አትሮኖስ
286K subscribers
117 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....ለጥያቄዋ መልስ በመጠበቅ ዐይነት ሦስቱንም ተመለከተቸቻው ፡ ዐይኖቿ አንድ ቦታ እይረጐም በነጭ ቆዳዋ
ላይ ሰማያዊ መሳይ ሥራሥሮቿ ዐልፎ ዐልፎ ይታያሉ ።ገጽታዋ ላይ ፍቅርና ትሕትና ይነበባል ።

ዮናታንና እስክንድር ቡና ሲመርጡ እቤል ሻይ አለ ።ሚስታቸው ወደ ጓዳ ከመሔዷ በፊት ዮናታን ክንዷን ይዘው እጅዋ ላይ ሳም እያረጓት ። ለመልካም መስተንግዶዋ
ምስጋናቸውን የሚገልጹበት መንገድ ነበር

እስክንድር ዐይኑን ማመን አቃተው ወይም ያየው ነገር ሕልም መሰለው ። እውነት ፍቅር ይሆን ? አለ በልቡ ።የትዳር ዕድሜአቸውን ለማወቅ ጓጓ አፍላ ፍቅረኞች ካልሆኑ በስተቀር ተጋብተው በቆዩ ሰዎች መሐል አይቶ የማያውቀውን ሁኔታ ማየቱ ነው ያስደነቀው ያውም በእንግዳ ፊት !

“ ሊብሊንግ ሚስቴም እናቴም ናት ። የሕይወት ጣእም የሚታወቀኝ እሷን አጠገቤ ሳገኛት ነው አሉ ዮናታን ፥
ሚስታቸው ወደ ጓዳ ከገባች በኋላ ። “ ሰውን ማስደሰት መቻል ቀላል ነገር አይደለም ። ሊብሊንግ ይህን ችሎታ በተፈጥሮዋ ታድላዋለች ። ሁል ጊዜ ደስተኛ ነች እንደሚገባኝ ፡ ደስታዋን የምታገኘው ሰዎችን በማስደሰት ነው ።
አቤል ሁኔታዎች እስኪመቻቹለት ከእኛ ጋር እንዲኖር ሐሳቡን ቀድማ ያቀረበችልኝ እሷ ናት ።

አቤል በጥያቄ መልክ ዐይኑን እቁለጨለጨ ።

ከአሁን በፊት የት ታውቀኛለች ?ብሎ ነበር ራሱን የጠየቀው ። ማንኛውም ነገር በዮናታን ሊደርሳት እንደሚችል ወዲያው ገመተ። ወደዚህ ቤት የመምጣቱ ሐሳብ ከእሷ መመንጨቱን ሲሰማ በልቡ ውስጥ ለሴትዮዋ ልዩ ስሜት ተፈጠረበት

“ ከተጋባችሁ ? ” ሲል እስክንድር ፈራ ተባ በሚል ድምፅ ጠየቀ ።

“ ኦ! ስድስት ዓመት ያህል ሆኖአል ። በርሊን በነበርኩበት ጊዜ፡አንዴ ታምሜ ተኝቼ ሐኪም ቤት ውስጥ አስታማሚዬ ሆና ነው ያገኘኋት ። ”

ዮናታን ይህን ሲናገሩ ድምፃቸው የተለየ ቃና ነበረው ።የፍቅረኞች የመጀመሪያ ትውውቅ በልባቸው ታላቅ ትውስት
ጥሎ ያልፋል ። ዮናታንም ለእስክንድር በሰጡት መልስ ሳቢያ ከስድስት ዓመት በፊት የተፈጸመ ትውስት ውስጥ ገቡ .....
ዮናታን በምሥራቅ ጀርመን ውስጥ በሚገኘው ትልቅ ዩኒቨርስቲ የድኅረ ምረቃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ለተወሰኑ ዓመታት በምቦልት ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህር ሆነው አገልግለው ነበር ። እዚያ ሳሉ አንድ ጊዜ የሆድ ውስጥ ሕመም ያድርባቸውና በርሊን ቤክ እሚባለው
ሆስፒታል ይገባሉ ።

በርሊን ቤክ ፣ ከመሃል ከተማው ሀያ ኪሎ ሜትር ያህል ይርቃል ። ውስጡ በአምስት ግቢዎች ተከፍሎ ፡ በጠቅላላ
ዐሥር ሺህ አልጋዎች ያሉት ሰፊ ሆስፒታል ነው ። ዮናታን የተኙት፡“ታይል አይንስ” በሚባለው ግቢ፡ “ እስታስዩን አይን ሁንደርት ሲ ” ክፍል ውስጥ ነበር ።
በማገገም ላይ እንዳሉ አንዲት ነርስ ሲያዩ ልባቸው ይደነግጣል ። ይህች ነርስ ፊቷ ላይ ፈገግታ የተሳለ እንጂ እንደ ሌላው ሰው አንዳንድ ጊዜ ብቻ የምትሥቅ አትመስልም ። ሕሙማንን ለመጎብኘት ስትገባ በሕመም የደከመ ስሜታቸውን በፈገግታ ታነቃቃዋለች ። በውስጥ ቁስል
የዳመነ ፊታቸውን ፈገግታዋ ብርሃን ሆኖ ያፈካዋል ። መስተንግዶዋ ፍቅር የሞላበት በመሆኑ'በክፍሏ ሕሙማን ዘንድ ተወዳጅ ነበረች ። ወደ በሽተኞቹ ክፍል ለመግባት የጉብኝት ወይም የመድኃኒት ዕደላ ሰዓት እስኪደርስ ወይም እነሱ በደወል እስኪጠሩዋት አትጠብቅም ። ብቅ ጥልቅ እንዳለች
ነው የምትውለው ። ልማድ ሆኖባት ሁሌ ትቸኩላለች ።እናም አንድ ቦታ ቆማ አትቆይም ።

ዮናታን ልባቸው ከደነገጠላት ጊዜ ጀምሮ ይህን ችኮላዋን አልወደዱላትም ። ክፍላቸው ገብታ ስትወጣ ፀሐይ
ብልጭ ብላ ድርግም ያለች ያህል ስሜታቸው ይከፋ ጀመር ።

ሥራዋን ጨርሳ ወደ ቤትዋ ልትሔድ በሽተኞቹን ስትሰናበታቸው። የዮናታን ልብ ይረበሽ ነበር ።ሌሊት አልመዋት አድረው ጠዋት ዐይኗን የሚያዩበትን ጊዜ መናፈቅ ሲጀምሩ ልባቸው ፍቅር ፍለጋ ዳዴ እያለ መሆኑን ገመቱ ። ሞኒካ የሚለው ስም አሁንም አሁንም ጆሮአቸው፡ ውስጥ ይደውል ጀመር ።

አንድ ቀን ከሥራ በኋላ እንደ ልማዷ ልትሰናበታቸው ወደ ክፍላቸው ስትግባ ዮናታን እጅዋን ያዝ አድርገው ቅሬታቸውን ተነፈሱላት ።

"ቆይ እንጂ አትቸኩዪ ። ትንሽ አጫውችኝ ሁሌ መቸኮል ምንድነው ?” አሏት ።

ሞኒካ ፈገግ ብላ ፍቃዳቸውን ለመፈጸም አልጋቸው አጠገብ ትንሽ ቆመች ።

“ እውነት ለምንድነው እንዲህ የምትቸኩዬው ” ሲሉ ጠየቋት ።

“ ልማድ ሆኖብኝ ነው ። በምሰራበት ጊዜ ፍጥነቴ አይታወቀኝም ” አለችና : ትንሽ አሰብ አድርጋ ! “ በዚህ በአራት ዓመት ውስጥ ያፈራሁት ጸባይ ነው” አለቻቸው ።

“ ግን ምነው ! ለምን ? ” አሏት ።

“ለአፍላ ፍቅሬ ያገኘሁት ማካካሻ ራሴን ከይዲያ ወዲህ በማራወጥ ዕረፍት መንሣት ነበር ” አለቻችው ሰሜቷን
ግልጽ አድርጋ።

ከዚህ ንግግሯ ጋር ፊቷ ፍም ሲመስል ተመለከቱት ። ስሜቷ መጨፍገጉን አገጽታዋ ላይ አጠኑ ሰው ሠራሽ
የሚመስሉት ዐይኖችዋ፡በቅርቧ ያለውን ነገር ለማየት የተከለከሉ ይመስል በመስኮቱ ማዶ ከሚታየወው ባዶ ሰማይ ላይ ዐረፉ ።

“ ነገሩ እንዲህ ነው ” ስትል ቀጠለች ። “ ከአራት ዓመት በፊት አፈቅረው የነበረው ወጣት የመጀመርያዬ ነበር ። በመሆንም እጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ልቤንና ፍቅሬን ሰጥቼው ነበር ለማለት እደፍራለሁ ። ነገር ግን ሁለት ዓመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ጥሎኝ ጠፋ” አለችና ዝም !

“ የት ነው የጠፋው ?” አሏት ዮናታን ፥ ተመስጠው ።

“ ወደ ምዕራብ ጀርመን። እኔ የሰማሁት ጠፍቶ ከሔደ በኋላ ነው እንጂ ምንም ያማከረኝ ነገር አልነበረም ። በእርግጥ
ልቡ መሸፈቱን በአንዳንድ ንግግሮቹ ገምቼ ነበር ። አብዛኛውን ጊዜ በአስተሳሰብ እንጋጫለን ። እኔ በፋሽስቶች ላይ ከፍተኛ ጥላቻ አለኝ ። በሂትለር ዘመን በናዚዎች ታስሮ የማቀቀው አባቴ ቆስሎ በእኔም ላይ ከባድ ተጽዕኖ ነበረው ።ፍቅረኛዬ ግን ያለፈው ትውልድ በፋሺዝም ምን ያህል
እንደ ተሠቃየ ለማጤን ደንታ አልነበረውም በኣፍላ ስሜት ግፊት እኔደሚነቃነቅ እገምት በር ። እናም መጨረሻውን እንደዚያ አደረገወ ። ”

ዮናታን በኀዘን ከንፈራቸውን መጠጡ።

“አያሳዝነኝም ። ልቤን አሳዝኖት ነው የሔደው ”አለች ሞኒካ ፥ ራሷን እየነቀነቀች “ ነገር ግን እሱን ብጠላውም ልቤ ውስጥ የተተከለውን ፍቅር በቀላሉ መንቀል
አልቻልኩም ነበር። ስለዚህ ራሴን በሥራ በማዋከብ ልረሳው ሞከርኩ ። በሚረባውም ፥ በማይረባውም ነገር ነበር ራሴን የማደክመው ። በማያሰፈልግበት ቦታ እፈጥን ነበር ። እየቆየ ሲሔድ ይህ ልማድ እውስጤ ሥር እየሰደያ መጣ። አሁን ያለ ሥራ ለአጭር ጊዜም ቢሆን መቀመጥ አልችልም ። መንፈሴም የሚረካው ፈጠን ፈጠን እያልኩ ከሠራሁ ነው ”አለቻቸውና ፥ ደመናውን ከፊቷ አባርራ ፈገግ አለች ።

ታሪኳ ዮናታንን አጥንታቸውን ሰርስሮ ገብቶ ወደ ፍቅር መዳህ የጀመረ ልባቸውን እደፋፍረው። ነገር ግን ፥
በአፍላነቱ የተጎዳወን የሞኒካን ልብ ለማዳን መቻላቸውን እርግጠኛ አልነበሩም እድሜአቸውን ለማመዛዘን ሞከሩ ።
በዐሥር ዓመት ያህል ይበልጧታል ። ይህ ሁሉ የእንምሮ ማመንታት ነው እንጂ ፥ ፍቅሩ ያለ ምንም ፍርሃት በልባቻው ውስጥ እያደገ መጥቷል ።

ሞኒካም ዮናታን ታሪኳን በተመስጦና በትካዜ ካዳመጡዋት ጊዜ ጀምሮ ስሜታቸውን በማጤን ልቧ ውስጥ ለየት
ያለ አዲስ ስሜት ሲያብብ ተሰማት እና የእሷም ልብ እንደ እሳቸው ልብ ወደ ፍቅር በመዳህ ላይ ሳለ መንገድ ላይ ተገናኙ።

የዘመን መለወጫ በዓል ሲከበር፡ ዮናታን እዚያው ሐኪም ቤት ውስጥ