አትሮኖስ
281K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
480 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰባት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


...በዲላ ከተማ ዜሮ አምስት ቀበሌ ውስጥ ስምንተኛ መንገድ ላይ ፊቱን ለማታ ፀሃይ ሰጥቶ በተገነባው በወይዘሮ ዘነቡ አሰግድ ግቢ ውስጥ በስተጓሮ በኩል ያለው የሽዋዬና የሔዋን መኖሪያ ቤት ከጣሪያና ግድግዳው በስተቀር በውስጡ ይታይ የነበረ ትዕይንት ሁሉ ዛሬ መልኩን ቀይሯል፡፡ የሁለት የእትማማች
ጣውንቶች መኖሪያ ሆኖ ደስታ ርቆታል፡፡ በፍቅር ተስፋ ለምልመው የነበሩ ልቦች ዛሬ የሀዘን ድባብ ጥሎባቸዋል፡፡ በሳቅ ይፍለቀለቁ የነበሩ ጥርሶች ዛሬ ተከድነዋል።
ፏ ብለው ይታዩ የነበሩ ፊቶች ዛሬ ግን አኩርፈው እንደ ኩልኩልት
ተንጠልጥለዋል። የአስቻለው እግሮች ተሰብስበው ቤቱ እንግዳ ናፍቆታል።
ሽዋዬ ፣ ሔዋንና አስቻለው በየራሳቸው የሀሳብ ጎዳና ይነጉዳሉ፡፡ የሽዋዬ ግን
ከሁሉም በተለየ ሁኔታ እንቅፋት የበዛበት ሆኗል፡፡ የሚቆጫት አስቻለውን ማጣቷ ብቻ አይደለም፤ በእሷ እምነት አስቻለውን የነጠቀቻት እህቷ በመሆኗ ከዚሁ ጋር ተያይዘው ይመጣሉ ብላ የምታስባቸው ማህበራዊ ቀውሶች ከወዲሁ ያስጨንቋት ይዘዋል። አስቻለውን በማፍቀሯና ከግንኙነታቸው መጥበቅ የተነሳ የኔ ነው ብላ
ለሌላ ሰው ያወራችም ይመስላታል። ዛሬ በእህቷ ተነጠቀች የሚል አሉባልታ
የሚነሣ እየመስላት ትሳቀቃለች:: ምናልባት አስቻለውና ሔዋን ወደፊት ቢጋቡ
“ትልቋ እያለች ትንሿ፣ ሥራ ያላት እያለች ተማሪዋ አገባች የሚል የዘመድ አዝማድ ሹክሹክታም ሲነሳባት ይታያታል፡፡ ወደፊት በሚፈጠር ቤተስባዊ ግንኝነት ሁልጊዜ እያየችው በቅናት እየተቃጠለች ልትኖር ነው። ዛሬ የገጠማትን የስሜት ሰቀቀን ሁልጊዜ እያስታወስች እንዴት መኖር እንደምትችል ይቸግራታል።
አዕምሮ ደግሞ ትንሽ የሀሳብ ቀዳዳ ከከፈቱለት ያቺነ በማስፋት የጭንቅ ተባይ እየፈጠረ ያቅበጠብጣልና የሽዋዬ መንፈስ በስጋት ተወጠረ፡፡ ቀኑን ያለ ዕረፍት
ሌሊቱን ያለ እንቅልፍ ታቀያይረው ጀመር፡፡

ከዚህ ሁላ ጭንቅ የሚገላግላት ብቸኛ መንገድ አስቻለውና ሔዋንን
ማለያየት ብቻ መሆኑ ታያት፣ ጨለማ የሆነባት ግን ማለያያው ዘዴ፡፡ አንዳንዴ ሔዋንን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ መፍትሄ የሚሆን መስሎ ይታያታል፡፡ ነገር ግን አስቻለው ሔዋንን፣ ሔዋን ደግሞ አስቻለውን እስካሉ ድረስ ከዚያስ ሄዶ ቢያመጣት? ወይም አስቻለው ከቤቷ ድርሽ እንዳይል ማድረግ ብትሞክርስ? ያም
አያዋጣ፡፡ ሔዋን ራሷ ወደ እሱ ቤት ልትሄድ ትችላለች። እንደ በግ አትዘጋባት፣ እንደ ጥጃ አታስራት፡ ወይ ደግሞ ስራዋን ትታ እሷን ስትጠብቅ አትውል! ሁሉም
መንገድ የማይጨበጥ ህልም ሆኖባታል::

ከመዋል ከማደር አንድ የተስፋ ብልጭታ ብቻ ማየት ጀመረች፡ ለዚያውም ይህ ነው ብላ የምትጠብቀው ግልጽ ውጤት ሳይኖር፡፡ ያም ቢሆን ከራሱ ከአስቻለው ያገኘችው ፍንጭ ነው። ከጥቂት ወራት በፊት አንድ ቀን እሷና አስቻለው በአንድ
ቡና ቤት ውስጥ ይዝናናሉ፡፡ የተቀመጠበት ቦታ መስኮት አጠገብ ስለነበረ መንገዱ
ይታያቸዋል። አስቻለው ድንገት ባርናባስን መንገድ ላይ ያየውና ሽዋዬን ጎሽም አድርጎ «ያን ሰውዬ ተመልከች» ይላታል፡፡
«የቱን?»
«ደማቅ ስማያዊ ካኪ የለበሰውን፡፡
«እሺ አየሁት»
«ዲላ ሆስፒታል ውስጥ ድርብ ስልጣን ያለው ሰው ነው፡፡» ካለ በኋላ በእሱና በባርናባስ መሀከል ያለውን ያለመግባባት የመነሻ ጀምሮ አሁን እስካሉብት ጊዚ ድረስ ያለውን ሁኔታ እንደ ቀልድ ያጫውታታል። ይህ ነገር በሸዋዬ ልብ ውስጥ አለ።

ግን ደግሞ አስቻለው አላወቀም እንጂ ሸዋዬና ባርናባስ በደንብ
ይተዋዉቃሉ፤ ያውም ከስምንት ዓመታት በፊት ጀምር፡፡ ሰበቡ ሸዋዩ ትምህርቷን እንደ ጨረሰች መምህርነት ተመድባ ወደ ያቤሎ መሄዷና ባርናባስ ደግሞ በወቅቱ
የግሉ ጤና ጣብያ የአስተዳደር ክፍል ኃላፊ ሆኖ ይሰራ የነበረ መሆኑ ነው። ሸዋዬ ያቤሎ ደርሳ ከመኪና እንደ ወረደች ማረፊያ የት እንደምታገኝ ስትጠይቅ የመኪና
ተራ ልጆች ወደ አንድ የማረፊያ ቦታ ይወስዷታል፡፡ ቤቱ ሆቴል ቤት አልነበረም፤ ነገር ግን ግቢው መስክ በርካታ በአልቤርጎ ዓይነት የተስሩ ክፍሎች አሉት።
ድንገተኛ እንግዳም ያርፍባቸዋል። ለወር ኮንትራትም ይሰጣል፡፡ ባርናባስም ከእነዚያ ክፍሎች እንዷን በኮንትራት ይዞ" ብቻውን ይኖር ነበር::

ሸዋዬ ከእነዚያ ክፍሎች በአንዷ ውስጥ አድራ በማግስቱም እዚያው ትደግማለች። በሦስተኛ ቀንም እንዲሁ። በኋላም ከዚያ የተሻለ መኖሪያ እንደማታገኝ
ሲገባት ልክ እንደ ባርናባስ ክፍሏን በኮንትራት ይዛ ትቀመጣለች፡፡ ከመዋል ከማደር ከየባርናባስ ጋር ይተዋወቃሉ፡፡ ቀስ በቀስ ይተራረባሉ። ይግባቡና ይፋቀራሉ፡፡መጨረሻ ላይ ልክ እንደ ደባል ሆነው አብረው መኖር ይጀምራሉ፡፡ ባርናባስ
በዕድሜው ጠና ያለ ቢሆንም ለሽዋዬ ግን ይመቻታል። እሷም ላእሱ ትሞቀዋለች።ያ ሁሉ ሲሆን ባርናባስ ባለ ትዳርና የልጆች አባት መሆኑን እንዲሁም ቤተሰቦቹ ዲላ
ከተማ ወስጥ እንደሚኖሩ ሸዋዬ አታውቅም ነበር። በእርግጥ ወደ ዲላ አዘውትሮ እንደሚሄድ ታውቃለች፡፡ ነገር ግን ለስራ ጉዳይ እያለ ስለሚያታልላት እሷም
አትጠረጥር ነበር።

በዚሁ ሁኔታ ለአንድ ዓመት ያህል ከቆዩ በኋላ ድንገት የባርናባስ የሰባት ወር ህጻን ልጁ ይሞትና ከዲላ መልዕክት የተቀበሉ የመሥሪያ ቤቱ ሠራተኞች
ወርዶው እንዲደርሰው ያደርጋሉ። በወቅቱ ሸዋዬ ማመን ቢያቅታትም ነገር ግን
በማግስቱ ጀምሮ ከባርናባስ ቤት ወጥታ ትሄዳለች፡፡ በዚያው ትቀራለች::ፍቅራቸውም ይቋረጣል።

ባርናባስ ከልጁ መሞት በኋላ በያቤሎ ብዙ አልቆየም፡፡ እድገትና ዝውውር አግኝቶ ዲላ በመግባት ከቤተሰቡ ጋር ይቀላቀላል። ይሁንና የባርናባስና የሸዋዬ
መለያየት የከረረ ጠብ አላስከተለም፤ ቆይቶም ቢሆን የፍቅር ውጭ ያለ ግንኙነት
ማስቀጠል የሚችል እርቅ ፈጽመዋል። ሸዋዬ ዲላ ከመጣችም ወዲሀ ከአለፈ ገደም እየተገናኙ ሰላምታ ይለዋወጣሉ። አስቻለው ስለ ባርናባስ ያወራት በነበረ ጊዜ ሸዋዬ ይህን ሁሉ በሆዷ ይዛለች፡ እሷ ግን ስለ ባርናባስ ለአስቻለው ትንፍሽ አላለችም::

ምን ሊያደርግላት እንደሚችል በውል ባይታወቃትም ሸዋዬ ለዛሬው ጭንቋ መላ ስታፈላልግ ባርናባስ ትዝ ብሏታል፡፡ የአስቻለው አለቃ ነውና፣ በዚያ ላይ አይስማሙምና፣ ለችግሬ መፍትሄ የሚያመጣ መላ ያፈላልግልኝ ይሆን?› እያለች
ለአንድ ወይም በሌላ ጉዳይ በልቧ ታውጠነጥነው ጀመር።
ነጋሪ
የሸዋዬ ሀሳብ በዚህ መልኩ ሲነጉድ ሔዋን ግን ስለ ጭንቀቷ እንጂ ችግሯን ሰለምታቃልልበት መንገድ የሚታያት አንዳች ነገር የለም፡፡ ሆነም አልሆነ ነገሩ ይበርድላት ዘንድ መጓጓት ብቻ ነው። ከዚያ ባለፈ አስቻለው ወደዚያ ግድም ድርሽ እንዳይል የጠበቀ አደራ በታፈሡ በኩል ልካበታለች:: ነገር ግን አደራውን
ስለመቀበሉ እርግጠኛ አይደለችም ድንገት የመጣ እንደሆነ እያለች ከመሳሳቀቅ
አልዳነችም፡፡

እስቻለው ደግሞ ያኮረፈው ወይም የሚያኮርፈው ሰው ስለሌለ ቤቴ ሰላም ይሁን እንጂ እዕምሮው ግን እረፍት አጥቷል። ዓይኖቹም ተለያይተዋል። በአካል አልጋው ላይ ተኝቶ ሀሳቡ ያለው በሸዋዬ ቤት ወስጥ ነው፡፡
በልሁና መርዕድ የነገሩት የሽዋዬና የሔዋን የተበላሸ ግንኙነት የጭንቁ ሁሉ መነሻ ነው። በዚያ ላይ ወደዚያ ቤት ድርሽ እንዳይል ሔዋን በታፈሡ በኩል ልካበት
👍7
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሰባት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

...እንዲህ እንዳይመስሉሽ። ኸግር እስተራስሽ እያገላበጡ ነው ሚያዩሽ።ቄንጥ ሲያወጡ አይጣል ነው” ሲሉ መከሯት።

“እሚታዬ ልቤ ፈራ” አለቻቸው፣ እጆቿን እያፍተለተለች።

“ምን ሚያስፈራ ነገር አለ?” አሉ፣ ቆጣ ብለው። ለራሳቸው፣ እንደዛ
ቆፍጣና ምትመስለኝ ልዥ ምን ሆነች? ማታውቀው ቦታ ስለምትኸድ ነው? አሉና ለእሷ፣ “አብሬሽ ማዶል እንዴ ምመጣው? ንጉሥ የሆኑ እንደሁ ልዣችንን እንዳው ዝም ብለን ምንሰድ ይመስልሻል? ጐንደርንም ቢሆን አገላብጨ ነው ማውቃት። ጃንሆይ ሳይነግሡ በፊት... ነፍሳቸውን ይማርና ኸነእንኰዬ አባት ጋር ኑረናል። ጃንሆይ ኸነገሡ በኋላ አልኸድኹም እንጂ” አሏት።

“አብረሽኝ ምትመጪ ባትኾኚ ምን ይውጠኝ ኑሯል?” ብላ፣አንገታቸው ሥር ገብታ ሳይታሰብ ተንሰቀሰቀች። ውስጥ ውስጡን
ያስለቀሳት ግን ከጥላዬ መለያየቷ ነው።

“ደሞ ለክፉ ሆነ ለደግ ግዝየ ሚሆን ወልደልዑልን የመሰለ ወንድም አለሽ። ስንኳን ላንቺ ለእህቱ፣ አላየሽም እንዴ ላገር ሲተርፍ? አርከሌድስም አለ። ልዤ ነው ብዬ ማዶል ። አንቺም ብትሆኚ ታውቂያሽ እንዴት ብርቱና ታማኝ እንደሆነ። እንደ ኒቆላዎስስ ቢሆን... ጋሻና መከታ እንደሚሆንሽ አንቺም ታቂያለሽ” አሉ፡ ደረታቸውን መታ፣ አንገታቸውን ነቀነቅ አድርገው።

ምንጊዜም ቢሆን ስለሚወዱት ታናሽ ወንድማቸው ስለኒቆላዎስ
ሲያወሩ ደስ ይላቸዋል፤ ይኮሩበታል ። ቀጠለና፣ “አጎትሽ እሽቴም አለ። ደሞስ ያጎቶችሽ ልዦች ጌታ፣ አውሳቢዮስና፣ ነጮ አሉ ማዶል እንዴ? የወገን ጥላ አያሳጣኝ ማለት ነው” እያሉ እንባዋን በነጠላቸው ከፊቷ
ላይ ጠራረጉላት።

“ግና የቤተመንግሥት ወግ ኸየት አባቴ አውቄ?” አለች።

“አንቺ ደሞ ያልቸገረሽን። ወጉንስ እኼው እያስተማርሁ ማዶል
እንዴ? ሌላውን ደሞ ግዝየው ሲደርስ ትማሪያለሽ።”

“እሚታዬ፣ ቤተመንግሥት ልገባ?”

“ቤተመንግሥት ለመግባት ምን ያንስሻል? አጥንተ ጥሩ... ያውስ
የንጉሥ ዘር ማዶለሽ? አባትሽስ ቢሆኑ የደንብያው ባላባት የአቤቴ
ተክለሃይማኖት ልዥ ማዶለ? መልክስ ቢሆን ማን ደረሰብሽ? ቀይ ሰው መልክ አይፈጅም ይላሉ፤ አንቺ ፈጅተሻል። ቅላትሽ እኮ የኔና የናትሽ ነው። እንዳባትሽ ጠይም ብትሆኚ ኑሮኮ ምን የመሰለች ጠይም አሳ መሳይ ትሆኚ ነበር። ምግባርና ብሩህ አይምሮም አክሎልሻል።
ለዝህም እኮ ነው ጃንሆይ የመረጡሽ። እቴ ኸንግዲህ ማቄን ጨርቄን የለም፤ መኸድ ብቻ ነው።”

“ልጄ ዕድል ነው። ተሰጥቶሽ ነው። ደግ ሁኖልሻል፤ ሁሉን
አብዝቶልሻል” አሏት፣ እስከዛ ድረስ እናታቸው የሚሉትንና
የሚያደርጉትን በፀጥታ ሲታዘቡ የቆዩት እናቷ።

“የምን ዕድል ነው ምትይ? ዕድል ከሰማይ ይወድቃል? እንዲሁ
ነው እንዴ ንጉሡ ልዣችንን ሊያገቡ የፈለጉ? ልዣችን ሚገባትን ነው ያገኘችው። በደም ግባቷ፣ በብሩህ አይምሮዋ፣ በመልካም ምግባሯና
ጎንበስ ቀና ብላ ስላስታመመቻቸው ነው ንጉሡ ለንግሥትነት የመረጧት፣ ንግሥትነት እንደሚገባት አይተው መዝነው ነው እንጂ እንደ መደዴው ለውበቷ ወይም እንደገበሬ ለሙያዋ ብቻ ብለው
አይደለም።” ዮልያና ልጃቸውን ቆጣ አሉ።

“መቸም ደመ ግቡ ሁሉ... ያስታመመ ሁሉ ንጉሥ ባል አያገኝም። እንዳው የዕድል ነገር ይገርማል። እኼን ማን አሰበው?” አሉ፣ የእናታቸውን አፍ ብዙም የማይዳፈሩት ወይዘሮ እንኰዬ።

“የኔ ልዥ ገና ንግሥት እሌኒን አረግሻለሁ” አሉ፣ አያትየው።

“እሳቸውን መሆን እንዴት ይቻለኛል?”

“አንቺ ደሞ... እሌኒን ትሆኛለሽ ስልሽ እኮ ልክ እንደሳቸው ሁኚ
ማለቴም ማዶል። እንዴት እንደምኖሪ ማወቅ ያንቺ ፈንታ ነው። ሁሉ እየቅል ነው።”

ለጊዜው የአያቷ ምክር በመጠኑም ቢሆን አረጋጋት።

በነጋታው መንገደኛ ናትና ጥሩ እንቅልፍ እንድታገኝ እናትና አያት
ትኩስ ወተት በማር አጠጥተው አስተኟት። እሷ ግን እንደ ትናንቱ
ሁሉ ዛሬም እንቅልፍ በዐይኗ ሳያልፍ ፍርሐት፣ ጥላዬን ለመጨረሻ ጊዜ ሳታየው የመሄድ ጭንቀት፣ ብሎም ቀስ እያለ ውስጧ እየተጫረ የመጣው ቤተመንግሥት የመግባት ጉጉት መሳይ ነገር ሲፈራረቁባት
ሌሊቱ እንደመንጋት አለ።

ዶሮ ሲጮህ ቀሰቀሷትና ተጣጠበች። ቁርስ ብዪ ብለው ሲያቀርቡላት ግን ተናነቃት። እናቷ፣ “ትንሽ አፍሽ አርጊ፤ ምንገድ ባዶ አፍ አይከድም” እያሉ ሊያግባቧት ሞከሩ። እሷ ግን እንኳን እናቷን፣
አባቷን፣ ወንድሟን፣ ጥላዬንና የቤት አገልጋዮቹን ቋራን ራሱን ጥላ መሄዱ ዳገት ሆነባት።

ዐይኗ እንባ አቀረረ።

የእናቷን ፊት የተጫጫነውን ሐዘን ስታይ፣ ዐይኖቿ ጥግ ተጠልሎ
የነበረው እንባዋ ወደ ጉንጮቿ ኮለል አለ። እናቷ እስከዛ ሰዐት አምቀውት የነበረውን እንባ እንደ ድንገተኛ ዝናብ አወረዱት። ጉልበታቸው ላይ ተደፍታ፣ “እነየ መተሽ አታይኝም?” ስትላቸው፣ ትከሻዋ ላይ ተደፍተው
እዬዬ ሲሉ እሷም ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።

አያትየው ልጃቸውን፣ “እንደማበርታት ጭራሽ ታባቢያታለሽ?” ብለው ቆጣ አሉና፣ ወለተጊዮርጊስን ትከሻዋን ነካ አድርገው፣ “ተይ እኮ የኔ ልዥ፣ በቅጡ እንዳልተኛሽ ስንኳ ያስታውቃል። ምንገደኛ ነሽ። ገና
ምንገዱ ሚያጠወልግሽ ይበቃል። ፊትሽን አታበላሺ። የቀባሁሽንም
ኩል እንባሽ አጠበው። በቃ እንድች ብለሽ እንዳታለቅሺ። በይ ነይ” አሉና ፊቷን በእጃቸው አባብሰው፣ እንደገና ሥር ኩል ዐይኗ ላይ አደረጉላት።

እንግዶቹ እህል አፋቸው ካደረጉ በኋላ፣ ለመሄድ ወደ ውጭ ሲወጡ በአቅራቢያ ያለ ቤተዘመድ፣ የወለተጊዮርጊስን ጐንደር መሄድ የሰማ
ጎረቤትና ጓደኞቿ ተሰብስበዋል። ወለተጊዮርጊስ የአያቷን ረጅም የሐር ቀሚስ ለብሳ፣ ከቀሚሱ ሥር በሐር ክር ጫፉ የተጠለፈና ተረከዟን ጠበቅ አድርጎ የያዘ ሱሪ ታጥቃ፣ በአያቷ ወርቅ አሸግና ብቅ ስትል፣እንግዶቹ ትንግርት እንጂ እውን ሰው የሚያዩ አልመስል አላቸው።

ዘመድና ጎረቤት ግቢውን በዕልልታ ሲያደምቀው፣ የወለተጊዮርጊስ ጓደኞች ዐይናቸው እያየ በጓደኛቸው ሕይወት ውስጥ ያልገመቱት
ዓይነት ለውጥ መምጣቱ፣ ካጠገባቸው ተነስታ ለንግሥትነት መታጨቷ አስደነቃቸው። በዓመት መለወጫ ቀን አደይ አበባ እያስቀጠፈች፣ከቤት ቤት በድፍረት ይዛቸው እየዞረች፣ የምታስተባብራቸውና እንደ
መሪያቸው የሚቆጥሯት ጓደኛቸው ከመሃከላቸው በመለየቷ አዘኑ፤
በታላቁ ዕድሏ ቀኑ፣ ተደሰቱ። በዚኹም ድብልቅልቅ ስሜት መሃል ግን በመለያየታቸው አለቀሱ።

ግራዝማች የልጃቸውን ውበት ገና ያን ቀን ያዩ ይመስል ዐይናቸው
ውሃ አቆረ። እሷን ለመሰናበት ማልደው የመጡት ታላቅ ወንድሟ
ወልደልዑል፣ አጎቷ አርከሌድስ፣ የዮልያና ወንድም ኒቆላዎስ፣ አጎቷ
እሽቴና የአጎቷ ልጆች አውሳቢዮስ፣ ጌታና ነጮ በኩራት ተመለከቷት።
ንጉሥ ቤት ነውና የምትገባው በልባቸው ዙርያ የተስፋ ድር አደራችበት።

እናትና ልጅ በሠሩት ጥበብ ተደንቀው ዐይን ለዐይን ተያዩ።
አያትየዋ ያ ሁሉ እንባ ምልክት ስንኳ አልተወም፡፡ ድንቅ እኒያ
ደርሰው ትከሻ ሚሰጡ የጐንደር ወይዛዝርት እንግዲኽ ዐይናቸው
ይደፍርስ አሉ።

ለሱ አይቅርበት አሉ እናትየው፣ እንባቸውን በነጠላቸው እየጠራረጉ።

ጎረቤትና ቤተዘመድ ምርቃት ሲያዘንብላት፣ ዕልል ሲልላት፣ ጓደኞቿ የደስታ እንባ ሲራጩላት፣ ምቀኛው ግን፣ “ታመው የተኙ ግዝየ መዳኒት አርጋባቸው እንደሁ እንጂ ውነት አሁን ንጉሡ…” እያለ ወሻከተ።
👍11