#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ስብሃት ለትምህርት ወደ ፈረንሳይ በተላከበት ጊዜ ከጓደኞቹ ጋር በፓሪስ ያሳለፈውን ጊዜ የሚተርክ። በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ከኢትዮጵያ ባህልና ስርአት ወጣ ያለ ልቦለድ ነው በርግጥ ከላይ ከላይ ለሚያነበው ከወሲብ ቀስቃሽ መፅሀፍነት ላይዘል ይችላል ነገር ግን በማስተዋል ብናነበው የብዙ ነገር ትኩሳቶች ያነሳልና ስናነብ በጥሞና ይሁን ያው ሁሉንም ይመቻል ተብሎ አይጠበቅምና ከዚህ ውጪ ወደ ላይ ብዙ ድርሰቶች አሉና ያላነበባችሁ ከሆነ እስከዚያው በነሱ አሳልፉ። አሁን ወደ #ትኩሳት እንሂድ።👇
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከውብ ሰማይ በታች
ባህራም
ከሩቅ
ይሄ ሁሉ የሆነውና የተደረገው ኤክስ ውስጥ ነበር.....
ኤክስ (ኤክስ-አን-ፕሮቫንስ) በፈረንሳይ ደቡብ ከማርሴይ አጠገብ የምትገኝ ትንሽ የዩኒቨርሲቲ ከተማ ናት፡ ህዝቧ ግማሽ በግማሽ ተማሪ ነው
የኤክስ ሰማይ አብዛኛውን ጊዜ ብሩህ ሰማያዊ ነው፡ አንዳንድ
ጊዜ ውሀ አረንጓዴ ይሆናል፣ ወደ ማታ ላይ እንደ ልጃገረዶቹ
ጉንጭ ይቀላል።
የኤክስ አየር ጠባይ የተመሰገነ በመሆኑ፣ ሀብታም በሽተኞችና
ሽማግሌዎች በሐኪም ምክር ወደ ኤክስ መጥተው ይኖራሉ፡፡ ስለዚህ
«ኩር ሚራቦ» የተባለው የኤክስ ዋና ጎዳና ላይ ሽማግሌዎች፣
አሮጊቶችና ባለሻኛዎች
እግራቸው ረዣዥም ቀጫጭን የሆነ፣የተነፋ ደረታቸው ውስጥ አንገታቸው የተቀበረ ባለሻኛ ሰዎች በቀስተኛ እርምጃቸው ሲዘዋወሩ ይታዩበታል። ባቡር መንገድ ዳር የተደረደሩት አግድም ወምበሮች ላይ የአሮጊትና የሽማግሌ መአት ቁጭ ብሎ ሹራብ እየሰራ ወይም ጋዜጣ እያነበበ ፀሀይ ይሞቃል፡
ወይም ዝም ብሎ ባዶ ብርጭቆ መሳይ ፈዛዛ አይኑን አተኩሮ (ምን
ያይ ይሆን?) ከንፈሩን ያለማቋረጥ ያንቀሳቅሳል (ምን ይል ይሆን?)
በጣም ይቀፋሉ የፈረንጅ ሽማግሌዎችና አሮጊቶች። ጨምጻዳ ቆዳቸው የተሰነጣጠቀ ደረቅ ሰም ይመስላል። ቀጥቃጣዎች::ዝምተኞች። አገጫቸው ተገንጥሎ ወደታች የወደቀ፣ ከንፈራቸው
የተንጠለጠለ፣ ጥርሳቸው የፈራረሰ ሽማግሌዎች፡፡ ጥርሳቸው አልቆ አፋቸው ወደ ውስጥ የጎደጎደ ፂማም አሮጊቶች፡፡ የመኖር ጊዜያቸው
አልፎ፤ የሞት ጊዜያቸውን ዘመናዊ ህክምና ከልክሏቸው፤ ታችኛው
ከንፈራቸውን እንደ ጡጦ እየጠቡ ሞትን ሲጠብቁ ሚውሉ
የህይወት ኦናዎች። ዝምተኞች፡፡ ለአይን ብቻ ሳይሆን ላፍንጫም
ይቀፋሉ፡፡ የልዩ ልዩ መድሀኒት፣ የእርጅና፣ የሞት ሽታ
ሳይቀበር መግማት የጀመረ ስጋ
ደሞ መብዛታቸው ከተማሪው እኩል ሳይሆኑ ይቀራሉ? ማታ
መቸስ ፀህይዋ ሙቀቷን ይዛ ስትሄድ ወደየአልጋቸው ይከተታሉ።
ቀን ግን የትም ይገኛሉ፣ ኤክስን ይወሯታል። ኩር ሚራ ግዛታቸው ነው፡ ዩኒቨርሲቲው አጠገብ ያለው መናፈሻ ቤት መንግስታቸው ነው! ካፌዎቹ ቅኝ ሀገራቸው ናቸው። ቀን ሲኒማ የገባህ እንደሆነህ በጭለማው ሳይታወቅህ፣ ሳይተኛ ከሚያንኰራፉ ሽማግሌ፣ ወይም በየሶስት ሰከንዱ አክ!» ከምትል አሮጊት አጠገብ ትቀመጣለህ. . .
ደግነቱ ይሄ ታሪክ ስለአሮጊቶችና ስለሽማግሌዎች አይደለም።
ስለኛ ስለወጣቶቹ ነው፤ ስለባህራም፣ ስለኒኮል፣ ስለሲልቪ ስለሉልሰገድ፣ ስለሌሎችም ወጣቶች ....
ጥሩ ነው ወጣት መሆን። ገንዘብ ባይኖርህም ጤና ይኖርሀል፡ መልክ ባይኖርህም አንጎል
ይኖርሀል! እውቀት ባይኖርህም ጉራ ይኖርሀል፡ ፍቅር ባይኖርህም
ተስፋ ይኖርሀል፤ ደስታ ባይኖርህም ንዴት ይኖርሀል መጨቆን ቢበዛብህ ሪቮሉሽን ታነሳለህ. .. መኖር ቢያስጠላህ ወይም ቢያቅትህ ራስህን ትገድላለህ....ሰው ባያውቀውም ቅሉ ታሪክ ይኖርሀል፤ወጣት ነህና
የኤክስ የበጋ ሙቀት እየከበደኝ አላስራ ስለሚለኝ የከሰአት
በኋላውን ተኝቼ ውልና ሌሊት ስሰራ ለማደር 'ሞክራለሁ።
አንዳንድ ሌሊት ስራው እምቢ ሲለኝ፣ ከሆቴሌ ወጥቼ በእግሬ
እዘዋወራው ደስ ይለኛል በሌሊቱ ኤክስን መዞር፡፡ ትንሽ ከተማ
ስለሆነች ሰባት ሰአት ሲደርስ ሁሉ ነገር ተዘግቷል (ከካፌ «ሰንትራ»
እና ከላ ፓሌት ናይት ክለብ በቀር) በቀን ጠባቦቹን መንገዶች
የሚያስጨንቃቸው ህዝብ በሙሉ ተኝቷል፡ እነዚያ የሚያስፈሩኝ፣ መምጫቸው የማይታወቅ እብድ ፈረንሳይ ነጂዎች
በየአልጋቸው ተከተዋል! ኤክስ-አን-ፕሮቫንስ ሰላም ነው፡፡ ቤቶቹ ሁሉ ጨልመው፣ የመንገድ መብራት በርቶ፣ በፀጥታው የጫማዬን ድምፅ ብቻ እየሰማሁ ስራመድ፣ ባዶ ከተማ ውስጥ እንዳለሁ ሆኖ ይሰማኛል። አልፎ አልፎ በየአደባባዩ የሚገኙት ሰው ሰራሽ ምንጮች ወደ ኮከቦቹ በኩል እየዘለሉ ከሌሊቱ ጋር ይንሾካሾካሉ
አንድ ሌሊት ወደ ስምንት ሰአት ላይ አንዱን መንገድ ይዤ
ስራመድ ቆይቼ ወደ ግራ በኩል ስታጠፍ፣ ከፊቴ አራት የሚታገሉ
ፈረንጆች ድንገት ብቅ አሉ። ብቅ ያልኩትስ እኔ ነበርኩ፣ ግን እነሱ
ብቅ ያሉብኝ መሰለኝ፡፡ በበጋው ሙቀት ምክንያት አራቱም በሽሚዝ ናቸው፣ ይታገላሉ። በሌሊቱ ፀጥታ ጫማዎቻቸው ከአስፋልቱ ጋር ሲፋተጉና ትንፋሻቸው ሲቆራረጥ ይሰማል። ለጊዜው ማን ከማን ጋር
እንደሚታገል ለማወቅ አልቻልኩም። ዝም ብዬ ስመለከት፣ ሶስት ግዙፍ ሰዎች አንዱን ደቃቃ ብጤ ገጥመውት ኖሮ፣ ከጥቂት ትግል በኋላ ሁለቱ በቀኝና በግራ በኩል ያዙት። ሶስተኛው ከፊቱ ቆመ::
ሁሉም ቁና ቁና ይተነፍሳሉ፡፡ ደቃቃው ሰውዬ ይፍጨረጨራል፣
ግን ድምፅ አያሰማም፡፡ ለምን ኡ ኡ እንደማይል እንጃለት
ከፊት የቆመው ግዙፍ አንዴ በጥፊ መታውና፣ ዘወር ብሎ አጠገባቸው ካለው ግድግዳ ስር አንድ ትንሽ ነገር አንስቶ መጥቶ፣ በዚህ
በጨበጠው ነገር የትንሹን ሰውዬ ግምባር ፈተገው። ትንሹ ሰውዬ
ተፋበት። ግዙፉ በሹክሹክታ እየተሳደበ ወይም እየተራገመ ከሱሪ ኪሱ መሀረብ አውጥቶ ፊቱን ጠረገና ሲያበቃ፣ ደቃቃውን አንድ ቃሪያ ጥፊ አላሰው፡፡ ጥፊው ጧ ሲል ቀሰቀሰኝ፣ ገና አሁን ከመፍዘዜ ነቃሁ። ዘወር ስል፣ አጠገቤ ለመንገድ መጠገኛ ይሁን ለቤት ማስሪያ የተከመረ ኮረት አየሁ። በፍጥነት አንድ ሰባት ከባድ ጠጠር አነሳሁና
እያነጣጠርኩ ሰዎቹ ላይ መወርወር ጀመርኩ (ስወረውር የሀበሻ ነገር!» የሚል ሀሳብ በሀይል አሳቀኝ) ከት ከት ብዬ እየሳቅኩ የወረወርኩት ድንጋይ (ሶስተኛዋ) በጥፊ ተማቺውን ሰውዬ ደረቱን ደለቀችው፣ አራተኛዋ የአንዱን ትክሻ መታች። ድንጋዩና ሳቁ አስደንግጧቸው፣ ትንሹን ሰውዬ ለቀቁትና ተፈተለኩ፡፡ ለምራቂ ያህል እጄ ውስጥ የቀሩትን ድንጋዮች ወረወርኩባቸው። በድንጋዮቼ
ሸኚነት ጥቂት እንደሮጡ ወደ ቀኝ በኩል ታጠፉ፣ ጠፉ።
ሳቄም ድንገት ጠፋ። የፍርሀት ሳቅ ኖሯል። አጠገባችን ምንጭ
ሰማሁ። ገና አሁን ሰማሁት! ለካስ «ፕላስ ዴ ካትር ዶፈን» እተባለው
አደባባይ ውስጥ ነን
ትንሹ ሰውዬ ግራ ገብቶት መንገዱ ጋር ቆሞ አኔን ያየኛል
እጄን እያራከፍኩ ወደሱ ሄድኩ።
ይህን ያህልም ደቃቃ አደለም ከኔ ትንሽ ተለቅ ይላል። ደቃቃ የመሰለኝ ጠላቶቹ በጣም ግዙፍ ስለነበሩ መሆን አለበት።
«Bon soir» አልኩት (ቦን ሷር)
«Bon soir! አንተ ነህ እንዴ? ሀለላሲ ሙት!» አለኝ እየሳቀ
ባህራም ነው፡፡ ከዚህ በፊት ከሀበሾቹ ጋር ብዙ ጊዜ
አይቼዋለሁ። ግን ያን ጊዜ ያገሬን ልጆች በብዙ ስለማልጠጋቸው፣
ይህን ባህራም ተዋውቄው ወይም አናግሬው አላውቅም ነበር።
ድምፁ ወፍራም ሆኖ ለጆሮ ደስ ይላል ፈረንሳይኛው የፈረንሳዮቹ አይደለም፣ መልኩ ግን ትንሽ የደቡብ ፈረንሳዮችን ይመስላል። ፊቱ እንደ ፈረንጅ ነጭ ሳይሆን፡ ፀጉሩ በጣም ጥቁር ነው:: «ሀለሰላሴ ሙት!» ያለኝ ሀበሻ መሆኔን ስላወቀ ነው።
አብሯቸው የሚሄድ ሀበሾች ብዙ ጊዜ ሀይለስላሴ ይሙት!» ሲሉ
ሰምቷል
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ስብሃት ለትምህርት ወደ ፈረንሳይ በተላከበት ጊዜ ከጓደኞቹ ጋር በፓሪስ ያሳለፈውን ጊዜ የሚተርክ። በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ከኢትዮጵያ ባህልና ስርአት ወጣ ያለ ልቦለድ ነው በርግጥ ከላይ ከላይ ለሚያነበው ከወሲብ ቀስቃሽ መፅሀፍነት ላይዘል ይችላል ነገር ግን በማስተዋል ብናነበው የብዙ ነገር ትኩሳቶች ያነሳልና ስናነብ በጥሞና ይሁን ያው ሁሉንም ይመቻል ተብሎ አይጠበቅምና ከዚህ ውጪ ወደ ላይ ብዙ ድርሰቶች አሉና ያላነበባችሁ ከሆነ እስከዚያው በነሱ አሳልፉ። አሁን ወደ #ትኩሳት እንሂድ።👇
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከውብ ሰማይ በታች
ባህራም
ከሩቅ
ይሄ ሁሉ የሆነውና የተደረገው ኤክስ ውስጥ ነበር.....
ኤክስ (ኤክስ-አን-ፕሮቫንስ) በፈረንሳይ ደቡብ ከማርሴይ አጠገብ የምትገኝ ትንሽ የዩኒቨርሲቲ ከተማ ናት፡ ህዝቧ ግማሽ በግማሽ ተማሪ ነው
የኤክስ ሰማይ አብዛኛውን ጊዜ ብሩህ ሰማያዊ ነው፡ አንዳንድ
ጊዜ ውሀ አረንጓዴ ይሆናል፣ ወደ ማታ ላይ እንደ ልጃገረዶቹ
ጉንጭ ይቀላል።
የኤክስ አየር ጠባይ የተመሰገነ በመሆኑ፣ ሀብታም በሽተኞችና
ሽማግሌዎች በሐኪም ምክር ወደ ኤክስ መጥተው ይኖራሉ፡፡ ስለዚህ
«ኩር ሚራቦ» የተባለው የኤክስ ዋና ጎዳና ላይ ሽማግሌዎች፣
አሮጊቶችና ባለሻኛዎች
እግራቸው ረዣዥም ቀጫጭን የሆነ፣የተነፋ ደረታቸው ውስጥ አንገታቸው የተቀበረ ባለሻኛ ሰዎች በቀስተኛ እርምጃቸው ሲዘዋወሩ ይታዩበታል። ባቡር መንገድ ዳር የተደረደሩት አግድም ወምበሮች ላይ የአሮጊትና የሽማግሌ መአት ቁጭ ብሎ ሹራብ እየሰራ ወይም ጋዜጣ እያነበበ ፀሀይ ይሞቃል፡
ወይም ዝም ብሎ ባዶ ብርጭቆ መሳይ ፈዛዛ አይኑን አተኩሮ (ምን
ያይ ይሆን?) ከንፈሩን ያለማቋረጥ ያንቀሳቅሳል (ምን ይል ይሆን?)
በጣም ይቀፋሉ የፈረንጅ ሽማግሌዎችና አሮጊቶች። ጨምጻዳ ቆዳቸው የተሰነጣጠቀ ደረቅ ሰም ይመስላል። ቀጥቃጣዎች::ዝምተኞች። አገጫቸው ተገንጥሎ ወደታች የወደቀ፣ ከንፈራቸው
የተንጠለጠለ፣ ጥርሳቸው የፈራረሰ ሽማግሌዎች፡፡ ጥርሳቸው አልቆ አፋቸው ወደ ውስጥ የጎደጎደ ፂማም አሮጊቶች፡፡ የመኖር ጊዜያቸው
አልፎ፤ የሞት ጊዜያቸውን ዘመናዊ ህክምና ከልክሏቸው፤ ታችኛው
ከንፈራቸውን እንደ ጡጦ እየጠቡ ሞትን ሲጠብቁ ሚውሉ
የህይወት ኦናዎች። ዝምተኞች፡፡ ለአይን ብቻ ሳይሆን ላፍንጫም
ይቀፋሉ፡፡ የልዩ ልዩ መድሀኒት፣ የእርጅና፣ የሞት ሽታ
ሳይቀበር መግማት የጀመረ ስጋ
ደሞ መብዛታቸው ከተማሪው እኩል ሳይሆኑ ይቀራሉ? ማታ
መቸስ ፀህይዋ ሙቀቷን ይዛ ስትሄድ ወደየአልጋቸው ይከተታሉ።
ቀን ግን የትም ይገኛሉ፣ ኤክስን ይወሯታል። ኩር ሚራ ግዛታቸው ነው፡ ዩኒቨርሲቲው አጠገብ ያለው መናፈሻ ቤት መንግስታቸው ነው! ካፌዎቹ ቅኝ ሀገራቸው ናቸው። ቀን ሲኒማ የገባህ እንደሆነህ በጭለማው ሳይታወቅህ፣ ሳይተኛ ከሚያንኰራፉ ሽማግሌ፣ ወይም በየሶስት ሰከንዱ አክ!» ከምትል አሮጊት አጠገብ ትቀመጣለህ. . .
ደግነቱ ይሄ ታሪክ ስለአሮጊቶችና ስለሽማግሌዎች አይደለም።
ስለኛ ስለወጣቶቹ ነው፤ ስለባህራም፣ ስለኒኮል፣ ስለሲልቪ ስለሉልሰገድ፣ ስለሌሎችም ወጣቶች ....
ጥሩ ነው ወጣት መሆን። ገንዘብ ባይኖርህም ጤና ይኖርሀል፡ መልክ ባይኖርህም አንጎል
ይኖርሀል! እውቀት ባይኖርህም ጉራ ይኖርሀል፡ ፍቅር ባይኖርህም
ተስፋ ይኖርሀል፤ ደስታ ባይኖርህም ንዴት ይኖርሀል መጨቆን ቢበዛብህ ሪቮሉሽን ታነሳለህ. .. መኖር ቢያስጠላህ ወይም ቢያቅትህ ራስህን ትገድላለህ....ሰው ባያውቀውም ቅሉ ታሪክ ይኖርሀል፤ወጣት ነህና
የኤክስ የበጋ ሙቀት እየከበደኝ አላስራ ስለሚለኝ የከሰአት
በኋላውን ተኝቼ ውልና ሌሊት ስሰራ ለማደር 'ሞክራለሁ።
አንዳንድ ሌሊት ስራው እምቢ ሲለኝ፣ ከሆቴሌ ወጥቼ በእግሬ
እዘዋወራው ደስ ይለኛል በሌሊቱ ኤክስን መዞር፡፡ ትንሽ ከተማ
ስለሆነች ሰባት ሰአት ሲደርስ ሁሉ ነገር ተዘግቷል (ከካፌ «ሰንትራ»
እና ከላ ፓሌት ናይት ክለብ በቀር) በቀን ጠባቦቹን መንገዶች
የሚያስጨንቃቸው ህዝብ በሙሉ ተኝቷል፡ እነዚያ የሚያስፈሩኝ፣ መምጫቸው የማይታወቅ እብድ ፈረንሳይ ነጂዎች
በየአልጋቸው ተከተዋል! ኤክስ-አን-ፕሮቫንስ ሰላም ነው፡፡ ቤቶቹ ሁሉ ጨልመው፣ የመንገድ መብራት በርቶ፣ በፀጥታው የጫማዬን ድምፅ ብቻ እየሰማሁ ስራመድ፣ ባዶ ከተማ ውስጥ እንዳለሁ ሆኖ ይሰማኛል። አልፎ አልፎ በየአደባባዩ የሚገኙት ሰው ሰራሽ ምንጮች ወደ ኮከቦቹ በኩል እየዘለሉ ከሌሊቱ ጋር ይንሾካሾካሉ
አንድ ሌሊት ወደ ስምንት ሰአት ላይ አንዱን መንገድ ይዤ
ስራመድ ቆይቼ ወደ ግራ በኩል ስታጠፍ፣ ከፊቴ አራት የሚታገሉ
ፈረንጆች ድንገት ብቅ አሉ። ብቅ ያልኩትስ እኔ ነበርኩ፣ ግን እነሱ
ብቅ ያሉብኝ መሰለኝ፡፡ በበጋው ሙቀት ምክንያት አራቱም በሽሚዝ ናቸው፣ ይታገላሉ። በሌሊቱ ፀጥታ ጫማዎቻቸው ከአስፋልቱ ጋር ሲፋተጉና ትንፋሻቸው ሲቆራረጥ ይሰማል። ለጊዜው ማን ከማን ጋር
እንደሚታገል ለማወቅ አልቻልኩም። ዝም ብዬ ስመለከት፣ ሶስት ግዙፍ ሰዎች አንዱን ደቃቃ ብጤ ገጥመውት ኖሮ፣ ከጥቂት ትግል በኋላ ሁለቱ በቀኝና በግራ በኩል ያዙት። ሶስተኛው ከፊቱ ቆመ::
ሁሉም ቁና ቁና ይተነፍሳሉ፡፡ ደቃቃው ሰውዬ ይፍጨረጨራል፣
ግን ድምፅ አያሰማም፡፡ ለምን ኡ ኡ እንደማይል እንጃለት
ከፊት የቆመው ግዙፍ አንዴ በጥፊ መታውና፣ ዘወር ብሎ አጠገባቸው ካለው ግድግዳ ስር አንድ ትንሽ ነገር አንስቶ መጥቶ፣ በዚህ
በጨበጠው ነገር የትንሹን ሰውዬ ግምባር ፈተገው። ትንሹ ሰውዬ
ተፋበት። ግዙፉ በሹክሹክታ እየተሳደበ ወይም እየተራገመ ከሱሪ ኪሱ መሀረብ አውጥቶ ፊቱን ጠረገና ሲያበቃ፣ ደቃቃውን አንድ ቃሪያ ጥፊ አላሰው፡፡ ጥፊው ጧ ሲል ቀሰቀሰኝ፣ ገና አሁን ከመፍዘዜ ነቃሁ። ዘወር ስል፣ አጠገቤ ለመንገድ መጠገኛ ይሁን ለቤት ማስሪያ የተከመረ ኮረት አየሁ። በፍጥነት አንድ ሰባት ከባድ ጠጠር አነሳሁና
እያነጣጠርኩ ሰዎቹ ላይ መወርወር ጀመርኩ (ስወረውር የሀበሻ ነገር!» የሚል ሀሳብ በሀይል አሳቀኝ) ከት ከት ብዬ እየሳቅኩ የወረወርኩት ድንጋይ (ሶስተኛዋ) በጥፊ ተማቺውን ሰውዬ ደረቱን ደለቀችው፣ አራተኛዋ የአንዱን ትክሻ መታች። ድንጋዩና ሳቁ አስደንግጧቸው፣ ትንሹን ሰውዬ ለቀቁትና ተፈተለኩ፡፡ ለምራቂ ያህል እጄ ውስጥ የቀሩትን ድንጋዮች ወረወርኩባቸው። በድንጋዮቼ
ሸኚነት ጥቂት እንደሮጡ ወደ ቀኝ በኩል ታጠፉ፣ ጠፉ።
ሳቄም ድንገት ጠፋ። የፍርሀት ሳቅ ኖሯል። አጠገባችን ምንጭ
ሰማሁ። ገና አሁን ሰማሁት! ለካስ «ፕላስ ዴ ካትር ዶፈን» እተባለው
አደባባይ ውስጥ ነን
ትንሹ ሰውዬ ግራ ገብቶት መንገዱ ጋር ቆሞ አኔን ያየኛል
እጄን እያራከፍኩ ወደሱ ሄድኩ።
ይህን ያህልም ደቃቃ አደለም ከኔ ትንሽ ተለቅ ይላል። ደቃቃ የመሰለኝ ጠላቶቹ በጣም ግዙፍ ስለነበሩ መሆን አለበት።
«Bon soir» አልኩት (ቦን ሷር)
«Bon soir! አንተ ነህ እንዴ? ሀለላሲ ሙት!» አለኝ እየሳቀ
ባህራም ነው፡፡ ከዚህ በፊት ከሀበሾቹ ጋር ብዙ ጊዜ
አይቼዋለሁ። ግን ያን ጊዜ ያገሬን ልጆች በብዙ ስለማልጠጋቸው፣
ይህን ባህራም ተዋውቄው ወይም አናግሬው አላውቅም ነበር።
ድምፁ ወፍራም ሆኖ ለጆሮ ደስ ይላል ፈረንሳይኛው የፈረንሳዮቹ አይደለም፣ መልኩ ግን ትንሽ የደቡብ ፈረንሳዮችን ይመስላል። ፊቱ እንደ ፈረንጅ ነጭ ሳይሆን፡ ፀጉሩ በጣም ጥቁር ነው:: «ሀለሰላሴ ሙት!» ያለኝ ሀበሻ መሆኔን ስላወቀ ነው።
አብሯቸው የሚሄድ ሀበሾች ብዙ ጊዜ ሀይለስላሴ ይሙት!» ሲሉ
ሰምቷል
👍37
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ቀና ሰው
በ1815 መሴ ቻርለስ ብየንቬኑ መሪል የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ነበሩ፡፡ እድሜያቸው 75 ሲሆን የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ሁነው የተሾሙት በ1806 ዓ.ም ነበር፡፡ ጳጳሱ ወደ ሀገረ
ስብከታቸው ሲመጡ እህታቸው ወ/ት ባፕቲስታን አብረዋቸው ነበር
የመጡት:: እህትዬዋ ምንም እንኳን ትዳር ባይዙም እድሜ የጠገቡ ሲሆኑ ወንድማቸውን በአሥር ዓመት ይበልጧቸዋል፡፡
ከጳጳሱ ቤት ውስጥ ሌላም ሴት ነበሩ፡፡ እኝህ ሴት የወ/ት ባፕቲስታን እኩያ ናቸው:: ሴትዬዋ ወ/ሮ ማግልዋር ይባላሉ:: ሴትዮዋ ቀደም ሲል የሌላ ሰው አገልጋይ ሆነው ሠርተዋል፡፡ አሁን ደግሞ የወ/ት ባፕቲስታንና
የጳጳሱ ቤት ጠባቂ ሁነው ተቀጥረው ይሠራሉ፡፡
ጳጳሱ ከሀገረ ስብከታቸው እንደደረሱ በሀገሩ ደምብ መሠረት ከፊልድ ማርሻል ቀጥሎ ያለውን ሹመት ይሰጣቸዋል፡፡ የክፍለ ሀገሩ መሪና የማዘጋጃ ቤቱ ሹም ከቤታቸው ሄደው «እንኳን ደህና መጡ» በማለት እጅ ይነስዋቸዋል፡፡ አቡኑም በተራቸው ከዚያ ለተገኙ ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ቡራኬ ይሰጣሉ፡፡ የከተማው ሕዝብ በአጠቃላይ አዲስ የተሾሙለትን ጳጳስ
ለማየት በጉጉት ሲጠባበቅ ነበር፡፡
የጳጳሱ ቤት ከአንድ ሆስፒታል አጠገብ ሲሆን ቤቱ እጅግ በጣም
ሰፊና ያማረ ነው:: ሆስፒታሉ ይገኝ የነበረው ከረባዳ ሥፍራ ላይ ሲሆን ግቢው እንደ ጳጳሱ ቤት አይሰፋም:: ጳጳሱ ወደዚያ ሲሄዱ በሦስተኛው ቀን ሆስፒታሉን ይጎበኛሉ:: ከጉብኝቱ በኋላ የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ ከቤታቸው
ድረስ መጥቶ እንዲያነጋግራቸው ይጋብዙታል:: አስተዳዳሪው ከጳጳሱ ቤት ይሄዳል::
በሆስፒታሉ ውስጥ «ስንት በሽተኞች አሉ? » ሲሉ አስተዳዳሪው ጠየቁ::
«ሃያ ስድስት» ሲል መለሰላቸው::
«ልክ እኔ እንደቆጠርኳቸው ናቸው አልተሳሳትክም» አሉ ጳጳሱ::
ጳጳሱ የቤታቸውን አዳራሽ በዓያናቸው ቃኙ:: አመለካከታቸው
አዳራሹን በዓይነ ሕሊናቸው የሚለኩና የሚያከፋፍሉ ይመስሉ ነበር ።
«ይህ ክፍል ብቻ ሀያ አልጋ ይይዛል» አሉ እርስ በራሳቸው? ሲነጋገሩ።
ከዚያም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚቀጥለውን ተናገሩ::
«ወዳጄ የምለውን አጢነህ ስማኝ፡፡ እዚህ ቦታ አንድ ስህተት የተፈጸመ ይመስላል፡፡ እናንተ አምስት ወይም ስድስት ጠባብ ክፍሎች ናቸው ያሏችሁ::
ከዚያ ውስጥ ሃያ ስድስት ሰዎች ይተኛሉ፡፡ እኛ እዚህ ሦስት ሰዎች ብቻ ነን፡፡ ያለው ቦታ ግን ለስልሣ ሰው የሚበቃ ነው:: ታዲያ ይህ የአደላደል ስህተት አይመስልህም? የእኔን ቤት አንተ ብትወስድ ፤ የአንተን ደግሞ እኔ
ብወስድ ይሻላል፡፡›
በሚቀጥለው ቀን ሃያ ስድስቱ በሽተኞች ወደ ጳጳሱ ቤት ተዛወሩ፡፡
ጳጳሱም ሆስፒታሉን ተረከቡ:: ወሬው በከተማው ተነዛ፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጳጳሱን በጎ ምግባር በመከተል ለበጎ ተግባር የሚውል እርዳታ ይጎርፍ ጀመር፡፡ በየቀኑ ከጳጳሱ ቤት በር የሚያንኳኳ ሰው ቁጥር እየበዛ
ሄደ፡፡ ሆኖም የሚመጣው ሰው ሁሉ እርዳታ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን ምፅዋት ለመቀበልም ነበር፡፡ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጳጳሱ የብዙ ችግረኞች ቀላቢ፣ ምፅዋት ሰጪና ገንዘብ ሰብሳቢ ሆነ፡፡ ብዙ ገንዘብም ከጳጳሱ እጅ እየገባ ለድሃ ይሰጥ ጀመር:: የሚገኘው ገቢ ግን ልክ ከደረቀ
አፈር ላይ እንደሚፈስ ውሃ ገና ከመገኘቱ ወጪ ሆኖ በቶሎ ያልቃል፡፡ጳጳሱ ገንዘብ ቢያገኙም ከተገኘው ገቢ ጥቂቱን እንኳን ለራሳቸው ወደኋላ አላሉም፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው የራሳቸውንም ይዞ ይሄድ ጀመር፡፡
ጳጳሳትን ከስማቸው አስቀድሞ ንጽህናቸውን ለማረጋገጥ ብፁዕ ወቅዱስ እያሉ መጥራት የተለመደ ቢሆንም በዚያ አካባቢ ይገኙ የነበሩት ነዳያን ፍቅራቸውንና ቅርበታቸውን ለመግለጽና የጳጳሱን ደግነት ለማውሳት ብፁዕ ወቅዱስ በማለት ፈንታ «አባ ደጉ» እያሉ ይጠርዋቸዋል፡፡
እኚህ ደግ ሰው በ1815 ዓ.ም ምንም እንኳን 75 ዓመት ቢሞላቸወም ከስልሣ ዓመት በላይ የሆናቸው አይመስሉም ነበር:: ቁመታቸው እጅግም ረጅም ሳይሆን መጠነኛ ሆኖ ሰውነታቸው ደልዳላ ነው:: ክብደታቸውን
ለመቆጣጠር በእግር መሄድ ያዘወትራሉ:: ሲራመዱ መሬት በኃይል እየረገጠ ከወገባቸው ትንሽ ጎበጥ ይላሉ::
የልጅ ፈገግታ በተጎናጸፈ አንደበት ሲናገሩ ከግርማ ሞገሳቸው ብዛት
የሰማቸው ሁሉ የመንፈስ እርካታን ያገኛል:: ከመላ ሰውነታቸው ደስታ
የሚንፀባረቅ ይመስላል፡፡ ደግነት የተቆራኘው አካላቸውና ወተት የመሰለው ጥርሳቸው ፈገግ ሲል እኚያ «ጨዋ ሰው ፤ እድሜ የተቸረ ሽማግሌ፤ ደግ ሰው» በማለት ለደጋግ ሰዎች የምንሰጠው ቅጻል ሁሉ በእኚህ ሰው ላይ ጎልቶ ይታያል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ላያቸው እንኳን ስለብቃታቸውና
ስለደግነታቸው አይጠራጠርም:: ነገር ግን አንድ ሰው ለጥቂት ሰዓት ከጳጳሱ ጋር ቢቆይና በአሳብ ባህር ተወጠው ቢያያቸወ ቀስ በቀስ
መለወጣቸውን ይገነዘባል፡: ግርማ ሞገሳቸው በቃላት ለመግለጽ በማይቻል ሁኔታ ያስፈራል፡፡ ሰፊውና ኮስታራው ፊታቸው እንዲሁም ሻሽ የመሰለው
ፀጉራቸው ክብር የተጎናጸፈ ለመሆነ በግልጽ ይታያል:: ግርማ ሞገስ ከውስጣቸው እየፈለቀ ሲወጣ የሚያልቅ ቢመስልም የእንዐባራቂነት ኃያል
እንዳለው አያጠራጥርም:: እንዲያውም አንድ ሰው ሁኔታቸውን በጥሞና ሲመለከት «አንድ መልአክ በፈገግታ አጊጦ ያየኛል» የሚል ስሜት
ያድርበታል፡፡ እኚህ ሰው የሚያሰላስሉት ስለ ክቡር ጉዳይ እንጂ ስለርካሽ ነገር ላለመሆኑ ጥርጣሬ አይገባውም::
ጸሎት ማድረስ፤ ምፅዋት መስጠት፧ የመንፈስ ስቃይ የደረሰበትን ማጸናናት፤ ወንድማማችነትን መስበክ፤ ራስን ለሌሎች መስዋዕት ማድረግ፤
በእምነት ራስን መግራት የጳጳሱ የእለት ተዕለት ኑሮ ሲሆን ይህም ኑር በበጎ አሳብ፤ በምርጥ ቃላትና በበጎ ተግባር የተሞላ ነበር፡፡
ክረምት ይሁን በጋ ሁለቱ ሴቶች ሲተኙ ብፁዕነታቸው ወደ ጓሮ
ሄደው አትክልት ውስጥ ለአንድ ወይም ለሁለት ሰዓት ፈጣሪያቸውን በማሰብ ከዚያ ካልቆዩ ኑሮአቸው የተሟላ አይመስላቸውም:: አሳባቸውን
ሰብስበውና የመንፈስ እርጋታን አግኝተው የምሽቱን ሰላምና ፀጥታ ከሰዎች የመንፈስ እርካታ ጋር እያነፃፀሩ የከዋክብትን ብዛት በመመልከት ከአትክልቱ
ውስጥ ይንሸራሸራሉ፡፡
በዚያች ሰዓት አበቦች ያለመስገበገብ የሚለግሱትን መልካም መዓዛ እየማጉ ጥቅጥቅ ካለ ጨለማ ውስጥ እንደበራ ሻማ ብቻቸውን በፍጥረታት
መካከል በደስታ የተዋበው ነፍሳቸውን ዘርግተው ይቆማሉ:: አእምሮአቸው ውስጥ ምን እንዳለ ራሳቸውን ቢጠይቁ መልሱን አያውቁትም:: ሆኖም ከሰውነታቸው ውስጥ አንድ ነገር ወጥቶ እንደሚሄድና አንድ ነገር ደግሞ ከሰውነታቸው ላይ እንደሚያርፍ ይሰማቸዋል ፤ አንድ ዓይነት ምሥጢር መከናወኑን ይገነዘባሉ::
እኚህ እድሜ የጠገበና ፈጣሪያቸውን የቀረበ ሰው የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ቀን ቀን አትክልት በመኮትኮት ሲሆን ማታ ማታ ደግሞ ፈጣሪያቸውን በጸሎት በማመስገን ስለሆነ ሌላ የሚፈልጉት
ነገር አልነበረም:: ምድሩ በአበባ ፤ ሰማዩ ከከዋክብት በማጌጡ የመንፈስ እርካታ ይሰጣቸዋል::
ውድቀት
ጊዜው 1815 ዓ.ም ወሩ ጥቅምት ነው:: ፀሐይዋ ልትጠልቅ አንድ ሰዓት ያህል ሲቀራት አንድ በእግሩ የሚጓገዝ ሰው ወደ ሞንቴስ ሱር ሞንቴስ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ቀና ሰው
በ1815 መሴ ቻርለስ ብየንቬኑ መሪል የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ነበሩ፡፡ እድሜያቸው 75 ሲሆን የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ሁነው የተሾሙት በ1806 ዓ.ም ነበር፡፡ ጳጳሱ ወደ ሀገረ
ስብከታቸው ሲመጡ እህታቸው ወ/ት ባፕቲስታን አብረዋቸው ነበር
የመጡት:: እህትዬዋ ምንም እንኳን ትዳር ባይዙም እድሜ የጠገቡ ሲሆኑ ወንድማቸውን በአሥር ዓመት ይበልጧቸዋል፡፡
ከጳጳሱ ቤት ውስጥ ሌላም ሴት ነበሩ፡፡ እኝህ ሴት የወ/ት ባፕቲስታን እኩያ ናቸው:: ሴትዬዋ ወ/ሮ ማግልዋር ይባላሉ:: ሴትዮዋ ቀደም ሲል የሌላ ሰው አገልጋይ ሆነው ሠርተዋል፡፡ አሁን ደግሞ የወ/ት ባፕቲስታንና
የጳጳሱ ቤት ጠባቂ ሁነው ተቀጥረው ይሠራሉ፡፡
ጳጳሱ ከሀገረ ስብከታቸው እንደደረሱ በሀገሩ ደምብ መሠረት ከፊልድ ማርሻል ቀጥሎ ያለውን ሹመት ይሰጣቸዋል፡፡ የክፍለ ሀገሩ መሪና የማዘጋጃ ቤቱ ሹም ከቤታቸው ሄደው «እንኳን ደህና መጡ» በማለት እጅ ይነስዋቸዋል፡፡ አቡኑም በተራቸው ከዚያ ለተገኙ ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ቡራኬ ይሰጣሉ፡፡ የከተማው ሕዝብ በአጠቃላይ አዲስ የተሾሙለትን ጳጳስ
ለማየት በጉጉት ሲጠባበቅ ነበር፡፡
የጳጳሱ ቤት ከአንድ ሆስፒታል አጠገብ ሲሆን ቤቱ እጅግ በጣም
ሰፊና ያማረ ነው:: ሆስፒታሉ ይገኝ የነበረው ከረባዳ ሥፍራ ላይ ሲሆን ግቢው እንደ ጳጳሱ ቤት አይሰፋም:: ጳጳሱ ወደዚያ ሲሄዱ በሦስተኛው ቀን ሆስፒታሉን ይጎበኛሉ:: ከጉብኝቱ በኋላ የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ ከቤታቸው
ድረስ መጥቶ እንዲያነጋግራቸው ይጋብዙታል:: አስተዳዳሪው ከጳጳሱ ቤት ይሄዳል::
በሆስፒታሉ ውስጥ «ስንት በሽተኞች አሉ? » ሲሉ አስተዳዳሪው ጠየቁ::
«ሃያ ስድስት» ሲል መለሰላቸው::
«ልክ እኔ እንደቆጠርኳቸው ናቸው አልተሳሳትክም» አሉ ጳጳሱ::
ጳጳሱ የቤታቸውን አዳራሽ በዓያናቸው ቃኙ:: አመለካከታቸው
አዳራሹን በዓይነ ሕሊናቸው የሚለኩና የሚያከፋፍሉ ይመስሉ ነበር ።
«ይህ ክፍል ብቻ ሀያ አልጋ ይይዛል» አሉ እርስ በራሳቸው? ሲነጋገሩ።
ከዚያም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚቀጥለውን ተናገሩ::
«ወዳጄ የምለውን አጢነህ ስማኝ፡፡ እዚህ ቦታ አንድ ስህተት የተፈጸመ ይመስላል፡፡ እናንተ አምስት ወይም ስድስት ጠባብ ክፍሎች ናቸው ያሏችሁ::
ከዚያ ውስጥ ሃያ ስድስት ሰዎች ይተኛሉ፡፡ እኛ እዚህ ሦስት ሰዎች ብቻ ነን፡፡ ያለው ቦታ ግን ለስልሣ ሰው የሚበቃ ነው:: ታዲያ ይህ የአደላደል ስህተት አይመስልህም? የእኔን ቤት አንተ ብትወስድ ፤ የአንተን ደግሞ እኔ
ብወስድ ይሻላል፡፡›
በሚቀጥለው ቀን ሃያ ስድስቱ በሽተኞች ወደ ጳጳሱ ቤት ተዛወሩ፡፡
ጳጳሱም ሆስፒታሉን ተረከቡ:: ወሬው በከተማው ተነዛ፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጳጳሱን በጎ ምግባር በመከተል ለበጎ ተግባር የሚውል እርዳታ ይጎርፍ ጀመር፡፡ በየቀኑ ከጳጳሱ ቤት በር የሚያንኳኳ ሰው ቁጥር እየበዛ
ሄደ፡፡ ሆኖም የሚመጣው ሰው ሁሉ እርዳታ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን ምፅዋት ለመቀበልም ነበር፡፡ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጳጳሱ የብዙ ችግረኞች ቀላቢ፣ ምፅዋት ሰጪና ገንዘብ ሰብሳቢ ሆነ፡፡ ብዙ ገንዘብም ከጳጳሱ እጅ እየገባ ለድሃ ይሰጥ ጀመር:: የሚገኘው ገቢ ግን ልክ ከደረቀ
አፈር ላይ እንደሚፈስ ውሃ ገና ከመገኘቱ ወጪ ሆኖ በቶሎ ያልቃል፡፡ጳጳሱ ገንዘብ ቢያገኙም ከተገኘው ገቢ ጥቂቱን እንኳን ለራሳቸው ወደኋላ አላሉም፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው የራሳቸውንም ይዞ ይሄድ ጀመር፡፡
ጳጳሳትን ከስማቸው አስቀድሞ ንጽህናቸውን ለማረጋገጥ ብፁዕ ወቅዱስ እያሉ መጥራት የተለመደ ቢሆንም በዚያ አካባቢ ይገኙ የነበሩት ነዳያን ፍቅራቸውንና ቅርበታቸውን ለመግለጽና የጳጳሱን ደግነት ለማውሳት ብፁዕ ወቅዱስ በማለት ፈንታ «አባ ደጉ» እያሉ ይጠርዋቸዋል፡፡
እኚህ ደግ ሰው በ1815 ዓ.ም ምንም እንኳን 75 ዓመት ቢሞላቸወም ከስልሣ ዓመት በላይ የሆናቸው አይመስሉም ነበር:: ቁመታቸው እጅግም ረጅም ሳይሆን መጠነኛ ሆኖ ሰውነታቸው ደልዳላ ነው:: ክብደታቸውን
ለመቆጣጠር በእግር መሄድ ያዘወትራሉ:: ሲራመዱ መሬት በኃይል እየረገጠ ከወገባቸው ትንሽ ጎበጥ ይላሉ::
የልጅ ፈገግታ በተጎናጸፈ አንደበት ሲናገሩ ከግርማ ሞገሳቸው ብዛት
የሰማቸው ሁሉ የመንፈስ እርካታን ያገኛል:: ከመላ ሰውነታቸው ደስታ
የሚንፀባረቅ ይመስላል፡፡ ደግነት የተቆራኘው አካላቸውና ወተት የመሰለው ጥርሳቸው ፈገግ ሲል እኚያ «ጨዋ ሰው ፤ እድሜ የተቸረ ሽማግሌ፤ ደግ ሰው» በማለት ለደጋግ ሰዎች የምንሰጠው ቅጻል ሁሉ በእኚህ ሰው ላይ ጎልቶ ይታያል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ላያቸው እንኳን ስለብቃታቸውና
ስለደግነታቸው አይጠራጠርም:: ነገር ግን አንድ ሰው ለጥቂት ሰዓት ከጳጳሱ ጋር ቢቆይና በአሳብ ባህር ተወጠው ቢያያቸወ ቀስ በቀስ
መለወጣቸውን ይገነዘባል፡: ግርማ ሞገሳቸው በቃላት ለመግለጽ በማይቻል ሁኔታ ያስፈራል፡፡ ሰፊውና ኮስታራው ፊታቸው እንዲሁም ሻሽ የመሰለው
ፀጉራቸው ክብር የተጎናጸፈ ለመሆነ በግልጽ ይታያል:: ግርማ ሞገስ ከውስጣቸው እየፈለቀ ሲወጣ የሚያልቅ ቢመስልም የእንዐባራቂነት ኃያል
እንዳለው አያጠራጥርም:: እንዲያውም አንድ ሰው ሁኔታቸውን በጥሞና ሲመለከት «አንድ መልአክ በፈገግታ አጊጦ ያየኛል» የሚል ስሜት
ያድርበታል፡፡ እኚህ ሰው የሚያሰላስሉት ስለ ክቡር ጉዳይ እንጂ ስለርካሽ ነገር ላለመሆኑ ጥርጣሬ አይገባውም::
ጸሎት ማድረስ፤ ምፅዋት መስጠት፧ የመንፈስ ስቃይ የደረሰበትን ማጸናናት፤ ወንድማማችነትን መስበክ፤ ራስን ለሌሎች መስዋዕት ማድረግ፤
በእምነት ራስን መግራት የጳጳሱ የእለት ተዕለት ኑሮ ሲሆን ይህም ኑር በበጎ አሳብ፤ በምርጥ ቃላትና በበጎ ተግባር የተሞላ ነበር፡፡
ክረምት ይሁን በጋ ሁለቱ ሴቶች ሲተኙ ብፁዕነታቸው ወደ ጓሮ
ሄደው አትክልት ውስጥ ለአንድ ወይም ለሁለት ሰዓት ፈጣሪያቸውን በማሰብ ከዚያ ካልቆዩ ኑሮአቸው የተሟላ አይመስላቸውም:: አሳባቸውን
ሰብስበውና የመንፈስ እርጋታን አግኝተው የምሽቱን ሰላምና ፀጥታ ከሰዎች የመንፈስ እርካታ ጋር እያነፃፀሩ የከዋክብትን ብዛት በመመልከት ከአትክልቱ
ውስጥ ይንሸራሸራሉ፡፡
በዚያች ሰዓት አበቦች ያለመስገበገብ የሚለግሱትን መልካም መዓዛ እየማጉ ጥቅጥቅ ካለ ጨለማ ውስጥ እንደበራ ሻማ ብቻቸውን በፍጥረታት
መካከል በደስታ የተዋበው ነፍሳቸውን ዘርግተው ይቆማሉ:: አእምሮአቸው ውስጥ ምን እንዳለ ራሳቸውን ቢጠይቁ መልሱን አያውቁትም:: ሆኖም ከሰውነታቸው ውስጥ አንድ ነገር ወጥቶ እንደሚሄድና አንድ ነገር ደግሞ ከሰውነታቸው ላይ እንደሚያርፍ ይሰማቸዋል ፤ አንድ ዓይነት ምሥጢር መከናወኑን ይገነዘባሉ::
እኚህ እድሜ የጠገበና ፈጣሪያቸውን የቀረበ ሰው የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ቀን ቀን አትክልት በመኮትኮት ሲሆን ማታ ማታ ደግሞ ፈጣሪያቸውን በጸሎት በማመስገን ስለሆነ ሌላ የሚፈልጉት
ነገር አልነበረም:: ምድሩ በአበባ ፤ ሰማዩ ከከዋክብት በማጌጡ የመንፈስ እርካታ ይሰጣቸዋል::
ውድቀት
ጊዜው 1815 ዓ.ም ወሩ ጥቅምት ነው:: ፀሐይዋ ልትጠልቅ አንድ ሰዓት ያህል ሲቀራት አንድ በእግሩ የሚጓገዝ ሰው ወደ ሞንቴስ ሱር ሞንቴስ
👍47😁3👏2👎1🔥1