#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“እምዬ ጐንደር እንግዳ ተቀባይ እኮ ናት።”
ጥላዬ፣ እምነቱንና ተስፋውን ጐንደር ላይ ጥሎ ሐሙስ ቀን እዚያች ብርቅየ ከተማ ገባ። ጨለማ የከተማዋን ሰማይ ለማልበስ በመጣደፍ ላይ
ነው። ጐንደሬዎች ቤታቸው ለመከተት ፈጠን ፈጠን እያሉ ሲራመዱ፣ጥላዬ፣ ብዛታቸው ብቻ ሳይሆን ዓይነታቸው አስደነቀው። እንደ ግሪኮች፣ አርመኖች፣ ህንዶችና አረቦች የመሳሰሉ የውጭ ሃገር ዜጎች ሕዝቡ መሃል ውር ውር ሲሉ፣ የቆዳቸው፣ የመልካቸውና የአለባበሳቸው
መለየት አስደመመው።
ጭቃ ምርጎቹን ባለሳር ክዳን ጎጆዎች ትክ ብሎ አያቸው። ባዘቶ
የለበሱ የሚመስሉ ዋንዛ ዛፎች ስር ችምችም ማለታቸውና እንደ ቋራ ተሰባጥረው አለመቀመጣቸው ገረመው። በየቦታው ጣል ጣል ያሉት
የድንጋይ ግንቦችና ነገሥታት ብቻ የታደሉባቸው የኖራ ቅብ ቤቶች
የከተማዋ ጌጥ መስለው ታዩት። ያየው ሁሉ ከቋራ የተለየ ሆነበት።
ጐንደር ልዩ ስፍራ ሆነችበት፤ አስገረመችው።
ዐዲስ ሕይወት ልትሰጠው ቃል ኪዳን ገባችለት። እየተዘዋወረ ከተማዋን ማየት ፈልጎ ጨለማው በፍጥነት ማደሪያ እንዲፈልግ አስገደደው። ቤተክርስቲያን ፍለጋ ዐይኑን ሲያዘዋውር፣ አንድ የቆሎ ተማሪ በፍጥነት ሲራመድ አየና ሮጦ ደረሰበት።
“ከርመህ ነው? ላገሩ እንግዳ፣ ለሰዉ ባዳ ነኝ። ማደሪያ ሚሆነኝ
ደጀሰላም ባገኝ ብየ” አለው።
“ኸደብረብርሃን ሥላሤ ማታድር? ምን የመሰለ ዛኒጋባ በቤተክሲያን
ዙሪያ እያለልህ። ወደዛው ነው ምኸድ፤ በል ና። አገርህ ወየት ነው?”
“እማር ብየ መጥቸ” አለ ጥላዬ፣ መናገር አልፈለገም።
“ጐንደር ደሞ ለትምርት። ኸየቦታው ሚመጡ ተማሮች፣ ሊቃውንት፣ ካህናትና መምህሮች ሁሉ ኸዝሁ ማዶል ያሉት?” ብሎ ነጫጭ ጥርሶቹን አሳየው፣ ተማሪው።
ገራ ገር ፈገግታው ጥላዬን ማረከው። ዕድሜ ልኩን የሚያውቀው መስሎ ተሰማው። ቀደም ብሎ ማደሪያውን ሲያስብ ባይተዋርነት የተሰማውን ያህል፣ ከትከሻው ሸክም እንደወረደ ሁሉ ቀለል አለው።
“ቅኔ ልትማር ነው የመጣህ?”
“ሥዕል ልማር ብየ ነው የመጣሁ።”
“ዛዲያ ጐንደር ምን ገዷት! እደብረብርሃን ሥላሤ መምህሮቹም ተማሮቹም አሉልህ፡፡”
ጥላዬ ተደሰተ። ተማሪው ገዱ ሆኖ ተሰማው። ልባዊ ፈገግታው ደግ
ሰው እጅ ላይ እንደወደቀ ጠቆመው። “ምን እየተማርህ ነው?” ሲል ጠየቀው።
“ቅኔ እየተማርሁ ነው። መወድስ እያኸድሁ ነው።”
“ደሕና አኸደሀል።”
“አንተስ ሞካክረኻል?”
“ሥላሤ ደርሻለሁ። ማድርበት ደጀሰላም የት አገኝ ይሆን እያልሁ?”
“ጐንደር መጥተህ ነው ስጋት ሚያድርብህ? አንተስ አለማወቅህ ...እምዬ ጐንደር እንግዳ ተቀባይ እኮ ናት። ሴቶች ወጥ ሲሰሩ ኸደረስህ
ይሽተዋል ብለው ሳትበላ ማትኸድባት አገር እኮ ናት። ጐንደር የሁሉ ናት፤ ማንም ኸየት መጣ ኸየት ቤቴ፣ የኔ ብሎ ሚኖርባት። አልሰማህም
እንዴ፣
ቤተስኪያን ስሞ ለመኖር፣
መልካም አገር ነው ጐንደር።
ሲባልላት?” እያለ ግጥሙን በዜማ አወረደለት።
ጥላዬ ሳቅ አለና፣ “ገና መድረሴ፣ ምኔ ሰምቸ? ጐንደሬ ሁሉ እንዳንተ
ጥሩ ነው?” ሲል ጠየቀው።
“እኔስ ኸተምብየን ነው የመጣሁ። ዐራት ዓመት አርጌያለሁ ኸዝኸ።”
ተማሪው ከላይ የደረበውን ለምድ፣ ትከሻው ላይ ያንጠለጠለውን
አኮፋዳና ለውሻ መከላከያ የያዛቸውን ሁለት በትሮች ጥላዬ ትክ ብሎ ተመለከተና ከልመና እንደመጣ ገባው። ወደ ቤተክርስቲያኑ ሲደርሱ
ደጀሰላሙን ተሳልመው ውስጥ ገቡ።
“እንዴት ያለ ቤተክሲያን ነው በል” አለው፣ ጥላዬ።
“አጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ መዠመሪያ አሠሩትና ተቃጠለ። ኸዚያ በኋላ፣ ልዣቸው... ሦስተኛው ሚባሉት አጤ ዳዊት እንደገና አሠሩት።
እሳቸው ግና ባባታቸው ስም እንዲጠራ ስለፈለጉ እኔ አሰራዋለሁ ስሙ ግን ባባቴ ይሁን አሉ።”
ጥላዬ ፈዞ ቆሞ የቤተክርስቲያኑን አሰራር ሲያደንቅ ተማሪው፣ “እኛ
ስንገባ ስንወጣ ለምደነዋል። እንግዲህ አንዱን ጥግ ይዘህ ተኛ። ኸኛ ዘንድ ምኝታ የለም ሁኖ ነው” ብሎት ሄደ።
ጥላዬ ቤተክርስቲያኑን እንደገና ተሳልሞ ዙርያውን ሲመለከት፣
እየጨለመ በመምጣቱ በወንዶቹ መግቢያ በኩል ጭንቅላቱን ጉልበቶቹ መሃል ቀብሮ ተቀመጠ። ግቢው ጭር ብሏል። መንገድ ሲመሽበት፣
“ቤት ያብርሃሙ ሥላሤ ነው” እያሉ ቁርበት ጣል፣ ትኩስ ሽሮ እንጀራ
ላይ ፈሰስ አድርገውለት፣ አለበለዚያ ቆሎ እንዲቆረጥም ወይ ቂጣ እንዲያላምጥ ሰጥተውት ያሳደሩት ሁሉ ትዝ አሉት። ከነጋ እህል አፉ አላደረገም። ሆዱ ከረሀብ ብዛት ዋይ ዋይ አለበት፤ ያለማቋረጥ
አዛጋው።
በዕድሜ ከእሱ ትንሽ ከፍ ስለሚለው ተማሪ አሰበና ባይለየው መረጠ። ስሙን እንኳ ሳይጠይቀው በመሄዱ ተቆጨ። አንገቱን እንደደፋ ሲያሰላስል ድምፅ ሰማ። ቀና ሲል ተማሪዎች ወደ መማሪያ ቦታቸው ወደ ቤተክርስቲያኑ ጀርባ ይሄዳሉ። ተማሪው ከእነሱ ነጠል ብሎ ወደእሱ ሲመጣ አየው። ሁለመናው ተበራታ።
“ራት ቢጤ አመጣሁልህ። የውሃ ቅሌን ልተውልህና ገሠሣ ሲያበቃ
መጥቸ ወስደዋለሁ። ስትተኛ ኸዚሁ ተወው። አነሳዋለሁ” ብሎት
መንገድ ሲጀምር ጥላዬ ከተቀመጠበት ተነስቶ፣ “ሥላሤ ያክብሩልኝ።ስሜንም ሳልነግርህ... ጥላዬ እባላለሁ... ከቋራ ነው የዘለቅሁ” አለው::
ቀደም ብሎ አባቱ ፈልገው እንዳያገኙት ሲል ማንነቱን ደብቆ፣
አሁን የተማሪው ደግነት ምሥጢሩን አሟሸሸበት።
“በል ነገ ያገናኘን። አብርሃ ነው ስሜ። ገሠሣ እንዳያመልጠኝ
ብሎት ተማሪዎቹ ወደሄዱበት አቅጣጫ አመራ።
ጥላዬ፣ አብርሃ የሰጠውን ፍርፋሪ በልቶ፣ ውሃውን በላዩ ቸልሶና
አምላኩን አመስግኖ የመንገድ ድካም ስለተጫጫነው አንዱ ዛኒጋባ ጋ ተጠግቶ ጋደም እንዳለ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰደው።
ጠዋት ድምፅ ሲሰማ ብንን አለ። የት እንዳለ ለማወቅ ጥቂት ጊዜ
ወሰደበት። የሌሊቱ ብርድ፣ ልብሱን ውሃ የነካው አስመስሉታል። አንድ ጋቢ መኝታም ከላይ የሚለበስም ሆኖ አገልግሎታል። ከተቀመጠበት
ተነስቶ የቤተክርስቲያኑን መግቢያ በር ተሳለመና ወንዶቹ መግቢያ
ትይዩ ያለ አንድ ዋንዛ ዛፍ ስር ሄዶ ዳዊቱን አውጥቶ መድገም ጀመረ።
“አድረህ ነው?” የሚል ድምፅ ሲሰማ ቀና አለ። አብርሃ ነው ።
“ደሕና... ደሕና ... ይመስገነው።”
“አንደዜ ጠሎት ላድርስና ኸየንታ ሔኖክ ዘንድ ወስድሀለሁ” ብሎት
ሄደ።
ጥላዬ፣ በእሽታ ራሱን ነቀነቀለትና ወደ ዳዊቱ ተመለሰ። የዕለቱን
አድርሶ ሲጨርስ ዳዊቱን ማኅደሩ ውስጥ ጨምሮ፣ ስንጥር አንስቶ
መሬት ላይ መሞነጫጨር ጀመረ። እንደለመደው የወለተጊዮርጊስን ምስል ሊሥል ፈልጎ እዚያ ያደረሰው ምን እንደሆነ ትዝ ሲለው
ስንጥሩን ወረወረው።
ከቤት የወጣበት ምክንያት በመንገድ ድካምና በረሐብ በአእምሮው ውስጥ እየደበዘዘ መጥቶ ነበርና አሁን ቁጭ ሲል ሁሉ ነገር ፊቱ ላይ ድቅን አለበት። ወለተጊዮርጊስ ጐንደር መግባት ከለመግባቷን የማወቅ ፍላጎቱ ጸና። እሷ ሐር ቀሚስ ለብሳ ከቤት እንደወጣችው ሳይሆን፣ እሱ
እሑድ ቤተክርስቲያን ስትሳለም እንደሚያያት የዐዘቦት ልብሷን ለብሳ፣ ነጠላ ተከናንባ በበቅሎ ስትሰግር በዓይነ ኅሊናው ታየው፤ ሆዱ ባባ።
ያርባ ቀን ዕድሌ ነው እንግዲህ ምን አረጋለሁ? አለ፣ ለራሱ።
እናቱንና አባቱን አስታወሰ። በእሱ መጥፋት እናቱ እንዴት ጨርቃቸውን እንደሚጥሉ አሰበና ሆድ ባሰው። አባቱም ቢሆኑ አመል ሆኖባቸው ይነዛነዙ እንጂ፣ የእሱ ነገር እንደማይሆንላቸው ያውቃልና ጉዳታቸው ተሰምቶት ለመጀመሪያ ጊዜ አዘነላቸው። ሳያስበው ፊቱ በእንባ ርሷል። በጋቢው ፊቱን ጠራርጎ ቀና ሲል አብርሃ ፊቱ ቆሟል።
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“እምዬ ጐንደር እንግዳ ተቀባይ እኮ ናት።”
ጥላዬ፣ እምነቱንና ተስፋውን ጐንደር ላይ ጥሎ ሐሙስ ቀን እዚያች ብርቅየ ከተማ ገባ። ጨለማ የከተማዋን ሰማይ ለማልበስ በመጣደፍ ላይ
ነው። ጐንደሬዎች ቤታቸው ለመከተት ፈጠን ፈጠን እያሉ ሲራመዱ፣ጥላዬ፣ ብዛታቸው ብቻ ሳይሆን ዓይነታቸው አስደነቀው። እንደ ግሪኮች፣ አርመኖች፣ ህንዶችና አረቦች የመሳሰሉ የውጭ ሃገር ዜጎች ሕዝቡ መሃል ውር ውር ሲሉ፣ የቆዳቸው፣ የመልካቸውና የአለባበሳቸው
መለየት አስደመመው።
ጭቃ ምርጎቹን ባለሳር ክዳን ጎጆዎች ትክ ብሎ አያቸው። ባዘቶ
የለበሱ የሚመስሉ ዋንዛ ዛፎች ስር ችምችም ማለታቸውና እንደ ቋራ ተሰባጥረው አለመቀመጣቸው ገረመው። በየቦታው ጣል ጣል ያሉት
የድንጋይ ግንቦችና ነገሥታት ብቻ የታደሉባቸው የኖራ ቅብ ቤቶች
የከተማዋ ጌጥ መስለው ታዩት። ያየው ሁሉ ከቋራ የተለየ ሆነበት።
ጐንደር ልዩ ስፍራ ሆነችበት፤ አስገረመችው።
ዐዲስ ሕይወት ልትሰጠው ቃል ኪዳን ገባችለት። እየተዘዋወረ ከተማዋን ማየት ፈልጎ ጨለማው በፍጥነት ማደሪያ እንዲፈልግ አስገደደው። ቤተክርስቲያን ፍለጋ ዐይኑን ሲያዘዋውር፣ አንድ የቆሎ ተማሪ በፍጥነት ሲራመድ አየና ሮጦ ደረሰበት።
“ከርመህ ነው? ላገሩ እንግዳ፣ ለሰዉ ባዳ ነኝ። ማደሪያ ሚሆነኝ
ደጀሰላም ባገኝ ብየ” አለው።
“ኸደብረብርሃን ሥላሤ ማታድር? ምን የመሰለ ዛኒጋባ በቤተክሲያን
ዙሪያ እያለልህ። ወደዛው ነው ምኸድ፤ በል ና። አገርህ ወየት ነው?”
“እማር ብየ መጥቸ” አለ ጥላዬ፣ መናገር አልፈለገም።
“ጐንደር ደሞ ለትምርት። ኸየቦታው ሚመጡ ተማሮች፣ ሊቃውንት፣ ካህናትና መምህሮች ሁሉ ኸዝሁ ማዶል ያሉት?” ብሎ ነጫጭ ጥርሶቹን አሳየው፣ ተማሪው።
ገራ ገር ፈገግታው ጥላዬን ማረከው። ዕድሜ ልኩን የሚያውቀው መስሎ ተሰማው። ቀደም ብሎ ማደሪያውን ሲያስብ ባይተዋርነት የተሰማውን ያህል፣ ከትከሻው ሸክም እንደወረደ ሁሉ ቀለል አለው።
“ቅኔ ልትማር ነው የመጣህ?”
“ሥዕል ልማር ብየ ነው የመጣሁ።”
“ዛዲያ ጐንደር ምን ገዷት! እደብረብርሃን ሥላሤ መምህሮቹም ተማሮቹም አሉልህ፡፡”
ጥላዬ ተደሰተ። ተማሪው ገዱ ሆኖ ተሰማው። ልባዊ ፈገግታው ደግ
ሰው እጅ ላይ እንደወደቀ ጠቆመው። “ምን እየተማርህ ነው?” ሲል ጠየቀው።
“ቅኔ እየተማርሁ ነው። መወድስ እያኸድሁ ነው።”
“ደሕና አኸደሀል።”
“አንተስ ሞካክረኻል?”
“ሥላሤ ደርሻለሁ። ማድርበት ደጀሰላም የት አገኝ ይሆን እያልሁ?”
“ጐንደር መጥተህ ነው ስጋት ሚያድርብህ? አንተስ አለማወቅህ ...እምዬ ጐንደር እንግዳ ተቀባይ እኮ ናት። ሴቶች ወጥ ሲሰሩ ኸደረስህ
ይሽተዋል ብለው ሳትበላ ማትኸድባት አገር እኮ ናት። ጐንደር የሁሉ ናት፤ ማንም ኸየት መጣ ኸየት ቤቴ፣ የኔ ብሎ ሚኖርባት። አልሰማህም
እንዴ፣
ቤተስኪያን ስሞ ለመኖር፣
መልካም አገር ነው ጐንደር።
ሲባልላት?” እያለ ግጥሙን በዜማ አወረደለት።
ጥላዬ ሳቅ አለና፣ “ገና መድረሴ፣ ምኔ ሰምቸ? ጐንደሬ ሁሉ እንዳንተ
ጥሩ ነው?” ሲል ጠየቀው።
“እኔስ ኸተምብየን ነው የመጣሁ። ዐራት ዓመት አርጌያለሁ ኸዝኸ።”
ተማሪው ከላይ የደረበውን ለምድ፣ ትከሻው ላይ ያንጠለጠለውን
አኮፋዳና ለውሻ መከላከያ የያዛቸውን ሁለት በትሮች ጥላዬ ትክ ብሎ ተመለከተና ከልመና እንደመጣ ገባው። ወደ ቤተክርስቲያኑ ሲደርሱ
ደጀሰላሙን ተሳልመው ውስጥ ገቡ።
“እንዴት ያለ ቤተክሲያን ነው በል” አለው፣ ጥላዬ።
“አጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ መዠመሪያ አሠሩትና ተቃጠለ። ኸዚያ በኋላ፣ ልዣቸው... ሦስተኛው ሚባሉት አጤ ዳዊት እንደገና አሠሩት።
እሳቸው ግና ባባታቸው ስም እንዲጠራ ስለፈለጉ እኔ አሰራዋለሁ ስሙ ግን ባባቴ ይሁን አሉ።”
ጥላዬ ፈዞ ቆሞ የቤተክርስቲያኑን አሰራር ሲያደንቅ ተማሪው፣ “እኛ
ስንገባ ስንወጣ ለምደነዋል። እንግዲህ አንዱን ጥግ ይዘህ ተኛ። ኸኛ ዘንድ ምኝታ የለም ሁኖ ነው” ብሎት ሄደ።
ጥላዬ ቤተክርስቲያኑን እንደገና ተሳልሞ ዙርያውን ሲመለከት፣
እየጨለመ በመምጣቱ በወንዶቹ መግቢያ በኩል ጭንቅላቱን ጉልበቶቹ መሃል ቀብሮ ተቀመጠ። ግቢው ጭር ብሏል። መንገድ ሲመሽበት፣
“ቤት ያብርሃሙ ሥላሤ ነው” እያሉ ቁርበት ጣል፣ ትኩስ ሽሮ እንጀራ
ላይ ፈሰስ አድርገውለት፣ አለበለዚያ ቆሎ እንዲቆረጥም ወይ ቂጣ እንዲያላምጥ ሰጥተውት ያሳደሩት ሁሉ ትዝ አሉት። ከነጋ እህል አፉ አላደረገም። ሆዱ ከረሀብ ብዛት ዋይ ዋይ አለበት፤ ያለማቋረጥ
አዛጋው።
በዕድሜ ከእሱ ትንሽ ከፍ ስለሚለው ተማሪ አሰበና ባይለየው መረጠ። ስሙን እንኳ ሳይጠይቀው በመሄዱ ተቆጨ። አንገቱን እንደደፋ ሲያሰላስል ድምፅ ሰማ። ቀና ሲል ተማሪዎች ወደ መማሪያ ቦታቸው ወደ ቤተክርስቲያኑ ጀርባ ይሄዳሉ። ተማሪው ከእነሱ ነጠል ብሎ ወደእሱ ሲመጣ አየው። ሁለመናው ተበራታ።
“ራት ቢጤ አመጣሁልህ። የውሃ ቅሌን ልተውልህና ገሠሣ ሲያበቃ
መጥቸ ወስደዋለሁ። ስትተኛ ኸዚሁ ተወው። አነሳዋለሁ” ብሎት
መንገድ ሲጀምር ጥላዬ ከተቀመጠበት ተነስቶ፣ “ሥላሤ ያክብሩልኝ።ስሜንም ሳልነግርህ... ጥላዬ እባላለሁ... ከቋራ ነው የዘለቅሁ” አለው::
ቀደም ብሎ አባቱ ፈልገው እንዳያገኙት ሲል ማንነቱን ደብቆ፣
አሁን የተማሪው ደግነት ምሥጢሩን አሟሸሸበት።
“በል ነገ ያገናኘን። አብርሃ ነው ስሜ። ገሠሣ እንዳያመልጠኝ
ብሎት ተማሪዎቹ ወደሄዱበት አቅጣጫ አመራ።
ጥላዬ፣ አብርሃ የሰጠውን ፍርፋሪ በልቶ፣ ውሃውን በላዩ ቸልሶና
አምላኩን አመስግኖ የመንገድ ድካም ስለተጫጫነው አንዱ ዛኒጋባ ጋ ተጠግቶ ጋደም እንዳለ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰደው።
ጠዋት ድምፅ ሲሰማ ብንን አለ። የት እንዳለ ለማወቅ ጥቂት ጊዜ
ወሰደበት። የሌሊቱ ብርድ፣ ልብሱን ውሃ የነካው አስመስሉታል። አንድ ጋቢ መኝታም ከላይ የሚለበስም ሆኖ አገልግሎታል። ከተቀመጠበት
ተነስቶ የቤተክርስቲያኑን መግቢያ በር ተሳለመና ወንዶቹ መግቢያ
ትይዩ ያለ አንድ ዋንዛ ዛፍ ስር ሄዶ ዳዊቱን አውጥቶ መድገም ጀመረ።
“አድረህ ነው?” የሚል ድምፅ ሲሰማ ቀና አለ። አብርሃ ነው ።
“ደሕና... ደሕና ... ይመስገነው።”
“አንደዜ ጠሎት ላድርስና ኸየንታ ሔኖክ ዘንድ ወስድሀለሁ” ብሎት
ሄደ።
ጥላዬ፣ በእሽታ ራሱን ነቀነቀለትና ወደ ዳዊቱ ተመለሰ። የዕለቱን
አድርሶ ሲጨርስ ዳዊቱን ማኅደሩ ውስጥ ጨምሮ፣ ስንጥር አንስቶ
መሬት ላይ መሞነጫጨር ጀመረ። እንደለመደው የወለተጊዮርጊስን ምስል ሊሥል ፈልጎ እዚያ ያደረሰው ምን እንደሆነ ትዝ ሲለው
ስንጥሩን ወረወረው።
ከቤት የወጣበት ምክንያት በመንገድ ድካምና በረሐብ በአእምሮው ውስጥ እየደበዘዘ መጥቶ ነበርና አሁን ቁጭ ሲል ሁሉ ነገር ፊቱ ላይ ድቅን አለበት። ወለተጊዮርጊስ ጐንደር መግባት ከለመግባቷን የማወቅ ፍላጎቱ ጸና። እሷ ሐር ቀሚስ ለብሳ ከቤት እንደወጣችው ሳይሆን፣ እሱ
እሑድ ቤተክርስቲያን ስትሳለም እንደሚያያት የዐዘቦት ልብሷን ለብሳ፣ ነጠላ ተከናንባ በበቅሎ ስትሰግር በዓይነ ኅሊናው ታየው፤ ሆዱ ባባ።
ያርባ ቀን ዕድሌ ነው እንግዲህ ምን አረጋለሁ? አለ፣ ለራሱ።
እናቱንና አባቱን አስታወሰ። በእሱ መጥፋት እናቱ እንዴት ጨርቃቸውን እንደሚጥሉ አሰበና ሆድ ባሰው። አባቱም ቢሆኑ አመል ሆኖባቸው ይነዛነዙ እንጂ፣ የእሱ ነገር እንደማይሆንላቸው ያውቃልና ጉዳታቸው ተሰምቶት ለመጀመሪያ ጊዜ አዘነላቸው። ሳያስበው ፊቱ በእንባ ርሷል። በጋቢው ፊቱን ጠራርጎ ቀና ሲል አብርሃ ፊቱ ቆሟል።
👍15❤2
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ሲልቪ
ውስጥ ውስጡን
በነጋታው ጧት የመኝታዬ በር በኃይል ሲንኳኳ ነቃሁ፡፡ ማነህ
ሳልል በሩን ከፈትኩ። ሲልቪ እየሳቀች ዘላ ተጠመጠመችብኝ፡፡
ተንገዳግደን አልጋዬ ላይ ወደቅን። የፀጉሯ ሽታ ደስ አለኝ
«ዛሬ ምን ሆነሻል?» አልኳት
«ፈተናዬን በማእረግ አለፍኩ። ተነስ እንሂድ»
«የት? »
«ፓሪስ። ቀጥሎ ጄኖቫ፣ ከዚያ ሮማ፣ ናፖሊ፣ ፊሬንዜ፣
ከዚያ ኒስ፣ ማርሰይ፣ ኤክስ፡፡ ፕላኑን በሙሉ አውጥቻለሁ፡፡ «ጎበዝ አደለሁም?»
«ጎበዝ ነሽ፡፡ መቼ ነው «ምንሄደው?»
«አሁኑኑ፡፡ ተነስ ተጣጠብ» አለችኝ፣ ሰሰፊ ኣፏ እየሳቀች
«ለባለሆቴሉ 'ምከፍለው ገንዘብ አልያዝኩማ»
«እኔ ይዣለሁ»
«በምንድነው የምንሄደው?»
«በባቡር። ባቡራችን ልክ ከዘጠና ሁለት ደቂቃ በኋላ ከማርሰይ
ይነሳል፡፡ ቶሎ በል»
እንደዚህ አጣድፋ፣ ማንንም ለመሰናበት ሳልችል ፓሪስ
ወሰደችኝ። ከሁሉ ቅር ያሰኘኝ አማንዳ ዱቤን ሳልሰናበት መሄዴ
ነበር በሚቀጥለው አስር ሳምንት
ውስጥ ስለባህራም በብዙም
አላሰብኩም፡፡ ስለ ምንም ነገር በብዙ አላሰብኩም፡፡ ሀሳቤን ሲልቪ ሞልታው ነበር
ባቡሩ ሞልቶ ቆይቶን አንድ ላይ ቦታ ለማግኘት ባለመቻላችን
ፊት ለፊቴ ተቀመጠች። ሁለታችንም መፅሀፍ ማንበብ ጀመርን።ትንሽ አነብና ሰርቄ አያታለሁ፡፡ ረዥም ፀጉሯ ውብ ነጭ ፈቷን እንደ ጥቁር ሀር ከቦታል። በጣም ቆንጆ ናት፣ የደስ ደስ አላት አንዳንድ ጊዜ ሳያት ትይዘኛለች። ትጠቅሰኝና ሳቅ ትላለች፡፡ መልሼ እጠቅሳታለሁ፡፡ ንባባችንን እንቀጥላለን። አልፎ አልፎ አንድ ያልገባኝን ቃል እጠይቃታለሁ:: ፈረንሳዮቹ
ብርቱካን ይበላሉ፣ ያወራሉ፣ ፖም ይበላሉ፣ ጋዜጣ ያነባሉ፣ ሳንድዊች ይበሳሉ፣ ወይን
ይጠጣሉ፣ ባቡሩን ያዝረከርኩታል፣ ያቆሽሹታል፣ ዝነኛውን «የፈረንሳይ ባቡር ግማት» ይሰጡታል
አቪኞን ስንደርስ አንዲት ኣሮጊት ከአጠገቤ ተነሳችና፣ ገና
ከመነሳቷ ቦታዋ ላይ እንድ ሰውዬ ተቀመጠ። ከኣቪኞን እንደወጣን
የሲልቪ አይኖች ደጋግመው እዚህ ሰውዬ ላይ ያርፉ ጀመር።
ሰውዬውን አየሁት። ፀጉሩ ላይ ነጭ ዘርቶበታል፣ ምናልባት ያርባ
አምስት አመት ሰው ይሆናል። አይኖቹ ንፁህ ሰማያዊ ሆነው፣
ቀጠን ያለ ፊቱ በጣም ቆንጆ ነው:: ሳየው ጠላሁት። ንባቤን ቀጠልኩ፣ ግን የማነበው ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ስርቄ ሲልቪን አየኋት።
ሰውዬውን በሰማያዊ እይኖቿ ብርህን ታየዋለች። እሷ እሱን ስታይ፣እኔ እሷን ሳይ፣ ንዴቱ ውስጤ ሲጠራቀም፣ ብዙ ጊዜ ሄድን ሳያት ያዘችኝ። አይኖቿ ተርገበገቡ፣ ወደ ታች አየች፣ ጉንጮቿ ደም ለበሱ፡፡ ማማሯ የንዴቴን ጥቁር ደመና የፍትወት ብልጭታ ሲሰነጣጥቀው ተሰማኝ። «ድንገት ሳብ ኣድርጌ ቀሚሷን ገልቤ ጭኖቿን ፈልቅቄ..
በመስኮቱ ወደ ውጭ ማየት ጀመርኩ፡፡ ለጥ ያለ ሜዳ መሬት
ረዥም ቀጭን የቤተ ክርስቲያን ደወል ቤት ሰማዩን እንደ መርፌ
ወግቶታል፤ አንድ ቀጭን መንገድ ከሹሉ ደወል ቤት ስር ወጥቶ
እየተጠማዘዘ ሄዶ አድማሱ ውስጥ ገብቷል፣ ሰማይና ምድር
የተሰፉበት ክር ይመስላል፡፡ መንደሩ እንደ ልጅነት ቀስ እያለ ወደ ኋላ እየተንሸራተተ ጠፋ
ዘወር ብዬ ሲልቪን አየኋት። ራሷን ወደ መፅሀፉ ደፍታለች፣
ፈቷ ደም እንደለበሰ ነው:: መፅሀፌን ማንበብ ጀመርኩ። አሁንም ቃላቱ አይኔን ዘልቆ እንጉሴ ውስጥ መግባት አቅቶት፣ አይኔ ብቻውን ያነባል። ሲልቪን አየኋት። አየችኝና ፈገግ አለች:: ሰማያዊ አይኖቿ ሳቂታ ናቸው፡ በጣም ቆንጆ ፈገግታ ኣሳየችው። እናቷን!
ንባቤን ቀጠልኩ። ከዚያ በኋላ እንደገና ደጋግማ ስታየው
አየኋት። አንድ ሶስት ጊዜ ያህል፣ ስታየው እንዳየኋት አይታ በጣም
አፈረች፥ አይኖቿ ተርገበገቡ፣ ጉንጮቿ ቀሉ፤ ንዴቴና ምኞቴ
ውስጤ እየታገለ አስጨነቁኝ
ሶስት ሰእት ያህል አለፈ
ከሊዮን በኋላ አንድ ሁለት ትንንሽ ከተማ እንዳለፍን ሰውየው
እግሮቹን የሚዘረጋ አስመስሎ የሲልቪን እግር ነካ፡፡ ቀና ብላ በውብ አይኖቿ በፈገግታ አየችው፡፡ በሰፊ እፏም ሳቅ አለችለት፡፡ ሰውዬው
በእግሩ እግሯን ማሻሸት ጀመረ። ቀላች። ውስጤ ስጋዊ ፍትወትና
ንዴት ታገለ፣ ንዴቱ አሸነፈ። እግሬን የምዘረጋ አስመስዬ የሰውዬውን ቅልጥም በኃይል መታሁትና፣ ዘወር ብዬ እያፈጠጥኩ
Pardon, monsieur» አልኩት (ይቅርታ መስዬ»)
ve vous en pries አለኝ («ኧረ ግድ የለም )
እግሩን ሰበሰበ። ፊቱ በንዴት ይሁን በእፍረት ደም ለብሷል።
ሲልቪን አየኋት። መፅሀፏን ታያለች፣ ፈገግታ ብጤ አፏ ዙሪያ
ይርበተበታል። ሰውየው የሲጋራ ፓኮ ከኪሱ አውጥቶ ወደ ሲልቪ
ዘረጋ፣ እየሳቀች ተቅበለችው:: አቀጣጠለላት ወደ ፓሪስ ነው : ሚሄዱት?» አለችው
«አዎን ማድሟዜል። እርስዎስ?» አላት ወሬ ጀመሩ። ብሽቅ አልኩ። ተነስቼ ትቻቸው ወጣሁ
መተላለፊያው ዘንድ አልፎ አልፎ የቆሙትን ፈረንሳዮች
እየገጨሁ Pardon! እያልኩ፣ አንድ አስር ሰረገላዎች እቋርጬ
ሂጂ ባቡሩ መጨረሻ ደረስኩ
ስመለስ ግማሽ መንገድ ላይ ቆምኩ። እቺ ንፍጣም!
ልታሰቃናኝ ፈልጋ አይደለም? እንደማልቀና ማወቅ አለባት። ግማሽ ሰአት እስኪያልፍ ወደሷ አልመለስም፡፡ ምን ያህል ግድ እንደሌለኝ ይግባት . .»
ግማሽ ሰአት እንዴት ረዥም ነው! ሰአቴን አስር ጊዜ አየኋት::
እሷ ታድያ አትንቀሳቀስም። አምስት ደቂቃ እንኳ ገና አላለፈም። ወደ ጆሮዬ አስጠጋኋት። ተኝታለች። የለም የለም፡ የባቡሩ ጩኸት
ድምፅዋን አላሰማ ስላለኝ ነው። . . . እኔና ሰአቷ ስንተያይ ሩብ ሰአት አለፈ። ከዚያ በኋላ ግን መቆየት አልቻልኩም፡፡ ሰዎቹን
እየገጨሁ «Partdom!» እያልኩ ወደነዚያ ውሾች መመለስ እንደ
ጀመርኩ፣ በመስኮቶቹ በኩል ቤቶች ብቅ እያሱ ወደኋላ ሽው ብለው ሲያልፉ ይታዩኝ ጀመር። አንድ ትንሽ ከተማ ደርሰናል፡፡ ባቡሩ በቆመልኝ! ማቆያ እንዲሆነኝ ጋዜጣ እገዛ ነበር. ጎሽ! ባቡሩ ቆመ፡፡ ወረድ ስል አንድ መለዮ የለበሰ የባቡሩ ኩባንያ ሰራተኛ አመስዬ፣ አይውረዱ፣ ሁለት ደቂቃ ብቻ ነው ያለን» አለኝ
«Je mn fous!» አልኩትና ወረድኩ («ደንታ የለኝም!»)
አንድ Le Monde ጋዜጣና ሁለት ሳንድዊች ገዝቼ እስክመለስ
ባቡሩ ተነሳ። ሮጬ ለትንሽ ደረስኩበት::
ጋዜጣውን ኣንብቤ ሳልጨርስ ወደሷ አልመለስም፡፡ ሳገኛት ደሞ ሳንድዊች እሰጣታለሁ፡፡
እየሳቅኩ። ጭራሽ አለመቅናቴ እንዲገባት የክሩስቼቭና የኬነዲ የቤንቤላ ስም አለ፤ የቪየትናም ሁከት ተጠቅሷል፣ ግን በደምብ አልገባኝም፡ የሲልቪ ፈገግታ፣ ለሌላ ያሰራችው ፈገግታ አንጎሌን በጥብጦታል። የሆነ ሆኖ፣ ያልኩት ግማሽ ሰአት አለፈልኝ። ኧረ ሰላሳ ሶስት ደቂቃ ነው ያለፈው! እኔ የሰውዬው ልጅ! ... ወደኛ ሰረገላ አመራሁ ሲልቪ የለችም። ሰውዬውም የለም፡፡
የታባታቸውን ሄዱ? እንደገና ፈረንሳዮቹን እየገጨሁ «Pardon!»
እያልኩ አንድ አምስት ሰረገላ ካቋረጥኩ በኋላ፣ ራሴን «የት ነው
ምትሄደው?» አልኩት፡፡
ቆምኩ «በቁላህ ሳይሆን በጭንቅላትህ አስብ» የሚል ሀሳብ ውስጡን አሳቀኝ። ለመሆኑ፣ ባገኛቸውስ ምን ላደርጋቸው ኖሯል ብዬ አሰብኩ። ተመልሼ ቦታዬ ቁጭ ብዬ ልጠብቃቸው ቆረጥኩ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ሲልቪ
ውስጥ ውስጡን
በነጋታው ጧት የመኝታዬ በር በኃይል ሲንኳኳ ነቃሁ፡፡ ማነህ
ሳልል በሩን ከፈትኩ። ሲልቪ እየሳቀች ዘላ ተጠመጠመችብኝ፡፡
ተንገዳግደን አልጋዬ ላይ ወደቅን። የፀጉሯ ሽታ ደስ አለኝ
«ዛሬ ምን ሆነሻል?» አልኳት
«ፈተናዬን በማእረግ አለፍኩ። ተነስ እንሂድ»
«የት? »
«ፓሪስ። ቀጥሎ ጄኖቫ፣ ከዚያ ሮማ፣ ናፖሊ፣ ፊሬንዜ፣
ከዚያ ኒስ፣ ማርሰይ፣ ኤክስ፡፡ ፕላኑን በሙሉ አውጥቻለሁ፡፡ «ጎበዝ አደለሁም?»
«ጎበዝ ነሽ፡፡ መቼ ነው «ምንሄደው?»
«አሁኑኑ፡፡ ተነስ ተጣጠብ» አለችኝ፣ ሰሰፊ ኣፏ እየሳቀች
«ለባለሆቴሉ 'ምከፍለው ገንዘብ አልያዝኩማ»
«እኔ ይዣለሁ»
«በምንድነው የምንሄደው?»
«በባቡር። ባቡራችን ልክ ከዘጠና ሁለት ደቂቃ በኋላ ከማርሰይ
ይነሳል፡፡ ቶሎ በል»
እንደዚህ አጣድፋ፣ ማንንም ለመሰናበት ሳልችል ፓሪስ
ወሰደችኝ። ከሁሉ ቅር ያሰኘኝ አማንዳ ዱቤን ሳልሰናበት መሄዴ
ነበር በሚቀጥለው አስር ሳምንት
ውስጥ ስለባህራም በብዙም
አላሰብኩም፡፡ ስለ ምንም ነገር በብዙ አላሰብኩም፡፡ ሀሳቤን ሲልቪ ሞልታው ነበር
ባቡሩ ሞልቶ ቆይቶን አንድ ላይ ቦታ ለማግኘት ባለመቻላችን
ፊት ለፊቴ ተቀመጠች። ሁለታችንም መፅሀፍ ማንበብ ጀመርን።ትንሽ አነብና ሰርቄ አያታለሁ፡፡ ረዥም ፀጉሯ ውብ ነጭ ፈቷን እንደ ጥቁር ሀር ከቦታል። በጣም ቆንጆ ናት፣ የደስ ደስ አላት አንዳንድ ጊዜ ሳያት ትይዘኛለች። ትጠቅሰኝና ሳቅ ትላለች፡፡ መልሼ እጠቅሳታለሁ፡፡ ንባባችንን እንቀጥላለን። አልፎ አልፎ አንድ ያልገባኝን ቃል እጠይቃታለሁ:: ፈረንሳዮቹ
ብርቱካን ይበላሉ፣ ያወራሉ፣ ፖም ይበላሉ፣ ጋዜጣ ያነባሉ፣ ሳንድዊች ይበሳሉ፣ ወይን
ይጠጣሉ፣ ባቡሩን ያዝረከርኩታል፣ ያቆሽሹታል፣ ዝነኛውን «የፈረንሳይ ባቡር ግማት» ይሰጡታል
አቪኞን ስንደርስ አንዲት ኣሮጊት ከአጠገቤ ተነሳችና፣ ገና
ከመነሳቷ ቦታዋ ላይ እንድ ሰውዬ ተቀመጠ። ከኣቪኞን እንደወጣን
የሲልቪ አይኖች ደጋግመው እዚህ ሰውዬ ላይ ያርፉ ጀመር።
ሰውዬውን አየሁት። ፀጉሩ ላይ ነጭ ዘርቶበታል፣ ምናልባት ያርባ
አምስት አመት ሰው ይሆናል። አይኖቹ ንፁህ ሰማያዊ ሆነው፣
ቀጠን ያለ ፊቱ በጣም ቆንጆ ነው:: ሳየው ጠላሁት። ንባቤን ቀጠልኩ፣ ግን የማነበው ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ስርቄ ሲልቪን አየኋት።
ሰውዬውን በሰማያዊ እይኖቿ ብርህን ታየዋለች። እሷ እሱን ስታይ፣እኔ እሷን ሳይ፣ ንዴቱ ውስጤ ሲጠራቀም፣ ብዙ ጊዜ ሄድን ሳያት ያዘችኝ። አይኖቿ ተርገበገቡ፣ ወደ ታች አየች፣ ጉንጮቿ ደም ለበሱ፡፡ ማማሯ የንዴቴን ጥቁር ደመና የፍትወት ብልጭታ ሲሰነጣጥቀው ተሰማኝ። «ድንገት ሳብ ኣድርጌ ቀሚሷን ገልቤ ጭኖቿን ፈልቅቄ..
በመስኮቱ ወደ ውጭ ማየት ጀመርኩ፡፡ ለጥ ያለ ሜዳ መሬት
ረዥም ቀጭን የቤተ ክርስቲያን ደወል ቤት ሰማዩን እንደ መርፌ
ወግቶታል፤ አንድ ቀጭን መንገድ ከሹሉ ደወል ቤት ስር ወጥቶ
እየተጠማዘዘ ሄዶ አድማሱ ውስጥ ገብቷል፣ ሰማይና ምድር
የተሰፉበት ክር ይመስላል፡፡ መንደሩ እንደ ልጅነት ቀስ እያለ ወደ ኋላ እየተንሸራተተ ጠፋ
ዘወር ብዬ ሲልቪን አየኋት። ራሷን ወደ መፅሀፉ ደፍታለች፣
ፈቷ ደም እንደለበሰ ነው:: መፅሀፌን ማንበብ ጀመርኩ። አሁንም ቃላቱ አይኔን ዘልቆ እንጉሴ ውስጥ መግባት አቅቶት፣ አይኔ ብቻውን ያነባል። ሲልቪን አየኋት። አየችኝና ፈገግ አለች:: ሰማያዊ አይኖቿ ሳቂታ ናቸው፡ በጣም ቆንጆ ፈገግታ ኣሳየችው። እናቷን!
ንባቤን ቀጠልኩ። ከዚያ በኋላ እንደገና ደጋግማ ስታየው
አየኋት። አንድ ሶስት ጊዜ ያህል፣ ስታየው እንዳየኋት አይታ በጣም
አፈረች፥ አይኖቿ ተርገበገቡ፣ ጉንጮቿ ቀሉ፤ ንዴቴና ምኞቴ
ውስጤ እየታገለ አስጨነቁኝ
ሶስት ሰእት ያህል አለፈ
ከሊዮን በኋላ አንድ ሁለት ትንንሽ ከተማ እንዳለፍን ሰውየው
እግሮቹን የሚዘረጋ አስመስሎ የሲልቪን እግር ነካ፡፡ ቀና ብላ በውብ አይኖቿ በፈገግታ አየችው፡፡ በሰፊ እፏም ሳቅ አለችለት፡፡ ሰውዬው
በእግሩ እግሯን ማሻሸት ጀመረ። ቀላች። ውስጤ ስጋዊ ፍትወትና
ንዴት ታገለ፣ ንዴቱ አሸነፈ። እግሬን የምዘረጋ አስመስዬ የሰውዬውን ቅልጥም በኃይል መታሁትና፣ ዘወር ብዬ እያፈጠጥኩ
Pardon, monsieur» አልኩት (ይቅርታ መስዬ»)
ve vous en pries አለኝ («ኧረ ግድ የለም )
እግሩን ሰበሰበ። ፊቱ በንዴት ይሁን በእፍረት ደም ለብሷል።
ሲልቪን አየኋት። መፅሀፏን ታያለች፣ ፈገግታ ብጤ አፏ ዙሪያ
ይርበተበታል። ሰውየው የሲጋራ ፓኮ ከኪሱ አውጥቶ ወደ ሲልቪ
ዘረጋ፣ እየሳቀች ተቅበለችው:: አቀጣጠለላት ወደ ፓሪስ ነው : ሚሄዱት?» አለችው
«አዎን ማድሟዜል። እርስዎስ?» አላት ወሬ ጀመሩ። ብሽቅ አልኩ። ተነስቼ ትቻቸው ወጣሁ
መተላለፊያው ዘንድ አልፎ አልፎ የቆሙትን ፈረንሳዮች
እየገጨሁ Pardon! እያልኩ፣ አንድ አስር ሰረገላዎች እቋርጬ
ሂጂ ባቡሩ መጨረሻ ደረስኩ
ስመለስ ግማሽ መንገድ ላይ ቆምኩ። እቺ ንፍጣም!
ልታሰቃናኝ ፈልጋ አይደለም? እንደማልቀና ማወቅ አለባት። ግማሽ ሰአት እስኪያልፍ ወደሷ አልመለስም፡፡ ምን ያህል ግድ እንደሌለኝ ይግባት . .»
ግማሽ ሰአት እንዴት ረዥም ነው! ሰአቴን አስር ጊዜ አየኋት::
እሷ ታድያ አትንቀሳቀስም። አምስት ደቂቃ እንኳ ገና አላለፈም። ወደ ጆሮዬ አስጠጋኋት። ተኝታለች። የለም የለም፡ የባቡሩ ጩኸት
ድምፅዋን አላሰማ ስላለኝ ነው። . . . እኔና ሰአቷ ስንተያይ ሩብ ሰአት አለፈ። ከዚያ በኋላ ግን መቆየት አልቻልኩም፡፡ ሰዎቹን
እየገጨሁ «Partdom!» እያልኩ ወደነዚያ ውሾች መመለስ እንደ
ጀመርኩ፣ በመስኮቶቹ በኩል ቤቶች ብቅ እያሱ ወደኋላ ሽው ብለው ሲያልፉ ይታዩኝ ጀመር። አንድ ትንሽ ከተማ ደርሰናል፡፡ ባቡሩ በቆመልኝ! ማቆያ እንዲሆነኝ ጋዜጣ እገዛ ነበር. ጎሽ! ባቡሩ ቆመ፡፡ ወረድ ስል አንድ መለዮ የለበሰ የባቡሩ ኩባንያ ሰራተኛ አመስዬ፣ አይውረዱ፣ ሁለት ደቂቃ ብቻ ነው ያለን» አለኝ
«Je mn fous!» አልኩትና ወረድኩ («ደንታ የለኝም!»)
አንድ Le Monde ጋዜጣና ሁለት ሳንድዊች ገዝቼ እስክመለስ
ባቡሩ ተነሳ። ሮጬ ለትንሽ ደረስኩበት::
ጋዜጣውን ኣንብቤ ሳልጨርስ ወደሷ አልመለስም፡፡ ሳገኛት ደሞ ሳንድዊች እሰጣታለሁ፡፡
እየሳቅኩ። ጭራሽ አለመቅናቴ እንዲገባት የክሩስቼቭና የኬነዲ የቤንቤላ ስም አለ፤ የቪየትናም ሁከት ተጠቅሷል፣ ግን በደምብ አልገባኝም፡ የሲልቪ ፈገግታ፣ ለሌላ ያሰራችው ፈገግታ አንጎሌን በጥብጦታል። የሆነ ሆኖ፣ ያልኩት ግማሽ ሰአት አለፈልኝ። ኧረ ሰላሳ ሶስት ደቂቃ ነው ያለፈው! እኔ የሰውዬው ልጅ! ... ወደኛ ሰረገላ አመራሁ ሲልቪ የለችም። ሰውዬውም የለም፡፡
የታባታቸውን ሄዱ? እንደገና ፈረንሳዮቹን እየገጨሁ «Pardon!»
እያልኩ አንድ አምስት ሰረገላ ካቋረጥኩ በኋላ፣ ራሴን «የት ነው
ምትሄደው?» አልኩት፡፡
ቆምኩ «በቁላህ ሳይሆን በጭንቅላትህ አስብ» የሚል ሀሳብ ውስጡን አሳቀኝ። ለመሆኑ፣ ባገኛቸውስ ምን ላደርጋቸው ኖሯል ብዬ አሰብኩ። ተመልሼ ቦታዬ ቁጭ ብዬ ልጠብቃቸው ቆረጥኩ፡፡
👍20