#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ሁለት ዓመታት እንደ ዋዛ አለፉ። በነዚህ ሁለት አመታት ውስጥ የአማረችና የጌትነት ግንኙነት ደረጃ በውል አልታወቀም። አማረች በሁለተኛው አመት መጀመሪያ ላይ የእናቷን ቡናማ ቀለም ያላት ዳትሰን መኪና
ይዛ መምጣት ጀመረች። ይሄ ሁኔታ ደግሞ በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ይበልጥ አጎላበትና ድህነቱ ተፅእኖ ያሳድርበት ጀመር፡፡ በልቡ የተሰማውን ስሜት በአንደበቱ ለመግፅ ከአቅም በላይ መንጠራራት እየመሰለው ፈራት፡ የግንኙነት ደረጃቸው እስከምን ድረስ እንደሆነ እሷ እንድትነግረው ፈለገ፡፡ እሷ ደግሞ ግፊቱ ከሱ እስከሚመጣ ድረስ ጠበቀችው፡፡
ሁለቱም ከሱ ይምጣ ከሷ ይምጣ ሲባባሉ ጊዜው ነጎደ። አማረች በቤት ውስጥ መነጫነጭ ጀመረች፡፡ እሷ ስትበሳጭ እናቷ አብረዋት ጭንቅ ጥብብ ይላሉ፡፡ “ምን ሆነሻል ልጄ?እስቲ የሆንሽውን ንገሪኝ?" ይሏታል።
ምክንያቱን እሷም በውል አታውቀውም፡፡ ይሄ ንጭንጫ ከጌትነት ጋር ስትገናኝ ድራሹ ይጠፋል፡፡ ደስተኛ ሆና አብራው ትቆያለች። ከሱ ስትለይ ደግሞ ያው ፀባይዋ ተመልሶ ይመጣል። ቀስ በቀስ ፍቅር እንደጀማመራት ተረዳች። ሲሽሻት በዘዴ የቀረበችው እሷ ትሁን እንጂ አፍ አውጥታ አፈቀርኩህ ብላ ለመጠየቅ ተቸገረች። ሴት ልጅ ለፍቅር ስትጠየቅ እንጂ ስትጠይቅ አልተለመደምና እንዴት አድርጋ ስሜቷን እንደምትገልጽለት
ከመጨነቅ የተነሳ የሌለባትን ፀባይ ማሳየት ጀመረች።
ዩኒቨርሲቲው ሊዘጋ ተቃርቧል። ጌትነትና አማረች ፈተና ጨርሰው
ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ ትምህርት ቤት ከተዘጋ ደግሞ በየቀኑ መገናኘት ሊቀር ነው። አልፎ አልፎ ስልክ መደዋወሉ ብቻ ብዙም ፋይዳ የለውም፡፡ በየግላቸው በናፍቆት ሲጠበሱ መክረማቸው ነው፡፡
ቢያንስ ዐይን ለዐይን እየተያዩ ረሃባቸውን ለመወጣት ሰበባቸው ትምህርት ቤት ነበረችና መዘጊያዋ ሲደርስ ሁለቱም ተጨነቁ፡፡ በተለይ አማረች ይሄው ለተወሰነ ጊዜ የመለያየቱ ነገር በይበልጥ አስጨንቋት ሙሉውን ሌሊት በሀሳብ ስትገላበጥ አነጋች፡፡ ጌትነትን ወኔ ለማላበስ ምን ማድረግ እንዳለባት ዕቅድ ስታወጣ ፕሮግራም ስትነድፍ አደረች።
"ጌትሽ ትምህርት ቤት ከመዘጋቱ በፊት በፈተና ሲጨነቅ የከረመ አእምሯችንን ትንሽ ለማዝናናት ወደ ላንጋኖ ብንሄድ ምን ይመስልሃል?' ከፊቷ ፈገግታ ባይጠፋም በልቧ እምቢ ብሎ እንዳያሳፍረኝ አምላኬ አደራህን እያለች ነበር፡፡
ያንን ከአማረች የተሰነዘረ የተቀደሰ ሃሳብ ሲሰማ የጌትነት ልብ በደስታ
ወከክ አለች። በተለይ የሀብታም ልጅ መሆኗን እየተረዳ ከመጣ በኋላ "እንድታስጠናኝ እንጂ እኩያህ ነኝ ወይ? እንዴት ያለአቅምህ ትንጠራራለህ? የሳቀና የተጫወተ ሁሉ አፈቀረ ማለት አይደለም የድሃ ልጅ!"ብላ ቅስሜን ብትሰብረውስ? የሚል ፍርሃት ሸምቅቆ ይዞት ነበር። ተንቀዥቅዦ ውርደት ከመቅመስ ይልቅ የሷን ፍላጎት ከሷ ከመጠበቅ ውጪ
አማራጭ የለውም ብሎ ወስኖ በነበረበት ሰዓት ይሄንን ሲመኘው የኖረውን ሰናይ ሃሳብ ስታቀርብለት አላንገራገረም፡፡
"ደስታውን አልችለውም አማረች ግን መቼ?" አላት፡፡ቅዳሜ ዕለት የዋና ልብስ እንዳትረሳ!... "
ቅዳሜ ከጠዋቱ ሁለት ስዓት ላይ ለገሀር እንዲጠብቃት ተቀጣጠሩ
ቅዳሜ ላንጋኖ ደርሰው ተዝናንተው በእለቱ ወደ አዲስ አበባ ሊመለሱ
እንደማይችሉ የታወቀ ነው። ነገሩ አዳር እንዳለበት በልቡ ገመተና ለማንኛውም ብሎ ለእህቱ ነገራት፡፡
"ዘይንዬ ነገ ወደ ላንጋኖ ሳልሄድ አልቀርም ምናልባት ካደርኩ ከጎረቤት የሚያስተዳድርሽ ሰው ልፈልግ?" አላት፡፡
"ወንድም ጋሼ ለምን አብሬህ አልሄድም?” አለችው፡፡ ደንገጥ አለ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ እህቱ ያቀረበችለትን ጥያቄ ላለመቀበልና ለመዋሸት ተገደደ::“ዘይንዬ ጉዞው ከመስሪያ ቤታችን ሰራተኞች ጋር ስለሆነ አይመችም::
በሌላ ጊዜ ፕሮግራም ይዘን እንሄዳለን እሺ?" አለና ተለማመጣት::"እሺ ወንድም ጋሼ ለእትዬ ጤናዳም እነግራቸውና ከሎሚ ጋር አብሬ አድራለሁ" የዕድሜ አቻ የጎረቤታቸውን ልጅ ማለቷ ነው፡፡
በከፍተኛ የንፋስ ሞገድ የታጀበ ውርጭ እንደ ጅራፍ እየተጋረፈ ይዘንባል። የብዙዎቹን ሰዎች ጃንጥላ የሚገለብጥ የሚያፏጭ ንፋስ ከታክሲ ላይ ወርዶ እየሮጠ ሄደና ከአንድ ህንፃ ስር ተጠለለ፡፡ ከቀጠሮው በፊት ስላሳ ደቂቃ ቀድሟል፡፡ የቀጠሮው ሰዓት ሊደርስ አምስት ደቂቃ ሲቀረው
ዐይኖቹን አሻግሮ ወረወረና ከወዲያ ማዶ ብቅ ባለችው ቡናማ ዳትሰን መኪና ላይ አሳረፋቸው። አማረች ከቀጠሮው በፊት አምስት ደቂቃ ቀደም ብላ መድረሷ ነበር። እየሮጠ ሄደ። ተገናኙ። ሞቅ ያለ ሰላምታ ተለዋወጡ። "ጎበዝ ሰዓት አክባሪ!" የጋቢናውን በር እየከፈተችለት በቀጠሮ አክባሪነቱ አድናቆቷን በፈገግታ ገለፀችለት፡፡
“አመሰግናለሁ" እሱም እየሳቀ ነበር፡፡ መቼም አማረች የጨዋታ ቅመም ነች፡፡ እንኳንስ ወደ ሽርሽር ቦታ ለመዝናናት እየሄዱ ይቅርና በአስጨናቂው ጥናት ላይም ቢሆን አፍ ታስከፍታለች። በተለይ የዛሬው ጉዞ የረጅም ጊዜ ጓደኝነታቸው ወደ ላቀ ደረጃ የሚሸጋገርበት አጋጣሚ ነውና
ፍፁም ነፃነት እንዲሰማው የተቻላትን ሁሉ ለማድረግ ወስናለች። ጉዞ ተጀመረና ቀስ እያሉ እየተዝናኑ አዋሳ ደረሱ። አዳር በቀለ ሞላ ሆቴል ነበር። ራታቸውን በልተው ሲጨዋወቱ አመሹ :: የተያዘው አልጋ
ሁለት ነው፡፡
“አንድ አልጋ ይበቃናል ለምን ለሁለት አልጋ ይከፈላል የሚል የተቀደሰ ሃሳብ ያቀረበ አልነበረም" መኝታ ክፍላቸው ጎን ለጎን ቢሆንም በመካከሉ የግንብ ግርዶሽ አለ፡፡ በይሉኝታና በፍራቻ ግርዶሽ ላይ የግንቡ ግርዶሽ ተጨምሮበት ለሊቱን ሙሉ ተለያይተው ማደራቸው ነው፡፡
የቅርብ ሩቅ... በመንፈስ እሱ ወደ እሷ እሷም ወደ እሱ እየሄዱ ቢፈላ
ለጉም ሃሳባቸውን በግልፅ አውጥተው መነጋገር አልቻሉምና መድረሻቸውን ያላወቁ መንታ መንገድ ላይ የቆሙ መንገደኞች ሆኑ። በስሜትዐረጅም ርቀት የተጓዙ ነገር ግን በይሉኝታ ልጓም ተሽብበው የተያዙ ተፈላላጊዎች። አማረች የዛሬው ግብዣዋ የሽርሽር ብቻ ሳይሆን የፍቅር ግብዣንም የሚያጠቃልል መሆኑን ከሁኔታዎች ይገነዘባል የሚል እምነት ነበራት፡፡ እሱ ደግሞ ይቺ ቆንጆ የሀብታም ቤተሰብ ልጅ በትምህርት ቤት ውስጥ በተመቻት ጊዜና ቦታ ሁሉ እየተገኘ የሚያስጠናትን እንደ ውለታ ቆጥራ ያንን ውለታ ለመክፈል የጋበዘችው እንጂ የፍቅር ግብዣ ጭምር መሆኑን አላወቀምና ፈራት፡፡ እሱ እንደሚያስበው በፍቅር አስባው ካልሆነ ሊያስቀይማት ሊጣላት ነው ማለት ነው፡፡ ይህንን ደግሞ
አልፈለገውም፡፡ ዐይኖቹ ያንን ልብ የሚያጠፋ ውበቷን በቅርበት እያስተዋሉ እንዲያደንቁ፣ ጆሮዎቹ ያንን የማይጠገብ ጨዋታዋን እንዲያደምጡ፣ አፍንጫው ያንን ጣፋጭ መአዛዋን ያለምንም ገደብ እያጣጣመ በሀሴት ይሞላ ዘንድ የተፈቀደለት ሰው ነውና ቢያንስ ቢያንስ ሌላው ባይሳካለት እንኳ እሷነቷን ጥሬ ጓደኛነቷን ላለማጣት ራሱን ቆጠበ፡፡ ሲያያት
ምራቁን የሚውጠው ወንድ ሁሉ ያልተፈቀደለትን እሱ ተፈቅዶለታል።
ይሄ ሁሉነቷ ገደብ ያልተደረገበት ሰው ነውና ከራሷ እስካልመጣ ድረስ ተሽቀዳድሞ ነገር ማበላሸት ይሆናል በሚል ፍራቻ ዝምታን መርጧል።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ሁለት ዓመታት እንደ ዋዛ አለፉ። በነዚህ ሁለት አመታት ውስጥ የአማረችና የጌትነት ግንኙነት ደረጃ በውል አልታወቀም። አማረች በሁለተኛው አመት መጀመሪያ ላይ የእናቷን ቡናማ ቀለም ያላት ዳትሰን መኪና
ይዛ መምጣት ጀመረች። ይሄ ሁኔታ ደግሞ በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ይበልጥ አጎላበትና ድህነቱ ተፅእኖ ያሳድርበት ጀመር፡፡ በልቡ የተሰማውን ስሜት በአንደበቱ ለመግፅ ከአቅም በላይ መንጠራራት እየመሰለው ፈራት፡ የግንኙነት ደረጃቸው እስከምን ድረስ እንደሆነ እሷ እንድትነግረው ፈለገ፡፡ እሷ ደግሞ ግፊቱ ከሱ እስከሚመጣ ድረስ ጠበቀችው፡፡
ሁለቱም ከሱ ይምጣ ከሷ ይምጣ ሲባባሉ ጊዜው ነጎደ። አማረች በቤት ውስጥ መነጫነጭ ጀመረች፡፡ እሷ ስትበሳጭ እናቷ አብረዋት ጭንቅ ጥብብ ይላሉ፡፡ “ምን ሆነሻል ልጄ?እስቲ የሆንሽውን ንገሪኝ?" ይሏታል።
ምክንያቱን እሷም በውል አታውቀውም፡፡ ይሄ ንጭንጫ ከጌትነት ጋር ስትገናኝ ድራሹ ይጠፋል፡፡ ደስተኛ ሆና አብራው ትቆያለች። ከሱ ስትለይ ደግሞ ያው ፀባይዋ ተመልሶ ይመጣል። ቀስ በቀስ ፍቅር እንደጀማመራት ተረዳች። ሲሽሻት በዘዴ የቀረበችው እሷ ትሁን እንጂ አፍ አውጥታ አፈቀርኩህ ብላ ለመጠየቅ ተቸገረች። ሴት ልጅ ለፍቅር ስትጠየቅ እንጂ ስትጠይቅ አልተለመደምና እንዴት አድርጋ ስሜቷን እንደምትገልጽለት
ከመጨነቅ የተነሳ የሌለባትን ፀባይ ማሳየት ጀመረች።
ዩኒቨርሲቲው ሊዘጋ ተቃርቧል። ጌትነትና አማረች ፈተና ጨርሰው
ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ ትምህርት ቤት ከተዘጋ ደግሞ በየቀኑ መገናኘት ሊቀር ነው። አልፎ አልፎ ስልክ መደዋወሉ ብቻ ብዙም ፋይዳ የለውም፡፡ በየግላቸው በናፍቆት ሲጠበሱ መክረማቸው ነው፡፡
ቢያንስ ዐይን ለዐይን እየተያዩ ረሃባቸውን ለመወጣት ሰበባቸው ትምህርት ቤት ነበረችና መዘጊያዋ ሲደርስ ሁለቱም ተጨነቁ፡፡ በተለይ አማረች ይሄው ለተወሰነ ጊዜ የመለያየቱ ነገር በይበልጥ አስጨንቋት ሙሉውን ሌሊት በሀሳብ ስትገላበጥ አነጋች፡፡ ጌትነትን ወኔ ለማላበስ ምን ማድረግ እንዳለባት ዕቅድ ስታወጣ ፕሮግራም ስትነድፍ አደረች።
"ጌትሽ ትምህርት ቤት ከመዘጋቱ በፊት በፈተና ሲጨነቅ የከረመ አእምሯችንን ትንሽ ለማዝናናት ወደ ላንጋኖ ብንሄድ ምን ይመስልሃል?' ከፊቷ ፈገግታ ባይጠፋም በልቧ እምቢ ብሎ እንዳያሳፍረኝ አምላኬ አደራህን እያለች ነበር፡፡
ያንን ከአማረች የተሰነዘረ የተቀደሰ ሃሳብ ሲሰማ የጌትነት ልብ በደስታ
ወከክ አለች። በተለይ የሀብታም ልጅ መሆኗን እየተረዳ ከመጣ በኋላ "እንድታስጠናኝ እንጂ እኩያህ ነኝ ወይ? እንዴት ያለአቅምህ ትንጠራራለህ? የሳቀና የተጫወተ ሁሉ አፈቀረ ማለት አይደለም የድሃ ልጅ!"ብላ ቅስሜን ብትሰብረውስ? የሚል ፍርሃት ሸምቅቆ ይዞት ነበር። ተንቀዥቅዦ ውርደት ከመቅመስ ይልቅ የሷን ፍላጎት ከሷ ከመጠበቅ ውጪ
አማራጭ የለውም ብሎ ወስኖ በነበረበት ሰዓት ይሄንን ሲመኘው የኖረውን ሰናይ ሃሳብ ስታቀርብለት አላንገራገረም፡፡
"ደስታውን አልችለውም አማረች ግን መቼ?" አላት፡፡ቅዳሜ ዕለት የዋና ልብስ እንዳትረሳ!... "
ቅዳሜ ከጠዋቱ ሁለት ስዓት ላይ ለገሀር እንዲጠብቃት ተቀጣጠሩ
ቅዳሜ ላንጋኖ ደርሰው ተዝናንተው በእለቱ ወደ አዲስ አበባ ሊመለሱ
እንደማይችሉ የታወቀ ነው። ነገሩ አዳር እንዳለበት በልቡ ገመተና ለማንኛውም ብሎ ለእህቱ ነገራት፡፡
"ዘይንዬ ነገ ወደ ላንጋኖ ሳልሄድ አልቀርም ምናልባት ካደርኩ ከጎረቤት የሚያስተዳድርሽ ሰው ልፈልግ?" አላት፡፡
"ወንድም ጋሼ ለምን አብሬህ አልሄድም?” አለችው፡፡ ደንገጥ አለ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ እህቱ ያቀረበችለትን ጥያቄ ላለመቀበልና ለመዋሸት ተገደደ::“ዘይንዬ ጉዞው ከመስሪያ ቤታችን ሰራተኞች ጋር ስለሆነ አይመችም::
በሌላ ጊዜ ፕሮግራም ይዘን እንሄዳለን እሺ?" አለና ተለማመጣት::"እሺ ወንድም ጋሼ ለእትዬ ጤናዳም እነግራቸውና ከሎሚ ጋር አብሬ አድራለሁ" የዕድሜ አቻ የጎረቤታቸውን ልጅ ማለቷ ነው፡፡
በከፍተኛ የንፋስ ሞገድ የታጀበ ውርጭ እንደ ጅራፍ እየተጋረፈ ይዘንባል። የብዙዎቹን ሰዎች ጃንጥላ የሚገለብጥ የሚያፏጭ ንፋስ ከታክሲ ላይ ወርዶ እየሮጠ ሄደና ከአንድ ህንፃ ስር ተጠለለ፡፡ ከቀጠሮው በፊት ስላሳ ደቂቃ ቀድሟል፡፡ የቀጠሮው ሰዓት ሊደርስ አምስት ደቂቃ ሲቀረው
ዐይኖቹን አሻግሮ ወረወረና ከወዲያ ማዶ ብቅ ባለችው ቡናማ ዳትሰን መኪና ላይ አሳረፋቸው። አማረች ከቀጠሮው በፊት አምስት ደቂቃ ቀደም ብላ መድረሷ ነበር። እየሮጠ ሄደ። ተገናኙ። ሞቅ ያለ ሰላምታ ተለዋወጡ። "ጎበዝ ሰዓት አክባሪ!" የጋቢናውን በር እየከፈተችለት በቀጠሮ አክባሪነቱ አድናቆቷን በፈገግታ ገለፀችለት፡፡
“አመሰግናለሁ" እሱም እየሳቀ ነበር፡፡ መቼም አማረች የጨዋታ ቅመም ነች፡፡ እንኳንስ ወደ ሽርሽር ቦታ ለመዝናናት እየሄዱ ይቅርና በአስጨናቂው ጥናት ላይም ቢሆን አፍ ታስከፍታለች። በተለይ የዛሬው ጉዞ የረጅም ጊዜ ጓደኝነታቸው ወደ ላቀ ደረጃ የሚሸጋገርበት አጋጣሚ ነውና
ፍፁም ነፃነት እንዲሰማው የተቻላትን ሁሉ ለማድረግ ወስናለች። ጉዞ ተጀመረና ቀስ እያሉ እየተዝናኑ አዋሳ ደረሱ። አዳር በቀለ ሞላ ሆቴል ነበር። ራታቸውን በልተው ሲጨዋወቱ አመሹ :: የተያዘው አልጋ
ሁለት ነው፡፡
“አንድ አልጋ ይበቃናል ለምን ለሁለት አልጋ ይከፈላል የሚል የተቀደሰ ሃሳብ ያቀረበ አልነበረም" መኝታ ክፍላቸው ጎን ለጎን ቢሆንም በመካከሉ የግንብ ግርዶሽ አለ፡፡ በይሉኝታና በፍራቻ ግርዶሽ ላይ የግንቡ ግርዶሽ ተጨምሮበት ለሊቱን ሙሉ ተለያይተው ማደራቸው ነው፡፡
የቅርብ ሩቅ... በመንፈስ እሱ ወደ እሷ እሷም ወደ እሱ እየሄዱ ቢፈላ
ለጉም ሃሳባቸውን በግልፅ አውጥተው መነጋገር አልቻሉምና መድረሻቸውን ያላወቁ መንታ መንገድ ላይ የቆሙ መንገደኞች ሆኑ። በስሜትዐረጅም ርቀት የተጓዙ ነገር ግን በይሉኝታ ልጓም ተሽብበው የተያዙ ተፈላላጊዎች። አማረች የዛሬው ግብዣዋ የሽርሽር ብቻ ሳይሆን የፍቅር ግብዣንም የሚያጠቃልል መሆኑን ከሁኔታዎች ይገነዘባል የሚል እምነት ነበራት፡፡ እሱ ደግሞ ይቺ ቆንጆ የሀብታም ቤተሰብ ልጅ በትምህርት ቤት ውስጥ በተመቻት ጊዜና ቦታ ሁሉ እየተገኘ የሚያስጠናትን እንደ ውለታ ቆጥራ ያንን ውለታ ለመክፈል የጋበዘችው እንጂ የፍቅር ግብዣ ጭምር መሆኑን አላወቀምና ፈራት፡፡ እሱ እንደሚያስበው በፍቅር አስባው ካልሆነ ሊያስቀይማት ሊጣላት ነው ማለት ነው፡፡ ይህንን ደግሞ
አልፈለገውም፡፡ ዐይኖቹ ያንን ልብ የሚያጠፋ ውበቷን በቅርበት እያስተዋሉ እንዲያደንቁ፣ ጆሮዎቹ ያንን የማይጠገብ ጨዋታዋን እንዲያደምጡ፣ አፍንጫው ያንን ጣፋጭ መአዛዋን ያለምንም ገደብ እያጣጣመ በሀሴት ይሞላ ዘንድ የተፈቀደለት ሰው ነውና ቢያንስ ቢያንስ ሌላው ባይሳካለት እንኳ እሷነቷን ጥሬ ጓደኛነቷን ላለማጣት ራሱን ቆጠበ፡፡ ሲያያት
ምራቁን የሚውጠው ወንድ ሁሉ ያልተፈቀደለትን እሱ ተፈቅዶለታል።
ይሄ ሁሉነቷ ገደብ ያልተደረገበት ሰው ነውና ከራሷ እስካልመጣ ድረስ ተሽቀዳድሞ ነገር ማበላሸት ይሆናል በሚል ፍራቻ ዝምታን መርጧል።
👍4
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...የተቃራኒ ፆታ ሱስ እስከሚያንጠራራው ድረስ ተጨነቀ ጭኖቹ በጭኖቿ መካከል ነበሩ አልቻለም፡፡ ከንፈሮቿን እየሳመ ቀስ ብሎ የሆነ ነገር በጆሮዋ ሹክ አላት፡በዚህ ጊዜ አማረች በጣም ተበሳጨች፡፡
ሂድ! ባለጌ! ወንዶች ስትባሉ ይሄው ናችሁ። ፍቅር ሲሏችሁ ዘላችሁ የምትሰፍሩት እዚያ ላይ ነው፡፡ ፍቅር ማለት እሱ ብቻ ነው የሚመስላችሁ፡፡ እኔኮ አንተን ለብዙ ነገር ነበር የምመኝህ፡፡ እንደዚህ አይነት ሰው አትመስለኝም ነበር፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ልጃገረድ መሆኔን ማወቅ አለብህ!ባንተ ዘንድ ረከስኩ እንጂ ውድ ነበርኩ፡፡ ሽርሙጣ አይደለሁም፡፡ ገባህ?!" ጮኽችበት። ደነገጠ።
“እንደሱ አይደለም የኔ ቆንጆ። በሌላ መልክ አይቼሽ አይደለም፡፡ በጣም ስለምወድሽ ነው በጣም አማረች.." ቃላት አጥረውት ተጨነቀ፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ስውነቱ በስሜት ግሏል። ነዷል። "እኔኮ እኔኮ . እወድሻለሁ.... እስከ መጨረሻው የኔ እንድትሆኚ እፈልጋለሁ" አፉ ሲወተውት
ጣቶቹ ባልተፈቀደላቸው ድንበር ዘለው ገብተው አሰሳ ማካሄዳቸውን አላቋረጡም ነበር፡፡ ድርጊቱ አማረችን የበለጠ አናደዳት።
"ልቀቀኝ! ልቀቀኝ!" መንጭቃው ተነሳች። "እኔው ነኝ ወረዳዋ! አንተ
ምን አደረክ? በለሊቱ በርህን አንኳኩቼ የገባሁት እኔ! ጥፋተኛዋ እኔ!" ፀጉሯን እየነሰነሰች….ያንን ውብ ዳሌዋን እያውረገረገች ከአልጋው ላይ ወረደች፡፡ በድንጋጤ ዐይኖቹ ፈጠጡ። የሚናገረው ጠፍቶበት በፈፀመው የብልግና ድርጊት ራሱን ወቀሰ፡፡ በስሜት ግፊት ተሸንፎ ከፍላጎትዋ ውጭ በፈፀመው ድርጊት ተፀፀተ።
ቆይ!!. . ቆይ! . ቆይ! " እጆቹን ዘርግቶ ተከትሏት ብድግ አለ።
“ሂድ!" በሩን አላትማ ወጣች።
“አማ.አማረች..አንዴ .ምን…. መሆንሽ ነው?ቆይ እስቲ..." ሲወራጭ የአልጋው ብረት ቅዝቃዜ እንደ ኤሌክትሪክ ነዘረውና ብንን አለ። ጭንቀቱ..
ቅዠቱ.. ላብ በላብ አድርጎት ነበር፡፡
“በስመአብ ወልድ!“ ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ ከለሊቱ ስምንት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ ቀስ ብሎ ያየውን ህልም ይመረምር ጀመር፡፡ ያንን የማይጨበጥ ጉም የማይዳሰስ ተስፋ መጨረሻው ባያምርም እቅፍ አድርጎ
በላይዋ ላይ እየተንፈላሰለ እንጆሪ ከንፈሮቿን የቀሰመበት ዓለም እንደ
ሰቀቀን ሆኖ አለፈ። ዐይኖቹን ጭፍን ክድን ጭፍን ክድን አደረጋቸው። መብራቱን አበራና ሁለቱንም ትራሶች ደራርቦ ከወገቡ በላይ ራቁቱን ሆነ፡ ዐይኖቹን ፊት ለፊቱ አማረችን በጋረደበት ግድግድ ላይ በንዴት ተክሎ በሀሳብ እሷ ክፍል ገባ፡፡ እንደ ንዴቱና እንደ ብሽቀቱ ቢሆን ኖሮ
ከዐይኖቹ የሚወረወሩት ጨረሮች ያንን የግንብ ግድግዳ የጤፍ መንፊያ ወንፊት ባደረጉት ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ እንቅልፍ በዐይኑ ሳይዞር ቀሪውን ጊዜ በመቀመጥና በመገላበጥ አሳለፈው፡፡ ጠዋት ቁርሳቸውን እዚያው በሉና በፕሮግራማቸው መሰረት ወደ ላንጋኖ ጉዞ ጀመሩ፡፡ ዛሬ አማረች
የዋና ተለማማጅና የህይወት አድን ሰራተኛ ፈላጊ ሆና ለመቅረብ አቅዳለች። ለዘዴዋ፡፡ ላንጋኖ ደርስው ለዋና ተዘጋጁ፡፡ አማረች ልብሷን አወላልቃ በውስጥ ሱሪ ብቻ ወደ ሃይቁ መጣች፡፡ ጌትነት ያንን ውብ ተክለ ቁመናዋን የሚያጓጓ ራቁት ገላዋን በውስጥ ሱሪ ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ
አየው። ልቡ ወደ ሰማይ ወጥታ እንደ እምቧይ ፈረጠች፡፡ ወደር የሌለው አፍ የሚያስከፍት ቅርፅ.. ስምንት ቁጥር ቁጭቁጭ.ያሉ ጡቶቿ ዐይኖቻቸውን አፍጠው ምራቃቸውን በሚውጡ ተመልካቾቿ ድርጊት ተቆጥተው እንደ ነብር ያበጡ ይመስላሉ። ጌትነት ዘወር ዘወር ብሎ ሲመለከት የበርካታ ዋናተኞች አፎች ተከፍተው መቅረታቸውን አስተዋለ። ቅንአት ቢጤ ቆነጠጠው...
"እውን የኔ ትሆኝ ይሆን ?"አለ በልቡ። ይሄንን ልቡ የተመኘውን ምኞት ዐይኑ እንዳያሳብቅበት ፈራና ለመሸፋፈን ጥረት አደረገ፡፡ ተወት ያደረጋት ለመምሰል ማዶ ማዶውን ማየት አበዛ... አማረች ደግሞ የጌትነትን አንጀት ለመብላት ስትል አንድ አላስፈላጊ ድርጊት ፈፀመች። ጡት ማስ
ያዣዋን በመጠኑ ዝቅ አደረገች። ማግኔት!!
"ጌትሽ ይሄኛው ጥልቅ ነው እኔ እዚህ አልዋኝም፡፡ እሰምጣለሁ። እዚ ቅርቡ ጋ ሄደን እንዋኝ?” ሰው ወደሌለበት አካባቢ በአገጭዋ እያሳየችው አካባቢውን ጠቆመችው። ወደዚያ እሷ ወዳለችው የሃይቁ ዳርቻ ተያይዘው ሄዱ፡፡ አማረች አዲስ ዋና ተማሪ ሆና ቁጭ አለች፡፡ ወይ አበሳው?!
ያንን መጠጋት የፈራውን እፍኝ የማይሞላ ወገቧን ይዞ ከፍ ዝቅ ወደ..ፊት ወደ ኋላ... እያደረገ ያለማምዳት ጀመር። በሷ እንቅስቃሴ አቅጣጫ
እየተመራች የሱም ልብ ከቦታዋ ለቃ እየተንከራተተች ነበር፡፡
ጌትነት የትናንትናው ህልም ዓለም ክፍል ሁለት እንዳይሆን ዐይኖቹን
ተጠራጠረ፡፡ ሲፈራው የኖረ ውብ ገላዋን በኒያ አለንጋ መሳይ ጣቶቹ
እያሻሽ አንዳንዴም ልቡ ሲከዳው ጣቶቹ ደግሞ ሳይታዘዙ ወደ ጡቶቿ እያዘገሙ ከዚያም ድንግጥ ብሎ ሲመልሳቸው ደግሞም ላያስበው በስሜት
ሌላ ሃሳብ ውስጥ ይገባና ወደ ዳሌዋ አድርሶ ሲመልሳቸው.. በአማረች ፈተና እንደያዘችው ቁም ስቅሉን ሲያይ ዋለ፡፡ እሷ አውቃ ስትፈራገጥ እሱም ጎበዝ አሰልጣኝ ለመሆን ሲታገል ሲተሻሹ ሲደባበሱ..ብዙ ቆዩ።
ሰው እንደ ጨው የሚሟሟ ቢሆን ኖሮ ሟሙተው ሟሙተው በጠፉ
ነበር፡፡ የሱ ጣቶች በገላዋ ላይ በሚርመሰመሱበት ጊዜ አማረች በከፍተኛ የፍቅር ስሜት ውስጥ ነበረች። ከውጭ ቀዝቃዛው ውሃ ባያቀዘቅዛት ኖሮ ውስጧ በስሜት እየጋለ እየነደደ ሄዶ እንደ ስም ቀልጣ በፈሰሰች ነበር፡፡
የሁለት ዓመት የትምህርት ቤት ጓደኛዋ ከአንገቷ ቀና አድርጎ ዐይን
ዐይኖቿን በፍቅር እያየ አበባ ከንፈሮችዋን ለመቅሰም ያልታደለ ንብ ሆኖ አንገቱን እያቀረቀረ እሷ በጉጉት ስትጠብቀው እያሳፈራት ሁለት አመታት እንደ ዋዛ አለፉ፡፡ እሱ እንደዚያ ማድረግ ቢችል ኖሮ ከወዲሁ ስሜቷን ቢረዳላት ኖሮ ያንን ያክል የሚባክን ጊዜ ባልተፈጠረ ነበር፡፡ ገና
ከጅምሩ ፍላጎትዋን አውቆ በአንደኛና በሁለተኛው ወር ላይ በአፉ ባያወጣው እንኳ ሚስጥሩን በዐይኖቹ ቢገልፅላት ኖሮ ተቀላጥፋ ምላሹን በደስታ በገለፀችለት ነበር፡፡ እሱ ግን ያንን ማድረግ ባለመቻሉ ግንኙነታቸው በጥናት ላይ ብቻ ተወሰነና ጊዜው ተላለፈና በእህትነት በወንድምት
በሚል ፈሊጥ ምኞታቸውን ከመገላለፅ ተቆጠቡ።
በልባቸው እየተፈላለጉ ከአሁን በኋላ ምን ይለኝ? ምን ትለኝ? በመባባል ተፈራርተው በመካከላቸው አፏን ከፍታ የምታዛጋውን ፍቅር ሁለት
ዓመት ሙሉ በሱስ እንድትሰቃይ አደረጓት። በይሉኝታ ገመድ በመታሰር ምን ይለኛል ምን ትለኛለች በሚል ፍራቻ ግልፅነት ሲጠፋ ትርፉ ውስጥ ውስጡን መሰቃየት ነውና አማረችና ጌትነት የዚህ የፍቅር ጋግርት የይሉኝታ ሰለባዎች ሆኑና የሱን ልወቀው ከሷ ይምጣ እየተባባሉ የመፈላለግ ደረጃቸው ገሃድ ሳይወጣ ሁለት ዓመታት ተቆጠሩ።
በማህበረሰቡ ዘንድ ሴት ልጅ ስትለመን፣ ደጅ ስታስጠና፣ ስትሽኮረመም ትወደዳለች የሚል አመለካከት በስፋት የሚንፀባረቅ በመሆኑ ፍቅሯን አስቀድማ ለመግለፅ ትቸገራለች። አማረችንም አፏን ያፈነው ይሄው
ነበር፡፡ በአንዳንድ ሁኔታዎቹ የተረታላት መሆኑን ብታውቅም አስጠናኝ ብዬ በግድ የቀረብኩት ልጅ ቀድሜ ወደድኩህ ብለውና "አልፈልግሽም ዞር በይ" ቢለኝስ? በሚል ፍራቻ ዝምታን መርጣ ቆየች። እሺ እንደ ሃሳብሽ ቢላት እንኳ ወደ ፊት አንድ ቀን “እሷ ራሷ ወደድኩህ አበድኩልህ ብላ ተለማምጣኝ ነው" ብሎ ሊያወራ ነው። ከዚህ ሁሉ እንደተከባበርን ቢቀርስ? ከዚህ ሁሉ ነገሩ ከሱ ገፍቶ እስከሚመጣ ድረስ በትዕግስት ብጠብቅስ? በማለት ሁለት ዓመት ሙሉ ታገሰች። ከጌትነት በኩል ገሀድ የሚወጣ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...የተቃራኒ ፆታ ሱስ እስከሚያንጠራራው ድረስ ተጨነቀ ጭኖቹ በጭኖቿ መካከል ነበሩ አልቻለም፡፡ ከንፈሮቿን እየሳመ ቀስ ብሎ የሆነ ነገር በጆሮዋ ሹክ አላት፡በዚህ ጊዜ አማረች በጣም ተበሳጨች፡፡
ሂድ! ባለጌ! ወንዶች ስትባሉ ይሄው ናችሁ። ፍቅር ሲሏችሁ ዘላችሁ የምትሰፍሩት እዚያ ላይ ነው፡፡ ፍቅር ማለት እሱ ብቻ ነው የሚመስላችሁ፡፡ እኔኮ አንተን ለብዙ ነገር ነበር የምመኝህ፡፡ እንደዚህ አይነት ሰው አትመስለኝም ነበር፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ልጃገረድ መሆኔን ማወቅ አለብህ!ባንተ ዘንድ ረከስኩ እንጂ ውድ ነበርኩ፡፡ ሽርሙጣ አይደለሁም፡፡ ገባህ?!" ጮኽችበት። ደነገጠ።
“እንደሱ አይደለም የኔ ቆንጆ። በሌላ መልክ አይቼሽ አይደለም፡፡ በጣም ስለምወድሽ ነው በጣም አማረች.." ቃላት አጥረውት ተጨነቀ፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ስውነቱ በስሜት ግሏል። ነዷል። "እኔኮ እኔኮ . እወድሻለሁ.... እስከ መጨረሻው የኔ እንድትሆኚ እፈልጋለሁ" አፉ ሲወተውት
ጣቶቹ ባልተፈቀደላቸው ድንበር ዘለው ገብተው አሰሳ ማካሄዳቸውን አላቋረጡም ነበር፡፡ ድርጊቱ አማረችን የበለጠ አናደዳት።
"ልቀቀኝ! ልቀቀኝ!" መንጭቃው ተነሳች። "እኔው ነኝ ወረዳዋ! አንተ
ምን አደረክ? በለሊቱ በርህን አንኳኩቼ የገባሁት እኔ! ጥፋተኛዋ እኔ!" ፀጉሯን እየነሰነሰች….ያንን ውብ ዳሌዋን እያውረገረገች ከአልጋው ላይ ወረደች፡፡ በድንጋጤ ዐይኖቹ ፈጠጡ። የሚናገረው ጠፍቶበት በፈፀመው የብልግና ድርጊት ራሱን ወቀሰ፡፡ በስሜት ግፊት ተሸንፎ ከፍላጎትዋ ውጭ በፈፀመው ድርጊት ተፀፀተ።
ቆይ!!. . ቆይ! . ቆይ! " እጆቹን ዘርግቶ ተከትሏት ብድግ አለ።
“ሂድ!" በሩን አላትማ ወጣች።
“አማ.አማረች..አንዴ .ምን…. መሆንሽ ነው?ቆይ እስቲ..." ሲወራጭ የአልጋው ብረት ቅዝቃዜ እንደ ኤሌክትሪክ ነዘረውና ብንን አለ። ጭንቀቱ..
ቅዠቱ.. ላብ በላብ አድርጎት ነበር፡፡
“በስመአብ ወልድ!“ ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ ከለሊቱ ስምንት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ ቀስ ብሎ ያየውን ህልም ይመረምር ጀመር፡፡ ያንን የማይጨበጥ ጉም የማይዳሰስ ተስፋ መጨረሻው ባያምርም እቅፍ አድርጎ
በላይዋ ላይ እየተንፈላሰለ እንጆሪ ከንፈሮቿን የቀሰመበት ዓለም እንደ
ሰቀቀን ሆኖ አለፈ። ዐይኖቹን ጭፍን ክድን ጭፍን ክድን አደረጋቸው። መብራቱን አበራና ሁለቱንም ትራሶች ደራርቦ ከወገቡ በላይ ራቁቱን ሆነ፡ ዐይኖቹን ፊት ለፊቱ አማረችን በጋረደበት ግድግድ ላይ በንዴት ተክሎ በሀሳብ እሷ ክፍል ገባ፡፡ እንደ ንዴቱና እንደ ብሽቀቱ ቢሆን ኖሮ
ከዐይኖቹ የሚወረወሩት ጨረሮች ያንን የግንብ ግድግዳ የጤፍ መንፊያ ወንፊት ባደረጉት ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ እንቅልፍ በዐይኑ ሳይዞር ቀሪውን ጊዜ በመቀመጥና በመገላበጥ አሳለፈው፡፡ ጠዋት ቁርሳቸውን እዚያው በሉና በፕሮግራማቸው መሰረት ወደ ላንጋኖ ጉዞ ጀመሩ፡፡ ዛሬ አማረች
የዋና ተለማማጅና የህይወት አድን ሰራተኛ ፈላጊ ሆና ለመቅረብ አቅዳለች። ለዘዴዋ፡፡ ላንጋኖ ደርስው ለዋና ተዘጋጁ፡፡ አማረች ልብሷን አወላልቃ በውስጥ ሱሪ ብቻ ወደ ሃይቁ መጣች፡፡ ጌትነት ያንን ውብ ተክለ ቁመናዋን የሚያጓጓ ራቁት ገላዋን በውስጥ ሱሪ ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ
አየው። ልቡ ወደ ሰማይ ወጥታ እንደ እምቧይ ፈረጠች፡፡ ወደር የሌለው አፍ የሚያስከፍት ቅርፅ.. ስምንት ቁጥር ቁጭቁጭ.ያሉ ጡቶቿ ዐይኖቻቸውን አፍጠው ምራቃቸውን በሚውጡ ተመልካቾቿ ድርጊት ተቆጥተው እንደ ነብር ያበጡ ይመስላሉ። ጌትነት ዘወር ዘወር ብሎ ሲመለከት የበርካታ ዋናተኞች አፎች ተከፍተው መቅረታቸውን አስተዋለ። ቅንአት ቢጤ ቆነጠጠው...
"እውን የኔ ትሆኝ ይሆን ?"አለ በልቡ። ይሄንን ልቡ የተመኘውን ምኞት ዐይኑ እንዳያሳብቅበት ፈራና ለመሸፋፈን ጥረት አደረገ፡፡ ተወት ያደረጋት ለመምሰል ማዶ ማዶውን ማየት አበዛ... አማረች ደግሞ የጌትነትን አንጀት ለመብላት ስትል አንድ አላስፈላጊ ድርጊት ፈፀመች። ጡት ማስ
ያዣዋን በመጠኑ ዝቅ አደረገች። ማግኔት!!
"ጌትሽ ይሄኛው ጥልቅ ነው እኔ እዚህ አልዋኝም፡፡ እሰምጣለሁ። እዚ ቅርቡ ጋ ሄደን እንዋኝ?” ሰው ወደሌለበት አካባቢ በአገጭዋ እያሳየችው አካባቢውን ጠቆመችው። ወደዚያ እሷ ወዳለችው የሃይቁ ዳርቻ ተያይዘው ሄዱ፡፡ አማረች አዲስ ዋና ተማሪ ሆና ቁጭ አለች፡፡ ወይ አበሳው?!
ያንን መጠጋት የፈራውን እፍኝ የማይሞላ ወገቧን ይዞ ከፍ ዝቅ ወደ..ፊት ወደ ኋላ... እያደረገ ያለማምዳት ጀመር። በሷ እንቅስቃሴ አቅጣጫ
እየተመራች የሱም ልብ ከቦታዋ ለቃ እየተንከራተተች ነበር፡፡
ጌትነት የትናንትናው ህልም ዓለም ክፍል ሁለት እንዳይሆን ዐይኖቹን
ተጠራጠረ፡፡ ሲፈራው የኖረ ውብ ገላዋን በኒያ አለንጋ መሳይ ጣቶቹ
እያሻሽ አንዳንዴም ልቡ ሲከዳው ጣቶቹ ደግሞ ሳይታዘዙ ወደ ጡቶቿ እያዘገሙ ከዚያም ድንግጥ ብሎ ሲመልሳቸው ደግሞም ላያስበው በስሜት
ሌላ ሃሳብ ውስጥ ይገባና ወደ ዳሌዋ አድርሶ ሲመልሳቸው.. በአማረች ፈተና እንደያዘችው ቁም ስቅሉን ሲያይ ዋለ፡፡ እሷ አውቃ ስትፈራገጥ እሱም ጎበዝ አሰልጣኝ ለመሆን ሲታገል ሲተሻሹ ሲደባበሱ..ብዙ ቆዩ።
ሰው እንደ ጨው የሚሟሟ ቢሆን ኖሮ ሟሙተው ሟሙተው በጠፉ
ነበር፡፡ የሱ ጣቶች በገላዋ ላይ በሚርመሰመሱበት ጊዜ አማረች በከፍተኛ የፍቅር ስሜት ውስጥ ነበረች። ከውጭ ቀዝቃዛው ውሃ ባያቀዘቅዛት ኖሮ ውስጧ በስሜት እየጋለ እየነደደ ሄዶ እንደ ስም ቀልጣ በፈሰሰች ነበር፡፡
የሁለት ዓመት የትምህርት ቤት ጓደኛዋ ከአንገቷ ቀና አድርጎ ዐይን
ዐይኖቿን በፍቅር እያየ አበባ ከንፈሮችዋን ለመቅሰም ያልታደለ ንብ ሆኖ አንገቱን እያቀረቀረ እሷ በጉጉት ስትጠብቀው እያሳፈራት ሁለት አመታት እንደ ዋዛ አለፉ፡፡ እሱ እንደዚያ ማድረግ ቢችል ኖሮ ከወዲሁ ስሜቷን ቢረዳላት ኖሮ ያንን ያክል የሚባክን ጊዜ ባልተፈጠረ ነበር፡፡ ገና
ከጅምሩ ፍላጎትዋን አውቆ በአንደኛና በሁለተኛው ወር ላይ በአፉ ባያወጣው እንኳ ሚስጥሩን በዐይኖቹ ቢገልፅላት ኖሮ ተቀላጥፋ ምላሹን በደስታ በገለፀችለት ነበር፡፡ እሱ ግን ያንን ማድረግ ባለመቻሉ ግንኙነታቸው በጥናት ላይ ብቻ ተወሰነና ጊዜው ተላለፈና በእህትነት በወንድምት
በሚል ፈሊጥ ምኞታቸውን ከመገላለፅ ተቆጠቡ።
በልባቸው እየተፈላለጉ ከአሁን በኋላ ምን ይለኝ? ምን ትለኝ? በመባባል ተፈራርተው በመካከላቸው አፏን ከፍታ የምታዛጋውን ፍቅር ሁለት
ዓመት ሙሉ በሱስ እንድትሰቃይ አደረጓት። በይሉኝታ ገመድ በመታሰር ምን ይለኛል ምን ትለኛለች በሚል ፍራቻ ግልፅነት ሲጠፋ ትርፉ ውስጥ ውስጡን መሰቃየት ነውና አማረችና ጌትነት የዚህ የፍቅር ጋግርት የይሉኝታ ሰለባዎች ሆኑና የሱን ልወቀው ከሷ ይምጣ እየተባባሉ የመፈላለግ ደረጃቸው ገሃድ ሳይወጣ ሁለት ዓመታት ተቆጠሩ።
በማህበረሰቡ ዘንድ ሴት ልጅ ስትለመን፣ ደጅ ስታስጠና፣ ስትሽኮረመም ትወደዳለች የሚል አመለካከት በስፋት የሚንፀባረቅ በመሆኑ ፍቅሯን አስቀድማ ለመግለፅ ትቸገራለች። አማረችንም አፏን ያፈነው ይሄው
ነበር፡፡ በአንዳንድ ሁኔታዎቹ የተረታላት መሆኑን ብታውቅም አስጠናኝ ብዬ በግድ የቀረብኩት ልጅ ቀድሜ ወደድኩህ ብለውና "አልፈልግሽም ዞር በይ" ቢለኝስ? በሚል ፍራቻ ዝምታን መርጣ ቆየች። እሺ እንደ ሃሳብሽ ቢላት እንኳ ወደ ፊት አንድ ቀን “እሷ ራሷ ወደድኩህ አበድኩልህ ብላ ተለማምጣኝ ነው" ብሎ ሊያወራ ነው። ከዚህ ሁሉ እንደተከባበርን ቢቀርስ? ከዚህ ሁሉ ነገሩ ከሱ ገፍቶ እስከሚመጣ ድረስ በትዕግስት ብጠብቅስ? በማለት ሁለት ዓመት ሙሉ ታገሰች። ከጌትነት በኩል ገሀድ የሚወጣ
👍4