#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...“ቤተመንግሥት ገብተሻል አሁን ዐዲስ ወግ አምጫ እንግዲህ
አሏት፣ ምጸት በተቀላቀለው አነጋገር። ቀጠሉና፣ “አንቺ ብትሆኚ ኑሮ ምን ታረጊ ኑሯል? እስቲ በይ ንገሪኝ” አሏት።
“እኔማ እዚያ ማን አድርሶኝ ... ብቻ መላ ፈልግ ነበር።”
“መላ? ለነገሩ አንቺ መለኛ ነሽ።”
ፈገግ ብላ ዝም አለች።
“ምን አይተሽ የኔ እህት” ሲሉ ቀጠሉ። “አንዳንዶቹ ሲነግሡ
ሲሻቸው የገዛ ወንድሞቻቸውን እጅና እግር እየቆረጡ ነው እወህኒ
ሚሰዱ... እንዳይነግሡ” አሉና አፄ በካፋ ወንድማቸውን አቤቶ ዮሐንስን አንድ እጃቸውን ማስቆረጣቸውን ሊነግሯት ፈለጉና ለራሳቸው ወደ ፊት ትደርስበት የለ? ብለው ለእሷ፣ “ኣካሉ የጎደለ ደሞ መንገሥ አይችል” አሏት።
“ስለምን? አካሉ ቢጎልስ?”
“አካሉ ኸጎደለ እንዴት ብሎ ጦር ይመራል? እስቲ ንገሪኝ በይ?
ብቻ አሁን እሱን ተይውና ስንት የሞቱ ነገሥታት ዝርያዎች አሉ
መሰለሽ ኸተራራው... እወህኒ አምባ። ወህኒ አምባ ማለት ለጐንደር ቅርብ ናት... ኸማክሰኚት ብዙም አትርቅ። ብቻዋን የቆመች ተራራ ናት። አንድ በር ብቻ ነው ያላት። አናቷ ሜዳ፣ መውጫም መውረጃም የላት። ኸዛው ኻምባው ላይ የደንጊያ ቤቶችም አሉ።”
ወለተጊዮርጊስ የሰማችው ሁሉ እንግዳ ነገር ሆነባት። “ዛዲያ እንዴት ነው ሰዎቹ ከተራራው ሚወጡ ሚወርዱ?”
“በመጫኛ። ተራራይቱን ኻየሻት ዝንዥሮ ወይ ጦጣ መሆን ኣለብሽ
እዛ ላይ ለመውጣትም ሆነ ለመውረድ። ዙርያዋ ጥድ ነው። ምሽግም አላት አሉ። ብቻ እንዳው ንጉሥ ሞተ ኸተባለ ወይ ደሞ አንዱን እናንግሥ ያሉ እንደሁ፣ በቃ እግር ብረቱን ፈታተው ያኮበልሉታል።”
“ጠባቂም የለባቸው?”
“አሉዋቸው እንጂ! ያውም ንጉሡ ራሳቸው የመረጧቸው ወታደሮች
ናቸዋ ሚጠብቁ! ወታደሮቹ ዘብ ሚቆሙበት ቦታ ሁሉ አለ እኮ።
ወታደሮቹ ኸቀደሙ ነገሥታት ልገባች እንዳይመሳጠሩ፣ ለንጉሡ
መሐላ ገብተው ነው ሚጠብቁ። ኸዛ ቦታ ያለ ንጉሡ ፈቃድ ማንም
ሊገባ ወይም ሊወጣ አይችልም። ግና ለዘበኞቹ ጉርሻ ይሰጧቸዋል።
ለጉርሻ ማይተኛ ስንት አለ? የሰው ልዥ እኮ ተላላ ነው፣ በቀላሉ
ይደለላል። ዛዲያ ለእንዲህ ያለው ክደት ቅጣቱ ሞት ነው። እንንገሥ
ባዮቹም አንዴ ኸተራራይቱ ኸወረዱ፣ ጭፍራ አስከትለው ጫካ ይገባሉ፣ ኸዚያ ነፍጥ ይዘው ገስግሰው ይመጣሉ። እልቂት ነው አልሁሽ ኸዝያ ወዲያ። አንዴ ያችን አልጋ ኸመዳፋቸው ኻረጉ ወዲያ ደሞ ሹም ሽር ያረጋሉ። ኸባላገሩ ርስት እህላሙን መሬት እየመረጡ ለሚፈልጉት በጉልት ይሰጣሉ፣ ሲፈልጉ ርስት ይተክላሉ፣ ገባርም ይሰጣሉ፣ ከብትም እንዲወስዱ ያረጋሉ። የጃንሆይ አባት አጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ ሰላም አምጥተው እሳቸው ከሞቱ በኋላ፣ ረብሻ፣ ጦር ሰበቃ ሆነ።
የጭንቅ ዘመን ነበር።”
ዮልያና፣ ስመ መንግሥታቸው አድያም ሰገድ የሆነው ቀዳማዊ ኢያሱ ከሞቱ በኋላ፣ የነገሡ ነገሥታት ተክለሃይማኖት፣ ቴዎፍሎስ፣ ዮስጦስና ሣልሳዊ ዳዊት፣ እያንዳንዳቸው ለአጭር ጊዜ እየገዙ ሃገሪቱ ሰላም
አጥታ ስትታመስ፣ በሃይማኖት ክርክርና ንትርክ ስትብረከረክ ብሎም በእልቂት ስትንጠራወዝ እንደነበረች በዝርዝር ሊነግሯት ፈልገው፣ ፊቷ ላይ በግልፅ የሚታየውን የመሸበር ስሜት አስተውለው ዝም አሉ።
ወለተጊዮርጊስ የሰማችው ነገር ሁሉ ከበዳት። ቤተመንግሥት
መግባት አስፈሪ ነገር ሆነባት። ፋሲል ቤተመንግሥት ቅጥር ግቢ
ስትገባ ያየችው ግርማ ሞገስ ሁሉ በውስጡ የማይመጥኑት አናሣ
ነገሮች ያቀፈ መሰላት።
“ማትቀመጪ? ቁመሽ ትዘልቂዋለሽ?” አሏት።
“እሚታዬ ለመሆኑ ሰዎቹ ምን እየበሉ ይኖራሉ፣ኸተራራ
ተቀምጠው?”
“ንጉሡ እኮ ቀለብ ይሰጣል። ውሃም ቢሆን ኸታች ምንጭ አለ::
እነሱም ኸዛው ይዋለዳሉ። ትምርት ይማራሉ፤ ቤተክሲያንም..
ጊዮርጊስና ማርያምም እኮ አሉ ኸዛው።”
“ሚገርም ነው። ስለዝኸ ስታወሪ ሰምቸሽም አላውቅ።”
ትናንት ፋሲለደስ ቤተመንግሥት ግቢ ስትገባ የነበራት የመደነቅ
ስሜት ኹሉ ጠፍቶባት ጭንቀት ያዛት። ለራሷ እኼ ቤተመንግሥት
ሚባል ነገር አስፈሪ ነው አለችና ወደ አልጋው ጫፍ አመራች።
ልብሶቹን በጥንቃቄ ወደ ኋላ ገፋ አድርጋ ተቀመጠች።
“ጌጦቹን አልጋው ላይ አኑሪያቸው” ብለው በቀኝ እጃቸው ኣልጋውን መታ አደረጉት።
“ልብሶቹን ደሞ እመንጠቆዎቹ ላይ ስቀያቸው” አሏት፣ ግድግዳ ላይ የተተከሉትን ከቀንድ የተሰሩ የልብስ መስቀያዎች
በእጃቸው እየጠቆሟት።
ጌጦቹን አልጋው ላይ ትታ ሄዳ ልብሶቹን አንድ በአንድ
ሰቀለቻቸውና ጫማዎቹን መሬት ላይ አስቀምጣ ተመልሳ አልጋው
ጫፍ ላይ ተቀመጠች።
“ምን እያልሽኝ ነበር? አዎ 'ስለዝህ ስታወሪ ሰምቸሽም አላውቅ
ነው ያልሽኝ” አለና፣ “ፊት ብታቂ ኑሮ ምን ይጠቅምሽ ኑሯል?
የዠመርሁትን ልጨርስልሽ እንጂ። ጃንሆይ እንዳልሁሽ በንጉሥ
ዮስጦስ ግዝየ ኸወህኒ አምባ ሲያመልጡ እኝሁ ዮስጦስ መልሰው አሰሯቸው። ያለቤታቸው ገብተው።”
“ያለቤታቸው ገብተው?”
“ዮስጦስ ማለት ልደታ ማርያምን እዝሁ እጐንደር የተከሉት
ያጤ ቴዎፍሎስ እንደራሴ ነበሩ እንጂ የነጋሢ ዘር የላቸውም። ኋላ
ጃንሆይ ደሞ ሲነግሡ ወህኒ አምባ ያሉ የነጋሢ ዝርያዎች ሁሉ የገዛ ወንድሞቻቸው ሳይቀሩ ተንጫጩ።”
“ምን ይሁን ብለው?”
“ሚነግሠውን እኛ እንመርጣለን፤ በካፋ ኃይለኛና ጨካኝ ነው
ብለው። ያው አልቀረም መሲሕ ሰገድ ተብለው ነገሡ። ይነግሣሉ ሚል ንግርትም ነበር። ጃንሆይ ወህኒ ሳሉ በሳቸው ልክ ጧሚና ጠሎተኛ አልነበረም ነው ሚሉ።
ምጥዋትም መስደድ ያዘወትሩ፣ መጻሕፍቱንም ያገላብጡ ነበር። ቅኔ አዋቂም ናቸው። ኸዛው እናታቸው አገር... ዲማ ነው ቅኔውን የተማሩ። ደሞ ምን የመሰለ ታንኳም አሠርተዋል እኮ።
ግብጦች ናቸው አሉ የሠሩላቸው። ኸጣና ነው ያለ...”
ድንገት ደንገጡሮቹ ሲገቡ ዝም አሉ። ሴቶቹ ወለተጊዮርጊስን
አልብሰው፣ አስጊጠውና እላይዋ ላይ ሽቱ አርከፍክፈው ግብር መታደሚያ ሰዐት ሲደርስ እንደሚመለሱና ግብር እንደ ንጉሠ ነገሥቱ ፍላጎትና
እንደ ሁኔታው የተለያየ አዳራሽ ውስጥ እንደሚደረግና ለዛሬ ግን ባለ ሁለት ደርቡ ወርቅ ሰቀላ ምድር ቤት አዳራሽ ውስጥ እንደሚሆን ነግረዋቸው ወጡ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ምንትዋብ ብያታለሁ።”
ወርቅ ሰቀላ ጥቁር እንግዳ ለመቀበል ዝግጁ ሆኗል። የእልፍኝ
አስከልካዩ በሥሩ ያሉትን እንደየደረጃቸው ነጠላ ያደገደጉትን፣ ወይም ካባ የደረቡትን ዐራቱን ጭፍሮቹን አሰማርቷል። ጠርዙ ባለወርቅ ቅብ
የሆነው የንጉሠ ነገሥቱ መንበረ መንግሥት የለበሰው የፋርስ ባለቀይ፣ባለሰማያዊና ባለነጭ ምንጣፍ በትክክል መነጠፉን፣ ከጎኑ ያለው ጠርዙ የወርቅ ቅብ የሆነው ድንክ አልጋ ዝግጁ መሆኑንና ከአልጋዎቹ ሥር
የተነጠፈው ቀይ የፋርስ ስጋጃ ላይ የሐር ምንጣፍ በትክክል መነጠፉን አረጋግጧል።
ከንጉሡ መንበር በስተጀርባ ያለውን ግድግዳ በቀይና በልዩ ልዩ
ቀለማት ያጌጠ ከቱርክ የመጣ ምንጣፍ ሸፍኖታል። ድንክ አልጋዎቹ የተቀመጡበትን አካባቢ ከሐር የተሠራ ነጭ አጎበር ከላይ ከልሎታል።አናቱ ላይ የዘውድ ቅርጽ ያለው ጉልላት ተቀምጦለታል። ንጉሠ
ነገሥቱ ሆኑ አብረዋቸው የሚቀመጡት እንግዶች እስኪገቡ አጎበሩ በግራና በቀኝ ያሉ እንጨቶች ላይ በቀጭን ሐር ሻሽ ታስሯል።ሲያስፈልግ የሚጋርዱትና የሚገልጡት ሁለት የቤተመንግሥት ባለሟሎች አደግድገው ግራና ቀኙን ቆመዋል። በአዳራሹ ግራና ቀኝ
ያሉ መስኮቶች የሐር መጋረጃ ተጋርደውባቸዋል።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...“ቤተመንግሥት ገብተሻል አሁን ዐዲስ ወግ አምጫ እንግዲህ
አሏት፣ ምጸት በተቀላቀለው አነጋገር። ቀጠሉና፣ “አንቺ ብትሆኚ ኑሮ ምን ታረጊ ኑሯል? እስቲ በይ ንገሪኝ” አሏት።
“እኔማ እዚያ ማን አድርሶኝ ... ብቻ መላ ፈልግ ነበር።”
“መላ? ለነገሩ አንቺ መለኛ ነሽ።”
ፈገግ ብላ ዝም አለች።
“ምን አይተሽ የኔ እህት” ሲሉ ቀጠሉ። “አንዳንዶቹ ሲነግሡ
ሲሻቸው የገዛ ወንድሞቻቸውን እጅና እግር እየቆረጡ ነው እወህኒ
ሚሰዱ... እንዳይነግሡ” አሉና አፄ በካፋ ወንድማቸውን አቤቶ ዮሐንስን አንድ እጃቸውን ማስቆረጣቸውን ሊነግሯት ፈለጉና ለራሳቸው ወደ ፊት ትደርስበት የለ? ብለው ለእሷ፣ “ኣካሉ የጎደለ ደሞ መንገሥ አይችል” አሏት።
“ስለምን? አካሉ ቢጎልስ?”
“አካሉ ኸጎደለ እንዴት ብሎ ጦር ይመራል? እስቲ ንገሪኝ በይ?
ብቻ አሁን እሱን ተይውና ስንት የሞቱ ነገሥታት ዝርያዎች አሉ
መሰለሽ ኸተራራው... እወህኒ አምባ። ወህኒ አምባ ማለት ለጐንደር ቅርብ ናት... ኸማክሰኚት ብዙም አትርቅ። ብቻዋን የቆመች ተራራ ናት። አንድ በር ብቻ ነው ያላት። አናቷ ሜዳ፣ መውጫም መውረጃም የላት። ኸዛው ኻምባው ላይ የደንጊያ ቤቶችም አሉ።”
ወለተጊዮርጊስ የሰማችው ሁሉ እንግዳ ነገር ሆነባት። “ዛዲያ እንዴት ነው ሰዎቹ ከተራራው ሚወጡ ሚወርዱ?”
“በመጫኛ። ተራራይቱን ኻየሻት ዝንዥሮ ወይ ጦጣ መሆን ኣለብሽ
እዛ ላይ ለመውጣትም ሆነ ለመውረድ። ዙርያዋ ጥድ ነው። ምሽግም አላት አሉ። ብቻ እንዳው ንጉሥ ሞተ ኸተባለ ወይ ደሞ አንዱን እናንግሥ ያሉ እንደሁ፣ በቃ እግር ብረቱን ፈታተው ያኮበልሉታል።”
“ጠባቂም የለባቸው?”
“አሉዋቸው እንጂ! ያውም ንጉሡ ራሳቸው የመረጧቸው ወታደሮች
ናቸዋ ሚጠብቁ! ወታደሮቹ ዘብ ሚቆሙበት ቦታ ሁሉ አለ እኮ።
ወታደሮቹ ኸቀደሙ ነገሥታት ልገባች እንዳይመሳጠሩ፣ ለንጉሡ
መሐላ ገብተው ነው ሚጠብቁ። ኸዛ ቦታ ያለ ንጉሡ ፈቃድ ማንም
ሊገባ ወይም ሊወጣ አይችልም። ግና ለዘበኞቹ ጉርሻ ይሰጧቸዋል።
ለጉርሻ ማይተኛ ስንት አለ? የሰው ልዥ እኮ ተላላ ነው፣ በቀላሉ
ይደለላል። ዛዲያ ለእንዲህ ያለው ክደት ቅጣቱ ሞት ነው። እንንገሥ
ባዮቹም አንዴ ኸተራራይቱ ኸወረዱ፣ ጭፍራ አስከትለው ጫካ ይገባሉ፣ ኸዚያ ነፍጥ ይዘው ገስግሰው ይመጣሉ። እልቂት ነው አልሁሽ ኸዝያ ወዲያ። አንዴ ያችን አልጋ ኸመዳፋቸው ኻረጉ ወዲያ ደሞ ሹም ሽር ያረጋሉ። ኸባላገሩ ርስት እህላሙን መሬት እየመረጡ ለሚፈልጉት በጉልት ይሰጣሉ፣ ሲፈልጉ ርስት ይተክላሉ፣ ገባርም ይሰጣሉ፣ ከብትም እንዲወስዱ ያረጋሉ። የጃንሆይ አባት አጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ ሰላም አምጥተው እሳቸው ከሞቱ በኋላ፣ ረብሻ፣ ጦር ሰበቃ ሆነ።
የጭንቅ ዘመን ነበር።”
ዮልያና፣ ስመ መንግሥታቸው አድያም ሰገድ የሆነው ቀዳማዊ ኢያሱ ከሞቱ በኋላ፣ የነገሡ ነገሥታት ተክለሃይማኖት፣ ቴዎፍሎስ፣ ዮስጦስና ሣልሳዊ ዳዊት፣ እያንዳንዳቸው ለአጭር ጊዜ እየገዙ ሃገሪቱ ሰላም
አጥታ ስትታመስ፣ በሃይማኖት ክርክርና ንትርክ ስትብረከረክ ብሎም በእልቂት ስትንጠራወዝ እንደነበረች በዝርዝር ሊነግሯት ፈልገው፣ ፊቷ ላይ በግልፅ የሚታየውን የመሸበር ስሜት አስተውለው ዝም አሉ።
ወለተጊዮርጊስ የሰማችው ነገር ሁሉ ከበዳት። ቤተመንግሥት
መግባት አስፈሪ ነገር ሆነባት። ፋሲል ቤተመንግሥት ቅጥር ግቢ
ስትገባ ያየችው ግርማ ሞገስ ሁሉ በውስጡ የማይመጥኑት አናሣ
ነገሮች ያቀፈ መሰላት።
“ማትቀመጪ? ቁመሽ ትዘልቂዋለሽ?” አሏት።
“እሚታዬ ለመሆኑ ሰዎቹ ምን እየበሉ ይኖራሉ፣ኸተራራ
ተቀምጠው?”
“ንጉሡ እኮ ቀለብ ይሰጣል። ውሃም ቢሆን ኸታች ምንጭ አለ::
እነሱም ኸዛው ይዋለዳሉ። ትምርት ይማራሉ፤ ቤተክሲያንም..
ጊዮርጊስና ማርያምም እኮ አሉ ኸዛው።”
“ሚገርም ነው። ስለዝኸ ስታወሪ ሰምቸሽም አላውቅ።”
ትናንት ፋሲለደስ ቤተመንግሥት ግቢ ስትገባ የነበራት የመደነቅ
ስሜት ኹሉ ጠፍቶባት ጭንቀት ያዛት። ለራሷ እኼ ቤተመንግሥት
ሚባል ነገር አስፈሪ ነው አለችና ወደ አልጋው ጫፍ አመራች።
ልብሶቹን በጥንቃቄ ወደ ኋላ ገፋ አድርጋ ተቀመጠች።
“ጌጦቹን አልጋው ላይ አኑሪያቸው” ብለው በቀኝ እጃቸው ኣልጋውን መታ አደረጉት።
“ልብሶቹን ደሞ እመንጠቆዎቹ ላይ ስቀያቸው” አሏት፣ ግድግዳ ላይ የተተከሉትን ከቀንድ የተሰሩ የልብስ መስቀያዎች
በእጃቸው እየጠቆሟት።
ጌጦቹን አልጋው ላይ ትታ ሄዳ ልብሶቹን አንድ በአንድ
ሰቀለቻቸውና ጫማዎቹን መሬት ላይ አስቀምጣ ተመልሳ አልጋው
ጫፍ ላይ ተቀመጠች።
“ምን እያልሽኝ ነበር? አዎ 'ስለዝህ ስታወሪ ሰምቸሽም አላውቅ
ነው ያልሽኝ” አለና፣ “ፊት ብታቂ ኑሮ ምን ይጠቅምሽ ኑሯል?
የዠመርሁትን ልጨርስልሽ እንጂ። ጃንሆይ እንዳልሁሽ በንጉሥ
ዮስጦስ ግዝየ ኸወህኒ አምባ ሲያመልጡ እኝሁ ዮስጦስ መልሰው አሰሯቸው። ያለቤታቸው ገብተው።”
“ያለቤታቸው ገብተው?”
“ዮስጦስ ማለት ልደታ ማርያምን እዝሁ እጐንደር የተከሉት
ያጤ ቴዎፍሎስ እንደራሴ ነበሩ እንጂ የነጋሢ ዘር የላቸውም። ኋላ
ጃንሆይ ደሞ ሲነግሡ ወህኒ አምባ ያሉ የነጋሢ ዝርያዎች ሁሉ የገዛ ወንድሞቻቸው ሳይቀሩ ተንጫጩ።”
“ምን ይሁን ብለው?”
“ሚነግሠውን እኛ እንመርጣለን፤ በካፋ ኃይለኛና ጨካኝ ነው
ብለው። ያው አልቀረም መሲሕ ሰገድ ተብለው ነገሡ። ይነግሣሉ ሚል ንግርትም ነበር። ጃንሆይ ወህኒ ሳሉ በሳቸው ልክ ጧሚና ጠሎተኛ አልነበረም ነው ሚሉ።
ምጥዋትም መስደድ ያዘወትሩ፣ መጻሕፍቱንም ያገላብጡ ነበር። ቅኔ አዋቂም ናቸው። ኸዛው እናታቸው አገር... ዲማ ነው ቅኔውን የተማሩ። ደሞ ምን የመሰለ ታንኳም አሠርተዋል እኮ።
ግብጦች ናቸው አሉ የሠሩላቸው። ኸጣና ነው ያለ...”
ድንገት ደንገጡሮቹ ሲገቡ ዝም አሉ። ሴቶቹ ወለተጊዮርጊስን
አልብሰው፣ አስጊጠውና እላይዋ ላይ ሽቱ አርከፍክፈው ግብር መታደሚያ ሰዐት ሲደርስ እንደሚመለሱና ግብር እንደ ንጉሠ ነገሥቱ ፍላጎትና
እንደ ሁኔታው የተለያየ አዳራሽ ውስጥ እንደሚደረግና ለዛሬ ግን ባለ ሁለት ደርቡ ወርቅ ሰቀላ ምድር ቤት አዳራሽ ውስጥ እንደሚሆን ነግረዋቸው ወጡ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ምንትዋብ ብያታለሁ።”
ወርቅ ሰቀላ ጥቁር እንግዳ ለመቀበል ዝግጁ ሆኗል። የእልፍኝ
አስከልካዩ በሥሩ ያሉትን እንደየደረጃቸው ነጠላ ያደገደጉትን፣ ወይም ካባ የደረቡትን ዐራቱን ጭፍሮቹን አሰማርቷል። ጠርዙ ባለወርቅ ቅብ
የሆነው የንጉሠ ነገሥቱ መንበረ መንግሥት የለበሰው የፋርስ ባለቀይ፣ባለሰማያዊና ባለነጭ ምንጣፍ በትክክል መነጠፉን፣ ከጎኑ ያለው ጠርዙ የወርቅ ቅብ የሆነው ድንክ አልጋ ዝግጁ መሆኑንና ከአልጋዎቹ ሥር
የተነጠፈው ቀይ የፋርስ ስጋጃ ላይ የሐር ምንጣፍ በትክክል መነጠፉን አረጋግጧል።
ከንጉሡ መንበር በስተጀርባ ያለውን ግድግዳ በቀይና በልዩ ልዩ
ቀለማት ያጌጠ ከቱርክ የመጣ ምንጣፍ ሸፍኖታል። ድንክ አልጋዎቹ የተቀመጡበትን አካባቢ ከሐር የተሠራ ነጭ አጎበር ከላይ ከልሎታል።አናቱ ላይ የዘውድ ቅርጽ ያለው ጉልላት ተቀምጦለታል። ንጉሠ
ነገሥቱ ሆኑ አብረዋቸው የሚቀመጡት እንግዶች እስኪገቡ አጎበሩ በግራና በቀኝ ያሉ እንጨቶች ላይ በቀጭን ሐር ሻሽ ታስሯል።ሲያስፈልግ የሚጋርዱትና የሚገልጡት ሁለት የቤተመንግሥት ባለሟሎች አደግድገው ግራና ቀኙን ቆመዋል። በአዳራሹ ግራና ቀኝ
ያሉ መስኮቶች የሐር መጋረጃ ተጋርደውባቸዋል።
👍18
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...«ለመሆኑ የትናንቱን ፖሊስ ፍንግል አርገኸው ነበር ለካ
የሮጥከው» አለኝ
«አዎን» አልኩት
«ተነስቶ ቢከተልህስ? እና ካንተ የፈጠነ ሯጭ ቢሆንስ? ወይም
ስትሮጥ ውጋትቢይዝህስ? ወይም ቢተኩስብህስ? ወይ ፊሽካ ቢነፋና
ሌሎች ፖሊሶች ከያለበት ወዳንተ ቢሮጡስ?»
«ታድያ እንዴት ማድረግ ነበረብኝ?» አልኩት
«አታውቅምን ?»
«አላውቅም»
«እንግዲያው ነገ ጧት በአስራ አንድ ተኩል ቤቴ ና....
ከዚያ በኋላ አራት ወር ሙሉ ጧት ጧት ካስራ አንድ ተኩል እስከ
አንድ ተኩል ድረስ የሚያውቀውን ሁሉ አስተማረኝ፡፡ ከሱ እኩል
ከሆንኩ በኋላ፣ አንድ ሌሊት ማጅራት መቺዎች የሚበዙበት
ሰፈር ወሰደኝና እኔ እንግዲህ አላግዝህም፣ ዝም ብዬ ማየት ነው።ይሄ የመጨረሻ ፈተናህ ነው አለኝ
አንድ ቦታ ስድስት ዱርዬዎች ከበቡና ማኑ «ወዲህ በኩል
ያሉት ሁለቱ የኔ ናቹው፣ አራቱን ውሰድ አለኝ በእንግሊዝኛ።
የኔን ሶስቱን አጋደምኳቸው፣ አንዱ ሸሸ። ፈተናዬን አለፍኩ
ግን አንድ ሌሊት አክስ ውስጥ ብቻዬን ስዘዋወር፣ ሶስት
አሜሪካኖች ግድግዳ ላይ ሲፅፍ ይዘውት፣ ሊደበድቡት እንደ ጀመሩ
ድንጋይ በመወርወር አስጥዬዋለሁ። ይህን የአምባጓሮ ችሎታውን ለምን ከነሱ ለማምለጥ አልተጠቀመበትም? ማወቅ ፈለግኩ፣ ግን አልጠየቅኩትም። ከፈለገ እሱ ራሱ እንደሚነግረኝ አውቃለሁ)
ማኑ አንድ ሊላ ነገር አስተኖሮኛል (አለ ባህራም) አየህ፣ ድሮ ሻህ ግርማ ሞገስ ያለው፣ ከነሲሩስ ከነዳርዮሽ የሚስተካከል ንጉስ
መስሎኝ ነበር። እና እየጠላሁትም አከብረው እፈራው ነበር። በማኑ
ቀልድ እየሳቅኩ በማኑ አይን ሳየው ግን ሽህ ምንም ግርማ ሞገስ የለውም። በነዳርዮሽ ዙፋን ላይ ተቀመጠ እንጂ፣ የነዳርዮሽ ደም ወይም ክብር ወይም ጀግንነት የለውም፡፡ የአንበሳ ቆዳ የለበሰ ውሻ ነው
ብኝ እሱን ተወው
አንድ ጊዜ የኮረምሻህር ወደብ ከተማ የሰራተኞች ማርበር
ሰላማዊ ሰልፍና ንግግር ለማድረግ በህግ ተፈቀደለት። የኛ ፓርቲ ላያግዛቸው ወስኖ፣ እኔና ማኑ በባቡር ሄድን፡፡ ስነ ስርአቱ
የሚካሄደው በታጠረ ኳስ ሜዳ ውስጥ ነበር። ቦታ ቦታችንን ይዘን
ንግግሩ የሚደረግበት ሰአት ጥቂት ደቂቃ ሲቀረው፣ ብዙ ብዙ
ፖሊሶች በትልቁ በር ሲገቡ አየሁ። እንደገቡ ፊታቸው ያገኙትን
በዱላ መጨፍጨፍ ጀመሩ
ማኑን «እንሂድ?» አልኩት
«አንተ ሂድ አለኝ
«አንተስ?» አልኩት
«እኔ ደህና ቦታ እንድይዝና ካለቆቻችን ትእዛዝ ካልመጣ
በስተቀር እንዳልለቅ ታዝዣለሁ»
ይህን ጊዜ ሜዳውን ጩኸትና ትርምስምስ ሞልቶታል
“አለቆቻችን የተፈቀደላቸው መስሏቸው ነበር፡፡ ግን ፈቃዱ
ወጥመድ ነው፡፡ ስለዚህ አሁን እዚህ መቆም ምንም ጥቅም የለውም፡፡
«ና እንሂድ» አልኩት
«አልሄድም፡፡ ኮሙኒስት ነኝ። አለቆቼ ሽሽ ካላሉኝ ልሸሽ
አልችልም» አለኝ
«እዚህ መቆምህ ጥቅም የለውማ!» አልኩት
“ምን ታውቃለህ? ይልቅ ሂድ ፖሊሶቹ እዚህ ሊደርሱ ነው።
በወዲያ በኩል ዝለልና አምልጥ» አለኝ
«አንተ ካልሄድክ አልሄድም» አልኩት
«እኔ አለቆቼን እታዘዛለሁ። አንተም አለቃህን ታዘዝ፡፡ አለቃህ
እኔ ነኝ፡፡ በል አሁን ሂድ። ሂድ!» አለኝ ሄድኩ። አጥሩን ልዘል ስል ዘወር ብዬ አየሁት። ዙሪያውን
ፖሊሱና ሰዉ ሲተራመስ ሲከታከት፣ እሱ ሁለት እጆቹን ደረቱ ላይ አጣምሮ እንደ ሀውልት ቆሟል። በአጥሩ ዘለልኩ
ማኑ ፖሊሶቹ ደብድበውት ሶስት ሳምንት ሙሉ ሀኪም ቤት ተኛ
መሀል ጣቱ ተሰብሮ ቀረ። አሁን ሊያጥፈው ኣይችልም
ማኑ እንዴት ኮሙኒስት እንደሆነ ልንገርህ?
አንድ የትምህርት ቤት ጓደኛ ነበረው። ጓደኝየው በጣም ጥሩ
ልጅ ነው:: ቆንጆ ቆንጆ ግጥሞችን ይደርሳል። ግን ድሀ ብጤ ነው።
ከዚህም በላይ እጅግ የተዋበ!
አንድ ቀን የዚህ ልጅ አባት ታሰሩ። በሽተኛ ሚስት፣ ስድስት
ትንንሽ ልጆች ኣሏቸው። እሱ የመጀመሪያ ልጃቸው ነው። አባትየው ታስረው ልጆቹ ምን ይብሉ? ልጁ ጨነቀው። ያባትየውን ጉዳይ የሚከታተለው የፖሊስ ሹም ቢሮ ሄደና እያለቀሰ የቤቱን ችግር ነገረው። ፖሊሱ ደግ ነበር። የልጁ ችግር ገባው። ጉዳዩ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ፣ አባትህን ዝም ብዬ ነፃ ብለቃቸው፣ የበላይ ሹማምንት ይቀጡኛል፡፡ ብቻ ለማንኛውም ዛሬ ማታ ለእራት ቤቴ ብቅ በልና እንመካከርበታለን» አለው
ሲመሽ ልጁ ፖሊሱ ቤት ሄደ፡፡ እራት ከበሉ በኋላ ፖሊሱ
ልጁን ያሻሽው ጀመር። ልጁ በመጀመሪያ ደነገጠ፤ በኋላ ተቆጣ::ይኸኔ የፖሊሱ ፊት ተለወጠ። ደግ የነበረው በሀይል ክፉ ሆነ፡፡ ረጋ ባለ ድምፅ ልጁን እንዲህ እላው
«አባትህ በኔ እጅ ነው:: ላስገድለውም እችላለሁ፣ ላሳስረውም እችላለሁ፣ ላስፈታውም እችላለሁ፡፡ ስለዚህ አባትህ ባንተ እጅ ነው
ማለት ነው:: እዚህ ከኔ ጋር ካደርክና ካስደሰትከኝ፣ ነገ አባትህ
ለምሳ ቤቱ ይመጣል፣ ተነገ ወዲያ መስሪያ ቤቱ ይሄዳል፣ በስህተት
መያዙን አስመሰክርለታለሁ፡ ቤቶችህ የሚበሉትን ያገኛሉ። እኔን
እምቢ ካልከኝ ግን አባትህ ወየውለት! ትንንሽ ወንድሞችህና
እህቶችህም ምን እንደሚውጣቸው አላውቅም፡፡ ባንተ አጅ ናቸው።
ሁሉም ባንተ እጅ ነው»
ልጁ እሺ እርስዎ እንዳሉኝ አደርጋለሁ አለ። አባትየው ተፈታ።
መስሪያ ቤቱም ተቀበሉት
ልጅየው ውርደቱን ተሸክሞ መጣና የተፈፀመበትን ግፍ
እያለቀሰ ለማኑ አጫወተው። ምን ባደርግ ይሻለኛል? አለው
አየሀ፣ ሲለያዩ ፖሊሱ ምን ብሎታል «እኔ የተገደልኩ ወይም
የተጎዳሁ እንደሆነ፣ ሁለት ሌሎች የፖሊስ ሹማምንት አሉ፤ ጓደኞቼ
ናቸው፡ ኣንተ እንደጎዳኸኝ ያውቃሉ፤
ስለዚህ አባትህን እነሱ
መልሰው ያሳስሩታል። ያን ጊዜስ አባትህን አያርገኝ፣ ቤቶችህን
አያርገኝ! ስለዚህ በኔ ላይ የበቀል ሀሳብ ባታስብ ጥሩ ነው።
ብሉታል። ልጁ ምን ይሁን? የተዋረደ ክብሩን ሊበቀል አልቻለም።
ግን ውርደቱ ሊረሳ የሚችል አይነት አይደለም። ልጁ አልቻለም።
በዛበት፡፡ ከሚችለው በላይ በዛበት፡ አበደ። አበደ በቃ! እብድ ሆነ።
ቤቶቹ በድህነታቸው ላይ ሀዘን ተጨመረጣቸው:: ደግሞስ ማን
ያውቃል? ኢራንም አንድ ታላቅ ደራሲ ባጭሩ ተቀጨባት ማለት
ይሆናል'ኮ
አይ ኢራን! ስንቱን ጉድ ትችያለሽ! ኢራን ውቢቱ! እንዴት
መሰለችህ! አቤት ህዝቡን ብታውቀው! ቋንቋውን ብትሰማው! አይ ህዝብ! እንደ ምንም ብዬ ከሻህና ከጋንግስተሮቹ ነፃ ባወጣው'ኮ የኢራን ህዝብ በደስታ ሊኖር የሚችል ህዝብ ነው። ክብሩን ልመልስለት ብችል፡ ማንንም ሳይፈራ ሰርቶ ለመብላት ቢችል፤ ህግ ካልጣስ ማንም ሊያስረው እንደማይችል እርግጠኛ ለመሆን ቢችል!
ሻህና አሜሪካኖቹ ሀብቱን ባይነጥቁት! ብቻዬን እንዳልመስልህ! በጭራሽ ብቻዬን አይደለሁም፡፡ እኔ ያየሁትን ያዩ፣ እንደኔ የሚቆረቆሩ፣ እንደኔ የተናደዱ፣ እንደኔ ደም ለማፍሰስ ዝግጁ የሆኑ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ኢራናውያን አሉ። አሉ! አሉ!
የሚመራቸውን ይጠብቃሉ! (አለ ባህራም)
ባህራምና እኔ ከተዋወቅን ጀምሮ እስከተለያየን ድረስ ስለኢራን
ያወራልኝ ነበር። ኢራን፣ ኢራን፣ ኢራን። አልሰለቸኝም ግን ይበዛብኝ ነበር። ይልቁንም የአገሩ መበስበስ ያንገሸግሸኝ ነበር፡፡ ሁሉ ነገር በጉቦ ነው። ፖሊሱ፣ ጃኛው፣ አስተማሪው ሳይቀር ጉቦ ይበላል።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...«ለመሆኑ የትናንቱን ፖሊስ ፍንግል አርገኸው ነበር ለካ
የሮጥከው» አለኝ
«አዎን» አልኩት
«ተነስቶ ቢከተልህስ? እና ካንተ የፈጠነ ሯጭ ቢሆንስ? ወይም
ስትሮጥ ውጋትቢይዝህስ? ወይም ቢተኩስብህስ? ወይ ፊሽካ ቢነፋና
ሌሎች ፖሊሶች ከያለበት ወዳንተ ቢሮጡስ?»
«ታድያ እንዴት ማድረግ ነበረብኝ?» አልኩት
«አታውቅምን ?»
«አላውቅም»
«እንግዲያው ነገ ጧት በአስራ አንድ ተኩል ቤቴ ና....
ከዚያ በኋላ አራት ወር ሙሉ ጧት ጧት ካስራ አንድ ተኩል እስከ
አንድ ተኩል ድረስ የሚያውቀውን ሁሉ አስተማረኝ፡፡ ከሱ እኩል
ከሆንኩ በኋላ፣ አንድ ሌሊት ማጅራት መቺዎች የሚበዙበት
ሰፈር ወሰደኝና እኔ እንግዲህ አላግዝህም፣ ዝም ብዬ ማየት ነው።ይሄ የመጨረሻ ፈተናህ ነው አለኝ
አንድ ቦታ ስድስት ዱርዬዎች ከበቡና ማኑ «ወዲህ በኩል
ያሉት ሁለቱ የኔ ናቹው፣ አራቱን ውሰድ አለኝ በእንግሊዝኛ።
የኔን ሶስቱን አጋደምኳቸው፣ አንዱ ሸሸ። ፈተናዬን አለፍኩ
ግን አንድ ሌሊት አክስ ውስጥ ብቻዬን ስዘዋወር፣ ሶስት
አሜሪካኖች ግድግዳ ላይ ሲፅፍ ይዘውት፣ ሊደበድቡት እንደ ጀመሩ
ድንጋይ በመወርወር አስጥዬዋለሁ። ይህን የአምባጓሮ ችሎታውን ለምን ከነሱ ለማምለጥ አልተጠቀመበትም? ማወቅ ፈለግኩ፣ ግን አልጠየቅኩትም። ከፈለገ እሱ ራሱ እንደሚነግረኝ አውቃለሁ)
ማኑ አንድ ሊላ ነገር አስተኖሮኛል (አለ ባህራም) አየህ፣ ድሮ ሻህ ግርማ ሞገስ ያለው፣ ከነሲሩስ ከነዳርዮሽ የሚስተካከል ንጉስ
መስሎኝ ነበር። እና እየጠላሁትም አከብረው እፈራው ነበር። በማኑ
ቀልድ እየሳቅኩ በማኑ አይን ሳየው ግን ሽህ ምንም ግርማ ሞገስ የለውም። በነዳርዮሽ ዙፋን ላይ ተቀመጠ እንጂ፣ የነዳርዮሽ ደም ወይም ክብር ወይም ጀግንነት የለውም፡፡ የአንበሳ ቆዳ የለበሰ ውሻ ነው
ብኝ እሱን ተወው
አንድ ጊዜ የኮረምሻህር ወደብ ከተማ የሰራተኞች ማርበር
ሰላማዊ ሰልፍና ንግግር ለማድረግ በህግ ተፈቀደለት። የኛ ፓርቲ ላያግዛቸው ወስኖ፣ እኔና ማኑ በባቡር ሄድን፡፡ ስነ ስርአቱ
የሚካሄደው በታጠረ ኳስ ሜዳ ውስጥ ነበር። ቦታ ቦታችንን ይዘን
ንግግሩ የሚደረግበት ሰአት ጥቂት ደቂቃ ሲቀረው፣ ብዙ ብዙ
ፖሊሶች በትልቁ በር ሲገቡ አየሁ። እንደገቡ ፊታቸው ያገኙትን
በዱላ መጨፍጨፍ ጀመሩ
ማኑን «እንሂድ?» አልኩት
«አንተ ሂድ አለኝ
«አንተስ?» አልኩት
«እኔ ደህና ቦታ እንድይዝና ካለቆቻችን ትእዛዝ ካልመጣ
በስተቀር እንዳልለቅ ታዝዣለሁ»
ይህን ጊዜ ሜዳውን ጩኸትና ትርምስምስ ሞልቶታል
“አለቆቻችን የተፈቀደላቸው መስሏቸው ነበር፡፡ ግን ፈቃዱ
ወጥመድ ነው፡፡ ስለዚህ አሁን እዚህ መቆም ምንም ጥቅም የለውም፡፡
«ና እንሂድ» አልኩት
«አልሄድም፡፡ ኮሙኒስት ነኝ። አለቆቼ ሽሽ ካላሉኝ ልሸሽ
አልችልም» አለኝ
«እዚህ መቆምህ ጥቅም የለውማ!» አልኩት
“ምን ታውቃለህ? ይልቅ ሂድ ፖሊሶቹ እዚህ ሊደርሱ ነው።
በወዲያ በኩል ዝለልና አምልጥ» አለኝ
«አንተ ካልሄድክ አልሄድም» አልኩት
«እኔ አለቆቼን እታዘዛለሁ። አንተም አለቃህን ታዘዝ፡፡ አለቃህ
እኔ ነኝ፡፡ በል አሁን ሂድ። ሂድ!» አለኝ ሄድኩ። አጥሩን ልዘል ስል ዘወር ብዬ አየሁት። ዙሪያውን
ፖሊሱና ሰዉ ሲተራመስ ሲከታከት፣ እሱ ሁለት እጆቹን ደረቱ ላይ አጣምሮ እንደ ሀውልት ቆሟል። በአጥሩ ዘለልኩ
ማኑ ፖሊሶቹ ደብድበውት ሶስት ሳምንት ሙሉ ሀኪም ቤት ተኛ
መሀል ጣቱ ተሰብሮ ቀረ። አሁን ሊያጥፈው ኣይችልም
ማኑ እንዴት ኮሙኒስት እንደሆነ ልንገርህ?
አንድ የትምህርት ቤት ጓደኛ ነበረው። ጓደኝየው በጣም ጥሩ
ልጅ ነው:: ቆንጆ ቆንጆ ግጥሞችን ይደርሳል። ግን ድሀ ብጤ ነው።
ከዚህም በላይ እጅግ የተዋበ!
አንድ ቀን የዚህ ልጅ አባት ታሰሩ። በሽተኛ ሚስት፣ ስድስት
ትንንሽ ልጆች ኣሏቸው። እሱ የመጀመሪያ ልጃቸው ነው። አባትየው ታስረው ልጆቹ ምን ይብሉ? ልጁ ጨነቀው። ያባትየውን ጉዳይ የሚከታተለው የፖሊስ ሹም ቢሮ ሄደና እያለቀሰ የቤቱን ችግር ነገረው። ፖሊሱ ደግ ነበር። የልጁ ችግር ገባው። ጉዳዩ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ፣ አባትህን ዝም ብዬ ነፃ ብለቃቸው፣ የበላይ ሹማምንት ይቀጡኛል፡፡ ብቻ ለማንኛውም ዛሬ ማታ ለእራት ቤቴ ብቅ በልና እንመካከርበታለን» አለው
ሲመሽ ልጁ ፖሊሱ ቤት ሄደ፡፡ እራት ከበሉ በኋላ ፖሊሱ
ልጁን ያሻሽው ጀመር። ልጁ በመጀመሪያ ደነገጠ፤ በኋላ ተቆጣ::ይኸኔ የፖሊሱ ፊት ተለወጠ። ደግ የነበረው በሀይል ክፉ ሆነ፡፡ ረጋ ባለ ድምፅ ልጁን እንዲህ እላው
«አባትህ በኔ እጅ ነው:: ላስገድለውም እችላለሁ፣ ላሳስረውም እችላለሁ፣ ላስፈታውም እችላለሁ፡፡ ስለዚህ አባትህ ባንተ እጅ ነው
ማለት ነው:: እዚህ ከኔ ጋር ካደርክና ካስደሰትከኝ፣ ነገ አባትህ
ለምሳ ቤቱ ይመጣል፣ ተነገ ወዲያ መስሪያ ቤቱ ይሄዳል፣ በስህተት
መያዙን አስመሰክርለታለሁ፡ ቤቶችህ የሚበሉትን ያገኛሉ። እኔን
እምቢ ካልከኝ ግን አባትህ ወየውለት! ትንንሽ ወንድሞችህና
እህቶችህም ምን እንደሚውጣቸው አላውቅም፡፡ ባንተ አጅ ናቸው።
ሁሉም ባንተ እጅ ነው»
ልጁ እሺ እርስዎ እንዳሉኝ አደርጋለሁ አለ። አባትየው ተፈታ።
መስሪያ ቤቱም ተቀበሉት
ልጅየው ውርደቱን ተሸክሞ መጣና የተፈፀመበትን ግፍ
እያለቀሰ ለማኑ አጫወተው። ምን ባደርግ ይሻለኛል? አለው
አየሀ፣ ሲለያዩ ፖሊሱ ምን ብሎታል «እኔ የተገደልኩ ወይም
የተጎዳሁ እንደሆነ፣ ሁለት ሌሎች የፖሊስ ሹማምንት አሉ፤ ጓደኞቼ
ናቸው፡ ኣንተ እንደጎዳኸኝ ያውቃሉ፤
ስለዚህ አባትህን እነሱ
መልሰው ያሳስሩታል። ያን ጊዜስ አባትህን አያርገኝ፣ ቤቶችህን
አያርገኝ! ስለዚህ በኔ ላይ የበቀል ሀሳብ ባታስብ ጥሩ ነው።
ብሉታል። ልጁ ምን ይሁን? የተዋረደ ክብሩን ሊበቀል አልቻለም።
ግን ውርደቱ ሊረሳ የሚችል አይነት አይደለም። ልጁ አልቻለም።
በዛበት፡፡ ከሚችለው በላይ በዛበት፡ አበደ። አበደ በቃ! እብድ ሆነ።
ቤቶቹ በድህነታቸው ላይ ሀዘን ተጨመረጣቸው:: ደግሞስ ማን
ያውቃል? ኢራንም አንድ ታላቅ ደራሲ ባጭሩ ተቀጨባት ማለት
ይሆናል'ኮ
አይ ኢራን! ስንቱን ጉድ ትችያለሽ! ኢራን ውቢቱ! እንዴት
መሰለችህ! አቤት ህዝቡን ብታውቀው! ቋንቋውን ብትሰማው! አይ ህዝብ! እንደ ምንም ብዬ ከሻህና ከጋንግስተሮቹ ነፃ ባወጣው'ኮ የኢራን ህዝብ በደስታ ሊኖር የሚችል ህዝብ ነው። ክብሩን ልመልስለት ብችል፡ ማንንም ሳይፈራ ሰርቶ ለመብላት ቢችል፤ ህግ ካልጣስ ማንም ሊያስረው እንደማይችል እርግጠኛ ለመሆን ቢችል!
ሻህና አሜሪካኖቹ ሀብቱን ባይነጥቁት! ብቻዬን እንዳልመስልህ! በጭራሽ ብቻዬን አይደለሁም፡፡ እኔ ያየሁትን ያዩ፣ እንደኔ የሚቆረቆሩ፣ እንደኔ የተናደዱ፣ እንደኔ ደም ለማፍሰስ ዝግጁ የሆኑ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ኢራናውያን አሉ። አሉ! አሉ!
የሚመራቸውን ይጠብቃሉ! (አለ ባህራም)
ባህራምና እኔ ከተዋወቅን ጀምሮ እስከተለያየን ድረስ ስለኢራን
ያወራልኝ ነበር። ኢራን፣ ኢራን፣ ኢራን። አልሰለቸኝም ግን ይበዛብኝ ነበር። ይልቁንም የአገሩ መበስበስ ያንገሸግሸኝ ነበር፡፡ ሁሉ ነገር በጉቦ ነው። ፖሊሱ፣ ጃኛው፣ አስተማሪው ሳይቀር ጉቦ ይበላል።
👍17🔥2