#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....የወይዘሮ ዘነቡና የታፈሡ ውይይት በዚህ መልኩ እየተከናወነ ባለበት ሰአት
ሸዋዬ አልጋዋ ላይ ቁጭ ብላ በሁለት እጇ ጆሮ ግንዶቿን ጠፍራ በመያዝና አተርትራ በማሰብ ላይ ናት። ታፈሡንና ወይዘሮ ዘነቡን እያሰበች ልክ በመሀላቸው ቁጭ ብላ እንደምታዳምጣቸው ዓይነት ስለ እሷ ሲያወራ በሀሳቧ "ቀንታ ነው እኮ ተቀጥላ ይስሟታል!
ሰው እንዴት በእህቱ ይቀናል! አረ የሷ የብቻው ነው ። አስቻለውን እንደሆነ አታገኘው ምን ያስለፋታል?» የሚሏት ይመስላታል። ወይዘሮ
ዘነቡ ታፈሡን ሲያሞካሹ!
ለአስቻለውና ለሄዋን ለሔዋን ፍቅር መልካም ሲመኙ እሷ በእሳቸው ፊት የምታሳየውን ድንጋጤና የብስጭት ስሜት ለታፈሡ ዝርዝር አድርገው ሲያወሩባት ሁሉ ይታያታል፡፡ በዚያ ልክ ቅጥል ንድድ ትችላለች፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ ግቢያቸው ውስጥ እንዴግቡ ወደ ቢታቸው ጎራ ሳይሉ
በቀጥታ ወደ ጓሮ ዞረው ወደ ሸዋዩ ቤት አመሩ። ሸዋዬ ድንገት የሰው ኮቴ ሰምታ ከአጎነሰችበት ቀና ስትል ወይዘሮ ዘነቡ ብቻቸውን ሲመጡ አየቻቻው። ወደ
ኋላቸው ዓይኗን ስታማትር ሔዋን የለችም። እንዴ አለችና እማማ ዘነብ! » ስትል ጠራቻቸው ገና ከሩቅ ሳሉ፡፡
«ወይ»
«አልተሳካሎትም?»
ወይዘሮ ዘነቡ ዝም ብለዋት ወደ ቤት ገቡና ዱካ ላይ ቁጭ ካሉ በኋላ ትሰሚያለሽ የኔ ልጅ!» አሏት ቀልብና ስሜቷን ሰብሰብ ለማድረግ፡፡
«እሺ» አለቻቸው በጉጉትና በፍርሀት ስሜት ተውጣ፡፡
ጓደኛሽም እህትሽሃም መልካም ሰዎች ናቸው። እህትሽ ጥፋቷን አምናለች፡፡ጓደኛሽም ተቆጥታለች። አንቺ የፈለግሽውን እርቅ እነሱ የበለጠ ፈልገውታል፡፡
እውነተኛ እርቅ ደግሞ አፍን ሳይሆን ልብን ከፍቶ ስለሆነ፣ ለዚህ ብርቱ ጉዳይ አንቺም ስትዘጋጂ እደሪና ነገ ሁለታችንም አብረን እንሂድና አንቺንም ከጓደኛሽ፣ እህትሽንም ከአንቺ በማስታረቅ ሁሉንም ነገር ፈጥሠን እንመጣለን። ከዚያ በኋላ እህትሽን ይዘናት እንመጣለን፡፡» ከማለት ውጭ ሌላ ምንም ሳይጨምሩ
ከተቀመጠበት ብድግ ብለው በይ ደህና እደሪl» ብለዋት ውልቅ አሉ፡፡
ሸዋዬ ድንግጥ አለች፡፡ እንዴ አለች በሆዷ፡፡ በዓይኗ ወይዘሮ ዘነቡን
እየተከተለች ይቺ አሮጊትና ያቺ ታፈሡ የምትባል መናጢ ምን ተማክረው ይሆን?' በማለት ብቻዋን ታወራ ጀመር። ሄደች በሀሳብ አሁንም ታፈሡ ከኔ ጋር
ታርቀ ሰላ እያለች ወደ ቤቴ በመምጣት የጀመረችውን ልትጨርስ!? እኔ ሳላውቅ
ከዚች አሮጊት ጋር ገጥማ ውስጥ ለውስጥ ሊያርዱኝ? በፍጹም ይህ የማይሆን ነው። ከታፈሡ ጋር እርቅ ብሎ ነገር የለም፡፡ ብቻ ያቺ ሰላቢ እህቴ እንደምንም ብላ
በእጄ ትግባልኝ፡፡ ይህ እንዲሆን የግድ ከታፈሡ ጋር ታረቂ ብባልም ለዚያች ቀን ብቻ በማግስቱ ግን አፈርሰዋለው በቃ።
ሸዋዬ ምሽቱን ሁሉ ስለዚሁ ስታስብ ቆይታ ሌሊቱንም ሳትረሳው መልሳ መላልሳ ስታመነዥገው አደረች። ፍላጎቷ አንድ! ሔዋንን በእጇ ማስገባት፤ ፉከራዋም እንድ፤ ከታፈሡ ጋር ፈጽሞ ከልብ ላለመታረቅ። ሀሳቧ ሁሉ ከዚሁ ሳይርቅ ሌቱ ነግቶ በጠዋቱ ፈረቃ ስራ ገባች፡፡
ከሰዓት በኋላ በታፈሡ ቤት የተያዘው የቀጠሮ ሠዓት ደረሰና ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር ወደ ታፈሡ ቤት ጉዞ ጀመሩ።
«እማማ ዘነብ!» ስትል ጠራቻቸው ከጎናቸው ሆና እየተራመደች
«ወይ»
«ለመሆኑ ታፈሡ እኔን ምን አደረገችኝ እለችዎት?»
«እረ እሷ እቴ! ምንም ያለችው ነገር የለም::»
«ታዲያ ከእሷ ጋር መታረቁ ለምን አስፈለገ?»
«በአንቺ ሆድ ውስጥ ያለ ነገር ሊኖር ይችላል ብዬ ነዋ!»
«እሱማ ብዙ አለ። ግን ዝም ነው የምለው፡፡»
«ያማ ቂመኝነት ነው:: የነገር ብዛት ባይጠቅምም የቂም ቋጠሮ ካልተፈታ እርቅ አይኖርምና ቅር ያለሽን ነገር አጠር አርግሽ መግለጥ ይኖርብሻል፡፡»
«እኔና እሷን ያቀያየመን እኮ ይሄው የእህቴ ጉዳይ ነው::»
ወይዘሮ ዘነቡ ድንገት ቁጥት አሉ፡፡ «የእህትሽ ጉዳይ የአንቺና የእሷ ጉዳይ አይደለም የራሷ ብቻ ነው:: በእሷ አታሳቡ፤ ተዋት!! አሉ ጠበቅ ባለ አነጋገር፡፡
«እንዴት እማማ ዘነበ? እኔማ የእህቴ ጉዳይ ያገባኛል::»
«ስለምታበያትና ስለምታጠጫት ተሆነ ተሳስተሻል። ሆድ የትም ይሞላል፡፡
ጭንቅላት ግን ነጣነት የሚያገኝበትን መንገድ ይፈልጋል፡፡ አትሞኚ »
«መረን ልቀቂያት ነው የሚሉኝ!»
«ተይ አንቺ ልጅ! ኋላ እንዳልጠላሽ! እህትሽን እንኳን አንቺ እኔ አውቄአታለሁ፡፡ ሥነስራት ያላት ጨዋ ናት፡፡ የሆዷን አይታ ድንግል ያን የመሰለ ጨዋ ልጅ ሰጥታተለች:: እንደኔ ቢሆን በእነሱ መሀል ባትገቢ ጥሩ ይመስለኛል፡፡»
አሏት ፈርጠም ባለ አነጋገር፡፡
ሽዋዬ ወይዘሮ ዘነቡን ክፉኛ ጠላቻቸው፡፡ ዛሬ ሔዋንን በእጇ የማስገባት ዓላማ ባይኖርባት ኖሮ በዚያ ሠዓት ወደ ቤቷ ምልስ ብትል በወደደች ነበር፡፡ ከዚያ
በኋላ ፀጥ እንዳለች ከታፈሡ ቤት በር ላይ ደረሱ፡፡
የታፈሡ ቤት እንግዳ ለመቀበል ተዘጋጅቷል። ወለሉ ተወልውሎ- ፏ ብሏል::ከሰል ተያይዞ የቡና ዕቃዎች ቀርበዋል። ታፈሡም እምር ብላለች። ቀላ ያለ ጉርድ
ቀሚስ በነጭ ሽሚዝ ለብሳ ሀብሏ በደረቷ ላይ እንደ ፀሐይ ያበራል፡፡ ያን ረጅም የጥቁር ዞማ ፀጉሯን ጎንጉና በጀርባዋ ላይ ለቃዋለች፡፡ ወይዘሮ ዘነቡ ሸዋዬን አስከትለው ወደ ቤት ራመድ ሲሉ ፈልቀቅ ባለ ፈገግታ ተቀበለቻቸው፡፡ በዚያ
ሠዓት ሔዋን ድንግጥ ብላ ወደ ጓዳ ስትሮጥ ወይዘሮ ዘነቡ ተመልክተዋት ኖሯል።
«ዛሬ ፈርቶ መደበቅ፣ እኩርፎ መንጋደድ የለም፡፡» አሉና መሀል ወለል ላይ ቆመው «በሉ እናንተ ቀድማችሁ በይቅርባይነት ያለ ወቀሳ ተሳሳሙ፡፡» አሏቸው
ታፈሡና ሸዋዬን ግራና ቀኝ አየት አየት እያረጉ፡፡ ታፈሡ ሁለት እጆቿን ዘርግታ ወደ ሸዋዬ ጠጋ በማለት «ሸዋዬ!!
ከአጠፋሁ ይቅርታ!» ብላ እንገቷን እቅፍ አድርጋ በመሳም ጨመጨመቻት፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ አጠገባቸው ቆመው «እሰይ እሰይ እልልል…» አሉ፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ ታፈሡ በዚያ ዓይነት ፈገግታ እየሳመቻት ሳለች የሸዋዬ
ፊት ግን ፈታ አለማለቱ እያናደዳቸው ነገር ግን የጀመሩትን ለመጨረስ ሲሉ፡ «በይ ያቺንም አበባ ጥሪልኝ፡፡ በእህቷ እግር ላይ ትወደቅ» ብለው ሔዋን ወዳላችበት ጓዳ አይናቸውን ወረወሩ።
«አንቺ ሒዩ» ስትል ታፈሡ ተጣራችና ቀጥላም ነይ እማማ ዘነብ ይፈልጉሻል» ስትላት ሔዋን ሽቁጥቁጥ እያለች ከወደ ጓዳ ብቅ አሉች፡፡ ለአንዴም ቀና ሳትል አቀርቅራ በመራመድ ከመሀላቸው ደረሰችና ከሸዋዬ እግር ላይ ወደቀች፡፡ወይዘሮ ዘነቡና ታፈሡም እልልእልል» በማለት ዕርቁን አደመቁት ።
ወይዘሮ ዘነቡ አሁንም ሆዳቸው በገነ ሔዋን ያን ያህል በእግሯ ላይ
ስትደፋ ሸዋዬ ግን ለመግደርደር ስትል እንኳ ቀና እንድትል አልጋበዘቻትም።በሆዳቸው ምኗ ድንጋይ ናት በማሪያም አሉ፡፡
የእርቅ ስነ ሥርዓት በዚህ ሁኔታ ተጠናቆ ሔዋን ብቻ ወደ ጓዳ ፈጥና ስትመለስ ሶስቱም ሶፋ ላይ ቁጭ አሉ የታፈሡ ሠራተኛ ቡና መቁላት ጀምራለች
«ሰላም ነሽ ሸዋዬ!» አለቻት ታፈሡ ቀድማ ፈገግ ብላ እያየቻት»
«እግዜሔርን አይክፋው»
«ሰሞኑን እንደተበሳጨሽ ይገባኛል ሔዩ አጥፍታለች» አለቻት ታፈሡ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....የወይዘሮ ዘነቡና የታፈሡ ውይይት በዚህ መልኩ እየተከናወነ ባለበት ሰአት
ሸዋዬ አልጋዋ ላይ ቁጭ ብላ በሁለት እጇ ጆሮ ግንዶቿን ጠፍራ በመያዝና አተርትራ በማሰብ ላይ ናት። ታፈሡንና ወይዘሮ ዘነቡን እያሰበች ልክ በመሀላቸው ቁጭ ብላ እንደምታዳምጣቸው ዓይነት ስለ እሷ ሲያወራ በሀሳቧ "ቀንታ ነው እኮ ተቀጥላ ይስሟታል!
ሰው እንዴት በእህቱ ይቀናል! አረ የሷ የብቻው ነው ። አስቻለውን እንደሆነ አታገኘው ምን ያስለፋታል?» የሚሏት ይመስላታል። ወይዘሮ
ዘነቡ ታፈሡን ሲያሞካሹ!
ለአስቻለውና ለሄዋን ለሔዋን ፍቅር መልካም ሲመኙ እሷ በእሳቸው ፊት የምታሳየውን ድንጋጤና የብስጭት ስሜት ለታፈሡ ዝርዝር አድርገው ሲያወሩባት ሁሉ ይታያታል፡፡ በዚያ ልክ ቅጥል ንድድ ትችላለች፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ ግቢያቸው ውስጥ እንዴግቡ ወደ ቢታቸው ጎራ ሳይሉ
በቀጥታ ወደ ጓሮ ዞረው ወደ ሸዋዩ ቤት አመሩ። ሸዋዬ ድንገት የሰው ኮቴ ሰምታ ከአጎነሰችበት ቀና ስትል ወይዘሮ ዘነቡ ብቻቸውን ሲመጡ አየቻቻው። ወደ
ኋላቸው ዓይኗን ስታማትር ሔዋን የለችም። እንዴ አለችና እማማ ዘነብ! » ስትል ጠራቻቸው ገና ከሩቅ ሳሉ፡፡
«ወይ»
«አልተሳካሎትም?»
ወይዘሮ ዘነቡ ዝም ብለዋት ወደ ቤት ገቡና ዱካ ላይ ቁጭ ካሉ በኋላ ትሰሚያለሽ የኔ ልጅ!» አሏት ቀልብና ስሜቷን ሰብሰብ ለማድረግ፡፡
«እሺ» አለቻቸው በጉጉትና በፍርሀት ስሜት ተውጣ፡፡
ጓደኛሽም እህትሽሃም መልካም ሰዎች ናቸው። እህትሽ ጥፋቷን አምናለች፡፡ጓደኛሽም ተቆጥታለች። አንቺ የፈለግሽውን እርቅ እነሱ የበለጠ ፈልገውታል፡፡
እውነተኛ እርቅ ደግሞ አፍን ሳይሆን ልብን ከፍቶ ስለሆነ፣ ለዚህ ብርቱ ጉዳይ አንቺም ስትዘጋጂ እደሪና ነገ ሁለታችንም አብረን እንሂድና አንቺንም ከጓደኛሽ፣ እህትሽንም ከአንቺ በማስታረቅ ሁሉንም ነገር ፈጥሠን እንመጣለን። ከዚያ በኋላ እህትሽን ይዘናት እንመጣለን፡፡» ከማለት ውጭ ሌላ ምንም ሳይጨምሩ
ከተቀመጠበት ብድግ ብለው በይ ደህና እደሪl» ብለዋት ውልቅ አሉ፡፡
ሸዋዬ ድንግጥ አለች፡፡ እንዴ አለች በሆዷ፡፡ በዓይኗ ወይዘሮ ዘነቡን
እየተከተለች ይቺ አሮጊትና ያቺ ታፈሡ የምትባል መናጢ ምን ተማክረው ይሆን?' በማለት ብቻዋን ታወራ ጀመር። ሄደች በሀሳብ አሁንም ታፈሡ ከኔ ጋር
ታርቀ ሰላ እያለች ወደ ቤቴ በመምጣት የጀመረችውን ልትጨርስ!? እኔ ሳላውቅ
ከዚች አሮጊት ጋር ገጥማ ውስጥ ለውስጥ ሊያርዱኝ? በፍጹም ይህ የማይሆን ነው። ከታፈሡ ጋር እርቅ ብሎ ነገር የለም፡፡ ብቻ ያቺ ሰላቢ እህቴ እንደምንም ብላ
በእጄ ትግባልኝ፡፡ ይህ እንዲሆን የግድ ከታፈሡ ጋር ታረቂ ብባልም ለዚያች ቀን ብቻ በማግስቱ ግን አፈርሰዋለው በቃ።
ሸዋዬ ምሽቱን ሁሉ ስለዚሁ ስታስብ ቆይታ ሌሊቱንም ሳትረሳው መልሳ መላልሳ ስታመነዥገው አደረች። ፍላጎቷ አንድ! ሔዋንን በእጇ ማስገባት፤ ፉከራዋም እንድ፤ ከታፈሡ ጋር ፈጽሞ ከልብ ላለመታረቅ። ሀሳቧ ሁሉ ከዚሁ ሳይርቅ ሌቱ ነግቶ በጠዋቱ ፈረቃ ስራ ገባች፡፡
ከሰዓት በኋላ በታፈሡ ቤት የተያዘው የቀጠሮ ሠዓት ደረሰና ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር ወደ ታፈሡ ቤት ጉዞ ጀመሩ።
«እማማ ዘነብ!» ስትል ጠራቻቸው ከጎናቸው ሆና እየተራመደች
«ወይ»
«ለመሆኑ ታፈሡ እኔን ምን አደረገችኝ እለችዎት?»
«እረ እሷ እቴ! ምንም ያለችው ነገር የለም::»
«ታዲያ ከእሷ ጋር መታረቁ ለምን አስፈለገ?»
«በአንቺ ሆድ ውስጥ ያለ ነገር ሊኖር ይችላል ብዬ ነዋ!»
«እሱማ ብዙ አለ። ግን ዝም ነው የምለው፡፡»
«ያማ ቂመኝነት ነው:: የነገር ብዛት ባይጠቅምም የቂም ቋጠሮ ካልተፈታ እርቅ አይኖርምና ቅር ያለሽን ነገር አጠር አርግሽ መግለጥ ይኖርብሻል፡፡»
«እኔና እሷን ያቀያየመን እኮ ይሄው የእህቴ ጉዳይ ነው::»
ወይዘሮ ዘነቡ ድንገት ቁጥት አሉ፡፡ «የእህትሽ ጉዳይ የአንቺና የእሷ ጉዳይ አይደለም የራሷ ብቻ ነው:: በእሷ አታሳቡ፤ ተዋት!! አሉ ጠበቅ ባለ አነጋገር፡፡
«እንዴት እማማ ዘነበ? እኔማ የእህቴ ጉዳይ ያገባኛል::»
«ስለምታበያትና ስለምታጠጫት ተሆነ ተሳስተሻል። ሆድ የትም ይሞላል፡፡
ጭንቅላት ግን ነጣነት የሚያገኝበትን መንገድ ይፈልጋል፡፡ አትሞኚ »
«መረን ልቀቂያት ነው የሚሉኝ!»
«ተይ አንቺ ልጅ! ኋላ እንዳልጠላሽ! እህትሽን እንኳን አንቺ እኔ አውቄአታለሁ፡፡ ሥነስራት ያላት ጨዋ ናት፡፡ የሆዷን አይታ ድንግል ያን የመሰለ ጨዋ ልጅ ሰጥታተለች:: እንደኔ ቢሆን በእነሱ መሀል ባትገቢ ጥሩ ይመስለኛል፡፡»
አሏት ፈርጠም ባለ አነጋገር፡፡
ሽዋዬ ወይዘሮ ዘነቡን ክፉኛ ጠላቻቸው፡፡ ዛሬ ሔዋንን በእጇ የማስገባት ዓላማ ባይኖርባት ኖሮ በዚያ ሠዓት ወደ ቤቷ ምልስ ብትል በወደደች ነበር፡፡ ከዚያ
በኋላ ፀጥ እንዳለች ከታፈሡ ቤት በር ላይ ደረሱ፡፡
የታፈሡ ቤት እንግዳ ለመቀበል ተዘጋጅቷል። ወለሉ ተወልውሎ- ፏ ብሏል::ከሰል ተያይዞ የቡና ዕቃዎች ቀርበዋል። ታፈሡም እምር ብላለች። ቀላ ያለ ጉርድ
ቀሚስ በነጭ ሽሚዝ ለብሳ ሀብሏ በደረቷ ላይ እንደ ፀሐይ ያበራል፡፡ ያን ረጅም የጥቁር ዞማ ፀጉሯን ጎንጉና በጀርባዋ ላይ ለቃዋለች፡፡ ወይዘሮ ዘነቡ ሸዋዬን አስከትለው ወደ ቤት ራመድ ሲሉ ፈልቀቅ ባለ ፈገግታ ተቀበለቻቸው፡፡ በዚያ
ሠዓት ሔዋን ድንግጥ ብላ ወደ ጓዳ ስትሮጥ ወይዘሮ ዘነቡ ተመልክተዋት ኖሯል።
«ዛሬ ፈርቶ መደበቅ፣ እኩርፎ መንጋደድ የለም፡፡» አሉና መሀል ወለል ላይ ቆመው «በሉ እናንተ ቀድማችሁ በይቅርባይነት ያለ ወቀሳ ተሳሳሙ፡፡» አሏቸው
ታፈሡና ሸዋዬን ግራና ቀኝ አየት አየት እያረጉ፡፡ ታፈሡ ሁለት እጆቿን ዘርግታ ወደ ሸዋዬ ጠጋ በማለት «ሸዋዬ!!
ከአጠፋሁ ይቅርታ!» ብላ እንገቷን እቅፍ አድርጋ በመሳም ጨመጨመቻት፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ አጠገባቸው ቆመው «እሰይ እሰይ እልልል…» አሉ፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ ታፈሡ በዚያ ዓይነት ፈገግታ እየሳመቻት ሳለች የሸዋዬ
ፊት ግን ፈታ አለማለቱ እያናደዳቸው ነገር ግን የጀመሩትን ለመጨረስ ሲሉ፡ «በይ ያቺንም አበባ ጥሪልኝ፡፡ በእህቷ እግር ላይ ትወደቅ» ብለው ሔዋን ወዳላችበት ጓዳ አይናቸውን ወረወሩ።
«አንቺ ሒዩ» ስትል ታፈሡ ተጣራችና ቀጥላም ነይ እማማ ዘነብ ይፈልጉሻል» ስትላት ሔዋን ሽቁጥቁጥ እያለች ከወደ ጓዳ ብቅ አሉች፡፡ ለአንዴም ቀና ሳትል አቀርቅራ በመራመድ ከመሀላቸው ደረሰችና ከሸዋዬ እግር ላይ ወደቀች፡፡ወይዘሮ ዘነቡና ታፈሡም እልልእልል» በማለት ዕርቁን አደመቁት ።
ወይዘሮ ዘነቡ አሁንም ሆዳቸው በገነ ሔዋን ያን ያህል በእግሯ ላይ
ስትደፋ ሸዋዬ ግን ለመግደርደር ስትል እንኳ ቀና እንድትል አልጋበዘቻትም።በሆዳቸው ምኗ ድንጋይ ናት በማሪያም አሉ፡፡
የእርቅ ስነ ሥርዓት በዚህ ሁኔታ ተጠናቆ ሔዋን ብቻ ወደ ጓዳ ፈጥና ስትመለስ ሶስቱም ሶፋ ላይ ቁጭ አሉ የታፈሡ ሠራተኛ ቡና መቁላት ጀምራለች
«ሰላም ነሽ ሸዋዬ!» አለቻት ታፈሡ ቀድማ ፈገግ ብላ እያየቻት»
«እግዜሔርን አይክፋው»
«ሰሞኑን እንደተበሳጨሽ ይገባኛል ሔዩ አጥፍታለች» አለቻት ታፈሡ
👍13❤1
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ፣ ኢያሱ ራቱን እስኪበላና እስኪተኛ ጠብቃ እሷም በድንጋጤና በለቅሶ የደነዘዘ ሰውነቷን ለማሳረፍ ከጎኑ ጋደም አለች። አካሏ ዝሎ፣ መንፈሷ ረግቦ፣ እንቅልፍ በዐይኗ አልዞር አለ። አእምሮዋ በውስጡ ያለተራ ብቅ ጭልጥ የሚለውን የሐሳብ ውዥንብር መቆጣጠር ተሳነው። መላ የጠፋው አእምሮዋ ቢሰክንልኝ ብላ ከመኝታ ክፍሏ ወደ ሰገነቱ ከሚያወጡት ከሶስቱ በሮች በመካከለኛው በኩል አድርጋ ሰገነቱ ላይ ቆመች። ባሏም ብዙ ጊዜ በዛ በር እየወጡ፣ አንዳንዴም አብረው እየሆኑ ከተማውንና ግቢውን ይቃኙ ነበርና እንባ ተናነቃት።
ለሰባት ዓመታት ያህል ከእሳቸው ጋር ያሳለፈችውን ሕይወት
በሐሳቧ መለስ ብላ አየች። ንጉሠ ነገሥቱ እንደ ተራ ሰው እናት አባቷ
ቤት መደብ ላይ ተኝተው ያስታመመቻቸውን አስታወሰች። ምንትዋብ ብለው ስም ያወጡላት፣ “የኔ ዓለም” እያሉ ያቆላመጧት ሁሉ በየተራ ፊቷ ድቅን አሉባት። ምነው እንዲህ ዕድሜያቸውን አሳጠረባቸው?
አለችና ምርር ብላ አለቀሰች።
ከቤተመንግሥት ግቢ አሻግራ ጥቅጥቅ ባለው ጭለማ ውስጥ ጐንደርን ለማየት ሞከረች። ማታ ማታ ጐንደርን ያለ ከልካይ ከሚፈትሹት ጅቦች ሌላ የሚንቀሳቀስ ነገር የለም። አልፎ አልፎ ጅቦቹን ከሚያስፈራሩት
ውሾች ጩኸት በስተቀር ድምፅም አይሰማም።
ምንትዋብ ከጐንደር ወደ ራሷ ተመለሰች። ሕይወት ያልታሰበ
ፀጋ አምጥታላት መልሳ መንጠቋ ገረማት። የሕይወት መንገዶች
አለመጣጣማቸው ደነቃት። ሞት ሌላው የሕይወት ገፅታ መሆኑን
አሰበች። ሕይወት ምስጢሯን ያካፈለቻት መስሎ ተሰማት። ነገ እዛ ራሷ ረጋፊ መሆኗ በአእምሮዋ ተመላለሰና ዘገነናት። ለጊዜውም ቢሆን የመኖር ትርጉሙ ተናጋባት። የሙት ሚስት መሆኗ ወለል ብሎ
ታያት። ሞት ተስፋዋን ሁሉ ሸራረፈባት።
በዚያች ቅጽበት ሕይወቷ ዳግመኛ እንደተለወጠ ተረዳች።
መኝታ ክፍላቸው ስትገባ እንደገና እንባ አሸነፋት። ቤቱ የሚበላት፣
አልጋው ብቻዋን በመምጣቷ የሚታዘባት መሰላት። ለባሏ እንደሚገባቸው ያላዘነች፣ ያላነባች መስሎ ተሰማት። ቆም ብላ ክፍሉን ቃኘች። በርካታ
ትዝታዎች በአእምሮዋ ውስጥ ተመላለሱ። ወደ ኢያሱ ስትመለከት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ላይ ነው። ሆዷ ባባ። አባቱን ሲሰናበታቸው ምን ተሰምቶት እንደሆነ መገመት አቃታት። እመንናለሁ ብላ የእሱን ሕይወት አደጋ ልትጥል እንደነበር አስታወሰችና ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። ተጠግታው ራሱን እያሻሸች፣ በዚች ምድር ላይ ካሉ ክፉ ነገሮች ሁሉ፣ከሞት ጭምር፣ ልትደብቀው እቅፏ ውስጥ ሽጉጥ አድርጋው ጋደም
አለች።
አእምሮዋ እረፍት አጥቶ እንቅልፍ በዐይኗ ሳይዞር ወፍ ተንጫጫ።
ተነስታ ወደ ሰገነቱ ወጣች። ሰማይና ምድር ገና አልተላቀቁም።
ጐንደርም ገና እንቅልፍ ላይ ናት። በቦዘዙ ዐይኖቿ ዙርያውን አየች።
የጠዋቱ ቅዝቃዜ ፊቷን ሲዳስሳት፣ ነቃ አለች።
አሻግራ ጐንደርን ወደከበቧት ተራሮች ተመለከተች። ፍም እሳት
የከበባት የምትመስለውን ፀሐይ ብቅ ስትል ስታይ የጥድፊያ ስሜት
ተሰማት። በመመርያ ኸዋና ዋናዎቹ ግቢ አዛዥና ኸሊጋባው፣
እንዲሁም ኸመሣፍንቱና ኸመኳንንቱ ጋር መክራለሁ። ጃንሆይ አገር አለ ምክር፣ ቤት አለ ማገር ይሉ ማልነበር? ኸዛ በኋላ፣ ኢያሱ በምሥጢር ይነግሣል። የልጄቼን አልጋማ ለማንም አሳልፌ አልሰጥም
ለካንስ እሷም መንገሷ ነው! ደነገጠች።
ይህ ሳይታሰብ እላይዋ ላይ የወደቀው ኃላፊነት ከየት እንደመጣ ማወቅ አቃታት። ሃገር ልታስተዳድር መሆኑ ሲገባት ታላቅ የኃላፊነት ስሜት ተጫጫናት፡፡ እሳቸው ያሰቡትን ሁሉ ሳያሳኩ አለፉ፤ እኔስ ብሆን መቸ እንደምሞት በምን አውቃለሁ? ሞት እንደሁ ለማንም አይመለስ፡ ብቻ እንዳው አንዴ የሳቸውን ቀብርና የልጄን ንግሥ
ያለምንም ሳንካ ላሳካ እያለች አእምሮዋ ውስጥ የሚወራጨውን ሐሳብ ሁሉ በየፈርጁ ማስቀመጥ ሞከረች።
ድንገት ክፉኛ የመንገሥ ፍላጎት አደረባት። ባሏ፣ “እሷ አገር
ማስተዳደር ትችላለች” ያሉት በከንቱ እንዳልሆነ፣
ስለቤተመንግሥትም ጉዳይ ቢሆን ላለፉት ሰባት ዓመታት በቂ
እውቀት እንዳካበተች፣ በደጉ ጊዜ ቤተመንግሥት ውስጥ ቦታቸውን
ያመቻቸችላቸው የኒቆላዎስ፣ የወልደልዑል፣ የአርከሌድስና
የሌሎቹም መኖር ታላቅ ድጋፍ እንደሚሆናት ተረዳች። ኒቆላዎስ
እያረጀ በመምጣቱ፣ ወንድሟ ወልደልዑል ጉልህ ችሎታ በማሳየቱና ቤተመንግሥት ውስጥ የማይናቅ አስተዋጽኦም በማድረጉ ቀኝ እጇ ሊሆን እንደሚችል አመነች። ዐዲስ ማንነት ውስጧ ሲጠነሰስ ተሰማት።
ከፍተኛውን የሥልጣን ዕርከን ስትወጣ ታያት።
ልቧ መታ፤ መላ ሰውነቷ ተቅበጠበጠ። ዳግም የጥድፊያ ስሜት ተሰማት። ይህንን ዕድል ለማንም አሳልፋ ልትሰጥ እንደማትችልና የኢያሱን ሆነ የራሷን ንግሥ ለማስከበር በችሎታዋና ሥልጣንዋ ስር ያለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለባት ለራሷ አስገነዘበች። አሁን ፊቷ ተደቅኖ
የሚታያት ምኞት ወይንም ተስፋ ሳይሆን በቅርብ ያለ፣ሊጨበጥ የሚችል በመሆኑና ከለቀቀችው፣ ካመነታች እዳው ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለልጇ ጭምር በመሆኑ በአስቸኳይ እርምጃ መውሰድ
እንዳለባት ተረዳች።
እኔም ኢያሱም ኸነገሥን በኋላ፣ ኣመጥ እንዳይኖር ጥርጣሬ
አስወግጀ ሰዉ እኔ ላይ አመኔታ እንዲኖረው ማረግ አለብኝ። መቸም መልካም ሥራ ኸሠራሁና ጥሩ አርጌ ኻስተዳደርሁ ሰዉ ይደግፈኛል::እምነትም ይጥልብኛል አለች፣ ሞላ ባለ ልብ። ከሁን ታሪክ የምትሠራበት፣ ስሟን ካለፉት ነገሥታት ተርታ የምታሰልፍበት ወቅት
እንደተቃረበ አስተዋለች። ሃገሯ ታላቅ ጥንካሬ፣ ዘዴ፣ ቆራጥነትና
ቀናነት እንደምትጠብቅባት ተረዳች።
ከሐሳቧ ስትነቃ ምድር ለቋል፤ ጐንደር ብርሃን ለብሳለች፤ ነፍስ
ዘርታለች። ። ጐንደርን ለመጀመሪያ ጊዜ በተለየ ዐይን አየቻት። ጐንደር
ጐንደር! አለች፣ በለሆሳስ፡ ፊቷን እያዟዟረች ከተማዋን የከበቡትን
ሰንሰለታማ ተራራዎች ትክ ብላ አየቻቸው። በተፈጥሮዋ የጠላት
መከላከያ አላት አለች። እንደገና ከተማዋን ከላይ ወደታች ቃኘች።
ጐንደር... ያቺ የነገሥታቱ፣ የመሣፍንቱና የመኳንንቱ የትንቅንቅ ቦታ ሳትሆን የተለየች ጐንደር ሆና፣ እንባዋን ጠራርጋ ወጣ ገባ ስትል ታየቻት። የዕድል ማሳ ሆና እሷ ማሳው ላይ ስትዘራ ጐንደር ስታብብ፣ስታፈራ፣ ይበልጥ ገናና ስትሆን ታያት።
በራሷ አምሳል የቀረጸቻት ጐንደር ፊቷ ወለል አለች።
ጐንደርን በጃን ተከል በኩል ለማየት ወደ ላይኛው ሰገነት በደረጃ ወጣች። የሁሉ መኖሪያ፣ ሁሉን እንደ ሃይማኖቱ፣ እንደ ሙያውና እንደ ልማዱ የምታስተናግደውንና፣ መንፈሰ ለጋሷን ጐንደርን እንደ
ዐዲስ ወደደቻት፤ ከክፉ ልትታደጋት ፈቀደች። ምን ዓይነት ቦታ እንደሆነችና ሕዝቧም ምን ዓይነት እንደሆነ ይበልጥ ማወቅ ፈለገች።
ልክ በዛን ሰዐት የእሷም የጐንደርም ዕጣ የተለየ አቅጣጫ ያዘ።
እንዴ! አገሬ? አገሬስ? ጐንደር አላገር ትኖራለች እንዴ? አለች
ደረቷን እየመታች። አገሬ ውስጥ ሰላም አምጥቸ እኼ ነው ምኞቴ
አለች፣ ባሏ የነበረባቸውን ዓመጽ አስባ። ሃገሯን ልትታደጋት፣
ልታረጋጋት፣ ሰላም ልታሰፍንባት ወሰነች።
የደብረብርሃን ሥላሤ ደወል ሲደወል ከሐሳቧ ነቃች፣ ተረበሸች።
ደወሉ ለአባታቸው ለአፄ አድያም ሰገድ ኢያሱ ከሆላንድ ንጉሥ
የተላከ ነበርና ንጉሠ ነገሥቱ ደወሉን ሲሰሙ ከእንቅልፋቸው ብንን ብለው ሲያማትቡ፣ ተነሥተው ዳዊታቸውንና ውዳሴ ማርያማቸውን ሲደግሙ ፊቷ ላይ ድቅን አለ። አየ ያ ሁሉ ቀረ አለችና እንባዋን ጠራረገች።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ፣ ኢያሱ ራቱን እስኪበላና እስኪተኛ ጠብቃ እሷም በድንጋጤና በለቅሶ የደነዘዘ ሰውነቷን ለማሳረፍ ከጎኑ ጋደም አለች። አካሏ ዝሎ፣ መንፈሷ ረግቦ፣ እንቅልፍ በዐይኗ አልዞር አለ። አእምሮዋ በውስጡ ያለተራ ብቅ ጭልጥ የሚለውን የሐሳብ ውዥንብር መቆጣጠር ተሳነው። መላ የጠፋው አእምሮዋ ቢሰክንልኝ ብላ ከመኝታ ክፍሏ ወደ ሰገነቱ ከሚያወጡት ከሶስቱ በሮች በመካከለኛው በኩል አድርጋ ሰገነቱ ላይ ቆመች። ባሏም ብዙ ጊዜ በዛ በር እየወጡ፣ አንዳንዴም አብረው እየሆኑ ከተማውንና ግቢውን ይቃኙ ነበርና እንባ ተናነቃት።
ለሰባት ዓመታት ያህል ከእሳቸው ጋር ያሳለፈችውን ሕይወት
በሐሳቧ መለስ ብላ አየች። ንጉሠ ነገሥቱ እንደ ተራ ሰው እናት አባቷ
ቤት መደብ ላይ ተኝተው ያስታመመቻቸውን አስታወሰች። ምንትዋብ ብለው ስም ያወጡላት፣ “የኔ ዓለም” እያሉ ያቆላመጧት ሁሉ በየተራ ፊቷ ድቅን አሉባት። ምነው እንዲህ ዕድሜያቸውን አሳጠረባቸው?
አለችና ምርር ብላ አለቀሰች።
ከቤተመንግሥት ግቢ አሻግራ ጥቅጥቅ ባለው ጭለማ ውስጥ ጐንደርን ለማየት ሞከረች። ማታ ማታ ጐንደርን ያለ ከልካይ ከሚፈትሹት ጅቦች ሌላ የሚንቀሳቀስ ነገር የለም። አልፎ አልፎ ጅቦቹን ከሚያስፈራሩት
ውሾች ጩኸት በስተቀር ድምፅም አይሰማም።
ምንትዋብ ከጐንደር ወደ ራሷ ተመለሰች። ሕይወት ያልታሰበ
ፀጋ አምጥታላት መልሳ መንጠቋ ገረማት። የሕይወት መንገዶች
አለመጣጣማቸው ደነቃት። ሞት ሌላው የሕይወት ገፅታ መሆኑን
አሰበች። ሕይወት ምስጢሯን ያካፈለቻት መስሎ ተሰማት። ነገ እዛ ራሷ ረጋፊ መሆኗ በአእምሮዋ ተመላለሰና ዘገነናት። ለጊዜውም ቢሆን የመኖር ትርጉሙ ተናጋባት። የሙት ሚስት መሆኗ ወለል ብሎ
ታያት። ሞት ተስፋዋን ሁሉ ሸራረፈባት።
በዚያች ቅጽበት ሕይወቷ ዳግመኛ እንደተለወጠ ተረዳች።
መኝታ ክፍላቸው ስትገባ እንደገና እንባ አሸነፋት። ቤቱ የሚበላት፣
አልጋው ብቻዋን በመምጣቷ የሚታዘባት መሰላት። ለባሏ እንደሚገባቸው ያላዘነች፣ ያላነባች መስሎ ተሰማት። ቆም ብላ ክፍሉን ቃኘች። በርካታ
ትዝታዎች በአእምሮዋ ውስጥ ተመላለሱ። ወደ ኢያሱ ስትመለከት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ላይ ነው። ሆዷ ባባ። አባቱን ሲሰናበታቸው ምን ተሰምቶት እንደሆነ መገመት አቃታት። እመንናለሁ ብላ የእሱን ሕይወት አደጋ ልትጥል እንደነበር አስታወሰችና ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። ተጠግታው ራሱን እያሻሸች፣ በዚች ምድር ላይ ካሉ ክፉ ነገሮች ሁሉ፣ከሞት ጭምር፣ ልትደብቀው እቅፏ ውስጥ ሽጉጥ አድርጋው ጋደም
አለች።
አእምሮዋ እረፍት አጥቶ እንቅልፍ በዐይኗ ሳይዞር ወፍ ተንጫጫ።
ተነስታ ወደ ሰገነቱ ወጣች። ሰማይና ምድር ገና አልተላቀቁም።
ጐንደርም ገና እንቅልፍ ላይ ናት። በቦዘዙ ዐይኖቿ ዙርያውን አየች።
የጠዋቱ ቅዝቃዜ ፊቷን ሲዳስሳት፣ ነቃ አለች።
አሻግራ ጐንደርን ወደከበቧት ተራሮች ተመለከተች። ፍም እሳት
የከበባት የምትመስለውን ፀሐይ ብቅ ስትል ስታይ የጥድፊያ ስሜት
ተሰማት። በመመርያ ኸዋና ዋናዎቹ ግቢ አዛዥና ኸሊጋባው፣
እንዲሁም ኸመሣፍንቱና ኸመኳንንቱ ጋር መክራለሁ። ጃንሆይ አገር አለ ምክር፣ ቤት አለ ማገር ይሉ ማልነበር? ኸዛ በኋላ፣ ኢያሱ በምሥጢር ይነግሣል። የልጄቼን አልጋማ ለማንም አሳልፌ አልሰጥም
ለካንስ እሷም መንገሷ ነው! ደነገጠች።
ይህ ሳይታሰብ እላይዋ ላይ የወደቀው ኃላፊነት ከየት እንደመጣ ማወቅ አቃታት። ሃገር ልታስተዳድር መሆኑ ሲገባት ታላቅ የኃላፊነት ስሜት ተጫጫናት፡፡ እሳቸው ያሰቡትን ሁሉ ሳያሳኩ አለፉ፤ እኔስ ብሆን መቸ እንደምሞት በምን አውቃለሁ? ሞት እንደሁ ለማንም አይመለስ፡ ብቻ እንዳው አንዴ የሳቸውን ቀብርና የልጄን ንግሥ
ያለምንም ሳንካ ላሳካ እያለች አእምሮዋ ውስጥ የሚወራጨውን ሐሳብ ሁሉ በየፈርጁ ማስቀመጥ ሞከረች።
ድንገት ክፉኛ የመንገሥ ፍላጎት አደረባት። ባሏ፣ “እሷ አገር
ማስተዳደር ትችላለች” ያሉት በከንቱ እንዳልሆነ፣
ስለቤተመንግሥትም ጉዳይ ቢሆን ላለፉት ሰባት ዓመታት በቂ
እውቀት እንዳካበተች፣ በደጉ ጊዜ ቤተመንግሥት ውስጥ ቦታቸውን
ያመቻቸችላቸው የኒቆላዎስ፣ የወልደልዑል፣ የአርከሌድስና
የሌሎቹም መኖር ታላቅ ድጋፍ እንደሚሆናት ተረዳች። ኒቆላዎስ
እያረጀ በመምጣቱ፣ ወንድሟ ወልደልዑል ጉልህ ችሎታ በማሳየቱና ቤተመንግሥት ውስጥ የማይናቅ አስተዋጽኦም በማድረጉ ቀኝ እጇ ሊሆን እንደሚችል አመነች። ዐዲስ ማንነት ውስጧ ሲጠነሰስ ተሰማት።
ከፍተኛውን የሥልጣን ዕርከን ስትወጣ ታያት።
ልቧ መታ፤ መላ ሰውነቷ ተቅበጠበጠ። ዳግም የጥድፊያ ስሜት ተሰማት። ይህንን ዕድል ለማንም አሳልፋ ልትሰጥ እንደማትችልና የኢያሱን ሆነ የራሷን ንግሥ ለማስከበር በችሎታዋና ሥልጣንዋ ስር ያለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለባት ለራሷ አስገነዘበች። አሁን ፊቷ ተደቅኖ
የሚታያት ምኞት ወይንም ተስፋ ሳይሆን በቅርብ ያለ፣ሊጨበጥ የሚችል በመሆኑና ከለቀቀችው፣ ካመነታች እዳው ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለልጇ ጭምር በመሆኑ በአስቸኳይ እርምጃ መውሰድ
እንዳለባት ተረዳች።
እኔም ኢያሱም ኸነገሥን በኋላ፣ ኣመጥ እንዳይኖር ጥርጣሬ
አስወግጀ ሰዉ እኔ ላይ አመኔታ እንዲኖረው ማረግ አለብኝ። መቸም መልካም ሥራ ኸሠራሁና ጥሩ አርጌ ኻስተዳደርሁ ሰዉ ይደግፈኛል::እምነትም ይጥልብኛል አለች፣ ሞላ ባለ ልብ። ከሁን ታሪክ የምትሠራበት፣ ስሟን ካለፉት ነገሥታት ተርታ የምታሰልፍበት ወቅት
እንደተቃረበ አስተዋለች። ሃገሯ ታላቅ ጥንካሬ፣ ዘዴ፣ ቆራጥነትና
ቀናነት እንደምትጠብቅባት ተረዳች።
ከሐሳቧ ስትነቃ ምድር ለቋል፤ ጐንደር ብርሃን ለብሳለች፤ ነፍስ
ዘርታለች። ። ጐንደርን ለመጀመሪያ ጊዜ በተለየ ዐይን አየቻት። ጐንደር
ጐንደር! አለች፣ በለሆሳስ፡ ፊቷን እያዟዟረች ከተማዋን የከበቡትን
ሰንሰለታማ ተራራዎች ትክ ብላ አየቻቸው። በተፈጥሮዋ የጠላት
መከላከያ አላት አለች። እንደገና ከተማዋን ከላይ ወደታች ቃኘች።
ጐንደር... ያቺ የነገሥታቱ፣ የመሣፍንቱና የመኳንንቱ የትንቅንቅ ቦታ ሳትሆን የተለየች ጐንደር ሆና፣ እንባዋን ጠራርጋ ወጣ ገባ ስትል ታየቻት። የዕድል ማሳ ሆና እሷ ማሳው ላይ ስትዘራ ጐንደር ስታብብ፣ስታፈራ፣ ይበልጥ ገናና ስትሆን ታያት።
በራሷ አምሳል የቀረጸቻት ጐንደር ፊቷ ወለል አለች።
ጐንደርን በጃን ተከል በኩል ለማየት ወደ ላይኛው ሰገነት በደረጃ ወጣች። የሁሉ መኖሪያ፣ ሁሉን እንደ ሃይማኖቱ፣ እንደ ሙያውና እንደ ልማዱ የምታስተናግደውንና፣ መንፈሰ ለጋሷን ጐንደርን እንደ
ዐዲስ ወደደቻት፤ ከክፉ ልትታደጋት ፈቀደች። ምን ዓይነት ቦታ እንደሆነችና ሕዝቧም ምን ዓይነት እንደሆነ ይበልጥ ማወቅ ፈለገች።
ልክ በዛን ሰዐት የእሷም የጐንደርም ዕጣ የተለየ አቅጣጫ ያዘ።
እንዴ! አገሬ? አገሬስ? ጐንደር አላገር ትኖራለች እንዴ? አለች
ደረቷን እየመታች። አገሬ ውስጥ ሰላም አምጥቸ እኼ ነው ምኞቴ
አለች፣ ባሏ የነበረባቸውን ዓመጽ አስባ። ሃገሯን ልትታደጋት፣
ልታረጋጋት፣ ሰላም ልታሰፍንባት ወሰነች።
የደብረብርሃን ሥላሤ ደወል ሲደወል ከሐሳቧ ነቃች፣ ተረበሸች።
ደወሉ ለአባታቸው ለአፄ አድያም ሰገድ ኢያሱ ከሆላንድ ንጉሥ
የተላከ ነበርና ንጉሠ ነገሥቱ ደወሉን ሲሰሙ ከእንቅልፋቸው ብንን ብለው ሲያማትቡ፣ ተነሥተው ዳዊታቸውንና ውዳሴ ማርያማቸውን ሲደግሙ ፊቷ ላይ ድቅን አለ። አየ ያ ሁሉ ቀረ አለችና እንባዋን ጠራረገች።
👍13❤2