አትሮኖስ
281K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
480 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምንትዋብ


#ክፍል_ዘጠኝ


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

...ጥላዬ ፊቱ ጥላሸት ለብሷል።
አብርሃ፣ የጥላዬን ፊት መለዋወጥና ለምንም ነገር ፍላጎት ማጣት አስተዋለና ስሜቱ ከየት እንደመጣ ተመራመረ። ኸቤቱ የወጣ..ናፍቆት ይሆናል አለ፤ ለራሱ።

በፋሲል ቤተመንግሥት በስተግራ በኩል ወደ ላይ ሲወጡ፣
ሰዎች ከላይ ወደእነሱ አቅጣጫ ሲመጡ፣ ወንዶች ቆባቸውን፣ ሴቶች ክንብንባቸውን እያወረዱ እጅ እየነሱ ሲያልፉ፣ ጥላዬ እርስ በርሳቸው ሰላምታ የሚሰጣጡ መስሎታል። ጥቂት እንደተራመዱ፣ አብርሃ የተማሪ
ቆቡን አውልቆ እጅ ሲነሳ አየው።
መንገዱ ላይ ካለሁለቱ በስተቀር
ማንም የለም።

ጥላዬ፣ “ማነን ነው እጅ ምትነሳ? ኸኔና ኻንተ በቀር ማነም የለ
በምንገዱ” ሲል ጠየቀው።
“ማነነም! ሰዎቹስ እጅ ሲነሱ አላየህም እንዴ? እኼን ምንገድ አየህ?”አለው፣ አገጩን ወደፊት ቀደም አድርጎ፣ ሰፊውን የእግር መንገድ እያሳየው። “የንጉሡ መኸጃ ነው። እሳቸው ሲወጡ ማንም በዝኽ አያልፍም። አየኸው ያን ደጋን የመሰለ የደንጊያ ግንብ መተላለፊያ?ንጉሡ ወደ ራስጌ
አጤ ፋሲል ያሠሩት የራሶቹ መኖሪያ ነው...ኸዝኸ ከፍ ብሎ ነው ያለ... ወይ ደሞ ወደ ሌላ ቦታ ሚሄዱበት ነው።እሳቸው ባይኖሩም ቆብ አውልቆ እጅ መንሳት ደንብ ነው። ቦታው
እስተስሙ ቆብ አስጥል ነው።”

“እንደቤተክሲያን ነው በለኛ!” አለ ጥላዬ፣ ፈገግ ብሎ።
“ንጉሥ እኮ ፊታቸው ተሸፍኖ ነው ሚሄዱ። አሁን ታቦት ትኩር
ብለህ ታያለህ? አታይም! እሳቸውንም ፊታቸውን ጨርሶ አታይም።
አብረዋቸው ሚኸዱት ስንኳ ኸጎናቸው ሲራመዱ መሬት መሬቱን
እያዩ ነው። ደሞም አለልህ ሊቀመኳሱ... ንጉሥ አሳሳች ሚባለው። ልክ
እንደሳቸው ሁኖ ይወጣል። ንጉሡ ኸቤት ተቀምጠው እሱ እሳቸውን
መስሎ ይወጣል። ያን ግዝየ ሰዉ ንጉሡ መጡ ብሎ ይሰግዳል።
እንዲህ ዋዛ መስሎሀል! ወሬ ስሰማ እቴጌዎቹ ደሞ ሲወጡ ምንግዝየም
በጃንደረሳ እየተጠበቁ ነው።”
“ጃንደረባ ደሞ ምንድርነው? ስለምንስ ይጠበቃሉ?”
“ጃንደረባማ ... እቴጌዋን ሚጠብቀው... ስልብ ነው። ሚጠብቀው
ያው እቴጌዋ ኸሌላ እንዳይኸዱ ነዋ!” አለ፣ ሳቅ ብሎ።
ጥላዬ ለራሱ፣ ወለቴ
ጉድ ፈላባታ አለና ለአብርሃ፣ “እኼ
ቤተመንግሥት ሚባል ነገር ብዙ ጣጣ አለው” አለው።
“ወጉ እንግዲህ እንደዝኸ ነው። እኼ ምታየው... ኸቤተመንግሥቱ
አጠገብ ያለው ሁሉ ደሞ የባለርስቶቹ ምንደር ነው።”
ጥላዬ ዞር ብሎም አልተመለከተ።
አብርሃ፣ ጥላዬ ለሚያየው ነገር ሁሉ እምብዛም ትኩረትና ፍላጎት
የሚያሳይ አልመስል አለው። ምን ማድረግ እንዳለበት ግራ ገባው።
“ትመለስ ይሆን?” አለው።
“እረገኝ ስለምን?”
“እንግዲያማ ተጫወት። እኔኮ ይህ የመጣሁት አገር ላላምድህ ብየ ነው። እኼ አሁን ምንኸድበት ዘመዴ መልካም ሰው ነው። አንዱም እሱን ብየ ነው እጐንደር የመጣሁት።”
አልፎ አልፎ እየተጫወቱ ቁልቁል ወርደው ረጅም መንገድ ተጓዙ።
ጥላዬ ከቦት የነበረው የመጫጫን ድባብ እየለቀቀው መጣ። ያየውን
ሁሉ እያደነቀና እየወደደ የሆዱን ባር ባር ማለት ረሳ።

“ኸዝኸ ወረድ ስትል የዕጨጌው ሰፈር አለ” አለው አብርሃ
ሊያጫውተው ፈልጎ። “ሸማኔውም ወዲያ ነው። ማዶ ደሞ የባለእጌዎች ምንደር አለ። ለብቻቸው ነው ሚኖሩ። መቸም ባለእጌዎቹ ግንበኞች
አናጢዎች፣ ሸማኔዎች፣ ቀጥቃጮችና ሸክላ ሠሪዎች ናቸው ቤተመንግሥትን ሚያስጌጡ እነሱ ማዶሉ? እስላምጌ ደሞ በዝያ ስትዘቀዘቅ አለልህ። የስላሞቹ የነጋዴዎቹ ሰፈር ነው። ብዙ ሰው ይኖራል ኸዛ። በቅሎና ፈረስ ገባያውም ኸዛው ነው።”

ድንጋይጌ ሲደርሱ፣ “እኼ ገባያው ነው። ቅዳሜ ነው ሚቆም። ዛሬ
ጭር ቢል እንዲህ እንዳይመስልህ። ነጋዴውም... ሁሉም ነው ሚወጣ። ነገ ማልደን እንመጣለን” አለው።

ጥላዬ መልስ አልሰጠውም። ወለተጊዮርጊስ ከንጉሥ ጋር ግብር
በምትቀመጥበት ቀን መውጣት አልፈለገም። ከቤተክርስቲያኑ ግቢ እንደማይወጣ ለራሱ አስገንዝቦ ዝም አለ።

አብርሃ ዘመድ ቤት ገብተው መልካም መስተንግዶ ተደረገላቸው።ጥላዬ አልፎ አልፎ የያዘውን ጠላ ፉት ከማለትና ከአብርሃ ዘመድ የሚቀርቡለትን አንዳንድ ጥያቄዎች ከመመለስ በስተቀር አብርሃና ዘመዱ በትግርኛ ስለሚያወሩ በዝምታ ተውጦ፣ ጠላውን እየተጎነጨ፣
አንዳንዴም እየሰለቸው ቆይቶ፣ ከሰዐት በኋላ፣ ተነሥተው ወጡ።
ደብረብርሃን ሥላሤ ሲደርሱ ተለያዩ። ጥላዬ ጠዋት ተቀምጦበት የነበረው ዋንዛ ዛፍ ሥር ተቀምጦ ያየውን ሁሉ አሰበ። ጐንደር ልዩ ቦታ፣ ከግምቱ በላይ ሆነችበት፤ ወደዳት። የገባ ዕለት ዐዲስ ሕይወት ልትሰጠው የገባችለትን ቃል ኪዳን አጸናችለት። ድንገት የፈሰሰ
ሐሞቱ ነፍስ ዘራ። የአለቃ ሔኖክ ምሽት እሑድ ይመለሳሉ ብለው
ነግረውናል። አብርሃ ደሞ ሰኞ ጠዋት እንኸዳለን ብሎኛል። ብቻ አንዴ እሳቸውን ላግኛቸው፣ ኸዝያ ወዲያ ማደርገውን እኔ አውቃለሁ አለ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ጐንደርና ቋራ ምንና ምን

ወለተጊዮርጊስ፣ አፄ ፋሲለደስ ቅጥር ግቢ ስትገባ፣ አያቷ
እርምጃቸውን ገታ አድርገው፣ “እኼ አጤ ፋሲለደስ ያስገነቡት አሁን ጃንሆይ ሚኖሩበት ነው። እንግዲህ አንቺም ኸዝኸ ነው ምትኖሪው”አሏት።

“ኸዝኸ?” ብላ ዐይኖቿ እስከመጨረሻው ተከፈቱ።

የባለሦስት ደርቡ ህንጻ ግዝፈት አስደነቃት። ሰማይ ጠቀስ
መሰላት። በግንቡ ማዕዘኖች የተሠሩትን የእንቁላል ቅርፅ ያላቸውን ግንቦች አይታ ተደነቀች። ሰገነቱ ላይ ያለው ሰቀሰቅ ለመተኮሻ ተብሎ እንደተሰራ መገመት አቃታት። በእንቁላል ግንቦቹ መሃል ወደ ሰገነቱ
የሚወስደውን የዕንጨት ደረጃ ተመልክታ ምን እንደሆነ አልገባ አላት።

ዮልያና ቀጠሉና፣ “ጃንሆይ ኸዚያ ኸሰገነቱ ቁመው ሁሉን ይቃኛሉ፤
አንዳንዴም ኸዚያው ላይ ሁነው አዋጅ ይነግራሉ። አንቺም እንግዲህ ኸዚያ ላይ ምትቆሚበት ቀን ሩቅ አዶለም” አሏት፣ ሳቅ ብለው።

ዝም አለች። ያን መሰል ነገር አይታ ባለማወቋ፣ ከመንገድ ድካም
ጋር ተደምሮ አእምሮዋ ያየችውን ሁሉ መመዝገብ አልሆንለት አለው።

የግንቡ ግዝፈት፣ የንጉሥ ሚስትነት ልኩ ምን ድረስ እንደሆነ
ገለፀላት። ስለዚህ ዓለም ያላትን ግንዛቤ ሁሉ ግልብጥብጡን አወጣባት።ስለራሷ የነበራትን ግምት አዛባባት። “ንግሥት እሌኒን አረግሻለሁ”እየተባለች፣ የአፄ ሚናስ ደም በደምስሯ እንደሚንቆረቆር እየተነገራትና
በእንክብካቤ ያደገችው ልጅ ለእዚያ ለምታየው ግርማ ሞገስ ሁሌ የማትመጥን መስሎ ተሰማት።

ከቋራ መጥታ ያን መሰል ኑሮ ውስጥ መግባት ምን ማለት እንደሆን ማወቅ ተሳናት። እኛ እናት አባቷ ቤት መደብ ላይ ተኝተው የነበሩት ሰው ንጉሥ ናቸው ሲባል ድንገት እንደ ጨረቃ የራቁባትን ያህል ዛሬ ደግሞ የሚኖሩበትን ቤት ስታይና ልትኖር እንደታጨችበት ጭምር
ስታስብ፣ የእሷም ሕይወት ምን መልክ ሊይዝ እንደሚችል ለመጀመሪያ ጊዜ ተገነዘበች።

ጐንደር ታላቅ የሕይወት ግብዣ እንዳቀረበችላት ታወቃት። ሁሉም ካሰበችው፣ ከገመተችውና ካለመችው በላይ ሆነባት::
ፍርሐት ፍርሐት አላት።አካባቢዋን እንደ ዋዛ ታልፍ የነበረችው ወለተጊዮርጊስ፣ ቋራ እንደዚያ ቆማ የምታደንቀው ሰው ሰራሽ ነገር ባለማየቷ ለመጀመሪያ
ጊዜ ያየችውን ውበት አደነቀች። ጐንደርና ቋራ ምንና ምን አለች።
ያየችው ሁሉ የሰው ልጅ የእጅ ጥበብ ውጤት መሆኑን ተጠራጠረች።ያንን የመሰለ ውበት የቀረጹትን ሰዎችና እጆች ማየት ተመኘች።
👍101
#ትኩሳት


#ክፍል_ዘጠኝ


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

..ፊሬንዜ ውብ ከተማ ናት፤ የነጻንቴ የነሚኪኤል አንጀሎ ከተማ!

አንዲት ትንሽ ሬስቶራንት ውስጥ እራት ስንበላ ነበር፡፡ ሲልቪ
ምግቧን ረስታ ወደ ኋላዬ በኩል ትኩር ብላ ማየት ጀመረች።
ሳይታወቃት በግራ እጂ ፀጉሯን አስተካከለች ብቻ መስተካከል
አያስፈልገውም ነበር። ገባኝ። የምትጎመጀው ወንድ አይታ መሆን አለበት። ሹካና ቢላዋን ቁጭ አድርጋ ወይን አንስታ ፉት አለችና፣ ብርጭቆውን መልሳ እንደማስቀመጥ፣ በእጆቿ ውስጥ በዝግታ እያሽከረከረችው ወደዚያው ወደ ኋላዬ ማየቷን ቀጠለች። ቀይ ከንፈሮቿ ገርበብ፣ በወይን ረጠብ ብለው ያስጎመጃሉ

እሷ ወደዚያ ስታይ እኔ እሷን ስመለከት፣ ቆንጆ ፊቷ ቀስ ብሎ
ፈገግ አለ፤ ሰማያዊ ኣይኖቿ ስልምልም ማለት ጀመሩ። ምኞቱ
ውስጤ ሲያድግ ተሰማኝ፡፡ አይኖቿ ከአይኖቼ ጋር ተጋጠሙ፣ ፊቷ መቅላት ጀመረ፡ አይኖቿ ተርገበገቡ። ሰውየው ማን እንደሆነ ማወቅ ፈለግኩ፡ ግን ወደኋላ ከተገላመጥኩ ነገሩ ይበላሻል፣ ስለዚህ ተውኩት

«ፍሬ ይምጣልሽ?» አልኳት
«የለም በቃኝ። አንተ ብላ »
«እኔም በቅቶኛል»
«እንግዲያው እንሂድ?» አለችኝ፣ ወደ ቅድሙ በኩል እያየች
ስንወጣ እሷ ታተኩርበት ወደነበረው በኩል ተመለከትኩ፡፡
በየጠረጴዛው የተበታተኑ አንድ አምስት ወንዶች አሉ፡ የትኛው
ፍላጎቷን እንደ ቀሰቀሰ ለማወቅ አልቻልኩም፡፡ ግን ፍላጐቷ በሀይል ተቀስቅሷል። አልጋ ውስጥ ስንገባ መብራቱን አጠፋችው፣ እየተንገበገበች አቀፈችኝ፤ በመጨረሻ ላይ በእንግሊዝኛ ቃዥች

«Please, my lord! Please, have mercy!

ሌላ ሰው ሆኜ፣ ግን ማን እንደሆንኩ ሳላውቅ፣ በቅንዝርና
በቅናት እየተቃጠልኩ፣ ጥልቅ የሆነ ስጋዊ ደስታን ተደሰትኩ።
በነጋታው ቀኝ ጡቷን እያመማት ዋለ። ሳይታወቀኝ ጨፍልቄው
ኖሯል በሌላ ቀን፣ «ማን ሆኜ ነበር?» አልኳት። ስንበላ በስተኋላዬ አንድ ሰውዬ እይታ ኖሯል። «ልክ ስመ ጥሩውን ባለቅኔ ሎርድ ሳይረንን ይመስል ነበር አለችኝ እንደዚሀ ስንል፣ እሷ ደስ የሚላትን ወንድ ስታይ፤ እኔ በጭለማ እሱን እየሆንኩ ሳቅፋት እሷ ስትቃዥ፣ እኔ ስነክሳት ስጨፈልቃት፣ እንደዚህ ስንል፣ በሰማያዊ, አይኖቿ ብርሀንና በሰፊ አፏ ሳቅ እያሞቀችኝ፣ በውብ ወጣት ገላዋ እያቃጠለችኝ፡የጣልያንን ከተማዎች እያዞረችኝ «Je men fous» አያለች አያሳቀችኝ፣ እንደዚህ ስንል የበጋው እረፍት ወደ ማለቂያው ተቃረበ፡፡ ከፊሬንዜ ሮማ
ከሮማ ናፖሊ፤ ከናፖሊ ኒስ (ፈረንሳይ) ከኒስ ማርሰይ ተጓዝን።

ከማርሰይ እሷ ቤቶቿን ጥየቃ ፓሪስ ሄደች፡፡ ባቡር ጣቢያው
ሄጄ ስሸኛት ልክ የዛሬ ዘጠኝ ቀን ማክሰኞ ኤክስ እገባለሁ፤ ማታ
ቤቴ እጠብቅሀለሁ» አለችኝ
የሲልቪ ናፍቆት የሚገድለኝ መስሎኝ፤ ዘጠኝ ቀን ሙሉ
እንዴት ሊያልፍልኝ ነው? እያልኩ ስሰጋ ነበር፡፡ ግን ባቡሩ ይዟት
እንደሄደ፣ በሀዘን ፈንታ እፎይታ ተሰማኝ፡፡ ማታ አልጋ ውስጥ
ገብቼ ብቻዬን እንደ ልቤ ስገላበጥ፣ ብቸኝነት ሳይሆን ምቾት ተሰማኝ፡፡ ምቾቴ በደምብ እንዲታወቀኝ ስል በብዙ ተገላበጠኩ።ጧት ስነቃ ሲልቪ የለችም፡ ብቻዬን ነኝ፡፡ በናፍቆት ፈንታ ደስታ ተሰማኝ፡፡ ሲልቪ ሰልችታኝ ኖሯል? ወይስ ከሰው ጋር ለመኖር አልተፈጠርኩም? ሊገባኝ አልቻለም

ኤክስ ሄጄ ሲቴ (ዩኒቨርሲቲ) ውስጥ አንድ የመኝታ ክፍል
ተቀበልኩ፡ ሁለተኛው አመት ወደ መጀመሩ ነበር ጧት ስነሳ በመስኮቱ ደማቅ ሰማያዊ የሆነ ንፁህ ሰማይ ታየኝ።ደስ አለኝ። ሳይታወቀኝ የኤክስ ውብ ሰማይ ናፍቆኝ ኖሯል
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ባህራም ከቅርብ

ኤክስ እንደተመለስኩ መጀመሪያ ያገኘሁት ተካን ነበር፡፡ ያው
እንደ ልማዱ ጥፍሩን እየነከሰ፣ የት ነበርክ? ከማን ጋር ነበርክ? ምን
አደረግክ? ምን አየህ? እያለ በጥያቄ አጣደፈኝ፡፡ ግን ሳየው የጥርሱ መበለዝ የቀነሰ መሰለኝ፡፡ አፉም አልገማኝም፡፡ ጊዜው ከእራት በኋላ ነበር፤ ና ቡና ላጠጣህ ብሎ ወደ ክፍሉ ወሰደኝ፡፡ ቤቱ በጭራሽ
አይገማም!

እንግዲህ፣ የዩኒቨርሲቲው መኝታ ቤቶች ባለ ሶስት ፎቅ
ሲሆኑ፣ እያንዳንዱ ፎቅ ላይ ለሚገኙት ሰላሳ ያህል ክፍሎች የጋራ የሆኑ አንድ የገላ መታጠቢያ ክፍልና፣ አጠገቡ ደግሞ (ልክ ደረጃው መጨረሻ ላይ) አንድ የቡና ማፍያ ምድጃ ያለው ክፍል አላቸው።ተካ ቡናውን ሊጥድ ወደ ማፍያው ክፍል ሲሄድ እኔ የሱን መኝታ ክፍል ተመለከትኩ፡፡ ንፁህ ነው። ፊት መታጠቢያው ዘንድ፡ ግማሹ ያለቀ ኮልጌት የጥርስ ሳሙናና አንድ የጥርስ ብሩሽ አለ። ተካ ጥርሱን ይቦርሻል! ምን ነካው?. ምን ይነካዋል? ያው
የተለመደው መሆን አለበታ! አንድን ጎረምሳ ጥርሱን ሊያስቦርሸው የሚችል ምንድነው? ሴት አይደለችም? ግምቴ ልክ ይሆን? ልክ
መሆን አለበት። አለዚያ ምኑን ደራሲ ሆንኩት?

አንገቴን በበሩ ብቅ አድርጌ አየሁ። ጨለም ያለው ረዥም
መተላለፊያ ኮሪዶር ባዶውን ነው፡፡ ኮሪዶሩ መጨረሻ ላይ ያለው
የቡና ማፍያ ክፍል ተዘግቷል። ተካ ገና ቡናውን በመጣድ ላይ ነው
ማለት ነው። ጊዜ አለኝ፡፡ በሩን ዘጋሁ፡፡ ቶሎ ወደ አልጋው ራመድ
አልኩ፡፡ አንሶላውን ላመሉ ገለጥ ከደረግኩት። ጎምበስ ብዬ ትራሱን
አሸተተኩት፡፡ የሴት ጠረን። ያለጥርጥር። እንዴት ያለች ትሆን?
ቶሎ አልጋውን አስተካከልኩና፣ ቁጭ ብዬ ጋዜጣ እያነበብኩ
ቆየሁት ቡና ከጠጣን በኋላ ሊሎቹን ሀበሾች ፍለጋ ወጣን
ተካ «ተመስገንን ግን አታገኘውም» አለኝ «ወደ ፓሪስ
ተዛውሯል። ለምን እንደተዛወረ ታውቃለህ?»
«ለምንድነው?» አልኩት
«ነጭ ሴት ሰለቸኝ አለ።»
«ምን?
«ጥቁር ሴት ካላገኘሁ ልማር አልችልም አለ፡፡ እዚህ ኤክስ
ውስጥ ሁለት ጥቁር ሴት ብቻ ነው ያለው፡ ሁለቱም አስቀያሚ
ናቸው። ስለዚህ ፓሪስ መሄዴ ነው:: ቢሆን እግዜር ብሎ አንዲት
ሀበሻ ልጅ ታጋጥመኝ ይሆናል፡፡ ባይሆን ደሞ ሌላ ጥቁር ሴት
አላጣም፣ ብሎ ሄዴ»
ተመስገን እውነቱን ነው። ኤክስ ውስጥ ጥቁር ሴት አይገኝም
ሀበሻ ሴት ይናፍቃል። ያገራችን ሴቶች ትዝ ይሉናል፤
አነጋገራቸው፣ አሳሳቃቸው፣ መሽኮርመማቸው ይናፍቀናል፡ ጥቁር ቆዳቸው፣ ነጭ ጥርሳቸው እንቅልፍ ይነሳናል፡ በሀሳባችን
አረ ንሺ» ሲሉ ይሰማናል።

አንዳንድ ጊዜ ተሰብስበን ስለነሱ እናወራለን፡፡ ናፍቆት ሲበዛብን
እየሳቅን እየጮህን እንዘፍናለን
«አንቺ ጥቁር ድንጋይ ፍቅር አይገባሽ በሰው አገር ሆኜ ተቃጠልኩልሽ»
ሉልሰገድማ “ልጆችዬ፣ አብረን አንዲት እምስ የተቀረፀባት ሻማ ለቁልቢው እናብራለትና » አለን እምስ በፖስታ ላክልን፣
መጋረጃ እናስገባልሀለን፣ እንበለው፡፡ እውነቴን'ኮ ነው! ያገሩ ልጆች ነን፡ ይሰማናል። ኧረ እናታችሁን! ይሄ ምኑ ያስቃል?»

እኔና ተካ ሀበሾቹን ሉልሰገድ ቤት እገኘናቸው:: ባህራምና
አንድ ሌላ ኢራናዊ አብረዋቸው አሉ፡፡ ይህ ሌላ ኢራናዊ ጀምሺድ
ይባላል። ረዥም መልከ ቀና ወጣት። ጥቁር ሱፍና ነጭ ሸሚዝ
ከቢራቢሮ ክራቫት ጋር ለብሷል። ግብዣ ለመሄድ የተዘጋጀ
ይመስሳል። ረዘም ያላ ፈት፡ ቀጥ ያለ ረዥም አፍንጫ። ከሀር
መሳይ ውብ ቅንድቦቹ በታች ሰማያዊ ትንንሽ አይኖች ሁልጊዜ
ይጨፍራሉ፡፡ ብርሀን ሳቅ፣ ብልጠት የሚፈራረቅባቸው፣ ህይወት የሞላባቸው አይኖች ናቸው፡፡ በኋላ እንደተረዳሁት፣ ጀምስድ ፈረንሳይ አገር ከመጣ አመት አልፎታል። ታድያ ቢበዛ ስምንት መቶ የፈረንሳይኛ ቃላት ቢያውቅ ነው (የቋንቋ ስጦታ የለውም) ግን እነዚህ ስምንት መቶ ቃላት ለንግግር ኮርተው ይበቁታል። ምክንያቱም ቀጭን ኮሚክ ድምፁና ትንንሽ ብልጮ አይኖቹ፣ ያለ ቃላትም ቢሆን የፈለገውን ይገልፁለታል
👍131