አትሮኖስ
286K subscribers
117 photos
3 videos
41 files
565 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ትኩሳት


#ክፍል_አስራ_አምስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

ባህራም
ሞት

ያን ሰሞን ጀምሺድ ታሞ ተኛ፡፡ ልጠይቀው ወደ ቤቱ ሄድኩ።
ሌሎቹ በሚጠይቁት ሰአት ብሄድ ምንም አልጠቅመውም በማለት፣
በትምህርት ሰአት ሄድኩ። ፎቁን ወጥቼ በሩን ብሞክረው ተቆልፏል። ደወሉን ተጫንኩት፣ ውስጥ ሲደውል ተሰማኝ፡፡ ቆየሁ
የጀምሺድ ቤት ሳይሆን፣ በግራ በኩል ያለው የጎረቤቱ በር
ተከፈተ። መነፅር ያደረገ መላጣ ሽማግሌ ሀኪም አንገቱን ብቅ ከርጎ አየኝ፡፡ አየሁት። ከበሩ ወጣ፡፡ ነጭ የሀኪም ኮቱ በጣም ንፁህ ነው፡፡በእጁ መርፌ ይዟል። ጀምሺድ የነገረኝን ታሪክ አስታወስኩ ሀኪሙ ዙሪያውን ተገላመጠና ሲያበቃ፣ ማንም እንደሌለ ካረጋገጠ በኋላ፣ በሹክሹክታ

«ይምጡ ልውጋዎት» አለኝ
ዝም ብዬ አየሁት
ካልፈለጉ ላስገድድዎት አልችልም፡፡ ነፃነትሳ? ዳሩ፤ ለኔ ያው ነው፡፡ ደሞ ደንታ የለኝም እንጂ» እያለ ለራሱ እያጉረመረመ ወደ ጀምሺድ ተኝቷል መሰለኝ ብዬ ደረጃውን መውረድ ስጀምር
በሩ ተከፈተ። ዘወር ስል ኒኮል ነች
“ይቅርታህን። አስጠበቅኩህ? ሽንት ቤት ነበርኩ» አለችኝ::
አመዳም ፀጉሯ ተሞነጫጭሯል። ሸሚዟ በአንድ በኩል ከጉርዷ
ወጥቷል። ገባኝ፡፡ ጀምሺድ አልጋው ውስጥ ትራስ ተደግፎ
እንደተቀመጠ፣ እየሳቀ
ዶክተር ሽቫይትዘር መርፌ ይውጉህ?» አለኝ፡፡ የሱም ፀጉር
ተሞነጫጭሯል ግምባሩ ላይ ወድቋል፡፡ ግን ፈፅሞ የታመመ
አይመስልም።
ኒኮልና ጀምሺድ እየተሻሙ ስለዶክተሩ ነገሩኝ። ሰውን
የማይጎዳ ሰላማዊ እብድ ነው፡፡ የመጣውን ሁሉ መርፌ ልውጋዎት? እያለ ይጠይቃል፣ አሉኝ። አነጋገራቸው አንድ ነገር ለመደበቅ የፈለገ ሰው አነጋገር ይመስላል

ትንሽ ቆይታ ኒኮል ከፍል አለብኝ ብላ ሄደች፡፡ ጀምሺድ
ስለጎረቤቱ ዶክተር ኮሚክ ወሬ እያወራ ሲያስቀኝ ቆየና ተነስቶ ወደ ሽንት ቤት ገባ
በፍጥነት በፀጥታ ተነስቼ የራስጌውን ፍራሽ አነሳሁ፡፡ አልጋው ሽቦ ላይ አንድ ጥቁር የሴት ሙታንቲ፡፡ ሙታንቲው ኣጠገብ አንድ አምስት የተጨማደደ ለስላሳ ክሊኔክስ ወረቀት ወረቀቶቹ ፅጌረዳ አይነት ስለሆኑ ርጥበታቸው ለአይን ያስታውቃል። ጎምበስ
ብዬ ወረቀቶቹን አሸተትኩ፡፡ የግብረ ስጋ ሽታ። ያለጥርጥር፡፡
ተመልሼ ወምበሬ ላይ ከተቀመጥኩ በኋላ፣ ተነስቼ የሰው ጉድ ሳሽት ታየኝና፣ ለራሴ ሸርሎክ ሆምዝ!» ብዬ በሀይል መሳቅ
ጀመርኩ ጀምሺድ ከሽንት ቤቱ «ለምን መሳቅ?» አለኝ
«መርፌ መውጋት» አልኩትና ሳቄን ቀጠልኩ
ሉልሰገድ ስለኒኮል ባይነግረኝ ኖሮ፣ ኒኮልንና ጀምሺድን እጠረጥር ነበር? አይመስለኝም
በጀምስድ አገር ደምብ የሚያፈላው ሻይ በጣም ይጣፍጣል።
እሱን እየጠጣን ወሬ ጀመርን
ጀምሺድ እንደሚለው ከሆነ፣ በቁማር መክበር አይቻልም።
በቁማር የሚከብር ቁማር ቤቱ ብቻ ነው፡፡ ምንም ያህል ብትበላ
ያችን የበላ ሀትን ተመልሰህ እስክታስበላ ያቁነጠንጥሀል። በቁማር ለመክሰር እንጂ ለመክበር አይቻልም። እንዲህ ከሆነ ጀምሺድ ለምን
ቁማር ይጫወታል? ... ሰካራሙ ለምን ይጠጣል?ለጀምሺድ እንደሚታየው፣ ኑሮ ጨቅጫቃ ሚስት ናት፡ ና ምግብ ብላ፣ ና ተኛ፣ ና ሽንት ቤት ሂድ፣ ና ትምህርት ተማር፣ ና ይህን አድርግ፣ ና ያንን ፈፅም፣ እያለች መነዝነዝ ነው ስራዋ፡፡ ታድያ የሰው ልጅ ከዚህ ሁሉ ጭቅጭቅ ለመሸሽ አንዳንድ ጊዜ ቢሰክር ይፈረድበታል?

ጀምሺድ ዮኑሮን ችኮነት ሊረሳ የሚችለው ቁማር ቤት የሄደ
እንደሆነ ነው። ቁማር ቤት ውስጥ ያለችው ኑሮ፣ ነዝናዛ ችኮ ሚስት
ሳትሆን፣ የማትጠገብ፣ ለዛዋ ሁልጊዜ የሚታደስ ውሽማ ናት። ኮት የምታስሽጥ ውብ ውሽማ!

«እኔ ቁማር ስጫወት መኖሬን እረሳለሁ፡፡ መኖሬን ሲረሳ፣ ያን
ጊዜ ኑሮን ኖርኳት ነኝ ማለት ነው:: ሌላ ጊዜ ኑሮን ሲኖራት፣ እኔን
እያታለልኩ ነው ችኮ ናት ደስታ የለም፡፡ ቁማር ጊዜ ግን፣ ቁማር
ፈፅሞ ሲውጠኝ ሳለ። ኑሮ መሀል ውስጥ እገባ፣ ከንቱ አይደለች፣
እላያትም እኖራታለሁ ማለት»

ጀምሺድ ስለቁማር ሲያወራ አይኖቹ አይስቁም

እንስሳ ኑሮ አይሰለቸውም (ይሄ የጀምሺድ አስተሳሰብ ነው)
ምክንያቱም እንሰሳ ይኖራል እንጂ መኖሩን አያውቅም። ስለዚህ ኑሮ
አይመረውምም አይሰለቸውምም። ስለዚህ ነው እንሰሳ ራሱን የማይገለው። «በሬ ወይም አህያ ወይም አይጥ ወይም ውሻ ወይም ሌላ፣ ራሱ ገደለ እሱ ሰምተሀቸዋል ታውቃለህ?» ሰውን ከእንሰሳ
የሚለየው ማሰቡ አይደለም፡፡ በመጠኑ ይሁን እንጂ እንሰሳም
ያስባል። ሰው ከእንሰሳ የሚለየው በመሳቁ አይደለም። ዝንጀሮም
ይስቃል። ሰው ከእንሰሳ የሚለየው፣ ህይወቱን እየኖራት እንደሚኖራት በማወቁ፣ ከህይወት በኋላ ሞት መከተሉን በማወቁ፤ እነዚህም እውቀቶች ለሰው ልጅ ኑሮን ከንቱ፣ ሞትን መራራ በማድረጋቸው በዚህ ነው ሰው ከእንሰሳ የሚለየው

በመሰረቱ ህይወት ግሩም ስጦታ ናት። ኑሮ ግን ይሰለቻል።
ሀዘን ሞልቶበታል፡፡ ብስጭት ይበዛበታል፡፡ በሽታ ወሮታል። ሞት
ደሞ ይቆያል እንጂ አይቀርም። ስለዚህ መሞት ላይቀር፣
ብስጭት ሊበዛ፣ ለምን አሁኑኑ
አንሞትም? ለምን ራሳችንን አንገድልም? ችኮ የሆነ ሀዘን፣ ብስጭት የወረሰው እውቀት ምኑ ይወደዳል? ራሳችንን የማንገድለው ሞትን
ስለምንፈራ ብቻ ነው። ፈሪ ነን በቃ፡፡ ይኸው ነው ስለዚህ፤ ልናደንቀው የሚገባ ሰው ማን ነው? ራሱን ለመግደል የደፈረ ሰው ነው፡፡ እሱ ብቻ ነው። እኛሳ ዋናው አላማችን ምን መሆን አለበት? ይህን የመሰልቸት ቀሚስ አውልቀን ወዲያ መጣል
በተቻለ ፍጥነት ራሳችንን መግደል
«እኔ ራሴ ለመግደል ዋና ምኞት፡፡ ግን እስካሁን ድፍረት የለም፡፡ አንድ ቀን ግን ለመድፈር ተስፋ! ያን ጊዜ እኔ ሰው::እውነተኛ ሰው፡፡ እስከዚያ ድረስ ግን ከንቱ ቁማርተኛ።»

ጀምሺድ ራስን ስለመግደል ሲያወራ አይኖቹ አይስቁም

በልግ ከዛፎቹ ላይ ቡናማ፣ ቀይና ወርቃማ ቀለማቱን ሰብስቦ
የሙቀትና የውበት ጓዙን ጠቅሎ ኤክስን ለቆ ሊሄድ ተነሳ የኤክስ አየር መብረድ ጀመረ። ሽማግሌዎቹ፣ አሮጊቶቹና
ጥቁሮቹ፣ ሹራብ መደረብ ካፖርት መልበስ ጀመርን። ወጣቶቹ
ፈረንጆች ግን ገና ብርዱ ሊሰማቸው አልጀመረም
ሉልሰገድን ኒኮል እምቢ ስትለው እኔጋ መጥቶ «ካፌ ኒኮል»
ይወስደኝና፣ እየቀረበን በመጣው የክረምት ብርድ ምክንያት፣ ቤት
ውስጥ ገብተን ቁጭ ብለን ስለኒኮል ያወራልኛል። የጭገሯ ፀጉር እንደራሷ ፀጉር አመዳም ሳይሆን፣ ንፁህ ወርቅ ቀለም የተቀባ ነው፤ወተት የመሰለው ነጭ ቆዳዋ ላይ ረዣዥም የተጠላለፈ ውብ ወርቃማ ሀረግ መስሎ በቅሏል። ታዲያ እምሷ ዳር የበቀሉት ፀጉሮች፣ ውሀ ዳር እንደበቀለ ቄጠማ ናቸው፤ አንዳንዶቹ ከሁለቱ ከናፍር ተንጠራርተው ተጠላልፈው፣ ጎምበስ ብለው እምሷ ውስጥ
የፍቅር ውሀ ይጠጣሉ. .. ወዘተርፈ

አንድ ቀን ግን፡ ስለሷ ያወራልኛል ብዬ ስጠብቅ ስለጀምሺድ
ሊነግረኝ ጀመረ፡፡ ሁለቱ ጓደኛሞች ሆነዋል። ጀምሺድ ቁማር
ለመጫወት ካዚኖ ሲሄድ ሉልሰገድን ይዞት ይሄዳል። ከዚህም በላይ ሉልሰገድ የጀምሺድ ሻይ ሱስ ይዞታል። ሁለቱም ሻይውን የሚጠ
ጡት በኢራን አገር ወግ ነው። በፊት ከአራት ማእዘኑ ስኳር ላይ
ይገምጡና፣ ቀጥሎ ሻይ ፉት ይሉበታል፣ እንጂ ስኳሩን ሻይው
ውስጥ አይጨምሩትም
👍232
#ምንዱባን


#ክፍል_አስራ_አምስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

እኔ እባ ሻምፕማትዩ ነኝ:: የኖርኩትም አአሀገሪዩ ከመሴይ ባሉ ቤት ነው፡፡ እኔ አሁን የሰለቸኝ እናንተ የምትሉትን ታሪክ መስማት ነው:: ልክ እብድ ውሻ እንደሆንኩ ዓይነት ሰው ሁሉ እኔን የሚከታተልበት ምክንያት
አይገባኝም፡፡»

አቃቤ ሕጉ የመሐል ዳኛን እያየ ተናገረ፡፡

«ጌታዬ፣ ይህ ሰው አላዋቂ በመምሰል የጮሌ ተግባር እየፈጸመ ነው:: ሆኖም የጀመረው የብልጠት ሥራ ፍሬ እንደማያፈራለት አውቃለሁ::
አሁንም የዚህን ሰው ብልጠት ለማክሸፍ የፍርድ ቤቱ፡ መልካም ፈቃድ ከሆነ አራቱ ምስክሮች ተጠርተው እንደገና በአንድነት እንዲመሰክሩበት
ይደረግ ዘንድ በአክብሮት እጠይቃለሁ::»
«አቃቤ ሕጉን ለማሳሰብ የምፈልገው ግን የፖሊሱ አዛዥ ዣቬር የምስክርነት ቃሉን ከሰጠ በኋላ አጣዳፊ ሥራ ስለነበረበት ይቅርታ ጠይቆ ሄዷል፡፡ የሄደውም ፍርድ ቤቱ ስለፈቀደለት ነው» አሉ የመሐል ዳኛው::

«እውነት ነው» አለ አቃቤ ሕጉ፧ መሴይ ዣቬር እዚህ ሊገኙ
አይችሉም፤ ሆኖም እርሳቸው ለፍርድ ቤቱ ያሰሙት የምስክርነት ቃል በድጋሚ ማሰማት ይቻላል:: መሴይ ዣቬር የተከበሩ ሰው ናቸው::ሥራቸውን የሚያከብሩና ለእውነት የቆሙ ሰው ናቸው:: ስለዚህ እርሳቸው የሰጡት የምስክርነት ቃል የሚጠራጠሩት አይሆንም:: እርሳቸውም ሲናገሩ
«የተከሳሹን ክህደት ለማስተባበል የመሐላ ቃል ወይም የተለየ ማረጋገጫ አያስፈልገንም:: ይህን ሰው በግልጽ ለመለየቴ ጥርጥር የሌለው ነው። የዚህ ሰው ስም ሻምፕማቲዩ ሳይሆን ወንጀለኛውና እጅግ የሚፈራው ዥን ቫልዣ ነው:: ቱሉን ውስጥ የሚገኘው እስር ቤት ዘቦች እዛዥ በነበርኩበት ጊዜ ሰውዬውን ብዙ ጊዜ አይቼዋለሁ:: ቃሌን እንደገና ብደግም ገና ሳየው ነው ያወቅሁት» ብለዋል፡፡

የዚህ ሰው አገላለጽ በዳኞቹና ከዚያ በነበረ ሕዝብ ላይ የማሳመን
ኃይል ነበረው፡፡ የመሴይ ዣቬርን የምስክርነት ቃል አስተዋጽኦ ካሰማ በኋላ ከእስር ቤት የመጡት እስረኞች ቃላቸውን በድጋሚ እንዲሰጡና አንዳንድ ጥያቄ እንዲቀርብላቸው አቃቤ ሕጉ ጠየቁ፡፡

የጠባቂዎች ኃላፊ ምስክሮችን በድጋሚ እንዲያስገባ ዳኛው አዘዙ።ዣን ቫልዣ ከእስር ቤት ካመለጠ በኋላ የእስራት ዘመኑን ጨርሶ የወጣውን ብሪቬት የተባለው ሰው በመጀመሪያ ተጠራ:: ብሪቬት እድሜው ስልሣ
ዓመት ነበር፡፡

«ብሪቬት» አሉ ዳኛው፤ «
ለመድገም የሚቀፍ የረጅም ጊዜ ቅጣት ተቀብለሃል፤ ስለዚህ መሐላ ለመማል አትችልም» ሲሉት ብሪቬት አቀረቀረ፡፡
ሆኖም» በማለት ዳኛው ንግግራቸውን ቀጠሉ፤ «አንድ ሕግ ያዋረደውና ሥራው ያስቀጣው ወንጀለኛ በውስጡ ሌላውን የማክበርና የሌላውን
መብት የመጠበቅ ስሜት ይኖረዋል፡፡ ምናልባት ቀደም ሲል በሰጠኸው የምስክርነት ቃል በሕሊናህ ዳኝነት የምታሻሽለው ነገር ቢኖር እንድታሰማን
እጠይቅሃለሁ፡ ተከሳሹም ተነስቶ እንዲቆምና መስካሪውም ተከሳሹን እያየ እንዲናገር እንዲሁም ጊዜው በመቆየቱ መስካሪው አስቦና አሰላስሎ አሳቡን እንዲሰጠን እያስታወስኩ ይህ ሰው ቀደም ብላችሁ እስር ቤት ውስጥ አብራችሁ የነበራችሁት ዣን ቫልዣ የሚባል እስረኛ ለመሆኑ አረጋግጠህ
በድጋሚ ለመመስከር ትችል እንደሆነ የምስክርነት ቃልህን እንድትሰጥ በድጋሚ እጠይቃለሁ፡፡

ብሪቬት እስረኛውን አተኩሮ ተመለከታቸው:: ከዚያም ፊቱን ወደ ዳኞቹ አዞረ:: ብሪቬትና ሻምፕማትዩ ዓይን ለዓይን ተፋጠጡ፡፡
«አዎን ጌታዬ፤ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ለመሆኑ በመጀመሪያ የለየሁት እኔ ነኝ፡፡ አሁንም ቢሆን ቃሌን አልለውጥም:: ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ራሱ ነው:: ቱሉን ከሚገኝ ወህኒ ቤት የገባው በ1796 ዓ.ም ሲሆን ከዚያ ያመለጠው በ1815 ዓ.ም. ነው:: እኔ ከእስር ቤት የወጣሁት እርሱ ባመለጠ በዓመቱ ነበር፡፡ ሰውዬው አሁን ሲያዩት በመጠኑም ቢሆን ለውጥ አለው:: ግን ይህ
ከእድሜ ጋር የሚሄድ በመሆኑ ያሳየው ለውጥ ሊያሳስተኝ አይችልም፤ዣን ቫልዣ ራሱ ነው፡፡»

«ቁጭ በል» አሉ ዳኛው:: ተከሳሹ ግን እንደቆመ ይቆይ::
ሸነልዲዩ የሚባል ምስክር እንዲገባ ተደረገ፡፡ ቱሉን ውስጥ ከሚገኝ እስር ቤት የእድሜ ልክ እስረኛ ነው:: የምስክርነት ቃሉን እንዲሰጥ ነው ከእስር ቤት የተጠራው:: ቁመቱ አጠር ያለ የሃምሣ ዓመት አዛውንት
ነው:: ምንም እንኳን ፊቱ የተጨማደደ ቢሆንም በሁኔታው ነቃ ነቃ ያለና ተቅበጥባጭ ሰው ነው፡፡ ዳኛው ለብሪቬት ያሉትን ለእርሱም ደገሙለት:: «በሠራኸው ወንጀል
የተነሣ በመማል ቃልህን ታከብራለህ ለማለት ስለማያስደፍር መማል
አትችልም» ሲሉት ሻምፕማቲዩ ቀና ብለው ተመልክተው ከዚያ የነበረውን ተመልካች በዓይን ቃኙት:: ዳኛው አሳቡን እንዲሰበስብና እስረኛውን በትክክል ያስታውሰውና ያውቀው እንደሆነ ጠየቁት፡፡

ሺኒልዲዩ ከት ብሎ ሳቀ፡፡
“ታውቀው እንደሆነ አሉኝ! አምስት ዓመት ሙሉ በአንድ ሰንሰለት
እኮ ነው ታስረን የነበረው አንተ በአንድ ብረት ታስረን አልነበረም?

‹‹ቁጭ በል» አሉ ዳኛው፡፡

የጠባቂዎች ኃላፊ ኮሽፔል የተባለውን መስካሪ አስገባ፡፡ ይህም ሰው የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት እስረኛ ሲሆን ኮሽፔል ከብቶችን የሚያግድ ገጠሬ ነበር፡፡ ወደኋላ ግን ከብት ማገዱን ትቶ ወደ ሽፍትነት የተዘዋወረ ሰው ሲሆን ይህ ሰው ሲያዩት ከተከሳሹ ይበልጥ የቂላቂል መልክ ነው
ያለው፡፡ ገና ሲፈጠር ተፈጥሮ ፊትዋን ያዞረችበት፧ የአውሬ መልክ ያለውና እስር ቤት እጣ ርስቱ የሆነ ፍጡር ይመስላል፡፡ ዳኛው ለሌላቹ ያሉትን የተናገሩትን በመድገም እርሱንም ጠየቁት::

«ይህ ከፊትህ የቆመውን ሰው ሳትጠራጠርና ሳታወላውል ትለየዋለህ፤ ታውቀዋለህ?»

«ዣን ቫልዣ ነው» አለ ኮሽፔል፡፡ «ዣን ቫልዣ እያለም ሰዎች
ይጠሩት ነበር፡፡ ጉልበት ያለው ሰው ነው::»
እያንዳንዱ መስካሪ በተናገረ ቁጥር ከዚያ የነበረ ሁሉ ተከሳሸ «ዣን ቫልዣ ነው ወይስ አይደለም» የሚለውን ጥርጣሬ እየተወ ወደ ማመን ደረጃ እየተቃረበ ሄደ፡፡ ሁሉም በየፊናው አጉረመረመ፡፡ መስካሪዎች ተመሳሳይ የሆነ የምስክርነት ቃላቸውን ሲሰጡ ሰው በይበልጥ ተንጫጫ፡፡ ሁሉም በያለበት በሻምፕማቲዩ ላይ ፈረደ:: ኣንድ ምስክር ያለወን ሌላው
እያጠናከረው ሲሄድ ተከሳሹ ጆሮአቸውን ማመን ተስኖአቸው በይበልጥ ፈዘዙ፡፡ የመጀመሪያው ምስክር ቃሉን እንደሰጠ «አያ ግድ የለም፧ ሌላ ምስክር አለ» በማለት እርስ በራሳቸው ሲነጋገሩ ከአጠገባቸው የነበረው
ምስክር ሰማቸው:: የሁለተኛው ምስክር ቃሉን ሲሰጥ ድምፃቸውን ትንሽ ከፍ አድርገው «ይሁና፣ ጥሩ ነው» አለ:: የመጨረሻውና ሶስተኛው ምስክር ቃሉን ሲሰጥ በጣም ጮክ ብለው «በጣም ጎበዝ ሲሉ ተናገሩ፡፡

ዳኛው ወደ ተከሳሹ ፊታቸውን አዞሩ፡፡

«መስካሪዎች ያሉትን ሰምተዋል፤ ታዲያ ምን ይላሉ?

«ምን እላለሁ! ሁሉም ጎበዞች ናቸው!»

ሁሉም በያለበት ተንጫጫ ፤ ሁሉም በየፊናው የግሉን ፍርድ
በመስጠት ይህ ሰው አለቀለት» አለ፡፡

«ፀጥታ እባካችሁ» አሉ ዳኛው፤ «አሁንስ አጠቃልለን የውሳኔ አሳብ
መስጠት ይኖርብናል፡፡»

ዳኞች ከተቀመጡበት አካባቢ ጎርነን ያለ ድምፅ ተሰማ፡፡

«ብሪቬት፣ ሽኔልዲዩና ኮሽጌል እስቲ አንድ ጊዜ ወደዚህ ተመልከቱ፡»
መስካሪዎች ገና ድምፁን ሲሰሙ ክወ አሉ:: በጥፊ የተመቱ መሰላቸው፡፡ ሦስቱም በአንድ ጊዜ ፊታቸውን አዞሩ:: ባለስልጣኖች
ከሚቀመጡበት ወንበር ላይ ተቀምጦ የነበረ አንድ ሰው ተነስቶ ወደ ችሎቱ፡፡መሐል ቀረበ፡፡ የመሐል ዳኛው፣ ሕግ አስከባሪውና ሌሎች አንድ ሃያ
የሚሆኑ ሰዎች ይህ ሰው ማን እንደሆነ አወቁት::

«መሴይ ማንደላይን!»
👍15👎1