#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ገባህህ፧ «ቴናድዬ» ሲል ዦንድሬ በድጋሚ ተናገረ: ሽጉጡ ከማሪየስ እጅ ሊወድቅ ምንም ያህል አልቀረው ዦንዴሬ ማን እንደሆነ ሲናገር ከአባባ ሸበቶ ይበልጥ ማሪየስን ነው የረበሸው:: ማሪየስ ገና ስሙን ሲሰማ
ይህ ሰው ማን እንደሆነ አወቀ፡፡ አባባ ሸበቶ ግን ቶሎ አላስታወሰውም::
የዚህ ሰው ስምና ሆቴል አባቱ ትቶለት ከሞተመ ወረቀት ላይ ተጽፎአል፡፡ የአባቱን አደራ ለመጠበቅ ሲያየውና ሊጠይቀው ብዙ ጊዜ ፈልጎ አልተሳካለትም:: በመጨረሻ ግን በዚህ ዓይነት ሁናቴ ተገናኘው፡፡ ለካስ
የአባቱን ሕይወት ያዳነው ሰውዬ ሽፍታ ነው! ምን የሚገርም ጉድ ነው ምን ዓይነት የሕይወት አጋጣሚ ነው? ሕይሀት ራስዋ ትቀልዳለች ሲል አሰበደ
ይህን ቴናድዬ የተባለውን ሰው ቢያገኘው እግሩ ላይ ወድቆና ጫማውን ስሞ ሊያመሰግነው ለራሱ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ እርግጥ ነው አሁን አግኝቶታል፡፡
ነገር ግን ማመስገኑ ቀርቶ ለፍርድ አሳልፎ ሊሰጠው ነው:: ቀልድ
አይመስልም፤ ግን አይደለም::
ማሪየስ ሁኔታውን ሲያሰላስል አሳቡን መቋጨት አቃተው:: ድንገት በገጠመው ሁኔታ እንኳን አባባ ሸበቶን ሊረዳ ራሱን መቆጣጠር ተሳነው:: ነገሩ ራሱን አዞረው:: ሁኔታው እየተፋፋመ መጣ፡፡ እርሱ ግን ራሱን
ሊስት ሆነ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአሁን በኋላ ቴናድዩ እንጂ ዦንድሬ ብለን
የማንጠራው ሰው ከወዲህ ወዲያ ይንቆራጠጥ ጀመር፡፡ የኩራትና ድል የመምታት ስሜት አድሮበታል፡፡ በድንገት ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ
«ተዘፈነ! ተበላ! ተጠጣ! ተተፋ!» ሲል ጮኸ፡፡
እንደገና መንቆራጠጥ ጀመረ::
«አይገርምም» ሲል ጩኸቱን ቀጠለ፡፡ ‹‹በመጨረሻ አገኘሁህ:: የእኛ ምፅዋተኛ፤ የእኛ አዛኝ ቅቤ አንጓች የእኛ ቱጃር! የእኛ አሻንጉሊት ለጋሽ አታውቀኝም? የለም ፧ ሞንት ፈርሜ ላይ ከሆቴል ቤቴ ውስጥ ገብተህ
ያደርህ አንተ አይደለህም፧ ከስምንት ዓመት በፊት የገና እለት፤ በ1823 ዓ.ም! የፋንቲንን ልጅ ከቤቴ የወሰድከው አንተ አይደለህም! የእኛ ቀጣፊ
ያን ጊዜ ለብሰኸው የነበረው ረጅም ብጫ ካፖርት ምን ደረሰ? አለቀ? እንደዛሬ ጠዋት ጠቅልለህ ይዘኸው የነበረውስ ጨርቅ! አሁን ውጣ ከዚህ፣ ዓይንህን ያውጣውና፡፡ አንተ ሰይጣን፤ የእኛ መጽዋች! አታውቀኝም፤ እ
ይሁና፤ እኔ ግን አውቅሃለሁ:: ከዚህች ቤት ውስጥ ገና ስትገባ ነው | የለየሁህ፤ ሞላጫ! ያን ጊዜ አታለልከኝ አሞኘኸኝ:: ለእድሌ መስበር ምክንያት የሆንከው አንተ ነህ:: አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ወርውረህልኝ ደህና ትረዳኝ፧ ታገለግለኝ የነበረችዋን ልጅ ወሰድክብኝ:: ልጅትዋ ይህን ጊዜ ብዙ ሀብት አስገኝታልኝ ነበር:: የሀብታም ወገን ስለነበረች በስምዋ ብዙ ሀብት ይመጣልኝ ነበር:: አንተ ግን ያንን ምንጭ አደረቅኸው:: ያቺን ሸቃባ ይዘክብኝ ስትጠፋ ድል ያደረገህ መስሎህ ነበር፡፡ ዛሬ ግን አታመልጠኝም፤አታሸንፈኝም:: አንተ ሽባ፤ በቀል ነው የሚታየኝ አሁን! ጻድቁ፣ ዛሬ አልቆልሃል፡፡ ደግሞ ገንዘብ ይዞልኝ መጣ እኮ! ቂል:: ዛሬ ጠዋት ሳይህ ፍዳህን እንደማስቆጥርክ ነው ለራሴ ቃል የገባሁት።
ቴናድዬ ንግግሩን አቋረጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው:: የሚያጨሰው ሲጃራ ፈላበት ፊቱ ግን እንደ ጠዋት ፀሐይ ፈካ፡፡ ሊዋጋ እንደሚዘል ፍየል ፈነጠዘ፡፡ አባባ ሸበቶን ከቀጥጥሩ ስር በማዋለ በጣም ደስ አለው:: ደስታው
የድንኮች ቀውሌን ጠልፎ የመጣል ፤ የቀበሮ የታመመ በሬን ዘንጥለ የመብላት ያህል ነበር፡፡ የታመመ በሬ እንዳይዋጋ አቅም ያንሰዋል፤ ዝም እንዳይል ነፍሰ አልወጣችምና ይንፈራገጣል::
ቴናድዬ ሲለፈልፍ አባባ ሸበቶ ሊያቋርጠው አልፈለገም:: ንግግሩን እስኪጨርስ ጠበቀው:: አሁን ግን ቆም ሲል እርሱ ተናገረ::
የምትለው ነገር አልገባኝም፤ ተሳስተሃል፡፡ እኔ ድሃ እንጂ ባለብዙ ብር ወይም ቱጃር አይደለሁም፡፡ አንተ ትላለህ እንጂ እኔ አንተን አላውቅህም::
ከሌላ ሰው ጋር ተምታትቼብህ ነው::
«እህ» ሲል ቴናድዬ ጮኸ፤ አሾፈ:: «አሁንም ታሾፋለህ፤ ትቀልዳለህ!
ጌታው ወጥመድ ውስጥ ነው የገባኸው:: አታስታውስማ፣ ማን እንደሆንኩ አልለየኸኝማ!
«ይቅርታህን» አለ አባባ ሸበቶ ተኮሳትሮ፧ «ሽፍታ መሆንህን እየለየሁ ነው»
ቴናድዬ የሰውዬው ድፍረት ከማስደንገጥ አልፎ በጣም አናደደው::ይዞት የነበረውን የወንበር ድጋፍ ንዴቱን የተወጣሰት ይመስል ጨምድዶ ያዘው:: ባለቤቱ «ሽፍታ» የሚለውን ቃል ስትሰማ ከአልጋ ጫፍ ተወረወረች፡፡ቴናድዬ «አትነቃነቂ» ሲል ባለቤቱን አስጠነቀቀ፡፡ ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ ሽፍታ አልክ፤ እናንተ ሀብታሞች እኮ እኛን በዚህ ስም እንደምትጠሩን መቼ አጣነው›› ሲል በመጮህ ተናገረ::
«አዎን ተሸነፍኩልህ ፤ ይኸው ተደብቄና ተሰውሬ የሃፍረት ማቄን
ለብሼ እኖራለሁ፡፡ የምበላውና የምልሰው የለኝም:: ግን ሽፍታ ነኝ:: ይኸው ሶስት ቀኔ ነው እህል ከቀመስኩ:: አንተ ደራርበህ ለብሰሃልና ሞቆሃል::እኔን እዚህ ቆፈን ይዞ ያንቀጠቅጠኛል:: አሽከር ቀጥረህ ፎቅ ቤት ውስጥ
ትኖራለህ:: እኔ እንደ ከብት በረት አድራለሁ:: አንተ ሰሐምሌና በነሐሴ ምግብ ስታማርጥ እኛ የማሽላ ቂጣ አሮብናል:: ይህም አነሰና ሽፍታ ትለናለህ! የግሌ የሆነ ሥራ የነበረኝ ሰው ነኝ:: ከዚህም ደግሞ ይበልጥ ሁለታችንም ፈረንሳዮች በመሆናችን አስተዳዳሪ ለመምረጥ እኩል
እንሰለፋለን፡፡ በል አሁን ከላይህ ላይ ወጥተን ከመጨፈራችን በፊት
የምትናገረው ነገር ካለ ተናገር» ሲል አፈጠጠበት::
አባባ ሸበቶ ዝም አለ፡፡ በዝምታው
መካከል የፈረስ ድምፅ ስለተሰማ
ሁሉም ቀና አሉ።
«የሚፈለጥ እንጨት ካለ እኔ እፈረካክሰዋለሁ:::» መጥረቢያ በእጁ የያዘው ሰው ነበር።
«ለምንድነው ፊትህን የሸፈንክበትን ጨርቅ ያነሳኸው?» ሲል ቴናድዬ በቁጣ ጠየቀው
የያዘው ሰው ነበር-
በቁጣ ጠየቀው::
«ለመሳቅ» ሲል መለሰለት::
አባባ ሸበቶ ቁጣው ገንፍሉበት ይንቆራጠጥ የነበረውን ቴናድ።
በዓይኑ ይጠብቃል፡፡ በሩ ላይ ሦስት ዘበኞች ቆመጥ ስለሚጠብቁት ቴናድዬ በጣም ተዝናንቷል፡፡ ከዚህም በላይ ሴትዬዋ እንኳን ባትቆጠር
ዘጠኝ ለአንድ ናቸው:: ስለዚህ አባባ ሸበቶን ናቅ በማድረግ ቴናድዬ ፊቱ ወደ ባለ መጥረቢያው አዞረ፡፡
አባባ ሽበቶ በዚህች እድል ለመጠቀም ወንበሩን በእግሩ፣ ጠረጴዛው በእጁ አሽቀነጠረና በሚያስደንቅ ፍጥነት ተወርውር ለቴናድዬ ጊዜ ሳይሰጠው
ከመስኮቱ ደረሰ፡፡ መስኮቱን ለመክፈትና ለመፈናጠጥ ጊዜ አልወሰደበትም ሆኖም ገና ግማሽ ሰውነቱን እንዳስወጣ ስድስት ሰዎች ከኋላ ጉትተው ወደ
ክፍሉ መለሱት፡፡ ሦስቱ የከሰል ሠራተኞች ከላዩ ላይ ተረባረቡ፡፡ የቴናድዩ ባለቤት በወንበር ጭንቅላቱን አለችው::
ጫጫታ ሲሰሙ ጊዜ ሌሉች ውጭ ቆመው የነበሩት ሽፍቶች ወደ ውስጥ ገቡ፡፡ አልጋ ላይ ተጋድሞ የነበረው ሽማግሌ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደ መዶሻ ይዞ መጣ፡፡
የሞትና የሽረት ትግል ቀጠለ:: አባባ ሸበቶ አንድ ጊዜ ደረቱ ላይ
በቡጢ ቢለው ሽማግሌው ከመሬት ላይ ተዘረረ: ሌሉች ሁለቱን ደግሞ አንዱን በእርግጫ ሌላውን በጡጫ ሲላቸው ጊዜ እነርሱም ከመሬት ተደፉ፡፡ ከዚያም ላያቸው ላይ ሲወጣ ጊዜ ልክ ድንጋይ እንደተጫነበት ሰው
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ገባህህ፧ «ቴናድዬ» ሲል ዦንድሬ በድጋሚ ተናገረ: ሽጉጡ ከማሪየስ እጅ ሊወድቅ ምንም ያህል አልቀረው ዦንዴሬ ማን እንደሆነ ሲናገር ከአባባ ሸበቶ ይበልጥ ማሪየስን ነው የረበሸው:: ማሪየስ ገና ስሙን ሲሰማ
ይህ ሰው ማን እንደሆነ አወቀ፡፡ አባባ ሸበቶ ግን ቶሎ አላስታወሰውም::
የዚህ ሰው ስምና ሆቴል አባቱ ትቶለት ከሞተመ ወረቀት ላይ ተጽፎአል፡፡ የአባቱን አደራ ለመጠበቅ ሲያየውና ሊጠይቀው ብዙ ጊዜ ፈልጎ አልተሳካለትም:: በመጨረሻ ግን በዚህ ዓይነት ሁናቴ ተገናኘው፡፡ ለካስ
የአባቱን ሕይወት ያዳነው ሰውዬ ሽፍታ ነው! ምን የሚገርም ጉድ ነው ምን ዓይነት የሕይወት አጋጣሚ ነው? ሕይሀት ራስዋ ትቀልዳለች ሲል አሰበደ
ይህን ቴናድዬ የተባለውን ሰው ቢያገኘው እግሩ ላይ ወድቆና ጫማውን ስሞ ሊያመሰግነው ለራሱ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ እርግጥ ነው አሁን አግኝቶታል፡፡
ነገር ግን ማመስገኑ ቀርቶ ለፍርድ አሳልፎ ሊሰጠው ነው:: ቀልድ
አይመስልም፤ ግን አይደለም::
ማሪየስ ሁኔታውን ሲያሰላስል አሳቡን መቋጨት አቃተው:: ድንገት በገጠመው ሁኔታ እንኳን አባባ ሸበቶን ሊረዳ ራሱን መቆጣጠር ተሳነው:: ነገሩ ራሱን አዞረው:: ሁኔታው እየተፋፋመ መጣ፡፡ እርሱ ግን ራሱን
ሊስት ሆነ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአሁን በኋላ ቴናድዩ እንጂ ዦንድሬ ብለን
የማንጠራው ሰው ከወዲህ ወዲያ ይንቆራጠጥ ጀመር፡፡ የኩራትና ድል የመምታት ስሜት አድሮበታል፡፡ በድንገት ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ
«ተዘፈነ! ተበላ! ተጠጣ! ተተፋ!» ሲል ጮኸ፡፡
እንደገና መንቆራጠጥ ጀመረ::
«አይገርምም» ሲል ጩኸቱን ቀጠለ፡፡ ‹‹በመጨረሻ አገኘሁህ:: የእኛ ምፅዋተኛ፤ የእኛ አዛኝ ቅቤ አንጓች የእኛ ቱጃር! የእኛ አሻንጉሊት ለጋሽ አታውቀኝም? የለም ፧ ሞንት ፈርሜ ላይ ከሆቴል ቤቴ ውስጥ ገብተህ
ያደርህ አንተ አይደለህም፧ ከስምንት ዓመት በፊት የገና እለት፤ በ1823 ዓ.ም! የፋንቲንን ልጅ ከቤቴ የወሰድከው አንተ አይደለህም! የእኛ ቀጣፊ
ያን ጊዜ ለብሰኸው የነበረው ረጅም ብጫ ካፖርት ምን ደረሰ? አለቀ? እንደዛሬ ጠዋት ጠቅልለህ ይዘኸው የነበረውስ ጨርቅ! አሁን ውጣ ከዚህ፣ ዓይንህን ያውጣውና፡፡ አንተ ሰይጣን፤ የእኛ መጽዋች! አታውቀኝም፤ እ
ይሁና፤ እኔ ግን አውቅሃለሁ:: ከዚህች ቤት ውስጥ ገና ስትገባ ነው | የለየሁህ፤ ሞላጫ! ያን ጊዜ አታለልከኝ አሞኘኸኝ:: ለእድሌ መስበር ምክንያት የሆንከው አንተ ነህ:: አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ወርውረህልኝ ደህና ትረዳኝ፧ ታገለግለኝ የነበረችዋን ልጅ ወሰድክብኝ:: ልጅትዋ ይህን ጊዜ ብዙ ሀብት አስገኝታልኝ ነበር:: የሀብታም ወገን ስለነበረች በስምዋ ብዙ ሀብት ይመጣልኝ ነበር:: አንተ ግን ያንን ምንጭ አደረቅኸው:: ያቺን ሸቃባ ይዘክብኝ ስትጠፋ ድል ያደረገህ መስሎህ ነበር፡፡ ዛሬ ግን አታመልጠኝም፤አታሸንፈኝም:: አንተ ሽባ፤ በቀል ነው የሚታየኝ አሁን! ጻድቁ፣ ዛሬ አልቆልሃል፡፡ ደግሞ ገንዘብ ይዞልኝ መጣ እኮ! ቂል:: ዛሬ ጠዋት ሳይህ ፍዳህን እንደማስቆጥርክ ነው ለራሴ ቃል የገባሁት።
ቴናድዬ ንግግሩን አቋረጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው:: የሚያጨሰው ሲጃራ ፈላበት ፊቱ ግን እንደ ጠዋት ፀሐይ ፈካ፡፡ ሊዋጋ እንደሚዘል ፍየል ፈነጠዘ፡፡ አባባ ሸበቶን ከቀጥጥሩ ስር በማዋለ በጣም ደስ አለው:: ደስታው
የድንኮች ቀውሌን ጠልፎ የመጣል ፤ የቀበሮ የታመመ በሬን ዘንጥለ የመብላት ያህል ነበር፡፡ የታመመ በሬ እንዳይዋጋ አቅም ያንሰዋል፤ ዝም እንዳይል ነፍሰ አልወጣችምና ይንፈራገጣል::
ቴናድዬ ሲለፈልፍ አባባ ሸበቶ ሊያቋርጠው አልፈለገም:: ንግግሩን እስኪጨርስ ጠበቀው:: አሁን ግን ቆም ሲል እርሱ ተናገረ::
የምትለው ነገር አልገባኝም፤ ተሳስተሃል፡፡ እኔ ድሃ እንጂ ባለብዙ ብር ወይም ቱጃር አይደለሁም፡፡ አንተ ትላለህ እንጂ እኔ አንተን አላውቅህም::
ከሌላ ሰው ጋር ተምታትቼብህ ነው::
«እህ» ሲል ቴናድዬ ጮኸ፤ አሾፈ:: «አሁንም ታሾፋለህ፤ ትቀልዳለህ!
ጌታው ወጥመድ ውስጥ ነው የገባኸው:: አታስታውስማ፣ ማን እንደሆንኩ አልለየኸኝማ!
«ይቅርታህን» አለ አባባ ሸበቶ ተኮሳትሮ፧ «ሽፍታ መሆንህን እየለየሁ ነው»
ቴናድዬ የሰውዬው ድፍረት ከማስደንገጥ አልፎ በጣም አናደደው::ይዞት የነበረውን የወንበር ድጋፍ ንዴቱን የተወጣሰት ይመስል ጨምድዶ ያዘው:: ባለቤቱ «ሽፍታ» የሚለውን ቃል ስትሰማ ከአልጋ ጫፍ ተወረወረች፡፡ቴናድዬ «አትነቃነቂ» ሲል ባለቤቱን አስጠነቀቀ፡፡ ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ ሽፍታ አልክ፤ እናንተ ሀብታሞች እኮ እኛን በዚህ ስም እንደምትጠሩን መቼ አጣነው›› ሲል በመጮህ ተናገረ::
«አዎን ተሸነፍኩልህ ፤ ይኸው ተደብቄና ተሰውሬ የሃፍረት ማቄን
ለብሼ እኖራለሁ፡፡ የምበላውና የምልሰው የለኝም:: ግን ሽፍታ ነኝ:: ይኸው ሶስት ቀኔ ነው እህል ከቀመስኩ:: አንተ ደራርበህ ለብሰሃልና ሞቆሃል::እኔን እዚህ ቆፈን ይዞ ያንቀጠቅጠኛል:: አሽከር ቀጥረህ ፎቅ ቤት ውስጥ
ትኖራለህ:: እኔ እንደ ከብት በረት አድራለሁ:: አንተ ሰሐምሌና በነሐሴ ምግብ ስታማርጥ እኛ የማሽላ ቂጣ አሮብናል:: ይህም አነሰና ሽፍታ ትለናለህ! የግሌ የሆነ ሥራ የነበረኝ ሰው ነኝ:: ከዚህም ደግሞ ይበልጥ ሁለታችንም ፈረንሳዮች በመሆናችን አስተዳዳሪ ለመምረጥ እኩል
እንሰለፋለን፡፡ በል አሁን ከላይህ ላይ ወጥተን ከመጨፈራችን በፊት
የምትናገረው ነገር ካለ ተናገር» ሲል አፈጠጠበት::
አባባ ሸበቶ ዝም አለ፡፡ በዝምታው
መካከል የፈረስ ድምፅ ስለተሰማ
ሁሉም ቀና አሉ።
«የሚፈለጥ እንጨት ካለ እኔ እፈረካክሰዋለሁ:::» መጥረቢያ በእጁ የያዘው ሰው ነበር።
«ለምንድነው ፊትህን የሸፈንክበትን ጨርቅ ያነሳኸው?» ሲል ቴናድዬ በቁጣ ጠየቀው
የያዘው ሰው ነበር-
በቁጣ ጠየቀው::
«ለመሳቅ» ሲል መለሰለት::
አባባ ሸበቶ ቁጣው ገንፍሉበት ይንቆራጠጥ የነበረውን ቴናድ።
በዓይኑ ይጠብቃል፡፡ በሩ ላይ ሦስት ዘበኞች ቆመጥ ስለሚጠብቁት ቴናድዬ በጣም ተዝናንቷል፡፡ ከዚህም በላይ ሴትዬዋ እንኳን ባትቆጠር
ዘጠኝ ለአንድ ናቸው:: ስለዚህ አባባ ሸበቶን ናቅ በማድረግ ቴናድዬ ፊቱ ወደ ባለ መጥረቢያው አዞረ፡፡
አባባ ሽበቶ በዚህች እድል ለመጠቀም ወንበሩን በእግሩ፣ ጠረጴዛው በእጁ አሽቀነጠረና በሚያስደንቅ ፍጥነት ተወርውር ለቴናድዬ ጊዜ ሳይሰጠው
ከመስኮቱ ደረሰ፡፡ መስኮቱን ለመክፈትና ለመፈናጠጥ ጊዜ አልወሰደበትም ሆኖም ገና ግማሽ ሰውነቱን እንዳስወጣ ስድስት ሰዎች ከኋላ ጉትተው ወደ
ክፍሉ መለሱት፡፡ ሦስቱ የከሰል ሠራተኞች ከላዩ ላይ ተረባረቡ፡፡ የቴናድዩ ባለቤት በወንበር ጭንቅላቱን አለችው::
ጫጫታ ሲሰሙ ጊዜ ሌሉች ውጭ ቆመው የነበሩት ሽፍቶች ወደ ውስጥ ገቡ፡፡ አልጋ ላይ ተጋድሞ የነበረው ሽማግሌ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደ መዶሻ ይዞ መጣ፡፡
የሞትና የሽረት ትግል ቀጠለ:: አባባ ሸበቶ አንድ ጊዜ ደረቱ ላይ
በቡጢ ቢለው ሽማግሌው ከመሬት ላይ ተዘረረ: ሌሉች ሁለቱን ደግሞ አንዱን በእርግጫ ሌላውን በጡጫ ሲላቸው ጊዜ እነርሱም ከመሬት ተደፉ፡፡ ከዚያም ላያቸው ላይ ሲወጣ ጊዜ ልክ ድንጋይ እንደተጫነበት ሰው
👍16❤1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ዣቬር ምልክት ሲሰጣቸው ብዙ መሣሪያ የያዙ ፖሊሶች ከክፍሉ
ውስጥ ገቡ፡፡ ሽፍቶቹን ያዝዋቸው: ክፍሉ ውስጥ በርቶ የነበረው ሻማ
አንድ ብቻ ስለነበር ክፍሉ ውስጥ ሰው ሲበዛ ጊዜ ብዙ ጥላ በማጥለሉ እየጨለመ ሄደ።
«ሁሉንም በብረት ሰንሰለት እጆቻቸውን እሰሩ» በማለት ዣቬር አዘዘ
«በሉ ወደዚህ ኑ» የሚል ቀጭን የሴት ድምፅ ተሰማ፡፡ ሚስስ
ቴናድዬ ነበረች፡፡ ባልዋ ከለበሰችው ሰፊ ካባ ስር ተሸሽጓል፡፡
ጠንቀቅ በሉ!» ስትል በመጮህ ተናገረች::
ሽፍቶቹ በሙሉ ያለማንገራገር እጆቻቸውን ሰጥተው ሲጠፈሩ
በማየትዋ «ፈሪ ሁሉ!» ስትል አጉረመረመች፡፡
ዣቬር ፈገግ አለ፡፡ ሚስስ ቴናድዬ ወደነበረችበት አመራ፡፡
«አይጠጉኝ፧ ከዚህ ቶሎ ቢወጡ ይሻላል» ስትል በማንጓጠጥ
ተናገረች::«እምቢ ካሉ ዋጋዎን ነው የምሰጥዎት::»
«ደፋር» አለ ዣቬር፡፡ «እመቤቴ እንደ ወንድ ጢም አብቅለዋል፤ እኔ
ደግሞ እንደ ሴት ጥፍር አሳድጌአለሁ» ሲል አሾፈባት።
ዣቬር እየተጠጋት መጣ፡፡ አጠገብዋ አንዳንዴ ልጆችዋ አንዳንዴም ራስዋ የምትቀመጥበት ድንጋይ ነበር፡፡ ዘልላ ሄዳ ያንን ድንጋይ አነሳችና
ዣቬርን ለመምታት ወረወረችው:: ዣቬር ጎንበስ በማለት ራሱን አዳነ፡፡ድንጋዩ ከግድግዳ ጋር ሄዶ ተላተመ:: የግድግዳው ቀለም ፈራርሶ ወለሉን ሞላው:: ድንጋዩ ሲመለስ እየተንከባለለ ከዣቬር እግር ስር ደረሰ።
ዣቬር ወደ ባልና ሚስቱ ሄደ:: በአንድ እጁ የሴትዮዋን፤ በሌላ እጁ የወንዱን ትከሻ ጨምድዶ ያዘ፡፡
«መሣሪያ አምጡ» ሲል ጮኸ፡፡
ወዲያው የብረት ማሠሪያ መጥቶ ሁለቱ ሰዎች ተቀፈደዱ። የራስዋና
የባልዋ እጆች መቀፍደዳቸውን ባየች ጊዜ «ወይኔ ልጆቼ» በማለት ከጮኸች ኋላ ከመሬት ላይ ተዘረረች፡፡
«በእድላቸው ያድጋሉ» ሲል አፌዘባት::
ሦስቱ ፊታቸውን በከሰል ያጠቆሩና ሦስቱ ፊታቸውን በጨርቅ የሸፈኑ ሽፍቶች እጃቸው ታስሮ ቆመዋል::
«ፊታችሁን እንደሽፈናችሁ ቆዩ» አለ ዣቬር፡-
እያንዳንዳቸውን በስም እየጠራ አንዱን «እንደምን አመሸህ»፣ ሌላውን ጤና ይስጥልኝ»፤ ሌላውን ደግሞ «ብርቱም አልሰነበትክ» በማለት
ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ገና ከክፍሉ ሲገባ አንገቱን ደፍቶ ቆሞ
የነበረው እስረኛ ታወሰው::
«እስረኛውን ፍቱት» ሲል አዘዘ፡፡ «ከዚህ ቤት ደግሞ አንድ ሰው .
እንዳይወጣ?»
ይህን እንደተናገረ ከወንበሩ ላይ ሄዶ ቁጭ አለ፡፡ ከኪሱ ወረቀትና
ብዕር አውጥቶ ከጠረጴዛው ላይ አስቀመጠ፡፡ ቀና ብሉ «እያየ እስረኛውን ወደዚህ አምጡት» አለ፡፡
ፖሊሶቹ በዓይን ፈለጉት::
«ምነው፤ ምን ያንቀረፍፋችኋል? የት አለ ሰውዬው?» ሲል
ጮኸባቸው::
እስረኛው አባባ ሸበቶ ከዚያ አልነበረም፧ ወጥቶ ሄዷል፡፡
በሩ ላይ ፖሊስ ቆሞአል፡፡ የነበሩበት ክፍል ፎቅ ቤት ነው:: ታዲያ የት ሄደ? መስኮቱ አጠገብ ፖሊስ አልነበረም:: ትርምሱ ሲበዛ ቀደም ሲል እነቴናድዬ ለማምለጫ ባዘጋጁት የገመድ መሰላል አድርጎ ሾልኮአል። የፖሊሶቹ ዓይን አርፎ የነበረው ሽፍቶቹ ላይ ነበር፡፡
«ጋኔላም!» አለ ዣቬር በጥርሶቹ መሀል፤ «ጥሩ ምስክር ይሆነን
ነበር፡፡»
በሚቀጥለው ቀን ማታ አንድ ልጅ በኃይል እያፏጨና እየዘመረ
በመንገድ ላይ ሲጓዝ ከአንድ ነገር ጋር ይጋጫል፡፡ የተጋጨው ከሴት ጋር ነበር፡፡ ለመውደቅ እንደ መንገዳገድ ይልና ወደኋላ ዞር ብሎ ይመለከታል::
«ምነው! ትልቅ ውሻ መስሎኝ ነበር፡፡»
አሮጊትዋ ገንፍላ ከተኛችበት ብድግ አለች፡፡
«የተረገምክ» አለች ፤ «ከድካም ብዛት ሰውነቴ ባይከዳኝ ምን
እንደማደርግህ አውቅ ነበር፡፡»
ልጁ ኣሁን ትንሽ ራቅ ብሎ ነበር የቆመው፡፡
«ፕስ... ፕስ...» በማለት ካሽሟጠጣት በኋላ «በካልቾ ማቅመሴ አልተሳሳትኩም ፤ አበጀሁ፤ አበጀሁ» ሲል ተናገራት፡፡
ሴትየዋ ከተቀመጠችበት ብድግ አለች፡፡ ልጁ ሮጦ ሸሽ፡፡ እርሱን ለመያዝ ስትሮጥ መብራት ከነበረበት ደረሰች፡፡ የፊትዋ መሸብሸብና የወገብዋ መጉበጥ በግልጽ ታየ:: ልጁ ራቅ ብሎ ቆሞ አጤናት።
«እኔ የምወደው መልክ የለሽም» ብሎአት እያዜመ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የቤት ቁጥር 50-52 ስለደረሰ ቆመ፡፡ በሩ መቆለፉን ሲያይ በእርግጫ መታው
አመታቱ የልጅ ሳይሆን የአዋቂ ነበር፡፡ ለካስ መንገድ ተኝታ
ያያት ሴት ትከተለው ኖሮ ከነበረበት ደረሰች::
ምንድነው ነገሩ እባካችሁ? ያ ከበሩ ላይ የቆመው ማነው? የእግዜር ያለህ በሩን እየሰበሩት ነው፤ ሌቦች ከቤቴ ሊገቡ ነው» ስትል ጮኸች፡፡
ልጁ በር መደብደቡን ቀጠለ፡፡ ሴትዬዋ ትንፋሽ አጥሮአት መተንፈስዋ በግድ ሆነ፡፡
«የአሁነስ ዘረፋ ዓይን በዓይን ሆነ እንዴ?» ብላ ከጠየቀች በኋላ ልጁን አተኩራ ስትመለከተው ማን እንደሆነ አወቀችው፡፡
«እንዴ! ያ ርኩስ፤ ያ ሰይጣን ነው እንዴ!»
«ጉድ ፈላ! አሮጊትዋ ናትና» አለ ልጁ ወደኋላ እየሸሸ፡፡ «ዘመዶቼን
መጠየቅ መጥቼ እኮ ነው::»
«ከዚህ ማንም የለም፤ አንተ ጋኔል» አለች ሴትዬዋ ጥላቻዋን ከፊትዋ ላይ ለማሳየት እየሞከረች::
«አይ ምን ይላሉ እርስዎ ደግሞ፤ ታዲያ አባቴ የት ሄደ?»
«ላ ፎርስ ከተባለ ሥፍራ፡፡»
«እናቴስ?»
«ሳን ላዛር፡፡»
«እሺ፧ እህቶቼስ?»
«ሌ ማደለኔ ሄደዋል፡፡»
ልጁ ጆሮውን አከክ እያደረገ ሴትዮዋን ቀና ብሎ አያት:: ሴትዮዋ እነቴናድዬ ይኖሩበት የነበረው ቤት ጠባቂ ነበረች፡፡
«እንዴት ይሆናል?» ሲል ራሱን ጠየቀ።
ከዚያም ፊቱን አዙሮ ቀደም ሲል ያዜመው የነበረውን ዜማ እያዜመ
መንገዱን ቀጠለ፡
ቅዱስ ዴኒስና ከፕሎሜ
ጎዳና ያስ ቤት
ኢፓኒን
ማሪየስ ባጠመደው ወጥመድ ፍርድ ሲገለባበጥ አየ:: የፖሊሱ
አዛዥ እስረኞቹን ይዞ ወጣ፡፡ ማሪየስም ከነበረበት ክፍል ወዲያው ሄደ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ገደማ ሆኖአል፡፡ ወደ ጓደኛው ቤት አመራ፡፡ ከጓደኛ
ው ከኩርፌይራክ ቤት እንደደረሰም ከእርሱ ጋር ለማደር እንደመጣ ገለጸለት፡፡ ኩርፌይራክም ከመሬት ላይ ፍራሽ አነጠፈለት::
በሚቀጥለው ቀን በጠዋት ከቤቱ ተመልሶ ያለበትን ቤት ኪራይ
ክፍሎ ቤቱን ለቀቀ፡፡ እቃውን በጋሪ አስጭኖ ከኩርፌይራክ ሰፈር ሄደ፡፡
ዣቬር የልጁን ስም ረስቶ ከቤቱ አገኘው እንደሆነ ብሉ ቢመጣ
አጣው:: ማሪየስን ለማግኘት ብዙ ሞከረ ፤ ግን አልተሳካለትም:: ምናልባትም ልጁ የሚደርሰውን አደጋ ላለማየት ብሎ በመፍራት ከአገር የጠፋ መሰለው::
ማሪየስ ግን ባየውና በተሰጠው ፍርድ እጅግ ተረብሾ ነበር፡፡ ሁሉም
ነገር ጨለመበት:: የሚያየው የወደፊት ተስፋ ከፊቱ ራቀ፡፡ ልቡ የተሰቀለላት ልጅና አባትዋ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ብቅ ብለው እንደገና ተሰወሩበት:: የእርሱ የወደፊት ተስፋ እነዚህ የማይታወቁ ፍጡሮች ነበሩ፡፡
ልቡ በልጅትዋ ፍቅር ታውሮአል፡፡ «ሂድና ፈልጋት» ብሎ ስሜቱን
ቢገፋፋውም ዓይኑ ማየት ስላልቻለ እንዲያው ዝም ብሎ መረበሽ፤ መጠበብ፤
መጨነቅ ሆነ፡፡ ቀቢጸ ተስፋ ተጠናወተው:: ተስፋ የተለየው ሕይወት ጨለማ ስለሆነ ፀሐይ ወጥቶ ሳለ ምድር ጨለመችበት:: ዓይኖቹ የፍቅር ረሃብተኞች ቢሆኑም ለማየት የፈለጉትን ባለማግኘታቸው ከማየት ተቆጠቡ::ጀሮዎቹ ለመስማት የፈለጉትን ድምፅ ባለመስማታቸው ሌላ ነገር ከመስማት አፈገፈጉ፡፡ ልቡ የፈለገውን ሳያገኝ ሲቀር የፍላጎቱ መጠንና ግለት እየጎላ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ዣቬር ምልክት ሲሰጣቸው ብዙ መሣሪያ የያዙ ፖሊሶች ከክፍሉ
ውስጥ ገቡ፡፡ ሽፍቶቹን ያዝዋቸው: ክፍሉ ውስጥ በርቶ የነበረው ሻማ
አንድ ብቻ ስለነበር ክፍሉ ውስጥ ሰው ሲበዛ ጊዜ ብዙ ጥላ በማጥለሉ እየጨለመ ሄደ።
«ሁሉንም በብረት ሰንሰለት እጆቻቸውን እሰሩ» በማለት ዣቬር አዘዘ
«በሉ ወደዚህ ኑ» የሚል ቀጭን የሴት ድምፅ ተሰማ፡፡ ሚስስ
ቴናድዬ ነበረች፡፡ ባልዋ ከለበሰችው ሰፊ ካባ ስር ተሸሽጓል፡፡
ጠንቀቅ በሉ!» ስትል በመጮህ ተናገረች::
ሽፍቶቹ በሙሉ ያለማንገራገር እጆቻቸውን ሰጥተው ሲጠፈሩ
በማየትዋ «ፈሪ ሁሉ!» ስትል አጉረመረመች፡፡
ዣቬር ፈገግ አለ፡፡ ሚስስ ቴናድዬ ወደነበረችበት አመራ፡፡
«አይጠጉኝ፧ ከዚህ ቶሎ ቢወጡ ይሻላል» ስትል በማንጓጠጥ
ተናገረች::«እምቢ ካሉ ዋጋዎን ነው የምሰጥዎት::»
«ደፋር» አለ ዣቬር፡፡ «እመቤቴ እንደ ወንድ ጢም አብቅለዋል፤ እኔ
ደግሞ እንደ ሴት ጥፍር አሳድጌአለሁ» ሲል አሾፈባት።
ዣቬር እየተጠጋት መጣ፡፡ አጠገብዋ አንዳንዴ ልጆችዋ አንዳንዴም ራስዋ የምትቀመጥበት ድንጋይ ነበር፡፡ ዘልላ ሄዳ ያንን ድንጋይ አነሳችና
ዣቬርን ለመምታት ወረወረችው:: ዣቬር ጎንበስ በማለት ራሱን አዳነ፡፡ድንጋዩ ከግድግዳ ጋር ሄዶ ተላተመ:: የግድግዳው ቀለም ፈራርሶ ወለሉን ሞላው:: ድንጋዩ ሲመለስ እየተንከባለለ ከዣቬር እግር ስር ደረሰ።
ዣቬር ወደ ባልና ሚስቱ ሄደ:: በአንድ እጁ የሴትዮዋን፤ በሌላ እጁ የወንዱን ትከሻ ጨምድዶ ያዘ፡፡
«መሣሪያ አምጡ» ሲል ጮኸ፡፡
ወዲያው የብረት ማሠሪያ መጥቶ ሁለቱ ሰዎች ተቀፈደዱ። የራስዋና
የባልዋ እጆች መቀፍደዳቸውን ባየች ጊዜ «ወይኔ ልጆቼ» በማለት ከጮኸች ኋላ ከመሬት ላይ ተዘረረች፡፡
«በእድላቸው ያድጋሉ» ሲል አፌዘባት::
ሦስቱ ፊታቸውን በከሰል ያጠቆሩና ሦስቱ ፊታቸውን በጨርቅ የሸፈኑ ሽፍቶች እጃቸው ታስሮ ቆመዋል::
«ፊታችሁን እንደሽፈናችሁ ቆዩ» አለ ዣቬር፡-
እያንዳንዳቸውን በስም እየጠራ አንዱን «እንደምን አመሸህ»፣ ሌላውን ጤና ይስጥልኝ»፤ ሌላውን ደግሞ «ብርቱም አልሰነበትክ» በማለት
ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ገና ከክፍሉ ሲገባ አንገቱን ደፍቶ ቆሞ
የነበረው እስረኛ ታወሰው::
«እስረኛውን ፍቱት» ሲል አዘዘ፡፡ «ከዚህ ቤት ደግሞ አንድ ሰው .
እንዳይወጣ?»
ይህን እንደተናገረ ከወንበሩ ላይ ሄዶ ቁጭ አለ፡፡ ከኪሱ ወረቀትና
ብዕር አውጥቶ ከጠረጴዛው ላይ አስቀመጠ፡፡ ቀና ብሉ «እያየ እስረኛውን ወደዚህ አምጡት» አለ፡፡
ፖሊሶቹ በዓይን ፈለጉት::
«ምነው፤ ምን ያንቀረፍፋችኋል? የት አለ ሰውዬው?» ሲል
ጮኸባቸው::
እስረኛው አባባ ሸበቶ ከዚያ አልነበረም፧ ወጥቶ ሄዷል፡፡
በሩ ላይ ፖሊስ ቆሞአል፡፡ የነበሩበት ክፍል ፎቅ ቤት ነው:: ታዲያ የት ሄደ? መስኮቱ አጠገብ ፖሊስ አልነበረም:: ትርምሱ ሲበዛ ቀደም ሲል እነቴናድዬ ለማምለጫ ባዘጋጁት የገመድ መሰላል አድርጎ ሾልኮአል። የፖሊሶቹ ዓይን አርፎ የነበረው ሽፍቶቹ ላይ ነበር፡፡
«ጋኔላም!» አለ ዣቬር በጥርሶቹ መሀል፤ «ጥሩ ምስክር ይሆነን
ነበር፡፡»
በሚቀጥለው ቀን ማታ አንድ ልጅ በኃይል እያፏጨና እየዘመረ
በመንገድ ላይ ሲጓዝ ከአንድ ነገር ጋር ይጋጫል፡፡ የተጋጨው ከሴት ጋር ነበር፡፡ ለመውደቅ እንደ መንገዳገድ ይልና ወደኋላ ዞር ብሎ ይመለከታል::
«ምነው! ትልቅ ውሻ መስሎኝ ነበር፡፡»
አሮጊትዋ ገንፍላ ከተኛችበት ብድግ አለች፡፡
«የተረገምክ» አለች ፤ «ከድካም ብዛት ሰውነቴ ባይከዳኝ ምን
እንደማደርግህ አውቅ ነበር፡፡»
ልጁ ኣሁን ትንሽ ራቅ ብሎ ነበር የቆመው፡፡
«ፕስ... ፕስ...» በማለት ካሽሟጠጣት በኋላ «በካልቾ ማቅመሴ አልተሳሳትኩም ፤ አበጀሁ፤ አበጀሁ» ሲል ተናገራት፡፡
ሴትየዋ ከተቀመጠችበት ብድግ አለች፡፡ ልጁ ሮጦ ሸሽ፡፡ እርሱን ለመያዝ ስትሮጥ መብራት ከነበረበት ደረሰች፡፡ የፊትዋ መሸብሸብና የወገብዋ መጉበጥ በግልጽ ታየ:: ልጁ ራቅ ብሎ ቆሞ አጤናት።
«እኔ የምወደው መልክ የለሽም» ብሎአት እያዜመ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የቤት ቁጥር 50-52 ስለደረሰ ቆመ፡፡ በሩ መቆለፉን ሲያይ በእርግጫ መታው
አመታቱ የልጅ ሳይሆን የአዋቂ ነበር፡፡ ለካስ መንገድ ተኝታ
ያያት ሴት ትከተለው ኖሮ ከነበረበት ደረሰች::
ምንድነው ነገሩ እባካችሁ? ያ ከበሩ ላይ የቆመው ማነው? የእግዜር ያለህ በሩን እየሰበሩት ነው፤ ሌቦች ከቤቴ ሊገቡ ነው» ስትል ጮኸች፡፡
ልጁ በር መደብደቡን ቀጠለ፡፡ ሴትዬዋ ትንፋሽ አጥሮአት መተንፈስዋ በግድ ሆነ፡፡
«የአሁነስ ዘረፋ ዓይን በዓይን ሆነ እንዴ?» ብላ ከጠየቀች በኋላ ልጁን አተኩራ ስትመለከተው ማን እንደሆነ አወቀችው፡፡
«እንዴ! ያ ርኩስ፤ ያ ሰይጣን ነው እንዴ!»
«ጉድ ፈላ! አሮጊትዋ ናትና» አለ ልጁ ወደኋላ እየሸሸ፡፡ «ዘመዶቼን
መጠየቅ መጥቼ እኮ ነው::»
«ከዚህ ማንም የለም፤ አንተ ጋኔል» አለች ሴትዬዋ ጥላቻዋን ከፊትዋ ላይ ለማሳየት እየሞከረች::
«አይ ምን ይላሉ እርስዎ ደግሞ፤ ታዲያ አባቴ የት ሄደ?»
«ላ ፎርስ ከተባለ ሥፍራ፡፡»
«እናቴስ?»
«ሳን ላዛር፡፡»
«እሺ፧ እህቶቼስ?»
«ሌ ማደለኔ ሄደዋል፡፡»
ልጁ ጆሮውን አከክ እያደረገ ሴትዮዋን ቀና ብሎ አያት:: ሴትዮዋ እነቴናድዬ ይኖሩበት የነበረው ቤት ጠባቂ ነበረች፡፡
«እንዴት ይሆናል?» ሲል ራሱን ጠየቀ።
ከዚያም ፊቱን አዙሮ ቀደም ሲል ያዜመው የነበረውን ዜማ እያዜመ
መንገዱን ቀጠለ፡
ቅዱስ ዴኒስና ከፕሎሜ
ጎዳና ያስ ቤት
ኢፓኒን
ማሪየስ ባጠመደው ወጥመድ ፍርድ ሲገለባበጥ አየ:: የፖሊሱ
አዛዥ እስረኞቹን ይዞ ወጣ፡፡ ማሪየስም ከነበረበት ክፍል ወዲያው ሄደ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ገደማ ሆኖአል፡፡ ወደ ጓደኛው ቤት አመራ፡፡ ከጓደኛ
ው ከኩርፌይራክ ቤት እንደደረሰም ከእርሱ ጋር ለማደር እንደመጣ ገለጸለት፡፡ ኩርፌይራክም ከመሬት ላይ ፍራሽ አነጠፈለት::
በሚቀጥለው ቀን በጠዋት ከቤቱ ተመልሶ ያለበትን ቤት ኪራይ
ክፍሎ ቤቱን ለቀቀ፡፡ እቃውን በጋሪ አስጭኖ ከኩርፌይራክ ሰፈር ሄደ፡፡
ዣቬር የልጁን ስም ረስቶ ከቤቱ አገኘው እንደሆነ ብሉ ቢመጣ
አጣው:: ማሪየስን ለማግኘት ብዙ ሞከረ ፤ ግን አልተሳካለትም:: ምናልባትም ልጁ የሚደርሰውን አደጋ ላለማየት ብሎ በመፍራት ከአገር የጠፋ መሰለው::
ማሪየስ ግን ባየውና በተሰጠው ፍርድ እጅግ ተረብሾ ነበር፡፡ ሁሉም
ነገር ጨለመበት:: የሚያየው የወደፊት ተስፋ ከፊቱ ራቀ፡፡ ልቡ የተሰቀለላት ልጅና አባትዋ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ብቅ ብለው እንደገና ተሰወሩበት:: የእርሱ የወደፊት ተስፋ እነዚህ የማይታወቁ ፍጡሮች ነበሩ፡፡
ልቡ በልጅትዋ ፍቅር ታውሮአል፡፡ «ሂድና ፈልጋት» ብሎ ስሜቱን
ቢገፋፋውም ዓይኑ ማየት ስላልቻለ እንዲያው ዝም ብሎ መረበሽ፤ መጠበብ፤
መጨነቅ ሆነ፡፡ ቀቢጸ ተስፋ ተጠናወተው:: ተስፋ የተለየው ሕይወት ጨለማ ስለሆነ ፀሐይ ወጥቶ ሳለ ምድር ጨለመችበት:: ዓይኖቹ የፍቅር ረሃብተኞች ቢሆኑም ለማየት የፈለጉትን ባለማግኘታቸው ከማየት ተቆጠቡ::ጀሮዎቹ ለመስማት የፈለጉትን ድምፅ ባለመስማታቸው ሌላ ነገር ከመስማት አፈገፈጉ፡፡ ልቡ የፈለገውን ሳያገኝ ሲቀር የፍላጎቱ መጠንና ግለት እየጎላ
👍20