታቸውና
ስለደግነታቸው አይጠራጠርም:: ነገር ግን አንድ ሰው ለጥቂት ሰዓት ከጳጳሱ ጋር ቢቆይና በአሳብ ባህር ተወጠው ቢያያቸወ ቀስ በቀስ
መለወጣቸውን ይገነዘባል፡: ግርማ ሞገሳቸው በቃላት ለመግለጽ በማይቻል ሁኔታ ያስፈራል፡፡ ሰፊውና ኮስታራው ፊታቸው እንዲሁም ሻሽ የመሰለው
ፀጉራቸው ክብር የተጎናጸፈ ለመሆነ በግልጽ ይታያል:: ግርማ ሞገስ ከውስጣቸው እየፈለቀ ሲወጣ የሚያልቅ ቢመስልም የእንዐባራቂነት ኃያል
እንዳለው አያጠራጥርም:: እንዲያውም አንድ ሰው ሁኔታቸውን በጥሞና ሲመለከት «አንድ መልአክ በፈገግታ አጊጦ ያየኛል» የሚል ስሜት
ያድርበታል፡፡ እኚህ ሰው የሚያሰላስሉት ስለ ክቡር ጉዳይ እንጂ ስለርካሽ ነገር ላለመሆኑ ጥርጣሬ አይገባውም::
ጸሎት ማድረስ፤ ምፅዋት መስጠት፧ የመንፈስ ስቃይ የደረሰበትን ማጸናናት፤ ወንድማማችነትን መስበክ፤ ራስን ለሌሎች መስዋዕት ማድረግ፤
በእምነት ራስን መግራት የጳጳሱ የእለት ተዕለት ኑሮ ሲሆን ይህም ኑር በበጎ አሳብ፤ በምርጥ ቃላትና በበጎ ተግባር የተሞላ ነበር፡፡
ክረምት ይሁን በጋ ሁለቱ ሴቶች ሲተኙ ብፁዕነታቸው ወደ ጓሮ
ሄደው አትክልት ውስጥ ለአንድ ወይም ለሁለት ሰዓት ፈጣሪያቸውን በማሰብ ከዚያ ካልቆዩ ኑሮአቸው የተሟላ አይመስላቸውም:: አሳባቸውን
ሰብስበውና የመንፈስ እርጋታን አግኝተው የምሽቱን ሰላምና ፀጥታ ከሰዎች የመንፈስ እርካታ ጋር እያነፃፀሩ የከዋክብትን ብዛት በመመልከት ከአትክልቱ
ውስጥ ይንሸራሸራሉ፡፡
በዚያች ሰዓት አበቦች ያለመስገበገብ የሚለግሱትን መልካም መዓዛ እየማጉ ጥቅጥቅ ካለ ጨለማ ውስጥ እንደበራ ሻማ ብቻቸውን በፍጥረታት
መካከል በደስታ የተዋበው ነፍሳቸውን ዘርግተው ይቆማሉ:: አእምሮአቸው ውስጥ ምን እንዳለ ራሳቸውን ቢጠይቁ መልሱን አያውቁትም:: ሆኖም ከሰውነታቸው ውስጥ አንድ ነገር ወጥቶ እንደሚሄድና አንድ ነገር ደግሞ ከሰውነታቸው ላይ እንደሚያርፍ ይሰማቸዋል ፤ አንድ ዓይነት ምሥጢር መከናወኑን ይገነዘባሉ::
እኚህ እድሜ የጠገበና ፈጣሪያቸውን የቀረበ ሰው የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ቀን ቀን አትክልት በመኮትኮት ሲሆን ማታ ማታ ደግሞ ፈጣሪያቸውን በጸሎት በማመስገን ስለሆነ ሌላ የሚፈልጉት
ነገር አልነበረም:: ምድሩ በአበባ ፤ ሰማዩ ከከዋክብት በማጌጡ የመንፈስ እርካታ ይሰጣቸዋል::
ውድቀት
ጊዜው 1815 ዓ.ም ወሩ ጥቅምት ነው:: ፀሐይዋ ልትጠልቅ አንድ ሰዓት ያህል ሲቀራት አንድ በእግሩ የሚጓገዝ ሰው ወደ ሞንቴስ ሱር ሞንቴስ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ቀና ሰው
በ1815 መሴ ቻርለስ ብየንቬኑ መሪል የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ነበሩ፡፡ እድሜያቸው 75 ሲሆን የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ሁነው የተሾሙት በ1806 ዓ.ም ነበር፡፡ ጳጳሱ ወደ ሀገረ
ስብከታቸው ሲመጡ እህታቸው ወ/ት ባፕቲስታን አብረዋቸው ነበር
የመጡት:: እህትዬዋ ምንም እንኳን ትዳር ባይዙም እድሜ የጠገቡ ሲሆኑ ወንድማቸውን በአሥር ዓመት ይበልጧቸዋል፡፡
ከጳጳሱ ቤት ውስጥ ሌላም ሴት ነበሩ፡፡ እኝህ ሴት የወ/ት ባፕቲስታን እኩያ ናቸው:: ሴትዬዋ ወ/ሮ ማግልዋር ይባላሉ:: ሴትዮዋ ቀደም ሲል የሌላ ሰው አገልጋይ ሆነው ሠርተዋል፡፡ አሁን ደግሞ የወ/ት ባፕቲስታንና
የጳጳሱ ቤት ጠባቂ ሁነው ተቀጥረው ይሠራሉ፡፡
ጳጳሱ ከሀገረ ስብከታቸው እንደደረሱ በሀገሩ ደምብ መሠረት ከፊልድ ማርሻል ቀጥሎ ያለውን ሹመት ይሰጣቸዋል፡፡ የክፍለ ሀገሩ መሪና የማዘጋጃ ቤቱ ሹም ከቤታቸው ሄደው «እንኳን ደህና መጡ» በማለት እጅ ይነስዋቸዋል፡፡ አቡኑም በተራቸው ከዚያ ለተገኙ ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ቡራኬ ይሰጣሉ፡፡ የከተማው ሕዝብ በአጠቃላይ አዲስ የተሾሙለትን ጳጳስ
ለማየት በጉጉት ሲጠባበቅ ነበር፡፡
የጳጳሱ ቤት ከአንድ ሆስፒታል አጠገብ ሲሆን ቤቱ እጅግ በጣም
ሰፊና ያማረ ነው:: ሆስፒታሉ ይገኝ የነበረው ከረባዳ ሥፍራ ላይ ሲሆን ግቢው እንደ ጳጳሱ ቤት አይሰፋም:: ጳጳሱ ወደዚያ ሲሄዱ በሦስተኛው ቀን ሆስፒታሉን ይጎበኛሉ:: ከጉብኝቱ በኋላ የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ ከቤታቸው
ድረስ መጥቶ እንዲያነጋግራቸው ይጋብዙታል:: አስተዳዳሪው ከጳጳሱ ቤት ይሄዳል::
በሆስፒታሉ ውስጥ «ስንት በሽተኞች አሉ? » ሲሉ አስተዳዳሪው ጠየቁ::
«ሃያ ስድስት» ሲል መለሰላቸው::
«ልክ እኔ እንደቆጠርኳቸው ናቸው አልተሳሳትክም» አሉ ጳጳሱ::
ጳጳሱ የቤታቸውን አዳራሽ በዓያናቸው ቃኙ:: አመለካከታቸው
አዳራሹን በዓይነ ሕሊናቸው የሚለኩና የሚያከፋፍሉ ይመስሉ ነበር ።
«ይህ ክፍል ብቻ ሀያ አልጋ ይይዛል» አሉ እርስ በራሳቸው? ሲነጋገሩ።
ከዚያም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚቀጥለውን ተናገሩ::
«ወዳጄ የምለውን አጢነህ ስማኝ፡፡ እዚህ ቦታ አንድ ስህተት የተፈጸመ ይመስላል፡፡ እናንተ አምስት ወይም ስድስት ጠባብ ክፍሎች ናቸው ያሏችሁ::
ከዚያ ውስጥ ሃያ ስድስት ሰዎች ይተኛሉ፡፡ እኛ እዚህ ሦስት ሰዎች ብቻ ነን፡፡ ያለው ቦታ ግን ለስልሣ ሰው የሚበቃ ነው:: ታዲያ ይህ የአደላደል ስህተት አይመስልህም? የእኔን ቤት አንተ ብትወስድ ፤ የአንተን ደግሞ እኔ
ብወስድ ይሻላል፡፡›
በሚቀጥለው ቀን ሃያ ስድስቱ በሽተኞች ወደ ጳጳሱ ቤት ተዛወሩ፡፡
ጳጳሱም ሆስፒታሉን ተረከቡ:: ወሬው በከተማው ተነዛ፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጳጳሱን በጎ ምግባር በመከተል ለበጎ ተግባር የሚውል እርዳታ ይጎርፍ ጀመር፡፡ በየቀኑ ከጳጳሱ ቤት በር የሚያንኳኳ ሰው ቁጥር እየበዛ
ሄደ፡፡ ሆኖም የሚመጣው ሰው ሁሉ እርዳታ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን ምፅዋት ለመቀበልም ነበር፡፡ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጳጳሱ የብዙ ችግረኞች ቀላቢ፣ ምፅዋት ሰጪና ገንዘብ ሰብሳቢ ሆነ፡፡ ብዙ ገንዘብም ከጳጳሱ እጅ እየገባ ለድሃ ይሰጥ ጀመር:: የሚገኘው ገቢ ግን ልክ ከደረቀ
አፈር ላይ እንደሚፈስ ውሃ ገና ከመገኘቱ ወጪ ሆኖ በቶሎ ያልቃል፡፡ጳጳሱ ገንዘብ ቢያገኙም ከተገኘው ገቢ ጥቂቱን እንኳን ለራሳቸው ወደኋላ አላሉም፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው የራሳቸውንም ይዞ ይሄድ ጀመር፡፡
ጳጳሳትን ከስማቸው አስቀድሞ ንጽህናቸውን ለማረጋገጥ ብፁዕ ወቅዱስ እያሉ መጥራት የተለመደ ቢሆንም በዚያ አካባቢ ይገኙ የነበሩት ነዳያን ፍቅራቸውንና ቅርበታቸውን ለመግለጽና የጳጳሱን ደግነት ለማውሳት ብፁዕ ወቅዱስ በማለት ፈንታ «አባ ደጉ» እያሉ ይጠርዋቸዋል፡፡
እኚህ ደግ ሰው በ1815 ዓ.ም ምንም እንኳን 75 ዓመት ቢሞላቸወም ከስልሣ ዓመት በላይ የሆናቸው አይመስሉም ነበር:: ቁመታቸው እጅግም ረጅም ሳይሆን መጠነኛ ሆኖ ሰውነታቸው ደልዳላ ነው:: ክብደታቸውን
ለመቆጣጠር በእግር መሄድ ያዘወትራሉ:: ሲራመዱ መሬት በኃይል እየረገጠ ከወገባቸው ትንሽ ጎበጥ ይላሉ::
የልጅ ፈገግታ በተጎናጸፈ አንደበት ሲናገሩ ከግርማ ሞገሳቸው ብዛት
የሰማቸው ሁሉ የመንፈስ እርካታን ያገኛል:: ከመላ ሰውነታቸው ደስታ
የሚንፀባረቅ ይመስላል፡፡ ደግነት የተቆራኘው አካላቸውና ወተት የመሰለው ጥርሳቸው ፈገግ ሲል እኚያ «ጨዋ ሰው ፤ እድሜ የተቸረ ሽማግሌ፤ ደግ ሰው» በማለት ለደጋግ ሰዎች የምንሰጠው ቅጻል ሁሉ በእኚህ ሰው ላይ ጎልቶ ይታያል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ላያቸው እንኳን ስለብቃታቸውና
ስለደግነታቸው አይጠራጠርም:: ነገር ግን አንድ ሰው ለጥቂት ሰዓት ከጳጳሱ ጋር ቢቆይና በአሳብ ባህር ተወጠው ቢያያቸወ ቀስ በቀስ
መለወጣቸውን ይገነዘባል፡: ግርማ ሞገሳቸው በቃላት ለመግለጽ በማይቻል ሁኔታ ያስፈራል፡፡ ሰፊውና ኮስታራው ፊታቸው እንዲሁም ሻሽ የመሰለው
ፀጉራቸው ክብር የተጎናጸፈ ለመሆነ በግልጽ ይታያል:: ግርማ ሞገስ ከውስጣቸው እየፈለቀ ሲወጣ የሚያልቅ ቢመስልም የእንዐባራቂነት ኃያል
እንዳለው አያጠራጥርም:: እንዲያውም አንድ ሰው ሁኔታቸውን በጥሞና ሲመለከት «አንድ መልአክ በፈገግታ አጊጦ ያየኛል» የሚል ስሜት
ያድርበታል፡፡ እኚህ ሰው የሚያሰላስሉት ስለ ክቡር ጉዳይ እንጂ ስለርካሽ ነገር ላለመሆኑ ጥርጣሬ አይገባውም::
ጸሎት ማድረስ፤ ምፅዋት መስጠት፧ የመንፈስ ስቃይ የደረሰበትን ማጸናናት፤ ወንድማማችነትን መስበክ፤ ራስን ለሌሎች መስዋዕት ማድረግ፤
በእምነት ራስን መግራት የጳጳሱ የእለት ተዕለት ኑሮ ሲሆን ይህም ኑር በበጎ አሳብ፤ በምርጥ ቃላትና በበጎ ተግባር የተሞላ ነበር፡፡
ክረምት ይሁን በጋ ሁለቱ ሴቶች ሲተኙ ብፁዕነታቸው ወደ ጓሮ
ሄደው አትክልት ውስጥ ለአንድ ወይም ለሁለት ሰዓት ፈጣሪያቸውን በማሰብ ከዚያ ካልቆዩ ኑሮአቸው የተሟላ አይመስላቸውም:: አሳባቸውን
ሰብስበውና የመንፈስ እርጋታን አግኝተው የምሽቱን ሰላምና ፀጥታ ከሰዎች የመንፈስ እርካታ ጋር እያነፃፀሩ የከዋክብትን ብዛት በመመልከት ከአትክልቱ
ውስጥ ይንሸራሸራሉ፡፡
በዚያች ሰዓት አበቦች ያለመስገበገብ የሚለግሱትን መልካም መዓዛ እየማጉ ጥቅጥቅ ካለ ጨለማ ውስጥ እንደበራ ሻማ ብቻቸውን በፍጥረታት
መካከል በደስታ የተዋበው ነፍሳቸውን ዘርግተው ይቆማሉ:: አእምሮአቸው ውስጥ ምን እንዳለ ራሳቸውን ቢጠይቁ መልሱን አያውቁትም:: ሆኖም ከሰውነታቸው ውስጥ አንድ ነገር ወጥቶ እንደሚሄድና አንድ ነገር ደግሞ ከሰውነታቸው ላይ እንደሚያርፍ ይሰማቸዋል ፤ አንድ ዓይነት ምሥጢር መከናወኑን ይገነዘባሉ::
እኚህ እድሜ የጠገበና ፈጣሪያቸውን የቀረበ ሰው የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ቀን ቀን አትክልት በመኮትኮት ሲሆን ማታ ማታ ደግሞ ፈጣሪያቸውን በጸሎት በማመስገን ስለሆነ ሌላ የሚፈልጉት
ነገር አልነበረም:: ምድሩ በአበባ ፤ ሰማዩ ከከዋክብት በማጌጡ የመንፈስ እርካታ ይሰጣቸዋል::
ውድቀት
ጊዜው 1815 ዓ.ም ወሩ ጥቅምት ነው:: ፀሐይዋ ልትጠልቅ አንድ ሰዓት ያህል ሲቀራት አንድ በእግሩ የሚጓገዝ ሰው ወደ ሞንቴስ ሱር ሞንቴስ
👍47😁3👏2👎1🔥1