አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ይድረስ_ለአያ_እከሌ

እኔ'ኮ
እንዳንተ በክብር የሚጠራ የገነነ ስም የለኝም
እንኳን ሀገሬው ቀርቶ መንደሬው በቅጡ አያውቀኝም፡፡
አንተና እኔ በተፈጥሮ
በሰውነት እኩል ብንሆንም
እንደሰው እኩያመች አይደለንም እንለያያለን በዝናም ሆነ በገድል
አንተ
የታዋቂነትን አክሊል ደፍተሃል ተቀዳጅተሃል የዝነኝነትን ድል
ጊዜ ሁኔታ ፈቅዶልህ ከፍ ከፍ ብለሃል በዕድል፡፡
ታድያ
እጅ ተፍንጅ ብይዝህ የፈጠራን መንፈስ። ስትገድል
“እንዲህ አረገኝ ብል
እኔን ማንም አያምንም
የፍትሕ ሚዛኑ አዘንብሎ ወደ አንተ ነው እሚያጋድል፡፡
ስለዚህ
ልፋ እንዳለው መነኩሴ ቆብን ቀዶ እንደመስፋት
ሥራፊ.ትነት መስሎ ቢታየኝ ቢሆንብኝ ከንቱ ልፋት
ስራፈትነት መስሎ ቢታየኝ ቢሆንብኝ ከንቱ ልፋት
ክፉ ስራህን ማጋለጥ
አንተን በክፉ ማንሣት ቸግሮኛል ስምህን ማጥፋት፡፡
ፈጠራው የኔ ሳይሆን የሱ ነው" ላትል
ስምህን በክፉ ሥራህ አሥሬ ባነሳ ብጥል
“ውጉዝ ከመአርዮስ” ብል በርግማንም ባብጠለጥል
“እኔን ከምድር አያነሳኝ “አንተን" ከሰማይ አይጥል፡፡
እውነቱ እንደንጋት እያደር ቆይቶ እስከሚጠራ
እስቲ በጐ በጐውን ስለልባችን ሐቅ እናውራ፡፡
ኧረ ለመሆኑ ምን ይሰማሃል? በተራሰው ድንቅ ሥራ
ከዳር እዳር ዝናህ ሲናኝ ስምህ በአክብሮት ሲጠራ::
ለእኔ ግን ይሰማኛል ስምህ ሲገዝፍ ከተራራ
ግዘፍ ነስቶ ሕይወት ዘርቶ ነፍስ ሲዘራ።
እፁብ ድንቅ በተሰኘው የኔ ያዕምሮ ፈጠሪ-
ስትባረክ ስትመረቅ ስትደነቅ ይደንቀኛል
አንዳንዴ
የእኔን ሐሳብ እንኳን ሰረቅክ ያሰኘኛል፡፡
እናም
እየኖርኩኝ ስላኖርከኝ ከፍ ብያለሁ ዕድሜ ላንተ!
ፈጠራዬማ ነፍስ ዘርቷል ስሜ ብቻ ነው በቁሙ የሞተ፡፡

🔘ፋሲል ተካልኝ🔘