አትሮኖስ
282K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
497 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_አምስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

...ጥላዬ፣ ከአለቃ ሔኖክ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እየመሠረተ ሲመጣ፣ብዙ ጊዜ አብሯቸው መቀመጥና መጫወት ሥዕል ከመሣል ቀጥሎ የሚያስደስተው ነገር ሆነ። ወደፊትም እንደሳቸው ጥበበኛ መሆን አበክሮ ተመኘ። ላደረጉለት ሁሉ ሲያመሰግናቸው ቢውል አላጠግበው አለ።

“አለቃ ላረጉልኝ ሁሉ እመቤቴ ምላሹን ትስጥዎ” አላቸው፣ አንድ
ቀን እንደወትሮዋቸው ግቢ ውስጥ ተቀምጠው ሲያወሩ።

“እኔኮ ማስተምረው ኸተማሪዎቸ ጥቅም አገኛለሁ ብየ ማዶል። ልክ
መምህሬ የነበሩት አለቃ ወልደሰንበት ደከመኝ ሳይሉ፣ ሚያውቁትን ሁሌ ሳይሸሽጉ እንዳሳተማሩኝ ሁሉ ተማሮቸን ማስተማር ፈልጋለሁ።ዋጋየ እናንተ ተማሮቸ ጥሩ ተምራችሁ ለጌታችን ያላችሁን እምነት፣ ክብርና ፍቅር በሥራችሁ ስታሳዩ፣ የመጻሕፍትን ምሥጢር አንብባችሁና ተረድታችሁ በሥዕል ስትገልጡ ነው። ሥዕል ዋናው ዓላማው ቤተስኪያንን ማስጌጥ ማዶል። ሥዕል እኮ ታሪክ ነው ሚነግር፤
ሥዕሉ ራሱ እኮ ወንጌል ነው። ምእመኑ የመጻሕፍቱን ምሥጢር
አውያቁም፣ አያነቡም፡ አይረዱም። ስለዝኸ የእናንተ ሥራ የመጻሕፍቱን ምሥጢር... ወንጌሉን በሥዕል እንዲረዱና መንፈሳዊነት፣ አክብሮትና
ፍራት በልባቸው እንዲያድር ማረግ ነው። ባለፈው እንደነገርኩህ ካህናቱ አምስቱን አዕማደ ምሥጢር በንባብ በሐተታ ይማራሉ።ምእመኑ ግን በሥዕል ነው ሚማር። ቀዳሚው ምሥጢረ ሥጋዌ ነው፣ኸገብርኤል ብሥራት ትጀምራለኽ። ገብርኤል ማርያምን ትፀንሲ ይላታል። ኸዚያ ልደቱን ትሥላለኸ። ልደቱን ስትሥል ሰብአ ሰገል እረኞቹም አሉ። ግዝረቱን ደሞ ቀጥለኽ መሣል ነው፤ ስምዖን አለ አሉ፣ አድግና ላሕም አሉ... ጌታን በትንፋሻቸው ያሞቁት፣ መልአኩም አብሮ ሚጠቀስ፤ ዓይኖቼ ማዳንህን ስላዩ በል ውሰደኝ ብሎ ጸልዮ
ይሞታል ። ኸዚያ ምሥጢረ ጥምቀቱ፣ ተአምራቱ፣ ቃና ዘገሊላው፣ አስተምህሮቱ አለ። ኸዚያ ምሥጢረ ቁርባንን ትሥላለህ፤ ሥቅለቱን አብረህ። ቀጥለህ ትንሣኤውንና ዕርገቱን ትሥላለህ። መጻሕፍት
በስንትና ስንት ምዕራፍ ያካተቱትን ታሪክ ሠዓሊው በጥቂት ብራናዎች አሣምሮ ቀምሮ ያስቀምጠዋል። ስለዚህ ምሥጢራቱን፣ የቱ ቀድሞ
የትኛው ሚከተል መሆኑን መመርመር ያስፈልጋል፤ የቀለም ማሳመር ብቻ ለሠዓሊነት አይበቃም።”

ጥላዬ፣ በተመስጦ አዳመጠና “እሺ የንታ፤ ንባቤንም ሥራዬንም
ተግቼ እቀጥላለሁ፤ ቃለ ሕይወት ያሰማልኝ” አላቸው፣ ትምህርታቸውን ከልቡ አዳምጦ።

“ዋናው ነገር እሱ ነው... ትጋት” አሉት፣ ሌባ ጣታቸውን እያወዛወዙ። “አንተን ትጉ ሁነህ አግኝቸኻለሁ። ምን ስጦታ ያለው ቢሆን ትጋት የሌለው ተማሪ አልወድም። ሥዕል ችሎታ ቢኖርህ ትጋት ኻላሳየህ ለሥራህ ጥሩ አይሆንም። አሁን በየቦታው ያሉት የተከበሩት ሠዓሊዎች አለሱ ሌላ ንሮ የላቸውም። አንዳንድ ተማሪ ይመጣል ኸኔ ዘንድ።እንዳው ብቻ ጫር ጫር አርጎ ቤተክሲያን ውስጥ ገብቶ ሥዕል
መሣል ይፈልጋል። ይኸ እንዴት ብሎ ይሆናል? ሥዕል ቀልድ ነው
እንዴ? እኔማ እንደዚያ ያለውን ተማሪ ኸኔ ዘንድ አላቆየውም። አንተ ለሥዕልም ለቤተክሲያንም አትሆንም ብየ ነው ምሰደው። ችሎታ አለ ትጋት ምንድርነው? አይምሰልህ ጥላዬ ሥራን ትልቅ ደረጃ ሚያደርሰው ትጋት ነው። እኔስ ብሆን አንድ ተማሪ ትጋት ካላሳየ ኸሱ ጋር ስለምን
እደክማለሁ? እስቲ በል ንገረኝ?”
“ውነት ነው... ውነት ነው” አለ፣ ጥላዬ ራሱን በአዎንታ እየነቀነቀ።

ልቡ ተነካ። ሥዕል እየሣለ ቤተክርስቲያንን ማገልገል እንዳለበት ይመኝ እንጂ፣ እንደዚህ ጠለቅ ብሎ ነገሩን አስቦበት አያውቅም።በአካባቢው የሚያያቸውን ቤቶች፣ ሰዎችና እንስሳት ቤታቸው ግድግዳ
ላይ ሲሥል ቢቆይም፣ የሚሥላቸውን ምስሎች ለዘላለም ቀርጾ ማስቀመጥ ከሚመኛቸው ነገሮች አንዱና ዋነኛው ምንትዋብን ነው። በተለይም
ደግሞ ነጠላ ተከናንባ ከቤተክርስቲያን ስትወጣ ያያት የነበረውን።

“ለሥዕል ያለኝ መውደድ ለብቻ ነው። ኸርሶ ዘንድ መማሬ ደሞ
ይበልጥ እንድወደው አድርጎኛል።”

“እኔም ለሥዕል ይኸ ነው ተብሎ ማይነገር ፍቅር አለኝ” አሉት።
“አለሱ ሌላ ሕይወት የለኝም። ሥዕል ሳይ እመራመራለሁ። የሠራሁትን ሥራ መልሼ ሳየው 'በውነት ይኸን የሠራኹ እኔ ነኝ ወይስ በኔ እጅ ራሱ ባለቤቱ ሣለው ብዬ እደነቃለኹ። ሥዕል የእዝጊሃር ወይም የደቂቀ
አማልክቱ ሥራ እንጂ የእኛ የደካሞቹ ፍጥረት አይመስለኝም። ጥላዬ...ሥዕል እኮ እንደ ቅኔ ከሳቴ ብርሃን ነው... የተደበቀውን ምሥጢር ሁሉ ሚገልጥ... ብርሃን ሚሰጥ። ለዝኽ ነው ቅኔን ብዙ ሊቃውንት ልሳነ መላእክት ነው ሚሉት።

ጥላዬ፣ መስማማቱን ለማሳየት ራሱን ነቀነቀ። “የንታ ሥዕል ለመማር እንደዛ ስመኝ ቆይቸ አሁን መማር በመቻሌ ዕድለኛ ሁኛለሁ።”

“ዕድል ኸሰማይ አይወድቅም” አሉት፣ ፊታቸውን ወደሱ መልሰው።
“ዕድል እንደ ሥዕል ነው። ሚገባው ዘንድ ነው ሚኸድ። ማይሆነው... ዝግጁ ሁኖ ማይጠብቀው ዘንድ አይኸድም። ወይም ማይሆነውን አይጣራም። ዕድል ልክ እንደ ሥዕል ሚፈልገውን ያውቃል፣ አውቆም
ይጣራል፣ ወይም ራሱ ወደሱ ይኸዳል። እንዳንተ ያለውን... የነፍሱን ጥሪ ሚያቀውን ኻለበት ፈልጎ ያወጣዋል። አንተም ዛዲያ ስትፈልገው፣ እሱም ሲፈልግህ... ስትፈላለጉ ቆይታችሁ ተገናኛችሁ።”

“አየ የንታ የእዝጊሃር ቸርነት ተጨምሮበት ነው።”

እዝጊሃር እኮ ማትችለውን አይሰጥህም። ጎበዝ ብትሆን ነው የሰጠህ።”

ውነት ነው አለ፣ ለራሱ።

“አሁን ይልቅ ምመክርህ” አሉት፣ ሌባ ጣታቸውን እያወዛወዙ፣ “ደብረ ወርቅ ኸደህ ሌሎች አስተማሮች ዘንድ መማርን ነው። እንደ ሌላው ትምርት ሁሉ ሥዕል እየተዘዋወርህ ስትማር ብዙ ትምርት ትቀስማለህ፣
ችሎታህንም ታዳብራለህ። ደብረ ወርቅ ታላላቅ የሥዕል መምህሮች
አሉ። እኔ እንደምታየው እያረዥሁ ነው። ኸንግዲህ እንደድሮው
ማስተማር አልችልም። አንተንም ገና ሳይህ ቀልቤ ስላረፈብህ
ተቀበልኩህ እንጂ ማስተማር እተዋለሁ እያልሁ ነበር” አሉት።

“የንታ ኸርሶ ዘንድ በቆየሁ። ኸርሶ መለየቱ ይከብደኛል።”

“ምን ይደረግ። እየደከመኝ መጣሁ።”

“ኸዝሁ ሌላ መምር ዘንድ ብቆይስ?”

“ሊቀጠበብት ኣዳሙ ዘንድ ነው እንድትማር የፈለግሁት። አዳሙ
ወደር ማይገኝለት መምህር ነው። ለኔም የረዥም ግዝየ ወዳጄ
ነው። እስታሁንም ብዙ ተማሮቸን ወደሱ ልኬያለሁ። አንተም ኸሱ
ዘንድ እንድትማር ነው ምፈልግ። ትምርትህን ስትጨርስ ተመልሰህ
ትመጣለህ።”

ጥላዬ፣ ጐንደር የዕድል በር ከፈተችልኝ፣ አለቃን መምህሬ፣ ጐንደርን ቤቴ ብሎ ተመቻችቶ ተቀምጦ፣ እንደዚህ ዓይነቱ ዱብ ዕዳ ሲመጣበት ደነገጠ፤ ሆድ ባሰው፤ መንፈሱ ተረበሸ፤ ተስፋ ሊቆርጥ ቃጣው።ከአለቃ ሔኖክ ሥር ሆኖ ታላቅ ሠዓሊ ለመሆን ያደረበትን ምኞት፣ከቤቱ ሲወጣ የሥዕል ንጉሥ ለመሆን የነበረውን ሕልም ሁሉ ጉም ሸፈነው። ደብረ ወርቅ ይሂድ ወይንም እዛው ጐንደር ሌላ አስተማሪ ዘንድ ይማር ለመወሰን አቃተው፤ ግራ ገባው። ምንትዋብን በአካል
ባያገኛትም እንኳ ከእሷ ርቆ መኖሩ ደግሞ አሳሰበው፣ አሳዘነው።....
።።።።።።።።።።፡፡።።።።።።።።።።።።

“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”
👍13😁1
#ትኩሳት


#ክፍል_አስራ_አምስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

ባህራም
ሞት

ያን ሰሞን ጀምሺድ ታሞ ተኛ፡፡ ልጠይቀው ወደ ቤቱ ሄድኩ።
ሌሎቹ በሚጠይቁት ሰአት ብሄድ ምንም አልጠቅመውም በማለት፣
በትምህርት ሰአት ሄድኩ። ፎቁን ወጥቼ በሩን ብሞክረው ተቆልፏል። ደወሉን ተጫንኩት፣ ውስጥ ሲደውል ተሰማኝ፡፡ ቆየሁ
የጀምሺድ ቤት ሳይሆን፣ በግራ በኩል ያለው የጎረቤቱ በር
ተከፈተ። መነፅር ያደረገ መላጣ ሽማግሌ ሀኪም አንገቱን ብቅ ከርጎ አየኝ፡፡ አየሁት። ከበሩ ወጣ፡፡ ነጭ የሀኪም ኮቱ በጣም ንፁህ ነው፡፡በእጁ መርፌ ይዟል። ጀምሺድ የነገረኝን ታሪክ አስታወስኩ ሀኪሙ ዙሪያውን ተገላመጠና ሲያበቃ፣ ማንም እንደሌለ ካረጋገጠ በኋላ፣ በሹክሹክታ

«ይምጡ ልውጋዎት» አለኝ
ዝም ብዬ አየሁት
ካልፈለጉ ላስገድድዎት አልችልም፡፡ ነፃነትሳ? ዳሩ፤ ለኔ ያው ነው፡፡ ደሞ ደንታ የለኝም እንጂ» እያለ ለራሱ እያጉረመረመ ወደ ጀምሺድ ተኝቷል መሰለኝ ብዬ ደረጃውን መውረድ ስጀምር
በሩ ተከፈተ። ዘወር ስል ኒኮል ነች
“ይቅርታህን። አስጠበቅኩህ? ሽንት ቤት ነበርኩ» አለችኝ::
አመዳም ፀጉሯ ተሞነጫጭሯል። ሸሚዟ በአንድ በኩል ከጉርዷ
ወጥቷል። ገባኝ፡፡ ጀምሺድ አልጋው ውስጥ ትራስ ተደግፎ
እንደተቀመጠ፣ እየሳቀ
ዶክተር ሽቫይትዘር መርፌ ይውጉህ?» አለኝ፡፡ የሱም ፀጉር
ተሞነጫጭሯል ግምባሩ ላይ ወድቋል፡፡ ግን ፈፅሞ የታመመ
አይመስልም።
ኒኮልና ጀምሺድ እየተሻሙ ስለዶክተሩ ነገሩኝ። ሰውን
የማይጎዳ ሰላማዊ እብድ ነው፡፡ የመጣውን ሁሉ መርፌ ልውጋዎት? እያለ ይጠይቃል፣ አሉኝ። አነጋገራቸው አንድ ነገር ለመደበቅ የፈለገ ሰው አነጋገር ይመስላል

ትንሽ ቆይታ ኒኮል ከፍል አለብኝ ብላ ሄደች፡፡ ጀምሺድ
ስለጎረቤቱ ዶክተር ኮሚክ ወሬ እያወራ ሲያስቀኝ ቆየና ተነስቶ ወደ ሽንት ቤት ገባ
በፍጥነት በፀጥታ ተነስቼ የራስጌውን ፍራሽ አነሳሁ፡፡ አልጋው ሽቦ ላይ አንድ ጥቁር የሴት ሙታንቲ፡፡ ሙታንቲው ኣጠገብ አንድ አምስት የተጨማደደ ለስላሳ ክሊኔክስ ወረቀት ወረቀቶቹ ፅጌረዳ አይነት ስለሆኑ ርጥበታቸው ለአይን ያስታውቃል። ጎምበስ
ብዬ ወረቀቶቹን አሸተትኩ፡፡ የግብረ ስጋ ሽታ። ያለጥርጥር፡፡
ተመልሼ ወምበሬ ላይ ከተቀመጥኩ በኋላ፣ ተነስቼ የሰው ጉድ ሳሽት ታየኝና፣ ለራሴ ሸርሎክ ሆምዝ!» ብዬ በሀይል መሳቅ
ጀመርኩ ጀምሺድ ከሽንት ቤቱ «ለምን መሳቅ?» አለኝ
«መርፌ መውጋት» አልኩትና ሳቄን ቀጠልኩ
ሉልሰገድ ስለኒኮል ባይነግረኝ ኖሮ፣ ኒኮልንና ጀምሺድን እጠረጥር ነበር? አይመስለኝም
በጀምስድ አገር ደምብ የሚያፈላው ሻይ በጣም ይጣፍጣል።
እሱን እየጠጣን ወሬ ጀመርን
ጀምሺድ እንደሚለው ከሆነ፣ በቁማር መክበር አይቻልም።
በቁማር የሚከብር ቁማር ቤቱ ብቻ ነው፡፡ ምንም ያህል ብትበላ
ያችን የበላ ሀትን ተመልሰህ እስክታስበላ ያቁነጠንጥሀል። በቁማር ለመክሰር እንጂ ለመክበር አይቻልም። እንዲህ ከሆነ ጀምሺድ ለምን
ቁማር ይጫወታል? ... ሰካራሙ ለምን ይጠጣል?ለጀምሺድ እንደሚታየው፣ ኑሮ ጨቅጫቃ ሚስት ናት፡ ና ምግብ ብላ፣ ና ተኛ፣ ና ሽንት ቤት ሂድ፣ ና ትምህርት ተማር፣ ና ይህን አድርግ፣ ና ያንን ፈፅም፣ እያለች መነዝነዝ ነው ስራዋ፡፡ ታድያ የሰው ልጅ ከዚህ ሁሉ ጭቅጭቅ ለመሸሽ አንዳንድ ጊዜ ቢሰክር ይፈረድበታል?

ጀምሺድ ዮኑሮን ችኮነት ሊረሳ የሚችለው ቁማር ቤት የሄደ
እንደሆነ ነው። ቁማር ቤት ውስጥ ያለችው ኑሮ፣ ነዝናዛ ችኮ ሚስት
ሳትሆን፣ የማትጠገብ፣ ለዛዋ ሁልጊዜ የሚታደስ ውሽማ ናት። ኮት የምታስሽጥ ውብ ውሽማ!

«እኔ ቁማር ስጫወት መኖሬን እረሳለሁ፡፡ መኖሬን ሲረሳ፣ ያን
ጊዜ ኑሮን ኖርኳት ነኝ ማለት ነው:: ሌላ ጊዜ ኑሮን ሲኖራት፣ እኔን
እያታለልኩ ነው ችኮ ናት ደስታ የለም፡፡ ቁማር ጊዜ ግን፣ ቁማር
ፈፅሞ ሲውጠኝ ሳለ። ኑሮ መሀል ውስጥ እገባ፣ ከንቱ አይደለች፣
እላያትም እኖራታለሁ ማለት»

ጀምሺድ ስለቁማር ሲያወራ አይኖቹ አይስቁም

እንስሳ ኑሮ አይሰለቸውም (ይሄ የጀምሺድ አስተሳሰብ ነው)
ምክንያቱም እንሰሳ ይኖራል እንጂ መኖሩን አያውቅም። ስለዚህ ኑሮ
አይመረውምም አይሰለቸውምም። ስለዚህ ነው እንሰሳ ራሱን የማይገለው። «በሬ ወይም አህያ ወይም አይጥ ወይም ውሻ ወይም ሌላ፣ ራሱ ገደለ እሱ ሰምተሀቸዋል ታውቃለህ?» ሰውን ከእንሰሳ
የሚለየው ማሰቡ አይደለም፡፡ በመጠኑ ይሁን እንጂ እንሰሳም
ያስባል። ሰው ከእንሰሳ የሚለየው በመሳቁ አይደለም። ዝንጀሮም
ይስቃል። ሰው ከእንሰሳ የሚለየው፣ ህይወቱን እየኖራት እንደሚኖራት በማወቁ፣ ከህይወት በኋላ ሞት መከተሉን በማወቁ፤ እነዚህም እውቀቶች ለሰው ልጅ ኑሮን ከንቱ፣ ሞትን መራራ በማድረጋቸው በዚህ ነው ሰው ከእንሰሳ የሚለየው

በመሰረቱ ህይወት ግሩም ስጦታ ናት። ኑሮ ግን ይሰለቻል።
ሀዘን ሞልቶበታል፡፡ ብስጭት ይበዛበታል፡፡ በሽታ ወሮታል። ሞት
ደሞ ይቆያል እንጂ አይቀርም። ስለዚህ መሞት ላይቀር፣
ብስጭት ሊበዛ፣ ለምን አሁኑኑ
አንሞትም? ለምን ራሳችንን አንገድልም? ችኮ የሆነ ሀዘን፣ ብስጭት የወረሰው እውቀት ምኑ ይወደዳል? ራሳችንን የማንገድለው ሞትን
ስለምንፈራ ብቻ ነው። ፈሪ ነን በቃ፡፡ ይኸው ነው ስለዚህ፤ ልናደንቀው የሚገባ ሰው ማን ነው? ራሱን ለመግደል የደፈረ ሰው ነው፡፡ እሱ ብቻ ነው። እኛሳ ዋናው አላማችን ምን መሆን አለበት? ይህን የመሰልቸት ቀሚስ አውልቀን ወዲያ መጣል
በተቻለ ፍጥነት ራሳችንን መግደል
«እኔ ራሴ ለመግደል ዋና ምኞት፡፡ ግን እስካሁን ድፍረት የለም፡፡ አንድ ቀን ግን ለመድፈር ተስፋ! ያን ጊዜ እኔ ሰው::እውነተኛ ሰው፡፡ እስከዚያ ድረስ ግን ከንቱ ቁማርተኛ።»

ጀምሺድ ራስን ስለመግደል ሲያወራ አይኖቹ አይስቁም

በልግ ከዛፎቹ ላይ ቡናማ፣ ቀይና ወርቃማ ቀለማቱን ሰብስቦ
የሙቀትና የውበት ጓዙን ጠቅሎ ኤክስን ለቆ ሊሄድ ተነሳ የኤክስ አየር መብረድ ጀመረ። ሽማግሌዎቹ፣ አሮጊቶቹና
ጥቁሮቹ፣ ሹራብ መደረብ ካፖርት መልበስ ጀመርን። ወጣቶቹ
ፈረንጆች ግን ገና ብርዱ ሊሰማቸው አልጀመረም
ሉልሰገድን ኒኮል እምቢ ስትለው እኔጋ መጥቶ «ካፌ ኒኮል»
ይወስደኝና፣ እየቀረበን በመጣው የክረምት ብርድ ምክንያት፣ ቤት
ውስጥ ገብተን ቁጭ ብለን ስለኒኮል ያወራልኛል። የጭገሯ ፀጉር እንደራሷ ፀጉር አመዳም ሳይሆን፣ ንፁህ ወርቅ ቀለም የተቀባ ነው፤ወተት የመሰለው ነጭ ቆዳዋ ላይ ረዣዥም የተጠላለፈ ውብ ወርቃማ ሀረግ መስሎ በቅሏል። ታዲያ እምሷ ዳር የበቀሉት ፀጉሮች፣ ውሀ ዳር እንደበቀለ ቄጠማ ናቸው፤ አንዳንዶቹ ከሁለቱ ከናፍር ተንጠራርተው ተጠላልፈው፣ ጎምበስ ብለው እምሷ ውስጥ
የፍቅር ውሀ ይጠጣሉ. .. ወዘተርፈ

አንድ ቀን ግን፡ ስለሷ ያወራልኛል ብዬ ስጠብቅ ስለጀምሺድ
ሊነግረኝ ጀመረ፡፡ ሁለቱ ጓደኛሞች ሆነዋል። ጀምሺድ ቁማር
ለመጫወት ካዚኖ ሲሄድ ሉልሰገድን ይዞት ይሄዳል። ከዚህም በላይ ሉልሰገድ የጀምሺድ ሻይ ሱስ ይዞታል። ሁለቱም ሻይውን የሚጠ
ጡት በኢራን አገር ወግ ነው። በፊት ከአራት ማእዘኑ ስኳር ላይ
ይገምጡና፣ ቀጥሎ ሻይ ፉት ይሉበታል፣ እንጂ ስኳሩን ሻይው
ውስጥ አይጨምሩትም
👍232