#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....«ስለ ልጅሽ አታስቢ አንቺንም በሚገባ እረዳሻለሁ። አየሽ አእምሮዩ ባንዲት ተስፋ ብቻ ትደሰታለች። ይኸውም ካንቺ ጋር እንደገና እንገናኛለን የሚለው ተስፋ ነው» ብያት ሳልወድ በግድ ዝም አልኩ።
ምላሴ ተቆልፋ እምቢ ባትለኝ ኖሮ በውስጤ የማግበሰበሰው ሐሳብስ ስፍር
ቁጥር አልነበረውም። በብስጭት ከመለብለብ ብዬ ጥያቸው ገለል አልኩ።
ጉልላትም ካሦስት ደቂቃ በኋላ ተለይቷት መጣ፡፡ የእሱን መኪና እንደ ተደገፈን
ብዙ ደቂቃዎች ዐለፉ። እንሒድ ተባብለን ወደ ፍርድ ቤቱ በር አካባቢ ተጠጋን፡፡
አንድ ወፈር ያለ ድምፅ «የወዲያአሉሽ አሸናፊ!» ብሎ ተጣራ፡፡ ለፈተና
እንዳልተዘጋጀ ሰነፍ ተማሪ ተርበተበትኩ፡፡ ሮጥ ሮጥ ብለን ሴቷን ወታደር
ደረስንባትና ስንተኛ ችሎት ነው የምትቀርበው?» ብለን ጠየቅናት።
«አንደኛ ወንጀል ችሎት» ብላ የወደያነሽን ለዕርድ እንደሚነዳ ሠንጋ ነዳቻት። በረዶ የመታኝ ያህል ተንዘፈዘፍኩ፡፡ ወደ ፍርድ ቤቱ ለመግባት ከባለጉዳዮችና ከአቸፍቻፊዎች ጋር ተደባልቄ ዘለቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ራመድ እንዳልኩ፣ ልክ ከፊት ለፊቴ ድንገተኛ መብረቅ የወደቀ ይመስል አካላቴ በታላቅ ድንጋጤ ተተረተረ። ወዲያም ወዲህ ሳላይ ቀንዷን እንደ ተመታች ላም ወደ ኋላ ተመለስኩ፡፡ ተከታትለው የሚይዙኝ ይመስል ሽሽቴን ቀጠልኩ፡፡ የምገባበት ጨነቀኝ፣ ተቅበዘበዝኩ፡፡ መሬት ተሰንጥቃ
ብትውጠኝ ባልጠላሁ ነበር። መለስ ብዬ ብመለከት የጉልላትም ፊት ቡን ብሏል፡፡
ጭንቅላቴን ይዤ አፈሩ ላይ ተጎለትኩ፡፡ መላ ሰውነቴን አሳከከኝ። ዐይኔ ውስጥ
አሽዋ የገባበት ይመስል ቆረቆረኝ፡፡ ዙሪያው ጨለመብኝ። አተነፋፈሴ ፈጠነ፡፡
የእጮኛውን ሞት እንዳረዱነት ወጣት መላ አካላቴ በውስጣዊ የኃዘን ማረሻ
ታርሶ ተበረቃቀሰ፡፡
«የወዲያነሽ ስንት ዓመት ይፈረድባት ይሆን?» እያልኩ ከእግር እስከ ራሴ በፍርሃትና በሥጋት ማጥ ውስጥ ተዘፈቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ገና ረገጥ ስናደርግ እኔንና ጉልላትን ያስበረገገን ግን
ከሦስቱ ዳኞች አንዱ ያውም የመኻል ዳኛው የእኔው አባት ባሻ ያየህይራድ
መሆኑ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም እንደዚያ ያለ ድንጋጤ አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡
አቀርቅሮ የክስ ፋይል ይመለከት ስለነበር አላየኝም፡፡ እነዚያ በሕይወቴ ውስጥ
ዕድሜ እየሆኑ የተቆጠሩት አስደንጋጭ ደቂቃዎች እንደ ማንኛውም ደቂቃ
ዐለፉ፡፡ በዚያ ቅፅበት በእእምሮዬ ውስጥ የጎረፈውን የስጋት ሽብር በተግባር
ለቀመሰው እንጂ በወሬ ለሚሰማው ክብደት የለውም፡፡
አቃቤ ሕጉ በየወዲያነሽ ላይ የሚያቀርበውን ክስና አባቴ ከሁለቱ ዳኞች ጋር ሆኖ የሚሰጠውን የቅጣት ፍርድ ፊት ለፊት ለማየትና ለመስማት ባለመቻሌ ምን ጊዜም የማልበቀለው ጉዳት አጨቀየኝ።
የየወዲያነሽ ሰውነት በጣም በመኮስመኑና ስሟም በመጠኑ ተለውጦ
የወዲያ አሉሽ በመባሏ አባቴ ሊያውቃት አይችልም፡፡ አለባበሷና አንገተ
ሰባራነቷ እንደሚያዛልቅ ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ጭንቅላቴን ይዤ እንዳቀረቀርኩና
ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ጉልላትም እንደ ማማ ተገትሮ እንደ ቆመ ግማሽ ሰዓት
ያህል ነጎደ። ወዴት እንደሚሔድ ባላውቅም የእግሩ ኮቴ ድምፅ ከወደ ኋላዬ እየራቀ ሄደ። አሁንም ጥቂት ደቂቃዎች ዐለፉ፡፡ እፎይታ ሳይሆን የመከራ ነዲድ በውስጤ ተግፈጠፈጠ።
የአባቴን ጠቅላላ የሕሊናና የአካል አቋም ከልጅነት እስከ ዕውቀት የማውቀውን ያህል እያሰላሰልኩ ከፊት ለፊቴ አቆምኩት፡፡ እርሱ በሚያነብበው
የሃይማኖት ታሪክ መጽሐፍ ውስጥ የሚነገርለት ሰው በላው ሰው ሰባ ስምንት
ሰዎች በልቷል እየተባለ ይነገራል። አባቴም በላዔ ሰብ እየተባለ የሚነገርለትን የክፉ ሰው አምሳል መስሎ ታየኝ።
እሱም እንደ ሰው በላው ሰው የሰው አካል አወራርዶና ግጦ የሰው ሥጋ ባይበላም ሰው በላ ነው:: የሰውን ሕይወት በማጥፋትና የሰውን ሕሊና በመግደል
መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡ ስለ እውነተኛ ርትእና ፍትሕ እየተናገረ
ከሓሰተኞች ጎን ቆሞ ፍርድ ያዛባል፡፡ ከሐቅ ጋር ለቆመ ድሃ ሳይሆን ከሐሰትና
ከክህደት ጋር ጡት ለተጣቡ ባለጊዜና ባለ ገንዘብ ይፈርዳል። ስለዚህም «ሰው
በላ» ነው፡፡
ስለ ድሀ መጨቆንና መበደል ሲያወራ ማንም የሚስተካከለው አይመስልም፡፡ የየአካላችን ደም ስለየሕሊናችን ቅንነትና መሠሪነት መስካሪ ቢሆን ኖሮ ከአባቴ ኣካል የሚንጠፈጠፍ ደም ምንኛ ባጋለጠው!
ከጥቅምና ከኑሮው ላይ ቅንጣት ታህል የሚነካ ሰው ከመጣ፡ አንዷ ሰው
በላው ሰው የሰው አካል ዘነጣጥሎ ባይበላም ነገር ሽርቦና ጉንጉኖ ዓመት ሳይተኩስ ጥርኝ ዐፈር ያደርገዋል።
«ጨርቅ ለባሽ፣ አጥንተርካሽ በማለት የሚጸየፋቸውን ሰዎች ስለ ስምና
ክብሩ ብሉ ያንገላታቸውን ድሆች ሳስታውስ አባቴ እንደዚያ እንደ ታሪኩ ሰው
በቀጥታ የሰው ሥጋ ሳይሆን የሰው ሕይወት በልቷል። ስለ ሰው ችግርና ሥቃይ ፍጹም ደንታ የለሹ አባቴ፣ ማንም ቢንገላታና በጊሳቆል የቁጫጭ ሞት ያህል አያሳዝነውም፡፡ በአባቴና በመሰሎቹ አካባቢ ግዙፍ በደል በድሉ፣ በእጅ አዙር ሰው አስገድሉ፣ ከድሆችና ከከልታሞች ዲቃላ ደቅሎ ምስጢርን መቅ መጨመር የመሠሪነት ሳይሆን «የትልቅ ሰውነት» መለዮ ነው:: ለዚህ ዐይነቱ ደባ የሹም ምልመላ ቢካሔድ አባቴ ያላንዳች ቀዳሚ በትራሹመቱን ይጨብጣል።
«እሳቸው የሞቱ ዕለት ስንቱ ዲቃላ ከየሥርቻ ስርኩቻው ይጎለጎል ይሆን?» በማለት ውስጥ ውስጡንና የሚያማው ብዙ ነው:: እንደ ሰው ሐሜትማ ከሆነ ከልዩ ልዩ ሴቶች ተወልደው በአባቴ የተካዱትን እኀት ወንድሞቼን በግምት ሳሰላስል፣ አባቴ ከሰው በላው ብሶ ታየኝ። በተለይም ጠለቅ ብሎ ሥር ከፍ ብሎ ግንድ የለሽ» እያለ ሌሎችን በማኮሰስ የራሱን የዘር ሐረግ ሲያሳምር ታየኝና አስተሳሰቡን ሁሉ ተፀየፍኩት፡፡
ጉልላት ተመልሶ ከፊት ለፊቴ ቆመ፡፡ በእጆቹ ጎትቶ አስነሣኝ፡፡ በፊቱ ላይ አደናጋሪ ፈገግታ እየታየ «የምሥራች ጌታነህ!» አለኝ፡፡
በዚያች አስጨናቂ ጊዜ ውስጥ አንዳችም የምሥራች ይገኛል ብዬ ስላልጠረጠርኩ ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ ቀጠል አደረገና «ምነው ዝም አልክ? የወዲያነሽ እኮ ተፈረደባት። የምሥራች ያልኩህ ግን እጅዋ ከተያዘበት ቀን አንሥቶ አምስት ዓመት እንድትታሠር ስለተፈረደባት ነው:: 'የፈረዱብኝ የጌታነህ አባትና አብረዋቸው ያሉት ናቸው” አለችኝ፡፡ የቅጣቱን ውሳኔ ግን በንባብ ያሰሙት ያንተ አባት ናቸው አለች፡ በስሜ መለወጥና በመጎሳቆሌ
አላወቁኝም በማለቷ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ አለቀ። በፍርሃት የሚጠብቁት ሥቃይ
ካለፈ እፎይታ ነው» ብሎ ከሚተናነቀው ምስቅልቅል ሲቃ ጋር ዝምታውን ቀጠለ።
ከፍርዱ በኋላ የወዲያነሽ ወደ ነበረችበት አካባቢ አብረን ሄድን፡፡ ያ የዐይኗ ቋንቋ የሆነው እንባዋ ገነፈለ። ሴቷ ወታደር ትካዜያችንን አይታ አዘነች፡፡ እኔና ጉልላት እንደገና ጠጋ ብለን ለማነጋገር አዲስ ፈቃድ አልጠየቅንም፡፡
«አይዞሽ! ብዙ ጊዜ አይደለም፡፡ በወህኒ ቤት ውስጥም ሆነ እስራትሽን ጨርሰሽ ስትወጪ የእኔ ነሽ። እኔም ያንቺ እንጂ የማንም የሌላ እይደለሁም፡፡ የልብሽ አዳራሽ በዚህ እውነተኛ በሆነ የቃል ኪዳን ተስፋ ይሞላ። ይህን በላይሽ ላይ የጫንኩትን የመከራ ቀንበር አብሬሽ እሸከመዋለሁ፡፡ በመጨረሻም አብረን
እንሰባብረዋለን፡፡ ያጠቆርኩትን ሕይወትሽን በአዲስ የኑሮ ብርሃን እንዲደሞቅ እስከ መጨረሻው እታገላለሁ» ብዬ የልቤን ፅላት ሰጠኋት። አፏ ባይናገርም ልቧ ተቀብሉኛል፡፡ ያደረግሁት ንግግር ተፅፎ የተጠና እንጂ እዚያው ተቀናብሮ የተነገረ ስለማይመስል እኔኑ መልሶ ገረመኝ፡፡
መለስ ብዩ ለሴቷ ወታደር ምናምን ጨበጥ እደረኩላት፡፡ የማይፈቀድ
ነገር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....«ስለ ልጅሽ አታስቢ አንቺንም በሚገባ እረዳሻለሁ። አየሽ አእምሮዩ ባንዲት ተስፋ ብቻ ትደሰታለች። ይኸውም ካንቺ ጋር እንደገና እንገናኛለን የሚለው ተስፋ ነው» ብያት ሳልወድ በግድ ዝም አልኩ።
ምላሴ ተቆልፋ እምቢ ባትለኝ ኖሮ በውስጤ የማግበሰበሰው ሐሳብስ ስፍር
ቁጥር አልነበረውም። በብስጭት ከመለብለብ ብዬ ጥያቸው ገለል አልኩ።
ጉልላትም ካሦስት ደቂቃ በኋላ ተለይቷት መጣ፡፡ የእሱን መኪና እንደ ተደገፈን
ብዙ ደቂቃዎች ዐለፉ። እንሒድ ተባብለን ወደ ፍርድ ቤቱ በር አካባቢ ተጠጋን፡፡
አንድ ወፈር ያለ ድምፅ «የወዲያአሉሽ አሸናፊ!» ብሎ ተጣራ፡፡ ለፈተና
እንዳልተዘጋጀ ሰነፍ ተማሪ ተርበተበትኩ፡፡ ሮጥ ሮጥ ብለን ሴቷን ወታደር
ደረስንባትና ስንተኛ ችሎት ነው የምትቀርበው?» ብለን ጠየቅናት።
«አንደኛ ወንጀል ችሎት» ብላ የወደያነሽን ለዕርድ እንደሚነዳ ሠንጋ ነዳቻት። በረዶ የመታኝ ያህል ተንዘፈዘፍኩ፡፡ ወደ ፍርድ ቤቱ ለመግባት ከባለጉዳዮችና ከአቸፍቻፊዎች ጋር ተደባልቄ ዘለቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ራመድ እንዳልኩ፣ ልክ ከፊት ለፊቴ ድንገተኛ መብረቅ የወደቀ ይመስል አካላቴ በታላቅ ድንጋጤ ተተረተረ። ወዲያም ወዲህ ሳላይ ቀንዷን እንደ ተመታች ላም ወደ ኋላ ተመለስኩ፡፡ ተከታትለው የሚይዙኝ ይመስል ሽሽቴን ቀጠልኩ፡፡ የምገባበት ጨነቀኝ፣ ተቅበዘበዝኩ፡፡ መሬት ተሰንጥቃ
ብትውጠኝ ባልጠላሁ ነበር። መለስ ብዬ ብመለከት የጉልላትም ፊት ቡን ብሏል፡፡
ጭንቅላቴን ይዤ አፈሩ ላይ ተጎለትኩ፡፡ መላ ሰውነቴን አሳከከኝ። ዐይኔ ውስጥ
አሽዋ የገባበት ይመስል ቆረቆረኝ፡፡ ዙሪያው ጨለመብኝ። አተነፋፈሴ ፈጠነ፡፡
የእጮኛውን ሞት እንዳረዱነት ወጣት መላ አካላቴ በውስጣዊ የኃዘን ማረሻ
ታርሶ ተበረቃቀሰ፡፡
«የወዲያነሽ ስንት ዓመት ይፈረድባት ይሆን?» እያልኩ ከእግር እስከ ራሴ በፍርሃትና በሥጋት ማጥ ውስጥ ተዘፈቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ገና ረገጥ ስናደርግ እኔንና ጉልላትን ያስበረገገን ግን
ከሦስቱ ዳኞች አንዱ ያውም የመኻል ዳኛው የእኔው አባት ባሻ ያየህይራድ
መሆኑ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም እንደዚያ ያለ ድንጋጤ አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡
አቀርቅሮ የክስ ፋይል ይመለከት ስለነበር አላየኝም፡፡ እነዚያ በሕይወቴ ውስጥ
ዕድሜ እየሆኑ የተቆጠሩት አስደንጋጭ ደቂቃዎች እንደ ማንኛውም ደቂቃ
ዐለፉ፡፡ በዚያ ቅፅበት በእእምሮዬ ውስጥ የጎረፈውን የስጋት ሽብር በተግባር
ለቀመሰው እንጂ በወሬ ለሚሰማው ክብደት የለውም፡፡
አቃቤ ሕጉ በየወዲያነሽ ላይ የሚያቀርበውን ክስና አባቴ ከሁለቱ ዳኞች ጋር ሆኖ የሚሰጠውን የቅጣት ፍርድ ፊት ለፊት ለማየትና ለመስማት ባለመቻሌ ምን ጊዜም የማልበቀለው ጉዳት አጨቀየኝ።
የየወዲያነሽ ሰውነት በጣም በመኮስመኑና ስሟም በመጠኑ ተለውጦ
የወዲያ አሉሽ በመባሏ አባቴ ሊያውቃት አይችልም፡፡ አለባበሷና አንገተ
ሰባራነቷ እንደሚያዛልቅ ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ጭንቅላቴን ይዤ እንዳቀረቀርኩና
ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ጉልላትም እንደ ማማ ተገትሮ እንደ ቆመ ግማሽ ሰዓት
ያህል ነጎደ። ወዴት እንደሚሔድ ባላውቅም የእግሩ ኮቴ ድምፅ ከወደ ኋላዬ እየራቀ ሄደ። አሁንም ጥቂት ደቂቃዎች ዐለፉ፡፡ እፎይታ ሳይሆን የመከራ ነዲድ በውስጤ ተግፈጠፈጠ።
የአባቴን ጠቅላላ የሕሊናና የአካል አቋም ከልጅነት እስከ ዕውቀት የማውቀውን ያህል እያሰላሰልኩ ከፊት ለፊቴ አቆምኩት፡፡ እርሱ በሚያነብበው
የሃይማኖት ታሪክ መጽሐፍ ውስጥ የሚነገርለት ሰው በላው ሰው ሰባ ስምንት
ሰዎች በልቷል እየተባለ ይነገራል። አባቴም በላዔ ሰብ እየተባለ የሚነገርለትን የክፉ ሰው አምሳል መስሎ ታየኝ።
እሱም እንደ ሰው በላው ሰው የሰው አካል አወራርዶና ግጦ የሰው ሥጋ ባይበላም ሰው በላ ነው:: የሰውን ሕይወት በማጥፋትና የሰውን ሕሊና በመግደል
መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡ ስለ እውነተኛ ርትእና ፍትሕ እየተናገረ
ከሓሰተኞች ጎን ቆሞ ፍርድ ያዛባል፡፡ ከሐቅ ጋር ለቆመ ድሃ ሳይሆን ከሐሰትና
ከክህደት ጋር ጡት ለተጣቡ ባለጊዜና ባለ ገንዘብ ይፈርዳል። ስለዚህም «ሰው
በላ» ነው፡፡
ስለ ድሀ መጨቆንና መበደል ሲያወራ ማንም የሚስተካከለው አይመስልም፡፡ የየአካላችን ደም ስለየሕሊናችን ቅንነትና መሠሪነት መስካሪ ቢሆን ኖሮ ከአባቴ ኣካል የሚንጠፈጠፍ ደም ምንኛ ባጋለጠው!
ከጥቅምና ከኑሮው ላይ ቅንጣት ታህል የሚነካ ሰው ከመጣ፡ አንዷ ሰው
በላው ሰው የሰው አካል ዘነጣጥሎ ባይበላም ነገር ሽርቦና ጉንጉኖ ዓመት ሳይተኩስ ጥርኝ ዐፈር ያደርገዋል።
«ጨርቅ ለባሽ፣ አጥንተርካሽ በማለት የሚጸየፋቸውን ሰዎች ስለ ስምና
ክብሩ ብሉ ያንገላታቸውን ድሆች ሳስታውስ አባቴ እንደዚያ እንደ ታሪኩ ሰው
በቀጥታ የሰው ሥጋ ሳይሆን የሰው ሕይወት በልቷል። ስለ ሰው ችግርና ሥቃይ ፍጹም ደንታ የለሹ አባቴ፣ ማንም ቢንገላታና በጊሳቆል የቁጫጭ ሞት ያህል አያሳዝነውም፡፡ በአባቴና በመሰሎቹ አካባቢ ግዙፍ በደል በድሉ፣ በእጅ አዙር ሰው አስገድሉ፣ ከድሆችና ከከልታሞች ዲቃላ ደቅሎ ምስጢርን መቅ መጨመር የመሠሪነት ሳይሆን «የትልቅ ሰውነት» መለዮ ነው:: ለዚህ ዐይነቱ ደባ የሹም ምልመላ ቢካሔድ አባቴ ያላንዳች ቀዳሚ በትራሹመቱን ይጨብጣል።
«እሳቸው የሞቱ ዕለት ስንቱ ዲቃላ ከየሥርቻ ስርኩቻው ይጎለጎል ይሆን?» በማለት ውስጥ ውስጡንና የሚያማው ብዙ ነው:: እንደ ሰው ሐሜትማ ከሆነ ከልዩ ልዩ ሴቶች ተወልደው በአባቴ የተካዱትን እኀት ወንድሞቼን በግምት ሳሰላስል፣ አባቴ ከሰው በላው ብሶ ታየኝ። በተለይም ጠለቅ ብሎ ሥር ከፍ ብሎ ግንድ የለሽ» እያለ ሌሎችን በማኮሰስ የራሱን የዘር ሐረግ ሲያሳምር ታየኝና አስተሳሰቡን ሁሉ ተፀየፍኩት፡፡
ጉልላት ተመልሶ ከፊት ለፊቴ ቆመ፡፡ በእጆቹ ጎትቶ አስነሣኝ፡፡ በፊቱ ላይ አደናጋሪ ፈገግታ እየታየ «የምሥራች ጌታነህ!» አለኝ፡፡
በዚያች አስጨናቂ ጊዜ ውስጥ አንዳችም የምሥራች ይገኛል ብዬ ስላልጠረጠርኩ ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ ቀጠል አደረገና «ምነው ዝም አልክ? የወዲያነሽ እኮ ተፈረደባት። የምሥራች ያልኩህ ግን እጅዋ ከተያዘበት ቀን አንሥቶ አምስት ዓመት እንድትታሠር ስለተፈረደባት ነው:: 'የፈረዱብኝ የጌታነህ አባትና አብረዋቸው ያሉት ናቸው” አለችኝ፡፡ የቅጣቱን ውሳኔ ግን በንባብ ያሰሙት ያንተ አባት ናቸው አለች፡ በስሜ መለወጥና በመጎሳቆሌ
አላወቁኝም በማለቷ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ አለቀ። በፍርሃት የሚጠብቁት ሥቃይ
ካለፈ እፎይታ ነው» ብሎ ከሚተናነቀው ምስቅልቅል ሲቃ ጋር ዝምታውን ቀጠለ።
ከፍርዱ በኋላ የወዲያነሽ ወደ ነበረችበት አካባቢ አብረን ሄድን፡፡ ያ የዐይኗ ቋንቋ የሆነው እንባዋ ገነፈለ። ሴቷ ወታደር ትካዜያችንን አይታ አዘነች፡፡ እኔና ጉልላት እንደገና ጠጋ ብለን ለማነጋገር አዲስ ፈቃድ አልጠየቅንም፡፡
«አይዞሽ! ብዙ ጊዜ አይደለም፡፡ በወህኒ ቤት ውስጥም ሆነ እስራትሽን ጨርሰሽ ስትወጪ የእኔ ነሽ። እኔም ያንቺ እንጂ የማንም የሌላ እይደለሁም፡፡ የልብሽ አዳራሽ በዚህ እውነተኛ በሆነ የቃል ኪዳን ተስፋ ይሞላ። ይህን በላይሽ ላይ የጫንኩትን የመከራ ቀንበር አብሬሽ እሸከመዋለሁ፡፡ በመጨረሻም አብረን
እንሰባብረዋለን፡፡ ያጠቆርኩትን ሕይወትሽን በአዲስ የኑሮ ብርሃን እንዲደሞቅ እስከ መጨረሻው እታገላለሁ» ብዬ የልቤን ፅላት ሰጠኋት። አፏ ባይናገርም ልቧ ተቀብሉኛል፡፡ ያደረግሁት ንግግር ተፅፎ የተጠና እንጂ እዚያው ተቀናብሮ የተነገረ ስለማይመስል እኔኑ መልሶ ገረመኝ፡፡
መለስ ብዩ ለሴቷ ወታደር ምናምን ጨበጥ እደረኩላት፡፡ የማይፈቀድ
ነገር