#ይድረስ_ለጥም_ሚኒስትር
ይድረስ ለጥም ሚኒስትር
ላልጠጣነው ለሚያስከፍሉ
ጥም በቧንቧ ለሚያከፋፍሉ
እንዴት አሉ
አንዴት ዋሉ፤
አለሁ በከፍተኛ ጥም
ባገሬ ተስፋ ብቆርጥም
በጅቡቲ አየተጽናናሁ
አቧራየን እየጠጣሁ
ጠጠሮቼን አየሸናሁ፤
ዘለቅሁት ይህን አመት
የተሸመነ እድፍ ለብሼ
እንደ ማለዳ ድመት፥ ፊቴን በምራቄ አብሼ
ሺህ ጀሪካን ከፊቴ
ሺህ ጀሪካን ከኋላየ፥ አግተልትየ አሰልፌ
ምድረ በዳውን በመስኖ፥ ቤቴ ድረሰ ጠልፌ።
ይድረስ ለጥም ሚኒስትር
ላልጠጣነው ለሚያስከፍሉ
ጥም በቧንቧ ለሚያከፋፍሉ
እንዴት አሉ
አንዴት ዋሉ፤
አለሁ በከፍተኛ ጥም
ባገሬ ተስፋ ብቆርጥም
በጅቡቲ አየተጽናናሁ
አቧራየን እየጠጣሁ
ጠጠሮቼን አየሸናሁ፤
ዘለቅሁት ይህን አመት
የተሸመነ እድፍ ለብሼ
እንደ ማለዳ ድመት፥ ፊቴን በምራቄ አብሼ
ሺህ ጀሪካን ከፊቴ
ሺህ ጀሪካን ከኋላየ፥ አግተልትየ አሰልፌ
ምድረ በዳውን በመስኖ፥ ቤቴ ድረሰ ጠልፌ።
#ይድረስ
እኔ የማውቀው፣ መለዮ ለባሽ
የገባሮች እንባ አባሽ
የግፍ ማዕበል ቀልባሽ
የደከመ ሚያበረታ፣ የዘመመ የሚደግፍ
የኑሮን ሸከም እንደ ሾላ፣ ከጫንቃ ላይ የሚያራግፍ።
አንተ ግን
የጀግኖችን ልብስ ለብሰህ
ከኑሯችን ጭነት ብሰህ
ላገርህ እንኳን ባትሞት፣ አገርህን ትገላለህ?
እንዴት እንደ ወረርሺኝ፣ በመደዳ ትጥላለህ
በላቡ ያወዛህ ገባር፣ የቀለበህ ጥሮ ግሮ
ተርቦ ያጎረሰህ፣ በለጋስ ምጣዱ ጋግሮ
አቤት ብሎ ቢጮህልህ፣ መሄጃ አጥቶ
ተቸግሮ
ልጁን ቤቱን ስታሸብር
ደረቱን በጥይት ስትገምስ፣ ጐኑን ቅልጥሙን ስትሰብር
ትንሽ እንኳን አታፍርም?
ህሊና ባይኖርህስ፣ ከሰው አትበደርም?
ያልገነባኸውን ስታፈርስ፣ ያልፈጠርከውን ስትገድል
ለራበው ለተቸገረ፣ ሞትን እንደ ቆሎ ስታድል
ስታወድም ስታከስም፣ ስትፈነከት ስታቆስል
ሁሌም ቃታ ስትስብ፣ ሁሌም ሳንጃህን ስትስል
የሰለባህን ቀሪ እድሜ፣ መውሰድ የምትችል ይመስል
የምትበላው ይስማማሃል፣ ከምትጠጣው ትስማማለህ?
ደም በላሱ ከንፈሮችህ፣ ልጆችህን ትስማለህ??
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
እኔ የማውቀው፣ መለዮ ለባሽ
የገባሮች እንባ አባሽ
የግፍ ማዕበል ቀልባሽ
የደከመ ሚያበረታ፣ የዘመመ የሚደግፍ
የኑሮን ሸከም እንደ ሾላ፣ ከጫንቃ ላይ የሚያራግፍ።
አንተ ግን
የጀግኖችን ልብስ ለብሰህ
ከኑሯችን ጭነት ብሰህ
ላገርህ እንኳን ባትሞት፣ አገርህን ትገላለህ?
እንዴት እንደ ወረርሺኝ፣ በመደዳ ትጥላለህ
በላቡ ያወዛህ ገባር፣ የቀለበህ ጥሮ ግሮ
ተርቦ ያጎረሰህ፣ በለጋስ ምጣዱ ጋግሮ
አቤት ብሎ ቢጮህልህ፣ መሄጃ አጥቶ
ተቸግሮ
ልጁን ቤቱን ስታሸብር
ደረቱን በጥይት ስትገምስ፣ ጐኑን ቅልጥሙን ስትሰብር
ትንሽ እንኳን አታፍርም?
ህሊና ባይኖርህስ፣ ከሰው አትበደርም?
ያልገነባኸውን ስታፈርስ፣ ያልፈጠርከውን ስትገድል
ለራበው ለተቸገረ፣ ሞትን እንደ ቆሎ ስታድል
ስታወድም ስታከስም፣ ስትፈነከት ስታቆስል
ሁሌም ቃታ ስትስብ፣ ሁሌም ሳንጃህን ስትስል
የሰለባህን ቀሪ እድሜ፣ መውሰድ የምትችል ይመስል
የምትበላው ይስማማሃል፣ ከምትጠጣው ትስማማለህ?
ደም በላሱ ከንፈሮችህ፣ ልጆችህን ትስማለህ??
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
#ይድረስ_ላድርባይ_ጓዴ
እየለየ ጊዜ ቦታ እየመረጠ
እስስታማ መልክ ገጽኽ ተለወጠ
አህያ እዳልነበርህ በሰርዶዎች መሀል
አህዮች ሲበዙ ዛሬ ጅብ ኾነሀል፡፡
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
እየለየ ጊዜ ቦታ እየመረጠ
እስስታማ መልክ ገጽኽ ተለወጠ
አህያ እዳልነበርህ በሰርዶዎች መሀል
አህዮች ሲበዙ ዛሬ ጅብ ኾነሀል፡፡
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ይድረስ_ለአያ_እከሌ
እኔ'ኮ
እንዳንተ በክብር የሚጠራ የገነነ ስም የለኝም
እንኳን ሀገሬው ቀርቶ መንደሬው በቅጡ አያውቀኝም፡፡
አንተና እኔ በተፈጥሮ
በሰውነት እኩል ብንሆንም
እንደሰው እኩያመች አይደለንም እንለያያለን በዝናም ሆነ በገድል
አንተ
የታዋቂነትን አክሊል ደፍተሃል ተቀዳጅተሃል የዝነኝነትን ድል
ጊዜ ሁኔታ ፈቅዶልህ ከፍ ከፍ ብለሃል በዕድል፡፡
ታድያ
እጅ ተፍንጅ ብይዝህ የፈጠራን መንፈስ። ስትገድል
“እንዲህ አረገኝ ብል
እኔን ማንም አያምንም
የፍትሕ ሚዛኑ አዘንብሎ ወደ አንተ ነው እሚያጋድል፡፡
ስለዚህ
ልፋ እንዳለው መነኩሴ ቆብን ቀዶ እንደመስፋት
ሥራፊ.ትነት መስሎ ቢታየኝ ቢሆንብኝ ከንቱ ልፋት
ስራፈትነት መስሎ ቢታየኝ ቢሆንብኝ ከንቱ ልፋት
ክፉ ስራህን ማጋለጥ
አንተን በክፉ ማንሣት ቸግሮኛል ስምህን ማጥፋት፡፡
ፈጠራው የኔ ሳይሆን የሱ ነው" ላትል
ስምህን በክፉ ሥራህ አሥሬ ባነሳ ብጥል
“ውጉዝ ከመአርዮስ” ብል በርግማንም ባብጠለጥል
“እኔን ከምድር አያነሳኝ “አንተን" ከሰማይ አይጥል፡፡
እውነቱ እንደንጋት እያደር ቆይቶ እስከሚጠራ
እስቲ በጐ በጐውን ስለልባችን ሐቅ እናውራ፡፡
ኧረ ለመሆኑ ምን ይሰማሃል? በተራሰው ድንቅ ሥራ
ከዳር እዳር ዝናህ ሲናኝ ስምህ በአክብሮት ሲጠራ::
ለእኔ ግን ይሰማኛል ስምህ ሲገዝፍ ከተራራ
ግዘፍ ነስቶ ሕይወት ዘርቶ ነፍስ ሲዘራ።
እፁብ ድንቅ በተሰኘው የኔ ያዕምሮ ፈጠሪ-
ስትባረክ ስትመረቅ ስትደነቅ ይደንቀኛል
አንዳንዴ
የእኔን ሐሳብ እንኳን ሰረቅክ ያሰኘኛል፡፡
እናም
እየኖርኩኝ ስላኖርከኝ ከፍ ብያለሁ ዕድሜ ላንተ!
ፈጠራዬማ ነፍስ ዘርቷል ስሜ ብቻ ነው በቁሙ የሞተ፡፡
🔘ፋሲል ተካልኝ🔘
እኔ'ኮ
እንዳንተ በክብር የሚጠራ የገነነ ስም የለኝም
እንኳን ሀገሬው ቀርቶ መንደሬው በቅጡ አያውቀኝም፡፡
አንተና እኔ በተፈጥሮ
በሰውነት እኩል ብንሆንም
እንደሰው እኩያመች አይደለንም እንለያያለን በዝናም ሆነ በገድል
አንተ
የታዋቂነትን አክሊል ደፍተሃል ተቀዳጅተሃል የዝነኝነትን ድል
ጊዜ ሁኔታ ፈቅዶልህ ከፍ ከፍ ብለሃል በዕድል፡፡
ታድያ
እጅ ተፍንጅ ብይዝህ የፈጠራን መንፈስ። ስትገድል
“እንዲህ አረገኝ ብል
እኔን ማንም አያምንም
የፍትሕ ሚዛኑ አዘንብሎ ወደ አንተ ነው እሚያጋድል፡፡
ስለዚህ
ልፋ እንዳለው መነኩሴ ቆብን ቀዶ እንደመስፋት
ሥራፊ.ትነት መስሎ ቢታየኝ ቢሆንብኝ ከንቱ ልፋት
ስራፈትነት መስሎ ቢታየኝ ቢሆንብኝ ከንቱ ልፋት
ክፉ ስራህን ማጋለጥ
አንተን በክፉ ማንሣት ቸግሮኛል ስምህን ማጥፋት፡፡
ፈጠራው የኔ ሳይሆን የሱ ነው" ላትል
ስምህን በክፉ ሥራህ አሥሬ ባነሳ ብጥል
“ውጉዝ ከመአርዮስ” ብል በርግማንም ባብጠለጥል
“እኔን ከምድር አያነሳኝ “አንተን" ከሰማይ አይጥል፡፡
እውነቱ እንደንጋት እያደር ቆይቶ እስከሚጠራ
እስቲ በጐ በጐውን ስለልባችን ሐቅ እናውራ፡፡
ኧረ ለመሆኑ ምን ይሰማሃል? በተራሰው ድንቅ ሥራ
ከዳር እዳር ዝናህ ሲናኝ ስምህ በአክብሮት ሲጠራ::
ለእኔ ግን ይሰማኛል ስምህ ሲገዝፍ ከተራራ
ግዘፍ ነስቶ ሕይወት ዘርቶ ነፍስ ሲዘራ።
እፁብ ድንቅ በተሰኘው የኔ ያዕምሮ ፈጠሪ-
ስትባረክ ስትመረቅ ስትደነቅ ይደንቀኛል
አንዳንዴ
የእኔን ሐሳብ እንኳን ሰረቅክ ያሰኘኛል፡፡
እናም
እየኖርኩኝ ስላኖርከኝ ከፍ ብያለሁ ዕድሜ ላንተ!
ፈጠራዬማ ነፍስ ዘርቷል ስሜ ብቻ ነው በቁሙ የሞተ፡፡
🔘ፋሲል ተካልኝ🔘
#ይድረስ_ላንተ
ጀግናዬ የቤትህ ድባብ
ቢናፍቅህ አውዳመቱ፣
ምንም ባይንህ ላይ ሽው ቢል
የዘመድ አዝማድ ጨዋታ
የቤተሰብ ናፍቆቱ፣
የኩበቱ ጭስ ሽታ
የዶሮ ወጥ አምሮቱ፣
የእህት የወንድም ትዝታ፣
ያባት ጠረን የናት ሽታ
የአደይ አበባው ውበት በለው
የገበያው ድምቀቱ፣
ከአብሮ አደጎች ጋር መቃለድ
አብሮ መብላት መጠጣቱ፣
እርግጥ ነው ይናፍቅሃል
አድባር ቀዬው አውዳመቱ፡
መቻል አንተ ልማድህ ነው
ናፍቆት ችለህ መክፈል ዋጋ፣
ማንም ይወቀው ልክህን
በዋዛ አይደለም ጀግናዬ
ሞተህልኝ ነው የምታነጋ፡፡
ቤተሰብ በማእድ ዙሪያ
ስለ አውደ አመት ሲስባስብ፣
አንተ ዛሬም በድንበር ላይ
ስለ ሰላም ነው የምታስብ፡፡
ልጆች ከአባቶቻቸው . . . የገና ስጦታን ሲቀበሉ፣
ጀግናዬ ያንተ ምስኪኖች . . . አይንህን ይናፍቃሉ፣
የሃገር የቁርጥ ቀን ልጅ
አንተ ወገን አፍቃሪ፣
አንተ ስለ ሰላም ሟች
አንተ ቃልህን አክባሪ፣
አንተ የሃገር ማገሯ
አንተ ስለ ህዝቧ ኗሪ፣
ከምትክ የለሽ ህይወት ላይ
እሷኑ ለድንበር ገባሪ፣
ደስ እያለህ ያበረከትክ
ነብስን የሚያህል ስጦታ፣
ጀግናዬ የሰውነት ልክ
ወታደር የፍቅር ጌታ፣
አውደ ዓመት ሲከበር በፌሽታ፣
በድንበርህ ላይ ዘብ ቆመህ
የሚያረካህ የወገንህ ደስታ።
በማን ሆነና መንጋቱ፣
የአዲስ ዘመን ጀንበር መታየቱ፣
ዘመን እንዲብትልን
ቀናችን መሽቶ እንዲነጋ፣
አንተ ነህ ከአምላክ ቀጥሎ
የከፈልክልን ውድ ዋጋ፡፡
በለሰለሰ መኝታ ጣፋጩን እንቅልፍ የጠገብነው፣
አሸዋ ልብሱ ወጥቶ አደር
እንቅልፍህን ጾመህልን ነው፣
ቀዝቃዛ ውሃ ጠጥተን
ስለ እርካታችን ስንናገር፣
የምትጎነጨውን ውሃ ግለት
የምታውቅ ኮዳህ ትመስክር፡፡
አዎ አዲስ ዘመን ባተ
እውነት ነው መስከረም መጣ፣
ክረምቱ አልፎ ተሻገርን
አየናት ምድር አጊጣ፣
ልዩ ነው ነብስ ያስደስታል
መስጠት መቀበል ስጦታ፣
የማይደበዝዝ ሃቅ ግን
ወታደር ያንተ ውለታ፡፡
እውነት ነው ወታደርነት
ስለ ሃገር ክብር መክፈል ህይወት፣
ስለ ህዝብ ፍቅር ኖሮ መሞት፡፡
ከተጋፈጥከው ተራራ
ካቋረጥከው ቆንጥር ጀርባ፣
አዲስ ፀሃይ እኛ አይተናልተ
በመስዋእትነትህ ታጅባ፡፡
በአንተ ነው አንተ ያገሬ ልጅ
ባንተ ነው ጨለማው የነጋ፣
ሃገርና ህዝብን አስቀድመህ
በከፈልክልን ውድ ዋጋ፡፡
ሃገር እስከ ጥግ ተጠራርቶ
አንዱ ለሌላው መልካም ሲመኝ፣
ስለ ሃገሩ ወጥቶ አዳሪው
አንተን ቢረሱህ አመመኝ፡፡
አድምጠኝ ጀግናዬ ጓዴ....
አንተ ባለህበት በረሃ
ባይኖርም እርጥብ ቄጠማ፣
ክትፎውን ከቁርጥ ባታማርጥ
ቀዝቃዛ ውሃን ብትጠማ፣
ወታደር ባንተ ልፋት ነው
መድመቁ በአል አውደ አመት፣
ለጥቁር አፈርህ ክብር
አፈር መስለህ የደከምክበት፡፡
እየሞትክ የምታቆማት ሃገር
ዛሬ ዘመኗን ስትቀይር፣
እንኳን አደረሰህ ልልህ ወደድኩ
ክብር ምስጋና ላንተ ይሁን
ለራስህ ያልኖርከው ወታደር፡፡
🔘ሻለቃ ወይንሐረግ በቀለ🔘
ጀግናዬ የቤትህ ድባብ
ቢናፍቅህ አውዳመቱ፣
ምንም ባይንህ ላይ ሽው ቢል
የዘመድ አዝማድ ጨዋታ
የቤተሰብ ናፍቆቱ፣
የኩበቱ ጭስ ሽታ
የዶሮ ወጥ አምሮቱ፣
የእህት የወንድም ትዝታ፣
ያባት ጠረን የናት ሽታ
የአደይ አበባው ውበት በለው
የገበያው ድምቀቱ፣
ከአብሮ አደጎች ጋር መቃለድ
አብሮ መብላት መጠጣቱ፣
እርግጥ ነው ይናፍቅሃል
አድባር ቀዬው አውዳመቱ፡
መቻል አንተ ልማድህ ነው
ናፍቆት ችለህ መክፈል ዋጋ፣
ማንም ይወቀው ልክህን
በዋዛ አይደለም ጀግናዬ
ሞተህልኝ ነው የምታነጋ፡፡
ቤተሰብ በማእድ ዙሪያ
ስለ አውደ አመት ሲስባስብ፣
አንተ ዛሬም በድንበር ላይ
ስለ ሰላም ነው የምታስብ፡፡
ልጆች ከአባቶቻቸው . . . የገና ስጦታን ሲቀበሉ፣
ጀግናዬ ያንተ ምስኪኖች . . . አይንህን ይናፍቃሉ፣
የሃገር የቁርጥ ቀን ልጅ
አንተ ወገን አፍቃሪ፣
አንተ ስለ ሰላም ሟች
አንተ ቃልህን አክባሪ፣
አንተ የሃገር ማገሯ
አንተ ስለ ህዝቧ ኗሪ፣
ከምትክ የለሽ ህይወት ላይ
እሷኑ ለድንበር ገባሪ፣
ደስ እያለህ ያበረከትክ
ነብስን የሚያህል ስጦታ፣
ጀግናዬ የሰውነት ልክ
ወታደር የፍቅር ጌታ፣
አውደ ዓመት ሲከበር በፌሽታ፣
በድንበርህ ላይ ዘብ ቆመህ
የሚያረካህ የወገንህ ደስታ።
በማን ሆነና መንጋቱ፣
የአዲስ ዘመን ጀንበር መታየቱ፣
ዘመን እንዲብትልን
ቀናችን መሽቶ እንዲነጋ፣
አንተ ነህ ከአምላክ ቀጥሎ
የከፈልክልን ውድ ዋጋ፡፡
በለሰለሰ መኝታ ጣፋጩን እንቅልፍ የጠገብነው፣
አሸዋ ልብሱ ወጥቶ አደር
እንቅልፍህን ጾመህልን ነው፣
ቀዝቃዛ ውሃ ጠጥተን
ስለ እርካታችን ስንናገር፣
የምትጎነጨውን ውሃ ግለት
የምታውቅ ኮዳህ ትመስክር፡፡
አዎ አዲስ ዘመን ባተ
እውነት ነው መስከረም መጣ፣
ክረምቱ አልፎ ተሻገርን
አየናት ምድር አጊጣ፣
ልዩ ነው ነብስ ያስደስታል
መስጠት መቀበል ስጦታ፣
የማይደበዝዝ ሃቅ ግን
ወታደር ያንተ ውለታ፡፡
እውነት ነው ወታደርነት
ስለ ሃገር ክብር መክፈል ህይወት፣
ስለ ህዝብ ፍቅር ኖሮ መሞት፡፡
ከተጋፈጥከው ተራራ
ካቋረጥከው ቆንጥር ጀርባ፣
አዲስ ፀሃይ እኛ አይተናልተ
በመስዋእትነትህ ታጅባ፡፡
በአንተ ነው አንተ ያገሬ ልጅ
ባንተ ነው ጨለማው የነጋ፣
ሃገርና ህዝብን አስቀድመህ
በከፈልክልን ውድ ዋጋ፡፡
ሃገር እስከ ጥግ ተጠራርቶ
አንዱ ለሌላው መልካም ሲመኝ፣
ስለ ሃገሩ ወጥቶ አዳሪው
አንተን ቢረሱህ አመመኝ፡፡
አድምጠኝ ጀግናዬ ጓዴ....
አንተ ባለህበት በረሃ
ባይኖርም እርጥብ ቄጠማ፣
ክትፎውን ከቁርጥ ባታማርጥ
ቀዝቃዛ ውሃን ብትጠማ፣
ወታደር ባንተ ልፋት ነው
መድመቁ በአል አውደ አመት፣
ለጥቁር አፈርህ ክብር
አፈር መስለህ የደከምክበት፡፡
እየሞትክ የምታቆማት ሃገር
ዛሬ ዘመኗን ስትቀይር፣
እንኳን አደረሰህ ልልህ ወደድኩ
ክብር ምስጋና ላንተ ይሁን
ለራስህ ያልኖርከው ወታደር፡፡
🔘ሻለቃ ወይንሐረግ በቀለ🔘